1 069
Subscribers
+224 hours
No data7 days
+230 days
Posts Archive
ሶስተኛው ዙር ብቃት_የወጣቶች_የስራ_ላይ_ልምምድ_ፕሮጀክት ትግበራ ሁለተኛው ዙር የህይወት ክህሎት እና የስራ አፈላለግ ስልጠና ወጣቶች በስልጠና ላይ እንደሚገኙ ተገለጸ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራ ክህሎት ቢሮ "ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት" ተጠቃሚ ለመሆን በአስተዳደሩ የወረዳ አንድ ማዕከላት የተመዘገቡ ወጣቶችን በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና በኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል በዚህም ሰልጣኞች ስልጠና ከመጀመራችው በፊት አስፈላጊውን ኦሬንቴሽን የተሰጣቸው ሲሆን ስልጠናውን ለቀጣይ 12 ቀናት በኮሌጆቹ እየወሰዱ የሚቆዩ ይሆናል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 17/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የስራ ማስታወቂያ ለድሬዳዋ ነዋሪዎች በሙሉ
የኢትዮጲያ አየር መንገድ አዲስ የስራ ማስታወቂያ ያወጣ ሲሆን በኤሌክትሮኒክስ በሜካኒካል ፣ በኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ እና ተያያዥ የትምህርት መስኮች የተመረቁትን ለመቅጠር ይፈልጋል ።
በመሆኑም እድሜያቸው ከ 18 እስከ 25 እንዲሁም ቁመት ሜትር ከ ስልሳ የሆናቹ ከሚያዚያ 20 አንስቶ እስከ ሚያዚያ 24 2017 ዓ.ም ድረስ አስፈላጊውን የትምህርት ማስረጃ በመያዝ እና ድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ በአካል በመገኘት መመዝገብ ይኖርባቸዋል ።
አስታውሱ የምዝገባው ቀን አጭር ስለሆነ ፈጥነው ይመዝገቡ !
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እና የወረዳ አንድ ማዕከላት አመራሮች የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የአንድነትና የአብሮነት መርሀ-ግብር አካሄዱ፤
መርሃ-ግብሩ በተለይም የቢሮው እና የአንድ ማዕከላት አመራሮች በስራ ላይ ካለው አብሮነት እና አንድነት ጎን ለጎን በማህበራዊ ጉዳይም ጠንካራ መስተጋብር መፍጠር መቻሉን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል።
ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ የረመዳን ጾም ላይ አመራሩ በጋራ መርሃግብር ማዘጋጀቱ የሚታወስ ሲሆን ይህም የድሬዳዋዊ ዕሴት መገለጫ መሆኑን ያሳየ ሆኗል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 13/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ስቅለቱ እና ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ፡፡ በዓሉ የደስታ፣ የሰላም፣ የጤና እንዲሁም የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ፡፡
መልካም በዓል!
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
የዛሬው ዕለት ለምዘና ማዕከልነት እውቅና ለመስጠት በተዘጋጀ በቼክ ሊስት መሰረት የማረጋገጥ (Accreditation of assessment center) ስራ ተሰራ።
ይህም ስራ በአስተዳደሩ የሚገኙ በፎቶግራፊ እና በቪዲዮግራፊ ሰልጥነው የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና መመዘን የፈለጉ እና የጠየቁ ባለሙያዎችን ለመመዘን የተሟላ ማዕከል በማስፈለጉ የድሬዳዋ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ጋር በመተባበር ማዘጋጀት ተችሏል።
በመሆኑም የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል በመደበኛ እና በኢ-መደበኛ የክህሎት ልማት እራሳቸውን አብቅተው መመዘን የሚፈልጉ ዜጎችን የማገልገል አድማሱን እያሰፋ ይገኛል።
የምዘና ማዕከሉ በተለይ ከተለመደው መደበኛ የትምህርትና ስልጠና ሂደት አጠናቀው ከሚመዘኑ በተጨማሪ በልምድ የተገኘ ክህሎት ያላቸውን ዜጎች የሚመዘኑበትን አግባብ ያመቻቸ መሆኑና በዚህም እስከ ደረጃ ሁለት ተመዝነው የእውቅና ማረጋገጫ እንደሚሰጥ ማወቅ ተችሏል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 9/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
#ዜና|የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የምርምር፣የቴክኖሎጂ እና ክህሎት ያላቸው ዜጎች መፍለቂያ ተቋም እንዲሆን እየተሰራ እንዳለ ተገለጸ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ብሩህ አእምሮዎች በክህሎት የበቁ እጆች በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው 4ተኛው የተግባር ተኮር ጥናትና ምርምር፣የቴክኖሎጂና የፈጠራ ስራ እንዲሁም የክህሎት ውድድር ላይ ተሳትፈው አመርቂ ውጤት ላስመዘገቡ መምህራንና ሰልጣኝ ተማሪዎች የእውቅና መርሃ ግብር አከናወነ፡፡
