1 068
Subscribers
+424 hours
-27 days
+230 days
Posts Archive
በፕሮግራም በጀት ዝግጅትና ትግበራ ዙሪያ የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ቴክኒካል ኮሚቴ ከአስተዳደሩ የፕላን ኮሚሽን ከተወከሉ ደጋፊ አካላት ጋር ቀጣይ አቅጣጫዎችን የማስቀመጥና ከስራው ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደረገ።
ከዚህ በፊት ሲተገበር የቆየው የላይን በጀቲንግ በስራ ላይ የሚገኝ ሲሆን ከዚሁ ጎን ለጎን ፕሮግራም በጀት ዝግጅቱ በዋናነት ስራና ስራ ላይ ትኩረቱን አድርጎ ይተገበራል፤ በአገር አቀፍ ደረጃ በፌደራል መስሪያ ቤቶች እየተተገበረ የሚገኝ ሲሆን በድሬዳዋ አስተዳደርም ቢሮውን ጨምሮ በአስራ አራት መስሪያ ቤቶች ላይ በቀጣይ 2018 ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናል፡፡
በመሆኑም የቢሮው ቴክኒካል ኮሚቴ የቀጣይ ሶስት አመታትን ዕቅድ የሚያዘጋጅ እንደሚሆንና በዚህም ተጠያቂነትን በማረጋግጥ፣ አፈጻጸምን በማሳደግ እንዲሁም የመንግስት ሃብት ብክነትን በመቀነስ ረገድ የፕሮግራም በጀት ትግበራ ፋይዳው ላቅ ያለ በመሆኑ ቢሮውም ለዚህ ስራ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚከታተልና እንደሚፈጽም የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው አረጋግጠዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት 15/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ከቤትዎ ሳይወጡ
ወደ ድሬዳዋ ይምጡ
እንዴት❓ በጣም ቀላል ነው። ከአሁን በኋላ የድሬ ጉዳይዎትን ለመጨረስ በአካል መምጣት አይጠበቅብዎትም።
በየትኛውም የአለም ጥግ ቢሆኑ፥ በእጅ ስልክዎ አማካኝነት የድሬዳዋ አስተዳደር መንግስታዊ ጉዳይዎትን፣ የንግድ ፍቃድ ማውጣትና ማሳደስን ጨምሮ፣ የመሬት እና ሌሎች ጉዳዮችን በOnline በቀላሉ መጨረስ ይችላሉ።
http://eservice.diredawa.et/ በመግባት እና በመመዝገብ የሚፈልጉትን የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አገልግሎቶች በፍጥነት ያገኛሉ።
አሁን! በአንድ ክሊክ ብቻ መገናኘት ችለናል። ገና ይቀጥላል። ይመዝገቡ፥ ቀልጣፋ አገልግሎት ያግኙ! አሁኑኑ ዲጂታል ድሬን ይቀላቀሉ
©️ Mayor Office ድሬዳዋ
የሥራ እድል ፈጠራን ዲጅታላይዝ በማድረግ አሰራራችንን ቀልጣፋ ማድረግ እና ውጤታማ ነትን ማረጋገጥ ያስችለናል።
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ካይዘንን በስራ ቦታና አካባቢ በቀጣይነት ተግባራዊ ማድረግ ምቹና ተስማሚ የስራ ቦታ መፍጠር ከማስቻሉ በተጨማሪ ዉጤታማ የጥራት አስተዳደር ስርዓትን በማሳደግ የስልጠና ጥራትን ማረጋገጥ ያስችላል ተባለ።
ግንቦት 05/09/2017 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የካይዘን ትግበራን በኮሌጁ በዘላቂነት መተግበር እንዲያስችል በተዘጋጀው የማስተግበሪያና የአፈፃፀም መከታተያ መመሪያ ላይ ለኮሌጁ የፑል አመራር አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል፡፡
በመድረኩ የካይዘን ማስተግበሪያ መመሪያው በኮሌጁ የኢ/ኤ/ቴ/ሽ/አ ስራ ሂደት የካይዘን ክፍል ተጠሪ በሆኑት አሰልጣኝ መ/ር አቤል ዘገየ አማካኝነት የቀረበ ሲሆን በተሰጠው ግንዛቤ መሰረትም በቀጣይ ለዚሁ ትግበራ በየክፍሉ በተመደቡ ባለሙያዎ አማካኝነት ካይዘንን በተቋሙ በተደራጀ መልኩ የመተግበርና የማስቀጠል ስራ እንደሚሰራም በመድረክ ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
+9
ካይዘንን በስራ ቦታና አካባቢ ተግባራዊ ማድረግ ብክነቶችን ከማስቀረት በተጨምሪም ቀልጣፋ የስራ እንቅስቃሴ እንዲኖር ያስችላል ተባለ::
ግንቦት 05/09/2017 ዓ.ም
