1 069
Subscribers
+224 hours
No data7 days
+230 days
Posts Archive
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና የተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት በሁለቱ የመንግስት እና የግል ኮሌጆች ላይ የኢንስፔክሽን ምልከታ ማካሄድ ጀመረ፤
በዚህም ኢንስፔክሽን ኮሌጆቹ የሚሰጡትን ትምህርትና ስልጠና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እየተሰጡ ስለመሆኑ በአካል በመመልከትና በማረጋገጥ የሚታዩ ክፍተቶችና ችግሮች ቢኖሩ በአጭር ጊዜ ለማስተካከል እዲያስችል ግብረመልስ የሚሰጣቸው ይሆናል።
የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ስለ ኢንስፔክሽኑ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠናን ጥራትን ማረጋገጥ ዋና አላማው አድርጎ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሴክተሮችን ባሳተፈ መልኩ እንደሚካሄድና በሁሉም ኮሌጆች በተመሳሳይ የሚቀጥል መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 25/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ወጣቶች በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያለውን ምቹ አጋጣሚ በመረዳትና ዘርፉንም በመቀላቀል በወርቃማ ጊዜያቸው አምራችና ተፅዕኖ ፈጣሪ ዜጋ የሚያደርጏቸው አማራጮች ላይ በንቃት ሊስተፉ እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ የሚሰራውን ግንዛቤ የመፍጠር ስራ በማጠናከር በሳብያን ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለሚገኙ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዘርፉን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄዷል::
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ ተማሪዎች ስለ ዘርፉ ተገቢውን ግንዛቤ እንዲኖራቸው ከማደረግ አኳያና እንደ ሀገር ከተያዘው የትኩረት አቅጣጫም አንፃር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ለወጣቱ በተለይም ከዚህ በኃላ ወደዘርፉ ለሚቀላቀሉ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ብዙ መልካም እድሎችን የያዘ ዘርፍ መሆኑን በዝርዝር ማብራሪያ በመስጠት በሰፊው ግንዛቤ የመፍጠር ስራ መስራት ተችሏል::
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ለተማሪዎች መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በንግግራቸው የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች በ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የሚያስመዘግቡትን ውጤት ተከትሎ ዩኒቨርሲቲ በመግባትና ባለመግባት አቅማቸው እንደማይለካ በመናገር የቴክኒክና ሙያም ሌላኛው የተሻለው አማራጭ መሆኑንም ከወዲሁ መረዳት ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን በተጨማሪም ባለው ነባራዊ ሁኔታ ዩኒቨርሲቲ ከሚገቡትም ይልቅ በቴክኒክና ሙያ ውስጥ የሚያልፉ ዜጎች በየትኛው መመዘኛ የተሻለ እድል ያላቸው መሆኑንም አፅዕኖት ሰተው ተናግረዋል::
አክለውም በተሻሻለው ፖሊሲ መሰረት የትኛውም በቴክኒክና ሙያ የሚያልፍ ሰልጣኝ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሊያሳካ የሚችለውን የመጨረሻውን የPHD (Level 8) ድረስ እራሱን እያሻሻለ መድረስ የሚያስችለው አሰራርም መዘርጋቱን የገለፁ ሲሆን ተማሪዎችም የወደፊት እጣፈንታቸውን የሚወስኑበት ምርጫቸውን በጥንቃቄና ብስለት በተሞላበት መንገድ እንዲወስኑ ምክር ለግሰዋል::
የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎቶችን በማስገንዘብ የፈጠራ ሃሳባቸውን በኮሌጃችን ውስጥ እንዲያዳብሩ ለማድረግ ዝግጅት መደረጉን የገለፁት በኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን የሆኑት አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ አክለውም በት/ቤቱ ውስጥ ፍላጎት ያላቸው ወጣቶችን በማቀናጀት የቴክኒክና ሙያ ክበብ እንደሚቋቋም ጠቅሰው ኮሌጁም ከዚህ ጋር ተያይዞ አስፈላጊው ድጋፍ ያደርጋልም ብለዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
የካቲት 25/2017 ዓ.ም
በአዲስ የተዘጋጁና የተከለሱ የሙያ ደረጃዎች፤ የስርዓተ-ስልጠና እና የማሰልጠኛ መሳሪያዎች የማስተዋወቂያ መድረክ ተዘጋጀ፤
በዚህም መድረኩም አዲሱ የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲን መሰረት ተደርገው በ8(ስምንት ዘርፍ) የአገሪቱ የትኩረት ዘርፎችን መሰረት ተደርገው የተከለሱና የተዘጋጁ 192 ሙያ ደረጃዎች፤ የስርዓተ ስልጠና እና የስልጠና መርጃ መሳሪያዎችን በመንግስት እና የግል ኮሌጆች የዲፓርትመንት ተጠሪዎች፤ ስልጠናውን ለሚመሩ የስልጠና አስተባባሪዎችና ስልጠናውን ለሚደግፉ የቢሮው ባለሙያዎች በነባሩና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ዝርዝር ሙያዎችን በማስተዋወቅ፤በማሰራጨትና አተገባበር ላይ የታዩ እና ያጋጠሙ አውንታዊና አሉታዊ ነገሮች ላይ በጋራ በመመክርና በመወያት ለመተግበርና በስራ ላይ ለማዋል መግባባት ተፈጥሯል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 21/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለታላቁ የረመዳን ፆም ወር በሰላም አደረሳችሁ።
ረመዳን ከሪም !!