ኮሌጁን የምርምር፣የቴክኖሎጂ እና ክህሎት ያላቸው ዜጎች መፍለቂያ እንዲሆን እየተሰራ እንዳለ የገለጹት በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ አያይዘውም በከተማ አስተዳደሩ ለቴክኒክና ሙያ ትኩረት ተሰጥቶ ሁሉም ዜጎች ሙያቸውን እንዲያዳብሩና የስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ በትጋት እየተሰራ ነው ይህ ተግባር ደግሞ ከግብ እንዲደርስ ኮሌጃችን ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራ ይሆናል ያሉ ሲሆን፡፡
በመጨረሻም ኮሌጁን ወክላችሁ በተወዳደራችሁበት መስክ አመርቂ ውጤት ላስመዘገባችሁ እና ከተማ አስተዳደሩን ወክላችሁ በአገር አቀፉ ውድድር ላይ ለምትሳተፉ በሙሉ መልካም እድል እንዲገጥማችሁ እመኛለሁ ብለዋል፡፡
በመቀጠል ንግግር ያደረጉት ደግሞ የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ የሆኑት አቶ አብዱልፈታህ አፈንዲ ሲሆኑ ኮሌጁን ወክላችሁ ይህን አመርቂ ውጤት ላስመዘገባችሁ እና ይህ ውጤት እንዲመጣ ቀን ከሌት የሰራችሁ በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሲሆን አያይዘውም ኮሌጁ ትምህርትና ስልጠናን ከመስጠት በዘለለ የቴክኖሎጂ እና የኢንተርፕራይዞች መፍለቂያ እንዲሆን ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን መስራት እንደሚገባቸው ተናግረዋል፡፡
ኮሌጁ በያዘው ራእይ መሰረት በኮሌጁ የሚሰለጥኑ እንዲሁም ድጋፍ የሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞች የፈጠራ ሃሳባቸውን ወደተግባር የሚለውጡበትን የኢንኩቤሽን ሴንተር አቋቁሞ ለሰልጣኞች እንዲሁም ለተለያዩ አካላቶች ድጋፍን እያደረገ ይገኛል ያሉት የኮሌጁ ም/ዲንና የኢ/ኤ/ቴ/ሽ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ አያይዘውም አሰልጣኞችም እንዲሁም ሰልጣኞች የሚኖርባቸውን የተለያዩ ክፍተቶችን ለመሙላት እየተሰራ እንዳለ ገልጸዋል፡፡
በእውቅና መርሃ ግብሩ ላይ በተግባር ተኮት ጥናትና ምርምር፣በቴክኖሎጂ እንዲሁም በክህሎት ውድደር አመርቂ ውጤት ላስመዘገቡ እንዲሁም ይህ ውጤት እንዲመጣ ለሰሩ ትምህርት ክፍሎች የእውቅና እና የምስጋና የምስክር ቀረቀት ተሰጥቷል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሚያዝያ 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥለው አንድ ወር 232 የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ምዘና እንደሚወስዱ ተገለጸ፤
በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ በሁለቱ የመንግስት ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች አዲስ በተከለሰው የሙያ ደረጃና የሆልስቲክ ምዘና አሰጣጥ ስርዓት የሙያ ምዘና በመውሰድ ላይ እንደሚገኙ የሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ አስታወቁ፤
አቶ ታሪኩ አክለው ከዚህ ቀደም ቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ከኢንዱስትሪው ጋር በመተባበር የማሰልጠኛ ሙያ ደረጃዎችን(Occupational Standards) የከለሰ ሲሆን በተከለሰው የሙያ ደረጃ መሰረት አሰልጣኝ መምህራንን በተለያዩ ሥርዓቶች በማብቃት ተከታታይነት ያለው የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችና የትምህርት ደረጃቸውን በማሻሻል እንዲበቁ መደረጉን አስታውሰዋል፡፡
በአስተዳደሩ 232 የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና በ12 ዘርፎች በ23 ሙያዎች(Occupation) መውሰድ መጀመራቸውንና ምዘናውም በሚቀጥለው አንድ ወር ውስጥ የሚጠናቀቅ መሆኑን በቢሮው የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል የሙያ ብቃት ምዘና ቡድን መሪ የሆኑት አቶ መኳንንት ዘውዴ ተናግረዋል፤
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 7/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የተዘጋጀ የሞዴል ኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽንና ባዛር ተጀመረ።
ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 10/2017 ዓ.ም ድረስ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፊት ለፊት የሚገኘው ቦታ ላይ የሚካሄደውን ይህን ኤግዚቢሽን እና ባዛር የቢሮው አመራሮች በተገኙበት በይፋ ተከፍቷል።
በዚህም ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች ምርትና አገልግሎቶቻቸውን ይዘው የሚቀርቡ ሲሆን ወቅቱም በዓል ሰሞን እንደመሆኑ በቦታው በመገኘት የአስተዳደሩ ነዋሪ ሞዴል ኢንተርፕራይዞችን በማበረታታት ተጠቃሚ እንዲሆን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
