es
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

Ir al canal en Telegram
913
Suscriptores
-124 horas
+27 días
-730 días
Archivo de publicaciones
ጳጉሜ 03/2018 ዓ/ም የ18ቱ የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጅ ሰልጣኝ እናቶች ምረቃ እና የሩራል ዋሽ (Rural WASH) ፕሮጀክት ማጠናቀቂያ ስነ-ስርዓት ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ፅህፈት ቤት ስር በሚገኘው የኢንጌ ጤና ጣቢያ ካችመንት የጊጬ ዲምቱ ቀበሌ በጤና እና በንፅህና (WASH) ዘርፍ የተመዘገቡ ታላላቅ ስኬቶች ዛሬ በደማቅ ሁኔታ ተመርቀዋል። በቀበሌው በሴቶች ልማት ህብረት አማካኝነት የ18ቱን የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጅ ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ 36 እናቶች የ52 ሰዓታት ስልጠናቸውን በስኬት አጠናቀው የሞዴል እማወራነት የምስክር ወረቀታቸውን ተቀብለዋል። እናቶቹ መደበኛ ስራቸውን ሳይበድሉ በየቀኑ ለሁለት ሰዓታት ስልጠናውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን፣ ይህም በየቤተሰባቸው ዘንድ የበሽታ መከላከል አቅምን ለማሳደግ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ታምኖበታል። በተጨማሪም በሩራል ዋሽ (Rural WASH) መርሃ ግብር ቀበሌዎችን በሦስት ወር ውስጥ ክፍት መጸዳጃ የሌለባቸው ለማድረግ ከተያዙት ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነው የዚሁ የጊጬ ዲምቱ ቀበሌ የንፅህና ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ዛሬ በጋራ ተመርቋል። በዚህ የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ የወረዳው ጤና ጽሕፈት ቤት ዋና ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ባስተላለፉት መልዕክት፣ ተመራቂ እናቶች ያገኟቸውን የጤና እና የንፅህና እውቀቶች ወደ ተግባር በመቀየር የአካባቢያቸውን ጤና ይበልጥ እንዲጠብቁና ለሌሎች አርአያ እንዲሆኑ አሳስበዋል። በፕሮግራሙ ላይ የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አብራር፣የወረዳው ሴቶችና ህጻናት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ፈትያ መህዲ እንዲሁም የወረዳ አመራሮች፣የጊጬ ዲምቱ ቀበሌ አመራርና ተመራቂ እናቶች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

ጳጉሜ 3 የጽናት ቀን “ፅኑ መሠረት ብርቱ ሀገር!” በሚል መሪ ቃል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በመሀል አምባ ከተማ ተከበረ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ጳጉሜ 3 የጽናት ቀን “ፅኑ መሠረት ብርቱ ሀገር!” በሚል መሪ ቃል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ አስተዳደር ግቢ በልዩ ልዩ ፕሮግራሞች እና የፓናል ውይይት በማድረግ አክብረዋል። የወረዳው ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙስማ በድሩ በፓናል ውይይቱ ወቅት እንኳን ለ2018 ዓ.ም የጳጉሜ ወር የሽግግር ቀናት እና ለጳጉሜ 3 “የጽናት ቀን” በሰላም አደረሳችሁ በማለት፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ በዜጎቿ ብርታትና ጽናት በርካታ ፈተናዎችን ተቋቁማ ዛሬ ላይ የደረሰችና ለሌሎች ምሳሌ መሆን የቻለች ሀገር መሆኗን ገልጸዋል። የጽናት ቀን"ፅኑ መሠረት ብርቱ ሀገር" በሚል ቃል ስናከብር የሀገርን ክብር፣ ሉዓላዊነትና ነፃነት ከልቡ የሚያከብር የአባቶቹን የትናንቱን የጀግንነት ታሪክና ክብር ወደ ዛሬ እና የዛሬውን አደራ ጽንተን ወደ ነገ እያስተላለፈ የሚጓዝ አኩሪና ባለድል ሠራዊት ነው መሆኑን አቶ ሙስማ አክለው ገልጸዋል። የጽናት ቀን ስናከብር ሁሉም ዜጋ ሀገራዊ ክልላዊና ዞናዊ ጉዳዮች በሚገባ ተረድተን የነገዋን ኢትዮጵያ የምናስብበት ለሕዝቦቻችን ሰላምና ደህንነት ልማትና ብልጽግና ለቀጣይ ትውልድ በጽናት፣ በአንድነት፣ በሰላምና በሀገር ፍቅር የተገነባ ሀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ ሊሆን እንደሚገባም በፓናል ውይይቱ ተመላክቷል።

