1 067
Subscribers
+424 hours
-27 days
+230 days
Posts Archive
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+3
#ዜና|የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASTRIP ፕሮጀክት የGRM ኮሚቴ 4ተኛ ሩብ አመት መደበኛ ስብሰባውን አከናወነ፡፡
በኮሌጁ እየተገነባ ያለው የልህቀት ማእከል ግንባታው ምንም ችግር ሳይፈጠር እና ማህበረሰቡ ላይ ተጽእኖ ሳይኖረው በአግባቡ ተገንብቶ ለሚፈለገው አላማ እንዲውል እንዲሁም ችግር ቢከሰት በተገቢው መንገድ እንዲፈታ እያደረገ ላለው አስተዋጽኦ የGRM ኮሚቴ ምስጋና ያቀረቡት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ አያይዘውም ባለፉት 3 ሩብ አመታት በኮሌጁ፣ በኮሚቴው እንዲሁም በፕሮጀክቱ በኩል የተሰሩ ስራዎች አመርቂ መሆናቸውን የተናገሩ ሲሆን በቀጣይም የሚሰሩ ስራዎች በሙሉ የማህበረሰቡን፣ የኮሌጁ እንዲሁም የመንግስትን ፍላጎት በተከተለ መልኩ ሊሰራና ችግሮችም በተገቢው መንገድ እንዲፈቱ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡
በስብሰባው ላይ በርካታ ባለድርሻዎች እና የማህበረሰቡ ተወካዮች የተገኙ ሲሆን በእለቱም በዓመታዊ የግንባታ ሂደት እና የቅሬታ አፈታት ሁኔታ እንዲሁም ቀጣይ የግንባታ ቦታ እና ከማህበረሰቡ የሚጠበቁ ስራዎች ላይ በሰፊው ውይይት የተደረገ ሲሆን ለቀጣይ ስራም አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሰኔ 16/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ በኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት እየተካሄደ የሚገኘው የምልከታ መድረክ በተጠናከረ መልኩ በመካሄድ ላይ ይገኛል::
ሰኔ 14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመንት በኮሌጁ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የስልጠና አሰጣጥ ትግበራን በተመለከተ እያካሄደ የሚገኘው የግምገማ መድረክ በዚህ ሳምንትም ቀጥሎ ተካሂዷል::
የምልከታ ቡድኑ በተዘጋጀው መርሃ-ግብር መሰረት በዚህ ሳምንት የኤሌክትሪካል/ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት እና የቢዝነስ ዲፓርትመትን የተመለከተ ሲሆን በዚህም የትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በ2017 ዓ.ም የስልጠና ዘመን ከተቀመጠው ግብ አንፃር ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራት መመልከትም ተችሏል::
የቀረቡት የአፈፃፀም ሪፖርቶችን መነሻ በማድረግም በምልከታ ቡድኑ ሀሳብ አስተያየት የተሰጠባቸው ሲሆን ጥሩ አፈፃፀም በታየባቸው ጉዳዮች ላይ አውቅናን በመስጠት እንዲሁም ዝቅተኛ እፈፃፀም በተስተዋለባቸው ጉዳዮች ላይም ዲፓርትመንቶቹ በቀጣይ ትኩረት ሰጠተው እንዲሰሩ ግብረ-መልስ ተስጥቷል::
በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የሚካሄደው ይህ የግምገማ መድረክ በቀጣይም በተቀረሩት ዲፓርትመንቶች ላይ በተቀመጠው መርሃ-ግብር መሰረት የሚቀጥልም ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+9
#ዜና| የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ከሴት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማጠናከር በዘርፉ ላይ ያለውን የግንዛቤ ችግር መፍታት ያስፈልጋቸዋል ተባለ።
ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያ ሴቶች ማህበር ለድሬዳዋ ቅርንጫፍ አባላት በኢንተርፕርነርሺፕ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና በዛሬው እለት አጠናቀቀ፡፡
በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ ዲን ወ/ሮ ትግስት በዙ እንደ ገለጹት ሃገራችን ኢትዮጵያ አሁን ላለችብት እድገት እንዲሁም ቀጣይ ለምትደርስበት የእድገት ደረጃ ለመድረስ የሴቶች ተሳትፎ ወሳኝ ነዉ። ስለዚህ ሴቶችን በማብቃትና አካታች እቅዶችን ማዘጋጀት ያስፈልጋል ይሆንንም ደግሞ ኮሌጁ እየሠራበት ይገኛል ያሉ ሲሆን፡፡
