en
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

Open in Telegram
912
Subscribers
-124 hours
+37 days
-730 days
Posts Archive
ሐምሌ 28/2018 ዓ/ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃድ ተግባር አንዱ የሆነው የደም ልገሳ መርሃ ግብር በዛሬው እለት በመሀል አምባ ከተማ ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨፨ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በጤና ጽ/ቤት አስተባባሪነት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነው የደም ልገሳ መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት በመሀል አምባ ከተማ 62 ዩኒት ደም ተሰብስቧል። የደም ልገሳ መርሃ ግብር ላይ የመንግስት ሰራተኞች፣የፖሊስ አባላት እንዲሁም በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ተሳትፈዋል። ‎ ‎የደም ልገሳወ በወሊድ ወቅት ደም የሚፈሳቸውን እናቶች፣ በድንገተኛ አደጋ ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች እና በጽኑ ህመም ላይ ያሉ ታካሚዎችን ህይወት በቀጥታ ያድናል። ደም መለገስ የህሊና እርካታን ከመስጠቱም ባሻገር ሰብዓዊ ሃላፊነትን የምንወጣበት ተግባር ነወ።

በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ላይ ልጆች የነገ ተስፋቸውን ሲተክሉ በምስል:-

ሐምሌ 27/2018 ዓ/ም በሀገር አቀፍ የሚካሄደው የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በጊጬ ዲምቱ ቀበሌ ወረዳ አቀፍ የእወጃ ፕሮግራም እየተካሄደ ይገኛል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በሀገር አቀፍ የሚካሄደው የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በጊጬ ዲምቱ ቀበሌ ወረዳ አቀፍ የእወጃ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ነው። በሀገራችን ኢትዮጵያ ለ8ኛ ጊዜ እየተካሄደ ያለው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል ከ8 ቢሊየን በላይ ችግኝ ይተክላሉ። በወረዳው በአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ከ2 መቶ 60 ሺህ 281 ችግኞች በላይ እንደሚተከሉ ሲሆን ከ8 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ይሳተፋሉ። የአረንጓዴ ዐሻራ ተግባራችን ሀገራችን የምግብ ዋስትናዋ በዘላቂነት የተረጋገጠ፣ በግብርናው ዘርፍ ምርታማነቷ የጨመረ እንዲሁም የአየር ንብረት መዛባት የማይበግራት ጽኑ ሀገር እንድትሆን ያደርጋታል። በፕሮግራሙ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን፣ የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳን ጨምሮ የአስተባባሪ አካላት፣ የወረዳው አመራሮች እንዲሁም የቀበሌው የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

"ተስፋን እንትከል"በሚል መሪ ሐሳብ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 800 ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል በተያዘው ዕቅድ መሠረት በወረዳው 260 ሺህ 281 ችግኞችን ለመትከል የቅደመ ዝግጅት ስራ ተጠናቋል!!!

ሐምሌ  26/2018 ዓ.ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በአንድ ጀምበር ከ260 ሺህ በላይ ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት መጠናቀቁን የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በጉራጌ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከ260 ሺህ በላይ ችግኞችን ለመትከል አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ጽ/ቤቱ አክሎ አስታወቋል። የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ "ተስፋን እንትከል"በሚል መሪ ሐሳብ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም ለሚካሄደው 800 ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል በተያዘው ዕቅድ መሠረት በወረዳው 260 ሺህ 281 ችግኞችን ለመትከል የቅደመ ዝግጅት ስራ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል። በአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በወረዳው ደሳ፣ጥላሞ እና በጊጬ ዲምቱ ቀበሌዎች ከ17 ሄ/ር በላይ በሆነ መሬት ላይ ለመትከል የተለየ ሲሆን ከ8 ሺህ በላይ የሚሆኑ የህብረ-ሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ 260,281 ችግኝ ለመትከል ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አቶ ከድር  መርጋ ጠቁመዋል። በነገው እለት በጊጬ ዲምቱ ቀበሌ ጎንግ ተፋሰስ ላይ ወረዳዊ የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከለ ፕሮግራም የሚካሄድ ሲሆን በእለቱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለቸው ለደን ልማት፣ለአካባቢ ውበትና ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ዓይነት ችግኞች መሆናቸውን ጠቅሰው የጉድጓድና የችግኝ አቅርቦት ዝግጅት መደረጉን ኃላፊው ተናግረዋል።

የሳምንቱ  ዓብይት ዜናዎች ሐምሌ 26/2018 ዓ.ም 🎤 ለተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች ከአደጋ ለመጠበቅ ሁሉም የድርሻው መወጣት እንደሚገባ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት አስታወቀ ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ወቅታዊ የንቅናቄ ተግባራት አፈፃፀም ተገመገመ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና 92.88% በመቶ የማለፊያ ውጤት መመዝገቡን የወረዳው ትምህርት ቤቶች ጽ/ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 ሀሚሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ ግብረ ሰናይ ድርጅት በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፕሮጀክት ዜሮ ወረዳ በወረዳ ፊስቱላን ከኢትዮጽያ የማጥፋት ፍኖተ ካርታ አፈጻጸም ከስትሪንግ ኮሚቴ ጋር ውይይት ተካሄዷል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የመሀል አምባ ማዘጋጃ ቤት የማዘጋጃ ቤታዊ ዲጂታል አገልግሎት አሰራርን ለመተግበር ለሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም  ባለድርሻ አካላት በተገኙበት መገምገሙን አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ መሀል አምባ ከተማ  የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አካል የሆነው ሳምንታዊ የከተማ ጽዳት ዘመቻ ተካሂዴል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በጎነት በብዙ ሀብትና ገንዘብ የሚወሰን ሳይሆን ከትልቅ ልብ፣ አዕምሮና ሀሳብ የሚመነጭ በመሆኑ ተግባሩ ሁሉም አጠናክሮ ሊያስቀጥለው እንደሚገባ ተገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የመሃል አምባ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አገልግሎት አሰጣጥ ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ ተግባራት ተጠናክሮ ቀጥሏል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 ለክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ስኬታማነት የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑን ተገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