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
#ዜና| ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ከመደበኛው ስልጠና በተጨማሪ ትምህርትና ስልጠናው ለሁሉም ተደራሽ እንዲሆን በገጠር ክላስተር የሚገኙ ወጣቶችን እና ሴቶችን በአጫጭር ስልጠናዎች በማሰልጠን የእድገቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚሰራው ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ተባለ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከ22 በላይ ከተለያዩ ገጠር ክላስተር ወረዳዎች የተውጣጡ ሰልጣኞችን የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዲሁም የቢሮው ም/ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በተገኙበት በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞች በዛሬው እለት አስመረቀ ፡፡
ትምህርት እና ስልጠና ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ እድገት ቁልፍ መሳሪያ ነው።ይህንን መሳሪያ ደግሞ የከተማው ወጣቶች ብቻ ሳይሆኑ በገጠር ክላስተር የሚገኙ ወጣቶችም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሊሰራ ይገባል ያሉት በምርቃቱ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው ሲሆኑ ፡፡ ኃላፊው አያይዘውም ይህ ስልጠና ከዚህ በፊት በገጠር ክላስተር የሚገኙ ሴቶች በስልጠና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይነሱ የነበሩ ጥያቄዎችን የመለሰ ነው ፡፡ በቀጣይም በዚህ ስልጠና የተሳተፉ ሴቶችን በማደራጀት እንዲሁም ከኮሌጁ ጋር በመተባበር የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ እንዲሰሩ እንደሚደረግ ገልጸዋል ፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያ ወደ ብልፅግና ለምታደርገው ጉዞ በሙያዊ ክህሎት እና በስነምግባር የታነፀ ተነሳሽነት የተላበሰ አምራች ዜጋን በጥራት እና በብዛት በመፍጠር ረገድ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ እድገት በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን የገለጹትየስራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ዳይሬክተር የሆኑት ክብርት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጣፋ ሲሆኑ አያይዘውም የሃገራችን ብልጽግና እንዲረጋገጥ በገጠር ክላስተር የሚገኙ ወጣቶችን ያማከለ ስራ ሊሰራ ይገባል ብለዋል ።
በመጨረሻም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ ኮሌጁ በመደበኛ ከሚሰጣቸው ትምህርትና ስልጠናዎች በተጨማሪ ብዛት ያላቸውን የአጫጭር ስልጠናዎች አዘጋጅቶ ለከተማው ወጣቶች ብሎም ለገጠሩ ክላስተር ወጣቶች እየሰጠ ይጋኛል ያሉ ሲሆን አያይዘውም በዛሬው እለት የተመረቃችሁ ለኮሌጁ አበንባሳደሮች ናችሁ በአካባቢያችሁ የሚገኙ ወጣቶች በኮሌጁ በመገኘት ትምህርትና ስልጠናዎችን እንዲያገኙ ማድረግ ይኖርባችኋል ብለዋል፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዛሬው እለት ያስመረቃቸው 10 በምግብ ስራ፣6 በጸጉር ስራ እንዲሁም 6 በልብስ ስፌት ሲሆን በአጠቃላይ 240 ሰአታትን በስልጠና አሳልፈዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
የካቲት 21/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር አዘጋጅነት ለሚካሄደው 4ኛው ዙር የ2017 ዓ.ም የክህሎት ውድድር በአስተዳደር ደረጃ ለማካሄድ ተወዳዳሪዎች በውድድር መስፈርቱ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