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የካይዘን ትግበራን በኮሌጁ በዘላቂነት መተግበር እንዲያስችል በተዘጋጀው የማስተግበሪያና የአፈፃፀም መመሪያ ላይ ለኮሌጁ የፑል አመራር አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል፡፡
በመድረኩ የካይዘን ማስተግበሪያ መመሪያው በኮሌጁ የኢ/ኤ/ቴ/ሽ/አ ስራ ሂደት የካይዘን ክፍል ተጠሪ በሆኑት አሰልጣኝ መ/ር አቤል ዘገየ አማካኝነት የቀረበ ሲሆን በተሰጠው ግንዛቤ መሰረትም በቀጣይ ለዚሁ ትግበራ በየክፍሉ በተመደቡ ባለሙያዎ አማካኝነት ካይዘንን በተቋሙ በተደራጀ መልኩ የመተግበርና የማስቀጠል ስራ እንደሚሰራም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
በድሬዳዋ አስተዳደር እየተካሄደ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራን የሙያ ብቃት ምዘና ቀጥሎ የማኑፋክቸሪንግ አሰልጣኝ መምህራን በደረጃ አራት በማሽኒግ እና ሜካኒክስ ሙያዎች ሀያ አሰልጣኝ መምህራን በመመዘን ላይ መሆናቸውና በቀጣይ ቀናት የሚቀጥል መሆኑ ተገለጸ።
በአገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የክህሎት ውድድር፥ በሀርድዌር እና ኔትወርኪንግ ሰርቪስ ዘርፍ ያሸነፈው ሰልጣኝ ተማሪ ዮሐንስ ሞላን ጨምሮ፥ ድሬዳዋን ወክላችሁ የተሳተፋችሁትን በሙሉ ከልብ እያመሰገንኩ፥ የተገኘው ውጤት የጋራ ነውና እንኳን ደስ አለን ለማለት እወዳለሁ።
በቀጣይ በዚህ ውድድር የታዩ ድክመቶችን ማሻሻል ብሎም የአስተዳደሩን 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ተማሪዎች የቴክኖሎጂ ፈጠራ አቅም ማጎልበት ከቻልን፥ በአለም አቀፍ መድረኮች ላይ አሸናፊ የሚሆኑ ክህሎት ያላቸው ወጣቶችን እንደምናፈራ ፅኑ እምነት አለኝ። በርቱ እንበረታለን!
Dorgommii ogummaa kan sadarkaa biyyaalessaatti gaggeeyfameen, damee gosa 'Hardware and Networking Services' tiin kan injifate Barataan leenjifamaa Yohaanniis Mollaa dabalatee, warreen Dirree Dhawaa bakka-buutanii hirmaattan hunda keeysan Onneerraa isin galatoomfachaa, Bu'aan argame kun kan hunda keenyaa waan taheef Baga gammanne baga gammaddan jechuudhaan barbaada.
Ittifufiinsaan Dorgommii kana keessatti hanqinaalee mudatan addaa baasuufi fooyyessuun, dandeettii barattoota bulchiinsaa kan roga kalaqa teeknooloojiitiin sadarkaa 1ffaa fi 2ffaa caalmayaan foyyeeysuu dandeenyaan, Dargaggoota ogummaa qaban hedduu kanneen waltajjiiwwan idil-addunyaa irratti mo’attoota ta’an ni horanna je'etiin ciminaan amana. Jabaadhaa Ni jajjabaannaa!
~~
Waxaan aad ugu mahadcelinayaa arday Yohanis Mola iyo kooxda nagu matalaysay tartanka xirfadaha iyo hal abuurka qaranka wareegiisa afaraad oo guul ay kasoo hooyeen dhanka hardware iyo networking service.
Hadaan maanta saxno habacsanaanteena oon diirada saarno ardayda dugsiyada hoose iyo dhexe waxaan ku rajo waynahay in aan guulo waa weyn kasoo hoyn karo masraxyada caalamka. Dadaala waanu idin dhiirigelinaynaaye!