ጳጉሜ 02/2018 ዓ/ም በነገው እለት በታላቅ ድምቀት የሚመረቀው የጉራጌ ዞን አስተዳደር ህንጻን አስመልክቶ የፌደራል ፖሊስ ማርሽ ባንድ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ትዕይንቱን አሳይቷል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የጉራጌ ዞን አስተዳደር B+G+9 ህንጻ በነገው እለት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ተጋዥ እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ይመረቃል። በጉራጌ ዞን የተገነባው እጅግ ዘመናዊ የዞኑ አስተዳደር( B+ G+9) ህንጻ ነገ በታላቅ ድምቀት ለመመረቅ ዝግጅቱ ተጠናቋል። ስለሆነም የፌደራል ፖሊስ ማርሽ ባንድ ጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በመገኘት የሙዚቃ ትዕይንቱን በዛሬው እለት አሳይቷል። የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱን አስመልክቶ ወደ ወልቂጤ ከተማ የገባውን የፌደራል ፖሊስ ማርሽ ባንድ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ላጫ ጋሩማና የዞኑ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በወልቂጤ ከተማ ተገኝተው በክብር ተቀብለዋል። የማርሽ ባንዱ በከተማዋ ያሳየው የሙዚቃ ትዕይንትም ለነገው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት የበዓል ድባብን በማጠናከር የከተማዋን ድምቀት አሳድጎታል። ይህ ትልቁ የጉራጌ ዞን አስተዳደር ህንጻ በአጠቃላይ እስከ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር የጨረሰ ሲሆን በዞኑ ይስተዋል የነበረው የቢሮ ጥበት ችግር በመቅረፍ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ያስችላል። በምረቃ ፕሮግራሙ የፌደራል፣የክልል የዞን የወረዳና የከተማ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን።

ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም በወረዳው በ2018 የምርት ዘመን በግብርናው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላሉ:- አቶ አብድረሂም ርዳ ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጳጉሜ 1 "የእምርታ ቀንን" በማስመልከት በግብርና ልማት የተሰሩ ስራዎች ምልከታ ተካሂዷል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብድረሂም ርዳ እንዳሉት በወረዳው 5ቱንም የጳጉሜ ቀናት በተለያዩ ስያሜዎች እንደሚከበሩ አንስተዋል። በዛሬው እለት ጳጉሜ 1 የእምርታ ቀን በማስመልከት በወረዳው በ2018 ዓ.ም በግብርና ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች ምልከታ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል። አክለውም በወረዳው በግብርና ኢንቨስትመንት ዘርፍ የተሰማራው የHLS አበባ እርሻ ልማት መጎብኘቱን ገልጸዋል። በግብርና ልማት ዘርፍ በተጠናቀቀው በጀት አመት በወረዳው ትላልቅ ስኬቶች እንደተመዘገበ አንስተው፤ ከዚህም ባለፈ የፓርቲው ኢንሼቲቭ በተገቢው በመተግበሩ አርሶ አደሩ ምርት ከራሳቸው አልፎ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል። እንደ አብድረሂም ገለጻ በወረዳው ከዚህ ቀደም ታርሰው የማይታወቁ 5 ሺህ ሄክታር መሬት በማረስ በሰብል መሸፈን እንደተቻለም ገልጸዋል። በ2018 በጀት ዓመት በግብርናው ልማት ዘርፍ የአርሶ አደሩን ህይወት ለመቀየር በዘርፉ የተመዘገቡ ስኬቶችን በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አመላክተዋል። የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ በበኩላቸው፥ በወረዳው በ2018 የምርት ዘመን 20 ሺህ 518 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ 17 ሺህ 812 ሄክታር መሬት በዘር መሸፈን መቻሉን ገልጸዋል። በመኸር ከለማው ማሳ ከ1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመላክተዋል። የዘንድሮ ማሳ ከአምናው ጋር ሲነጻጸር 5 ሺህ 6 ሄክታር መሬት በላይ እድገት እንዳለውም አስረድተዋል። በወረዳው በመኸር ከለማው ማሳ ውስጥ ስንዴ፣ ጤፍና ገብስ በሰፊው በክላስተር መልማቱንም አንስተው፤ ይህም በወረዳው በክላስተር የማልማት ዘዴ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቷል ብለዋል። በመስክ ምልከታውም የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣ የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና ፕላን ልማት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ዘይነብ ወራቄ ጨምሮ የወረዳው የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ጳጉሜ 01/2018 ዓ.ም ጉራጌ በንግድ ብቻ ሳይሆን በተሰማራበት ዘርፍ ሁሉ በርትቶና ፀንቶ በመስራት ውጤታማ መሆን እንደሚችል ዳግም ስላሳያችሁ እናመሰግናለን:-አቶ ሸምሱ አማን ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በኢትዮጵያ ETFC በተዘጋጀው ውድድር አሸናፊ የሆነው ቦክሰኛ ረቢቅ ሳኒና ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ሳቦም መሀመድ መኪ ጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ መሀል አምባ ከተማ በዛሬው እለት ደማቅ አቀባበል ተደረጎላቸዋል። የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን እንዳሉት ኢትዮጵያም ሆነ ዞናችን ከዚህ ቀደም በአትሌቲክስ ስፖርት ዘርፍ ብቻ ይታወቁ እንደነበር አንስተው፤ አሁን ላይ መንግስት የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ወጣቶች ሀገሪቷ በቦክስ ስፖርትን እንድትታወቅ እያደረጉ ነው ብለዋል። ጉራጌ በንግድ ብቻ ሳይሆን በተሰማራበት ዘርፍ ሁሉ በርትቶና ፀንቶ በመስራት ውጤታማ መሆን እንደሚችል ዳግም ስላሳያችሁ እናመሰግናለን ሲሉም ተናግረዋል። ቦክሰኛ ረቢቅ ሳኒና ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ሳቦም መሀመድ መኪ በቦክስ የስፖርት ውድድር እያሳዩት ያለው ድንቅ ብቃት አድንቀዋል። የጉራጌ ዞን የብዙ ስፖርተኞች መፍለቂያ ነው ያሉት አቶ ሸምሱ መሰል ስፖርተኞች የሀገራችን ወጣቶች ከተለያዩ ሱሶች እንዲወጡና ጊዜያቸውን አልባሌ ቦታ እንዳያሳልፉ አርአያ ከመሆን ባለፈ ስፖርት ላይ እንዲያዘወትሩና ለነጋቸውን ትልቅ ተስፋ እንዲሰንቁ እንደሚያደርጋቸውም ገልጸዋል። ከዚህም ባሻገር የሀገር ኩራት የሆኑ ተተኪ ስፖርተኞች ለማፍራት በዘርፉ የተሰማሩትን ተገቢውን እውቅናና ክብር መስጠት እንደሚገባ አቶ ሸምሱ አስገንዝበዋል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን በበኩላቸው ስፖርት ነጠላ ትርክት በማስቀረት የጋራ ትርክትን ከመገንባት ባለፈ ለአንድነት፣ ለትብብር፣ ለሰላምና ለሀገር ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም ገልጸዋል። ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ሳቦም መሀመድ መኪና አትሌት ረቢቅ ሳኒ ወረዳው ያፈራቸው ስፖርተኞች መሆናቸው ጠቁመው፤ እነዚህ ስፖርተኞች የሀገራቸውን ባንድራ በተለያዩ በአፍሪካና በአለም ሀገራት ከፍ ማድረግ ችለዋል ብለዋል። ወጣቱ በስፖርቱ ዘርፍ እንዲሳተፉ በማድረግ በቀጣይ የወጣቱን እጣ ፋንታ ልንታደግ ይገባል ያሉት አቶ ሚፍታ ለዚህም በወረዳው የወጣት ማሰልጠኛ ተቋማት ማብዛት ላይ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል። የኢትዮጵያ ግሎባል ቴኳንዶ ፌደሬሽን መስራችና ፕሬዝዳንት ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ሳቦም መሀመድ መኪ እንዳሉት ዞኑ በአለም፣ በአፍሪካና በሀገር ደረጃ ታዋቂ ስፖርተኞችን በማፍራት ማበርከቷንም አንስተዋል። ወጣቶች ጊዜያቸውን በመልካም ነገር በማዋል በስፖርት ዘርፍ መሰማራት እንዳለባቸው መክረው ከዚህም ባለፈ የወረዳው ልማት ለማረጋገጥ በአንድነት መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል። በETFC 02 በተዘጋጀው ውድድር አሸናፊ ቦክሰኛ ረቢቅ ሳኒ ወጣቶች ነገአቸውን የተሻለ ለማድረግ በስፖርቱ ዘርፍ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው መክረው የወረዳው አስተዳደር ላደረገላቸው አቀባበልም አመስግነዋል።

የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ላይ ልዩ ተሸላሚ በመሆን የዋንጫና ሰርተፍኬት ተበረከተለት። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ የ2018 በጀት አመት ማጠቃለያ ሴክቶሪያል ጉባኤ "አንድነት ለጽዳት፣ ትጋት ለአገልግሎት፣ ውሳኔ ለልማት" በሚል መሪ ቃል የምክክር መድረክ በወልቂጤ ከተማ ባካሄደበት ወቅት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ላይ ልዩ ተሸላሚ በመሆን የዋንጫና ሰርተፍኬት ተበርክቷለታል።

በኢትዮጵያ ETFC የተዘጋጀው ውድድር አሸናፊ የሆነው ቦክሰኛ ረቢቅ ሳኒ እና የኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ሳቡም መሀመድ መኪ የወረዳችን ተወላጅ ጀግኖቻችን በነገው እለት በመሀል አምባ ከተማ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ አስተዳደር አማካኝነት ደማቅ አቀባበል ያደረግላቸዋል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ አስተዳደር ያዘጋጀው የወረዳችን ተወላጅ ጀግኖቻችን አቀባበል እና የማበረታቻ ፕሮግራም በነገው እለት በመሀል አምባ ከተማ በከተማው ወጣቶችና ነዋሪዎች በዳማቁ አቀባበል የሚደረግላቸው ይሆናል።

በሁሉም ዘርፎች የምናስመዘግበው የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ ተጠናክሮ እየቀጠለ፣ ይበልጥም እየለማ ይሄዳል- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ነሐሴ 29/2018 ዓ/ም በወረዳው ''በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የክርምት በጎ ፍቃድ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጅማ ቀበሌ እና በጅማ 01 ከተማ ለሚገኙ አቅመ ደካማ አረጋዊያንና ለተማሪዎች የቤት መገልገያ ቁሳቁስ እንዲሁም ደበተር እና እስክሪብቶ ድጋፍ አድርገዋል። በወረዳው ''በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ'' በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የክርምት በጎ ፍቃድ ተግባር አንዱ የሆነው የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ ግብዓት የማስተባበርና ለአቅመ ደካማዎች የተለያዩ እገዛዎች ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጿል። በወረዳው በጉራጌ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ አማካኝነት በዛሬው እለት ለጅማ ቀበሌ አቅመ ደካማ ለሆኑት ለአቶ ሸምሱ መልካ የፍራሽ፣ብርድልብስ፣ለልጆቻቸው ደብተርና እስክሪብቶ በተጨማሪም ዘይትና ሳሙና ጨምሮ ድጋፍ የተደረገ ሲሆን በሌላ በኩል በጅማ ቀበሌ እና በጅማ 01 ከተማ ለትምህርት ለደረሱ ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ ህፃናት 30 ደርዘን ደብተር እና እስኪርብቶ ድጋፍ በዛሬው እለት ማድረግ ተችሏል። የጅማ ቀበሌ ደጋፊ አመራር በቴሌግራም ቻሌንጅ በተለያዩ ወጣቶች በማስተባበር ለቤት ክዳን የሚሆን ቆርቆሮ እና ሚስማር ለአቶ ሸምሱ መልካ ድጋፍ ተደርጓል። በድጋፉ ወቅት የጉራጌ የዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ነጅቢያ ማህሙድ እንደገለፁት የበጎ ስራ ከመልካም እሳቤ የመነጨ ተግባር ክፍያው በፈጣሪ ዘንድ ከፍ ያለ ሲሆን የህሊና እርካታ የሚሰጥ በመሆኑ ሁሉም ሰው በበጎ ስራ ላይ የበኩሉ ድርሻ እንዲወጣ በመግለፅ የተጀመረው ቤት በአጭር ጊዜ ተጠናቆ ለአቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ርክክብ መፈጸም እንዳለበት ጠቅሰው ይህን በጎ ተግባር ላስተባበሩ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በርክክብ ወቅት የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ነጅቢያ ማህሙድ እና የመምሪያው ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ አፀደ ሳህሌ በተጨማሪም የሴቶች ፌዴሬሽን ወይዘሮ ሊዲያ ሳኒ እና የወረዳው ሴቶችና ህፃናት ፅ/ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ፈቲያ መህዲ እና የቀበሌው ደጋፊ አመራር አቶ ፋሪስ ከማል አመራሮች ተገኝተዋል ።