በቀጣይም በተለያዩ ሙያዎች ላይ በአስተዳደር ደረጃ ውድድር የሚያካሂዱ ሲሆን ውድድሩን በበላይነት የሚያጠናቅቁ ተወዳዳሪዎች አስተዳደሩን በመወከል በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው የክህሎት ውድድር አልፎም እስከ አለም አቀፍ ድረስ የሚዘልቅ በዋናነት የስልጠና ጥራትንም ከማሳደግ አንፃር ጉልህ አስተዋፅኦ የሚኖረው ይሆናል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 20/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ለግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎችና ለአገልግሎት ተጠቃሚ ድርጅቶች አዲስ ተሸሽሎ የወጣውን አሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 እና አዋጁን መሰረት በማድረግ በወጣው መመሪያ ቁጥር 45/2013 ዙሪያ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ አካሄደ፤
በዋናነት ስልጠናው እንዲዘጋጅ የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ሕግና አሠራርን በመከተል ፍትሃዊ፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው የሥራ ስምሪት አገልግሎት በሀገር ውስጥ የሚሰጡበትን ሁኔታ መወሰን በማስፈለጉ፤ በኤጀንሲ አማካኝነት ለሥራ የተሰማራውን ሠራተኛ መብትና ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ኤጀንሲው እና የአገልግሎት ተጠቃሚው ድርጅት ሊኖራቸው የሚገባውን የጋራና የተናጠል ኃላፊነት ለይቶ የማመልከቱ ተገቢነት ስለታመነበት ነው፤
በዚህም የስልጠና መድረክ ይህንን መመሪያ ኤጀንሲዎቹ እንዲረዱ ከማድረጉ ጎንለጎን እንደከዚህ ቀደሙ ህገወጥ የሆኑትን ለመከታተልና ለመቆጣጠር የሚያስችል አሰራር በመዘርጋት ህጋዊነትን የሚያበረታታ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 20/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+4
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASTRIP ፕሮጀክት የGRM ኮሚቴ 3ተኛ ሩብ አመት መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው እለት አከናወነ፡፡
የGRM ኮሚቴ ችግሮችን ለመፍታት የሚሰራቸው ስራዎች የልህቀት ማእከሉ በአግባቡ ተገንብቶ ለሚፈለገው አላማ እንዲውል እያስቻለ ነው ያሉት የEASTRIP ፕሮጀክት ኮርድኔተር የሆኑት ወ/ሮ አሽረፊያ አብዲ ሲሆኑ አያይዘውም ኮሚቴው ስራዎችን በትጋትና በጥራት እንዲሁም በታማኝነት ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡
በመድረኩ ያለፉትን 8 ወራት ህንጻውን እየገነባ ባለው ኮንትራክተር በኩል የተሰሩ ስራዎችን እንዲሁም የተፈቱ ቅሬታዎችን ለኮሚቴው በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን፡፡ በቀረበው ሪፖርት ላይና በቀጣይ ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ የኮሚቴው አባላት በጥልቀት ተወያይተዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
የካቲት 20/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+6
#ዜና| ሴት አሰልጣኝ መምህራንን በማብቃት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠናን ሁሉን አካታች ተደርጎ ሊሰራ ይገባል ተባለ፡፡
ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ EASTRIP ፕሮጀክት ለኮሌጁ ለሴት የአካዳሚክ ባለሙያዎች፣ ሴት ዎርክ ሾፕ ቴክኒሻን እና የዲፓርትመንት ኃላፊዎች በሥርዓተ-ፆታ ምላሽ የማስተማር ዘዴዎች ላይ(Gender-responsive teaching methods for Female Academic staff , female work shop technician and Department heads )ስልጠናዎችን ከሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ በመጡ ባለሙያ ሲሰጥ የነረውን ስልጠና በዛሬው እለት አጠናቀቀ ፡፡
