en
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

Open in Telegram
912
Subscribers
+124 hours
+47 days
-430 days
Posts Archive
በሁሉም ዘርፎች የምናስመዘግበው የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ተጠናክሮ እየቀጠለ፣ ይበልጥም እየለማ ይሄዳል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ነሐሴ 29/2018 ዓ/ም በወረዳው ''በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የክርምት በጎ ፍቃድ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጅማ ቀበሌ እና በጅማ 01 ከተማ ለሚገኙ አቅመ ደካማ አረጋዊያንና ለተማሪዎች የቤት መገልገያ ቁሳቁስ እንዲሁም ደበተር እና እስክሪብቶ ድጋፍ አድርገዋል። በወረዳው ''በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የክርምት በጎ ፍቃድ ተግባር አንዱ የሆነው የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ ግብዓት የማስተባበርና ለአቅመ ደካማዎች የተለያዩ እገዛዎች ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጿል። በወረዳው በጉራጌ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ አማካኝነት በዛሬው እለት ለጅማ ቀበሌ አቅመ ደካማ ለሆኑት ለአቶ ሸምሱ መልካ የፍራሽ፣ብርድልብስ፣ለልጆቻቸው ደብተርና እስክሪብቶ በተጨማሪም ዘይትና ሳሙና ጨምሮ ድጋፍ የተደረገ ሲሆን በሌላ በኩል በጅማ ቀበሌ እና በጅማ 01 ከተማ ለትምህርት ለደረሱ ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ ህፃናት 30 ደርዘን ደብተር እና እስኪርብቶ ድጋፍ በዛሬው እለት ማድረግ ተችሏል። የጅማ ቀበሌ ደጋፊ አመራር በቴሌግራም ቻሌንጅ በተለያዩ ወጣቶች በማስተባበር ለቤት ክዳን የሚሆን ቆርቆሮ እና ሚስማር ለአቶ ሸምሱ መልካ ድጋፍ ተደርጓል። በድጋፉ ወቅት የጉራጌ የዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ነጅቢያ ማህሙድ እንደገለፁት የበጎ ስራ ከመልካም እሳቤ የመነጨ ተግባር ክፍያው በፈጣሪ ዘንድ ከፍ ያለ ሲሆን የህሊና እርካታ የሚሰጥ በመሆኑ ሁሉም ሰው በበጎ ስራ ላይ የበኩሉ ድርሻ እንዲወጣ በመግለፅ የተጀመረው ቤት በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ለአቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ርክክብ መፈጸም እንዳለበት ጠቅሰው ይህን በጎ ተግባር ላስተባበሩ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በርክክብ ወቅት የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ነጅቢያ ማህሙድ እና የመምሪያው ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ አፀደ ሳህሌ በተጨማሪም የሴቶች ፌዴሬሽን ወይዘሮ ሊዲያ ሳኒ እና የወረዳው ሴቶችና ህፃናት ፅ/ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ፈቲያ መህዲ እና የቀበሌው ደጋፊ አመራር አቶ ፋሪስ ከማል አመራሮች ተገኝተዋል ።

ቃልን በተግባር የመለወጥ እውነተኛ ማረጋገጫ ከ1.5 ሚሊዮን ቤቶች ግንባታ እቅድ እስከ ታሪካዊው የሞርጌጅ ፋይናንስ ስምምነት ******** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ከጉባ ብስራቶች እና ሀገራዊ የማንሰራራት ፕሮጀክቶች መካከል አንዱና ዋነኛው የቤት ልማት ጉዳይ መሆኑን ገልጸው ነበር። በባለፉት ሰባት ዓመታት 1.2 ሚሊዮን ቤቶች መገንባታቸውን በወቅቱ ያሳወቁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ አሁን ደግሞ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት በመንግሥት፣ በግል እንዲሁም በመንግሥትና የግል አጋርነት ቢያንስ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለመገንባት መታቀዱን ይፋ አድርገዋል። ይህንን ግብ ለማሳካት የ3D ቴክኖሎጂዎችን ጨምሮ ዘመናዊ አሠራሮችን ማስገባት፣ የኮንስትራክሽን ግብዓት ፋብሪካዎችን ማጠናቀቅ እና የሞርጌጅ ሥርዓት በመዘርጋት ዜጎች በረጅም ጊዜ ክፍያ የቤት ባለቤት የሚሆኑበት ወይም በተመጣጣኝ ዋጋ የሚከራዩበት መፍትሔ እንደሚበጀው ተናግረው ነበር። ይህ በምክር ቤት የተገባው ቃል ሳይዘገይ በፍጥነት ወደ ተጨባጭ ተግባር መለወጡን የሚያሳይ ታሪካዊ እርምጃ ዛሬ ተወስዷል። በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ተፈረሟል። በ100 ቢሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመውና በIFC በኩል እስከ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅኦ የሚደረግበት ይህ ታላቅ ተቋም፣ በባንክ ዘርፉ የሚታየውን የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠን በመቅረፍ ተደራሽ የቤት መግዣ ብድር እንዲኖር ያስችላል። ይህም የተመጣጣኙን 1.5 ሚሊዮን ቤቶች ግንባታ ግብ የሚያሳካ፣ የግል ዘርፉን ተሳትፎ የሚያሳድግ እና ኢትዮጵያ ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ ለመገንባት የምታደርገውን ስኬታማ ጉዞ የሚያፋጥን ትልቅ የፖሊሲ እና የተግባር ውጤት ነው። #HousingEthiopia #MortgageFinance #EthiopiaDevelopment #IFCEthiopia #EconomicGrowth

የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎች ጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን” ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን” ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን” ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን” ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”

እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን! የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ባስመዘገው የላቀ ውጤት ክልሉ ባዘጋጀው ዓመታዊ ጉባኤ 1ኛ ወጣ!! ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ እውቅናና ሽልማቱ የዞናችን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ ተረክበዋል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ዛሬ ነሓሴ 26/2018 በወልቂጤ ከተማ ባካሄደው የ2018 አፈጻጸምና የ2019 እቅድ ግምገማ ሴክቶሪያል ጉባኤ የዞናችን ጤና መምሪያ በ1ኛነት አጠናቋል። የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የዞኑን የጤና ልማት ስራዎችን በላቀ ውጤታማነት በመፈጸም ከክልሉ ዞኖች 1ኛ ደረጃን ይዞ የዋንጫ ሰርተፊኬትና ቁሳቁስ ተሸላሚ ሆኗል። ለውጤቱ መገኘት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት በሙሉ መምሪያው ያመሰገነ ሲሆን በቀጣይ የጀመርናቸው ስራዎችን በማጠናከር ህዝባችን በሚመጥን እና በላቀ ደረጃ ለመገኘት ለምናደርገው ጥረት ሁሉም ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አስተላልፏል። ለህዝባችን ተጠቃሚነትና ውጤታማነት ዘወትር ተግተን እንሰራለን!!

ነሐሴ 26/2018 ዓ/ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የሚገኘው የገሬኖ ጤና ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈፃፀሙን የቦርድ አባላት በተገኙበት ገምግሟል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በመድረኩ ላይ የጤና ጣቢያው ኃላፊ አቶ ሙኒር ሙደሲር የሩብ ዓመቱን የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ለቦርድ አባላቱ ያቀረቡ ሲሆን፣ በቀረበው ሰነድ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በመድረኩም የቦርድ አባላቱ በሩብ ዓመቱ የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል፣ የታዩ ጉድለቶችንና ክፍተቶችን ፈጥኖ በማስተካከል ለቀጣይ የተሻለ የጤና አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ነሐሴ 23/2018 ዓ/ም የትምህርት ጥራትና የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻል ህብረተሰቡና ባለሀብቱ በመማሪያና ማስተማሪያ መጽሐፍት አቅርቦት ላይ እያደረጉት ያለው ተሳትፎ የሚበረታታ ነው:- ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማ ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በዞኑ ከ37 ሚሊዮን ብር በላይ በህብረተሰቡና ባለሀብቱ ተሳትፎ የታተሙ መጽሕፍት ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) በተገኙበት ለወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ርክክብ ተደርጓል። የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እንደተናገሩት በዞኑ የትምህርት ጥራት ለማሻሻል በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የትምህርት ቤቶች ደረጃ ማሻሻል ላይ ሰፋፊ ስራዎች እየተሰራ ነው። የትምህርት ጥራት ለማሻሻል የትምህርት ግብአት ወሳኝ ነው ያሉት አቶ ላጫ ከዚህም አንዱ የመማሪያ መጽሀፍ እንደሆነ ተናግረዋል። አንድ መጽሀፍ ለአንድ ተማሪ ንቅናቄ ተከትሎ በዞኑ መንግስት ህብረተሰቡን በማሳተፍ መጽሀፍ የሟሟላት ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ በተለይም በየአመቱ ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ ባለሀብቱና ህብረተሰብ በማሳተፍ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዞኑ ከቅድመ አንደኛ ጀምሮ መጽሀፍት ለተማሪዎች ለማዳረስ ከ160 ሺህ በላይ መጽሀፍት የ7ኛና የ8ኛ ክፍል በፌደራልና በክልል መንግስት ያልተሸፈኑ ከ22 በላይ የትምህርት አይነቶችን ማሳተም ተችሏል ብለዋል። የክልሉ መንግስት ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል በዩኒሴፍ ድጋፍ አሳትሞ ለዞኑ ማቅረቡን ያነሱት አቶ ላጫ ይህም የትምህርት ጥራት በማረጋገጥ ረገድ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል። በዞኑ የትምህርት ጥራት ለማሻሻልና ግብአት ለማሟላት የተጀማመሩ ስራዎች ውጤታማ ለማድረግ ህብረተሰቡና ተወላጅ ባለሀብቱ እያደረጉት ያለው ስራ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል። የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ መብራቴ ወልደማርያም አንድ መጽሀፍ ለአንድ ተማሪ ንቅናቄ ተከትሎ በዞኑ በባለፉት 3 አመት ከ184 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ ከ6 መቶ 27 ሺህ በላይ መጽሀፍት በማህበረሰብ ተሳትፎ በማሳተም ለተማሪዎች ማሰራጨት መቻሉን ገልጸዋል። በዘንድሮ አመት 3ኛ አመት የአንድ መጽሀፍት ለአንድ ተማሪ ንቅናቄ ተከትሎ 65 ሚሊዮን 829 ሺህ ብር በማሰባሰብ ከ227 ሺህ በላይ መጽሀፍ ማሳተም መቻሉን አንስተው ከነዚህም ከታተሙ መጽሀፍቶች 53 ሺህ በላይ መጽሀፍት ከዚህ ቀደም ለተማሪዎች ማሰራጨት መቻሉን አንስተዋል። በዛሬው እለት ከ37 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የታተሙ 160 ሺህ 166 የጉራጊኛን ትምህርት ጨምሮ መጽሀፍቶች በማሳተም የክልሉ ፕሬዚዳንትና ምክትል ርዕሰ መስተዳድር በተገኙበት ለወረዳዎች ማስረከብ ተችሏል ብለዋል። እነዚህ መጽሀፍቶች ሲሰራጩ የተማሪ መጽሀፍት ጥምርታ ከቅድመ አንደኛ እስከ 8ኛ ክፍል 1 ለ 2 ተደራሽ እንደሚሆንም ተናግረዋል። መጽሀፉቱ ከፍተኛ ሀብት ወጪ የተደረገበት በመሆኑ ተማሪዎች በተገቢው እንዲይዙትና እንዲጠቀሙበት ማድረግ ላይ ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ መምህራንና የትምህርት አመራር የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም አስገንዝበዋል።