አያይዘውም የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ከሴት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማጠናከር በዘርፉ ላይ ያለውን የግንዛቤ ችግር መፍታት ያስፈልጋቸዋል እንዲሁም ባለሙያዎችን በማብቃት ሴቶችን ወደ አመራር ለማምጣት እድል ልንሰጥ ይገባል ብለዋል፡፡
በስልጠናው ላይ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሙያ ሴቶች ማህበር ከድሬዳዋ ቅርንጫፍ አባላት የተውጣጡ ከፍተኛ ባለሞያዎች የተሳተፉ ሲሆን ከዚህ በፊት በ ህይወት ክህሎት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና መሠጠቱ ይታወሳል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ሰኔ 14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 ዓ.ም "ብሩህ" የንግድ ፈጠራ ሀሳብ ውድድር አካሄደ።
ውድድሩ የንግድ ፈጠራ ሀሳብ ያላቸው ወጣቶች፥ ሀሳባቸውን ወደ ተግባር መለወጥ እንዲችሉ የሚያግዝ ነው ተብሏል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፥ ቢሮው የአስተዳደሩን ተጨባጭ ሁኔታ በማገናዘብ ለዜጎች የስራ እድል የመፍጠርና የማመቻቸት ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጠቁመው፥ በዚህ ውድድር የተሳተፉ ወጣቶችን በሀሳብ ከመደገፍ በተጨማሪ ለአሸናፊዎች የገንዘብ ሽልማት መዘጋጀቱን ገልፀዋል።
በቢሮው የስራ እድል ፈጠራና የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማስተባበሪያ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሰኢድ አሊ በበኩላቸው፥ በውድድሩ የተሻለ የንግድ ፈጠራ ሀሳብ መኖሩን ከማሳየት ባሻገር፥ በሀገር አቀፍ ደረጃ ተሸላሚ የሚሆኑ የድሬዳዋ ወጣት ስራ ፈጣሪዎች እንደሚወጡ ይጠበቃል ብለዋል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ባዘጋጀው ውድድር ላይ በተሳታፊ ተወዳዳሪዎች አረንጓዴ አካባቢ መፍጠር ፥ ፕላስቲክን መልሶ የመጠቀም ቴክኖሎጂ፥ የዲጂታል ገበያ እና የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ጨምሮ በርካታ የፈጠራ ሀሳቦች ቀርበዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 13/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ሠራተኞች ይቀነሳሉ በሚል የሚናፈሰውን ወሬ በሚመለከት የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) የሰጡት ማብራሪያ
ለተሟላ ነፃነትና ኢኮኖሚያዊ እድገት የስራ ባህልን ማሳደግ ቁልፍ ጉዳይ ነው - ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር "የስራ ባህልና ምርታማነት ለሀገር ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሃሳብ ያዘጋጀው የፓናል ውይይት በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል።
ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት÷ ከዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጋር አብሮ ለመራመድ ከስራ ባህል አስተሳሰብ ጀምሮ እስከ ተግባር መለወጥ ያስፈልጋል።
ለተሟላ ነፃነትና ኢኮኖሚያዊ እድገት የስራ ባህልን ማሳደግ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን አንስተው÷ የስራ ባህልን ለማምጣት የአስተሳሰብ እና የእይታ ለውጥ ማድረግ እንዲሁም በየአካባቢው ያለ ፀጋን መመልከት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ ስራ መገለጫቸው የሆኑና ኢኮኖሚያዊ ህልውናቸውን ያረጋገጡ ዜጎች አንዲኖሯት የስራ ባህልን እያሳደገች እንደምትገኝ ጠቅሰው÷ ቀጣዩ ትውልድም በዚህ የታነፀ እንዲሆን በትኩረት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ በበኩላቸው÷ ተቋማቸው የስራ ባህል ሊያሳድጉ የሚችሉ በርካታ ተሞክሮዎችን በማስተላለፍ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።