©️ ክቡር ከንቲባ kadir Juhar Ibrahim
4ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ተጠናቀቀ
“ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች” በሚል መሪ ሐሳብ ሲካሄድ የነበረው 4ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የማጠናቀቂያ መርሐ-ግብር ተካሂዷል፡፡
በውድድሩ 1ኛ የወጡ ተወዳዳሪዎች 500 ሺህ ብር፣ 2ኛ ለወጡ 400 ሺህ ብር እንዲሁም 3ኛ ለወጡ 300 ሺህ ብር ተሸልመዋል፡፡
ከድሬዳዋ አስተዳደርም በክህሎት፣ በቴክኖሎጂ እና በተግባራዊ ጥናትና ምርምር አሰልጣኝ መምህራን፣ ሰልጣኝ ተማሪዎች እና ኢንተርፕራይዞች ተሳታፊ ሆነዋል።
በውድድሩም ሰልጣኝ ተማሪ ዮሐንስ ሞላ በሀርድዌር እና ኔትወርኪንግ ሰርቪስ መስክ ተወዳድሮ አንደኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳልያ እና የ500 ሺህ ብር ተሸላሚ ሆኗል ለዚህም በተገኘው ውጤት የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት 2/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ሦስተኛ ዙር ትግበራ በሁለት ተከታታይ ዙሮች የህይወት ክህሎትና የስራ አፈላለግ ስልጠና ወስደው ያጠናቀቁ 1200 ሰልጣኞች የምርቃት መርሃግብር በድምቀት ተካሄደ፡፡
በዚህም የሰልጣኞች የምርቃት መርሃግብር ላይ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር ለሰልጣኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በስልጠናው ያገኙትን እውቀት በቀጣይ በስራ ላይ ለሚኖራቸው ስልጠና እንዲጠቀሙበት በማሳሰብ የሚመጡ እና የሚገጥሟቸን ፈተናዎች በጥንካሬ በማለፍ ለራሳቸውና ለሃገራቸው የሚጠቅሙ ዜጎች እንዲሆኑ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው በሁለት ዙሮች ለ12 ቀናት የህይወት ክህሎትና የስራ አፈላለግ ስልጠና በኮሌጆቹ ውስጥ ሲሰጣቸው የቆየ ሲሆን ይህንንም ሲያጠናቅቁ በመረጡት የሙያ ዘርፍ በአስተዳደሩ በሚገኙ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንደስትሪዎች ላይ የኪስ ገንዘብ እየታሰበላቸው በተግባር እየሰሩ እውቀትና ክህሎታቸውን የሚያዳብሩ እንደሚሆን ገልጸው በስልጠና ቆይታቸውም በኮሌጆቹ የህጻናት ማቆያ ቦታዎች ተዘጋጅቶላቸዋል በዚህም የልጅ እናት የሆኑ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች ስልጠናውን ሳይስተጓጎሉ እንዲወስዱ መቻሉን በማስታወስ ለዜጎች ሁሉን ተደራሽ የሚያደርግ የስራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎች በመሰራት ላይ ለመሆናቸው ይህ መርሃግብር ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።
በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ በአጠቃላይ በሁለት ዙር በሁለቱም ኮሌጆች ሰልጥነው ያጠናቀቁ ሰልጣኞች ብዛት አንድ ሺህ ሁለት መቶ መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይ ቀናትም ሰልጣኞቹን ከኢንዱስትሪዎች ጋር የማስተሳሰር ስራ የሚጠናቀቅ መሆኑን አስታውቀው ሰልጣኞቹን በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች በማሰልጠንና ሁኔታዎችን በማመቻቸት የተሳተፉ አካላትን ሁሉ አመስግነዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት 1/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ዛሬ የምናስቃኛቹ በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰልጣኝ ተማሪዎች የተሰሩና በ4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ላይ ለኤግዚቢሽን የቀረቡ ቴክኖሎጂዎችን ይሆናል፡፡