በሰልጠናው ማብቂያ ወቅት ተገኝተው ስልጠናውን በንግግር የዘጉት የኮሌጁ EASTRIP ፕሮጀክት ኮርድኔተር ወ/ሮ አሽረፊያ አብዲ ሲሆኑ በንግግራቸውም የሃገር ብልጽግና ያለሴቶች ተሳትፎ እንደማይረጋገጥ ሁሉ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠናም ያለሴቶች ተሳትፎ እንዲሁም ሁሉን አካታች በሆነ መለኩ ካልተሰራበት ከግብ ሊደርስ አይችልም ብለዋል፡፡ አያይዘውም ኮሌጁ በሴቶች ተሳትፎ ላይ አካታች እቅዶችን በማዘጋጀት እየሰራ እንዳለ መስልጠናው ማጠናቀቂያ ወቅት ለተሳታፊዎች አስረድተዋል፡፡
በስልጠናው ላይም የተሳተፉ ሴት አሰልጣኝ መምህራን እንዲሁም ወርክሾፕ ባለሙያዎች እና የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች ስልጠናው በመሰጠቱ እንደተደሰቱና በቀጣይም የስልጠናውን ውጤት በሚሰሩት ስራዎች ላይ በማስገባት እንደሚተገብሩት ተናግረዋል፡፡
ከዚህ ቀደም በስርዓተ-ፆታ ላይ የተመሰረተ ጥቃትን እንዲሁም የህይወት ክህሎት እና ስራ ፈጠራ በተመለከተ የአቅም ግንባታ ስልጠና ለሴቶች የአስተዳደር ሰራተኞች መሰጠቱ የሚታወስ ነው፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
የካቲት 20/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ የከተማ ዘጠኝ ወረዳዎች ስር የሚገኙ አስራ አንድ አንድ ማዕከላት ስር የሚገኙና በቢሮው ኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የተለያዩ ድጋፎች የሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞችን ወደ ሞዴል ኢንተርፕራይዝነት ለማሳደግ የሚያስችል የመስክ ምልከታና ልየታ ተደረገ።
በዚህም የተለዩ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች በበጀት አመቱ መጨረሻ በአስተዳደር ደረጃ ዕውቅና የሚሰጣቸው ሲሆን በአስተዳደሩ ገጠር ወረዳዎች ላይ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች በተመሳሳይ ልየታ የሚደረግ ይሆናል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 19/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+4
#ሁለተኛ ቀን የስልጠና ውሎ|
ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በEASTRIP ፕሮጀክት አማካኝነት በሥርዓተ-ፆታ ምላሽ የማስተማር ዘዴዎች ላይ ለሴት የአካዳሚክ ባለሙያዎች፣ ሴት ዎርክ ሾፕ ቴክኒሻን እና የዲፓርትመንት ኃላፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ በተጋበዙ አሰልጣኞች ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል፡፡
በመጀመሪያው ቀን ስልጠና በኮሌጆች የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራንና ባለሙያዎች ከጀንደር ጉዳዮች ጋር የተገናኙ ሃሳቦችና ተሞክሮዎችን ከስራና ክህሎት ቢሮ፣የሁለቱም የመንግስት ኮሌጆች በጋራ በመሆን የተመለከቱ ሲሆን ከዚህ ባለፈ የእርስበርስ ግንኙነትን ሊያጠናክሩና ወደ መጡበት ተቋም ሲመለሱ ግብ ተኮር የሆነ ውጤት የሚያስገኝ ስራ መስራት የሚያስችላቸውን ግንዛቤ እዲፈጥሩ የሚያስችል ስልጠና እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡
በሁለተኛው ቀን ደግሞ ለኮሌጁ ለሴት የአካዳሚክ ባለሙያዎች፣ ሴት ዎርክ ሾፕ ቴክኒሻን እና የዲፓርትመንት ኃላፊዎች በሥርዓተ-ፆታ ምላሽ የማስተማር ዘዴዎች ላይ(Gender-responsive teaching methods for Female Academic staff , female work shop technician and Department heads )ስልጠናዎችን ከሃሮማያ ዩኒቨርሲቲ በመጡ ባለሙያ ተሰጥቷል፡፡
በስልጠናው ላይ በኮሌጁ የሚገኙ ሴት አሰልጣኝ መመህርራኖች፣ሴት ዎርክ ሾፕ ቴክኒሻን ባለሙያዎችእንዲሁም የዲፓርትመንት ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ ፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
የካቲት 19/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