የፓናል ውይይቱም የስራ ባህል ለውጥ ማምጣት ላይ ከባለድርሻ አካላት ለመምከርና የጋራ አቋም ይዘው ለመስራትና ለማገዝ ያለመ መሆኑን አመላክተዋል፡፡
በመድረኩ ጥናታዊ ጽሑፍ ቀርቦ ከፌደራልና ከክልል ተቋማት የተውጣጣና ሌሎች ተጋባዥ ተሳታፊዎች እየተወያዩበት ይገኛል፡፡
©️FMC
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከኔዘርላንድ የልማት ድርጅት (SNV) ጋር በመተባበር በወጣት፣ ሴቶች እና አካል ጉዳተኞች ለሚመሩ በአስተዳደሩ ከተማና ገጠር ለሚገኙ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በበግና ፍየል ማድለብ ለተሰማሩ በአጠቃላይ አስር ማህበራት ስልጠና አዘጋጀ፡፡
እንደሚታወቀው ከአራት ወር በፊት ለእያንዳንዱ ኢንተርፕራይዝ 100,000 ብር የሚገመት ስራ ማስጀመሪያ ድጋፍ የተደረገላቸው ሲሆን የድጋፍ ርክክብ ስነ ስርዓቱ የቢሮው ተወካይ እና የልማት ድርጅቱ ተወካይ እንዲሁም የእንስሳት ጤና እና ሀብት ልማት ተወካይ በተገኙበት የተደረገ ነበር የተደራጁት ወጣቶች፣ ሴቶችና አካል ጉዳተኛ ዜጎች የሥራ እድል ለራሳቸውና ለሌሎች እንዲፈጥሩ ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡
የዛሬው መድረክም ኢንተርፕራይዞቹ በSNV እና በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ትብብር በአስተዳደሩ ገጠር ሁለት በከተማ ስምንት ተደራጅተው ወደ ስራ የገቡ ለስራ ማስጀመሪያም የተደረገላቸው ድጋፍ ተጠቅመው ያስገኙትን ውጤት ከአራት ወራት በኋላ ክትትልና ድጋፍ በሚደረግላቸው ጊዜ የጋጠሟቸውን ችግሮች መነሻ በማድረግ ልምድ የሚለዋወጡበትና በስልጠና አቅማቸው የሚገነባበት ሁኔታ ያመቻቸ ሆኗል፡፡
በመድረኩ የተገኙት የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ቢሮው የአስተዳደሩ ዜጎች በማህበር ተደራጅተው ኢንተርፕራይዝ መስርተው ወደ ስራ ለሚሰማሩ የተለያዩ የማደራጀት፣ የስልጠና እና የብድር ምችችት ድጋፎችን እንደሚያደርግ ገልጸው በተለይም እንደ SNV ካሉ አጋር አካላት ጋር በመቀናጀት ብዙዎችን ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 11/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ከ2014-2017 ዓ.ም በስድስት የተለያዩ አገር በቀል እውቀቶች ላይ የተደረገ የዳሰሳ ጥናት ቀረበ፡፡
በዳሰሳ ጥናቱ የተለዩ የሙያ አይነቶች
• የሐረሪ ማህበረሰብ ባህል የእደ ጥበብ ውጤቶች
• ባህላዊ ህክምና
• የአሉሚኒየም ውጤቶች
• የንብ ማነብ
• ብረታ ብረት
• ባህላዊ ሽመና
በዚሁም መሰረት በ2017 ዓ.ም ላይ የአሰልጣኝና የሰልጣኝ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ሰነድ ለማዘጋጀት በሁሉም በአስተዳደሩ ወረዳዎች መጠይቅ በመሙላት የተሰበሰበና የዳሰሳ ጥናቱ የተዘጋጀ መሆኑና በቀጣይም በተለዩት ሙያዎች ለስልጠና የሚያስፈልጉ ግብዓቶች፤ የስልጠና ቦታና አሰልጣኞችን በማዘጋጀት ለአስተዳደሩ ሥራ ፈላጊ ዜጎች አማራጭ የስራ ዕድል እንደሚፈጠር የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 11/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ከ2014-2017 ዓ.ም በስድስት የተለያዩ አገር በቀል እውቀቶች ላይ የተደረገ የዳሰሳ ጥናት ቀረበ፡፡
በዳሰሳ ጥናቱ የተለዩ የሙያ አይነቶች
• እደ ጥበብ (የሐረሪ ኮፍያ)
• ባህላዊ ህክምና
• የአሉሚኒየም ውጤቶች
• የንብ ማነብ
• ብረታ ብረት
• ባህላዊ ሽመና
በዚሁም መሰረት በ2017 ዓ.ም ላይ የአሰልጣኝና የሰልጣኝ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ሰነድ ለማዘጋጀት በሁሉም በአስተዳደሩ ወረዳዎች መጠይቅ በመሙላት የተሰበሰበና የዳሰሳ ጥናቱ የተዘጋጀ መሆኑና በቀጣይም በተለዩት ሙያዎች ለስልጠና የሚያስፈልጉ ግብዓቶች፤ የስልጠና ቦታና አሰልጣኞችን በማዘጋጀት ለአስተዳደሩ ሥራ ፈላጊ ዜጎች አማራጭ የስራ ዕድል እንደሚፈጠር የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሰኔ 11/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from E-LMIS - ብቁ
የስራ ማስታወቂያ ለስራ ፈላጊዎች!