የቢሮው ኃላፊ አክለው ኢንተርፕራይዞች የሚገጥማቸውን የገበያ ተደራሸነትን ለመቅረፍ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሚመራው የኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ስርአት(E-LMIS) ተግባራዊ የሆነው መተግበሪያና ድህረገፅ ላይ በሰፊው እንዲመዘገቡ እየተደረገ መሆኑና ኢንተርፕራይዞች ምርታቸውን ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ሀገራት ኦንላይን በማስተዋወቅ የሚሸጡበትና ክፍያ የሚቀበሉበት ዕድል መመቻቸቱን ተናግረዋል፡፡
በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ በበኩላቸው በቢሮው ለኢንተርፕራዞች ከሚሰጡ የድጋፍ ማዕቀፎች አንዱ የገበያ ትስስር ሲሆን ኤግዚቢሽንና ባዛር ወሳኝ ሚና አለው በመሆኑም ኢንተርፕራይዞች ያመረቱትን ምርት ይዘው የሚቀርቡበት ገበያተኛውም በሚፈልገው ልክ ተገበያይቶ የሚወጣበት መድረክ መፍጠሪያ ዘዴ አንዱ ይህ በመሆኑ እንዲሁም ያለውን የኑሮ ውድነት ለማረጋጋትም ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 6/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
“በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የአሰልጣኝ መምህራንን ምዘና ማካሄዳችን ለቀጣይ የለውጥ ጉዞ ውጤታማነት ዝግጁ የሚያደርገን ይሆናል”
ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ዳይሬክተር እና የቢሮው ም/ ኃላፊ
ኃላፊዋ በዛሬው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በአገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን የአሰልጣኝ መምህራን ምዘና በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ ለማስጀመር ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን አስታውቀዋል፤ የምዘናው ዋና አላማም አሰልጣኝ መምህራኑን ከአዲሱ የዘርፉ ፖሊሲ ጋር የማስተዋወቅና የማብቃት እንዲሁም የዘርፉን የስልጠና ጥራት ከመጠበቅ አኳያ ምዘናው ሚናው ላቅ ያለ እንደሚሆን አስታውቀዋል፡፡
በአስተዳደር ደረጃ በዚህም ምዘና የማያልፍ የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ የማይኖር መሆኑን እና የሚመዝኑ መዛኞችም ከዚህ ቀደም የነበሩት ሳይሆን በአዲስ መልክ ከኢንዱስትሪ እና ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የፈሩ መሆናቸውና በቢሮው የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል በኩል ለአዳዲስ እጩ መዛኞች ስልጠና መሰጠቱ ተገልጻል፤ በዚህም በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆችና በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የምዘና ማዕከላት ምዘናው የሚካሄድ ሲሆን በአጠቃላይ ሁሉም አሰልጣኝ መምህራን በምዘናው የሚያልፉ ሲሆን በመጀመሪያው ዙር በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች የሚያሰለጥኑ አሰልጣኝ መምህራን ይመዘናሉ በቀጣይ ደግሞ የግል የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ ላይ የሚያሰለጥኑ አሰልጣኝ መምህራን በተመሳሳይ የሚመዘኑ ይሆናል፡፡
በዋናነት ይህ ምዘና የሚካሄደው አሰልጣኝ መምህሩ ከዚህ ቀደም በምዘና ስርዓት ያላለፈ ሆኖ ሳይሆን የዘርፉ ፖሊሲ በመቀየሩ ከጊዜው ጋር የተናበበ አቅም ለመፍጠር ታስቦ የሚከናወን ሲሆን በሌቭል የነበረው የምዘና ስርአት አካሄድም በሆልስቲክ ተተክቶ የሚመዘኑ ሲሆን በመጀመሪያው ዙር ምዘና ብቁ ሆነው ያልተገኙ አሰልጣኝ መምህራን ክፍተታቸውን በመለየትና እስከ ፌደራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ድረስ በመላክ አቅማቸው የሚገነባ ይሆናል፤ ይህም በመጪው 2018 ዓ.ም ለሚደረገው የሰልጣኝ ተማሪዎች ቅበላ ቅድመ ዝግጅት አካል ሆኖ የሚሰራበት ነው፡፡
ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በመግለጫው ማጠቃለያ እንደገለጹት አስተዳደሩ የኢንዱስትሪ ማዕከል እንደመሆኑ መጠን ከፍተኛ የሆና በቴክኒክና ሙያ የበቃ የሰው ሃይል ፍላጎት በመኖሩ ይሄንንም ለማሟላት አሰልጣኝ መምህሩን መመዘንና ማብቃት ትኩረት እንደተሰጠው ጠቅሰው በአጠቃላይ በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ የኢንዱስትሪዎችን አቅም ከመገንባትና አስፈላጊ የሙያዊም ሆነ የቴክኖሎጂ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝና ከዚህ በተጨማሪም በአጠቃላይ ትምህርት ላይ የሚገኙ ተማሪዎችንም ተደራሽ ያደረገ የተለያዩ ስራወች እየተሰሩ መሆኑን አንስተው ለዚህ ሁሉ ዋና እና መሰረቱ የአሰልጣኝ መምህራኑ መብቃት በመሆኑ ከነገ ሚያዚያ 7/2017 ዓ.ም ጀምሮ ምዘናው የሚካሄድ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 6/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