አንደኛው ኤሌክትሮኒክ ኢኪውፕመንት ኮንትሮል ሲስተም ሲሆን በቀላሉ በውሃ፣ በጸሃይ እንዲሁም በተለያየ ምክንያት ሊጎዱ ወይም ሊበላሹ የሚችሉ የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶችን ደህንነታቸውን ለማስጠበቅ ድጋፍ የሚያደርግ ቴክኖሎጂ ሲሆን ቁሳቁሶቹ ያሉበትን ሁኔታ እየተከታተለ ለሚመለከተው አካል መረጃ ይሰጣል፡፡
ሁለተኛው ወተር ቢሊንግ ሲስተም ሲባል በተለምዶ ባለው አሰራር የውሃ ቆጣሪ ንባብ የሚያደርግ ባለሙያ አድካሚ እና ጊዜ የሚወስድ ቤት ለቤት በመዞር የማንበብና ክፍያን የማሳወቅ ሂደትን በቀላሉ በእያንዳንዱ የውሃ ቆጣሪ የሚያልፈውን የውሃ ልኬት በተገጠመለት ሴንሰር በመለካት ለሚመለከተው አካል መረጃ የሚያደርስ ይሆናል፡፡
በቀጣይ ቴክኖሎጂዎቹን በሰፊው ወደ ስራ ለማስገባት ከሚመለከታቸው የዘርፍ አካላት ጋር ከኢትዮ ቴሌኮም ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየደረገ ሲሆን ከአስተዳደሩ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ጋር በቅርበት እየተሰራ ይገኛል፤ በተጨማሪም በኤግዚቢሽኑ ላይ ለኢንዱስትሪዎች ከሚደረግ ድጋፍ ጋር በተያያዘ በኮሌጁ የተሰሩ ችግር ፈቺ የሆኑ ስፔርፓርቶች ቀርበዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት 1/2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ሶስተኛ ዙር ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ የህይወት ክህሎት እና የስራ አፈላለግ ስልጠና ማጠቃለያ መድረክ በዛሬው ዕለት ተካሄደ።
የአረንጓዴ ክህሎት ቀን
አረንጓዴ ቀለም ብቻ ተደርጎ የተቆጠረበት ጊዜ ያበቃ ይመስላል ዛሬ ላይ አረንጓዴ ታዳሽ ሀይልን፣ ስማርት ግብርናን፣ ተረፈ ምርቶችንና ቆሻሻን መልሶ መጠቀም የሚያስችሉ የፈጠራ ሥራዎችን፣ አዲስ የኢነርጂ አማራጭ፣ የኤሌክትሪክ መኪና እያልን ብዙ ጉዳዮችን የሚወክል ሆኗል፡፡
በተለይ አረንጓዴ ክህሎት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ መገንባት ሚናው ላቅ ያለ ነው ለዚህም ወቅታዊና ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለው ጉዳይ ምላሽ የሰጠ በአስተዳደር ደረጃ በቴክኖሎጂ ድሬዳዋን ወክሎ በ4ኛው ሀገራዊ የክህሎት ውድድር ላይ ተሳታፊ የሆነ አሰልጣኝ መምህር ያሬድ ሁሉአለም በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአውቶሞቲቭ አሰልጣኝ መምህር ሲሆን ለውድድር ያቀረበው ቴክኖሎጂ አማራጭ ኃይል(Alternative Fuel) ከወዳደቁ የፕላስቲክ ቁሶች እና ከጃትሮፋና ከጥጥ ፍሬ ተክሎች በመቀላቀል(ባዮዲዝል) የተመረተ ለተሸከርክሪ የነዳጅ ፍጆታ የሚውል ነው፡፡
በተለያዩ ሂደቶች ውስጥ አልፎ የሚመረተውን ይህን አማራጭ የኃይል አቅርቦት ወደ ጥቅም ለማዋል ከሚመለከተው አካል የላብራቶሪ ሙከራ ተደርጎ ማረጋገጫ አግኝቷል፤ ከንጹህ ነዳጅ ጋር በመቀላቀልም መጠቀም የሚቻል መሆኑና በዚህም ከውጪ የሚገባውን ነዳጅ መቀነስ የሚያስችል በተለይ በምርቱ ሂደት ለዜጎች ቋሚና ጊዚያዊ የስራ ዕድል ከመፍጠር በተጨማሪ በተኪ ምርትነት የውጭ ምንዛሪን የሚያስቀር በመሆኑ በቀጣይ በመንግስትና በግሉ ዘርፍ ትብብርና ድጋፍ በሰፊው ወደ ስራ መግባት እንደሚፈልግና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን አረጋግጦልናል፡፡
‹‹ብሩህ አእምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች››
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 30/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