የሥራ አይነት፡ ሞግዚት /Nanny/
የሥራ ቦታ፡ ኳታር
ብዛት፡ ሰማንያ (80)
ጾታ፡ ሴት (ሴ)
ሀይማኖት፡ የእስልምና እምነት ተከታይ የሆነች
እድሜ፡ ወጣት (18 እስከ 40)
መስፈርት፡ ቢያንስ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ያጠናቀቀች፣ የአእምሮ እና የጤና እክል የሌለባት፣ ቶሎ ከአካባቢው ጋር መላመድ የምትችል፣ ጥሩ ስነምግባር ያላት፣ ታማኝ እና ቀልጣፋ የሆነች።
ተጨማሪ ክህሎት፡ የቋንቋ ችሎታ ዐረቢኛ
የቅጥር ሁኔታ፡ የተመረጡ ዜጎች ለ6 ወራት በኳታር የሞግዚት ማሰልጠኛ አካዳሚ /Qatar Nanny Training Academy/ ውስጥ ተከታታይ ስልጠና ይወስዳሉ። በስልጠና ቆይታቸው፤ መጠለያ፣ ምግብ፣ የጤና ኢንሹራንስ፣ አበል፣ እና የቲኬት ወጪ በማሰልጠኛ ተቋሙ የሚሸፈን ሲሆን ከስልጠና በኋላ በማሰልጠኛ ተቋሙ በሚደረግ የቅጥር ምደባ ወደ ስራ የሚገቡ ይሆናል። በስራ ላይ ሆነው ሙሉ የጤና ኢንሹራንስ ቀጣሪው ድርጅት ይሸፍናል
ማሳሰቢያ፡ በዚህ የሥራ እድል ተጠቃሚ ለመሆን በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ካዛንቺስ በሚገኘው የሥራ ስምሪት ቢሮ ያላችሁን የት/ት ማስረጃ፣ መታወቂያ/ፓስፖርት/መንጃ ፍቃድ እንዲሁም ሌሎችን ማስረጃዎችን በመያዝ፤ በአካል በመምጣት ወይም ይህንን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም (https://forms.gle/KBwUTKYYJBXipGbb6) እስከ ሰኔ 11 2017 ድረስ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
በግል የስልክ ቁጥራችሁን በE-LMIS ስርዓት ላይ (lmis.gov.et) የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ተመዝግባችሁ የሰራተኛ መለያ ቁጥር ማግኘት ይጠበቅባችኋል።
የሰው ሃይል ጥያቄውን ያቀረቡት ድርጅቶች እራሳቸው በE-LMIS ሲስተም በኩል አወዳድረው ስለሆነ የሚቀጥሩት ከላይ የተቀመጡትን መስፈርቶች ማሟላት የግድ ይጠበቅባችኋል።
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
በኮሌጁ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች ላይ የስልጠና አሰጣጥ ትግበራ የምልከታ መድረክ መካሄድ ጀመረ::
ሰኔ 9/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመት በኮሌጅ የሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የስልጠና አሰጣጥ ትግበራን በተመለከተ የግምገማ መድረክ እያካሄደ ይገኛል::
ለግምገማ መድረኩ በተዘጋጀው መርሃ-ግብር መሰረት የአውቶሞቲቭ እና የአይ.ሲ.ቲ ዲፓርትመንቶች በ2017 ዓ.ም ያከናወኗቸውን ዝርዝር ተግባራት የማኔጅመንትና አካዳሚክ ኮምሽን አባላት በተገኙበት ያቀረቡ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት መሰረትም ሰፊ ውይይቶች ተካሂደው ግብረ-መልስ ተሰጥቶባቸዋል::
የግምገማ መድረኩ ዋና አላማ በበጀት አመቱ በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች በተሻለ ደረጃ የተከናወኑ አፈፃፀሞችን ይበልጥ ተጠናክረው እዲቀጥሉ ለማስቻል እንዲሁም እንደ ክፍተት በተለዩ ችግሮች ላይ በቀጣይ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ለማስቻልም እንደሆነ ተገልፇል::
በትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የሚካሄደው ይህ የግምገማ መድረክ በቀጣይም በተቀረሩት ዲፓርትመንቶችም ላይ በተቀመጠው መርሃ-ግብር መሰረት የሚቀጥልም ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