ነሐሴ 21/2018 ዓ/ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ወረዳዊ የንቅናቄ መድረክ በዛሬው በመሀል አምባ ከተማ ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የወረዳው ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት ከስራ ዕድል ፈጠራ ኢንተርፕራይዝ ተቋም ጋር በመተባበር የውጭ ሀገር የስራ ስምሪ ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት ምክክር መድረክ በዛሬው እለት ተካሂዷል። የውይይቱን መነሻ ሰነድ በሁለቱም ተቋማት ኃላፊዎች አማካኝነት ቀርቦ ከተሳታፊዎች ጋር በመግባባት የቀጣይ አቅጣጫ ተቀምጧል። መድረኩን የመሩት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ፅ/ቤት ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሚፍታ አረቦ የውይይቱ አላማ በወረዳው ህጋዊ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አዋጁን ተገንዝቦ ተግባራዊ በማድረግ ዜጎች በህጋዊ መንገድ ተጠቃሚ የሚሆኑበት የአሰራር ስርአት ለማጠናከር ያለመ ነው ብለዋል። በመሆኑም ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር የሚያስከትለው አስከፊ ጉዳት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ማጠናከር እንደሚገባ አቶ ሚፍታ አረቦ ገልፀዋል። በዚህ ህገ ወጥ ተግባር ላይ እየተሳተፉ ያሉ ደላሎች ህጋዊ እንዲሆኑ አለያም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራም አመላክተዋል። የወረዳው ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አይደር ዝይን በበኩላቸው ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ህጋዊ ለማድረግ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ከመፍጠር ስራ ጎን ለጎን የመረጃ ልውውጥና የቁጥጥር ሂደቱን ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጠቁመው በወረዳው ህገ ወጥነቱን ለመቆጣጠርና ብቁ ዜጋ ፈጥሮ የዕድሉን ተጠቃሚ ለማድረግ የወረዳው ዋነኛ አጀንዳ ተደርጎ አፈጻጸሙ የሚገመገም መሆኑንም ገልጸዋል። የወረዳው ስራ ዕድል ፈጠራ ኢንተርፕራይዝ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጅላሉ ወራቄ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ህይወት የሚያሳጣና ቤተሰብ የሚበትን ድርጊት መሆኑን ገልጸው ተቋምና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት መታቀዱንም ተናግረዋል። ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ዜጎች ለከፍተኛ እንግልትና ሰቆቃ የሚዳርግ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ የሚያስከትልና ህይወት የሚያሳጣ በመሆኑ የተለያዩ ሚዲያዎች፣የወጣቶችና የሴቶች አደረጃጀቶችን ተጠቅሞ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር ህጋዊ የስራ ስምሪት ለማስፈን ይሰራል ብለዋል። አቶ ጀላሉ አክለውም በወረዳ ደረጃ ስራውን በንቅናቄ ለመምራት የተቋቋመ የአብይና የቴክኒክ ኮሚቴ ተግባርና ኃላፊነት አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር መከላከልና መቆጣጠር ትውልድ የማዳን ጉዳይ በመሆኑ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል።

ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ስራ ዕድል ፈጠራ ፅህፈት ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ስራ ዕድል ፈጠራ ፅህፈት ቤት የ2018 ዓ.ም የአፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 ዓ.ም ዕቅድን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል። በመድረኩ ላይ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2019 ዓ.ም ዕቅድን ያቀረቡት የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ጂላሉ ወራቄ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ 6 ሺህ 844 ስራ አጥ ወጣቶችን መለየት ተችሏል። ከተለዩት መካከል 6 ሺህ 768 ወጣቶች የክህሎት ስልጠና አግኝተው ወደ ስራ እንዲገቡ የተደረገ ሲሆን፣ ለስራ አጥ ወጣቶችም 8 ሚሊዮን 352 ሺህ 605 ብር ብድር ተሰራጭቷል። በተጨማሪም 11 የማምረቻና መሸጫ ሼዶች ለስራ አጦች የተላለፉ ሲሆን፣ ከ29 ሚሊዮን 304 ሺህ 806 ብር በላይ የገበያ ትስስር ተፈጥሯል። በበጀት ዓመቱ 6 ሚሊዮን 750 ሺህ ብር ዕዳ ማስመለስና 9 ሚሊዮን 489 ሺህ 393 ብር ማስቆጠብ መቻሉም በሪፖርቱ ተመላክቷል። በ2019 በጀት አመትም 7 ሺህ 377 ስራ አጥ ወጣቶችን ለመለየትና ለ6 ሺህ 225 ወጣቶች የስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዷል። ለዚህም 34 ሚሊዮን 24 ሺህ 960 ብር ብድር ለማሰራጨት፣ 17 ሚሊዮን 498 ሺህ 160 ብር ዕዳ ለማስመለስ እንዲሁም 12 ሚሊዮን 558 ሺህ 354 ብር ለማስቆጠብ መታቀዱን ኃላፊው ገልጸዋል። መድረኩን የመሩት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የመንግስት ረዳት ተጠሪና የፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሚፍታ አረቦ የስራ እድል ፈጠራ በዜጎች ሁለንተናዊ ህይወት ላይ ዘላቂ ለውጥ ማምጣት እንዲችል በትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል። በአንድ ቤተሰብ ውስጥ ገቢ ሲጨምር የሃገር ኢኮኖሚ እንደሚያድግ የገለጹት አቶ ሚፍታ፣ የወጣቶችን የስራ ባለቤትነት ለማረጋገጥ ልዩ ልዩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የተቀናጀ ስራ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል። አቶ ሚፍታ አክለውም ወጣቶችን ሙሉ በሙሉ ወደ ስራ በማስገባት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጸው፤ በበጀት አመቱ የታዩ ጉድለቶችን በመቅረፍ ለላቀ ውጤታማነት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል። የወረዳው ስራ ዕድል ፈጠራ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጂላሉ ወራቄ በበኩላቸው የወጣቶችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻልና የአካባቢውን ኢኮኖሚ ለማሳደግ የስራ ዕድል ፈጠራ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ የገበያ ትስስርን ለማጠናከርና ስራ ፈጣሪዎች ስራቸውን እንዲያስፋፉ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀው በአካባቢው ያለውን ጸጋና ሀብት ጥቅም ላይ በማዋል ስራ ፈላጊ ወጣቶችን አሟጦ ወደ ስራ ለማስገባት ከመድረኩ የተገኙ ግብዓቶችን በቀጣይ ዕቅድ ውስጥ በማካተት በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል። የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ስራ አጥ ወጣቶችን የስራ ባለቤት ማድረግ፣ ዕዳን ለማስመለስ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት፣ ለወጣቶች ምቹ የብድር ሁኔታዎችን መፍጠር እና የተላለፉ የማምረቻና መሸጫ ሼዶች በአግባቡ ስራ ላይ እንዲውሉ ክትትል ማድረግ እንደሚገባ ጠቅሰው ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸወን አስታውቀዋል።