en
Feedback
ጎህ የልዩ-ፍላጎት ማዕከል

ጎህ የልዩ-ፍላጎት ማዕከል

Open in Telegram

ይህ ቻናል ብቁ የሆኑ የልዩ-ፍላጎት፣የስነ- ልቦና፣ እና ሌሎች ባለሙያዎች የሚገኙበት ሲሆን የተለያዩ ትምህርታዊ፣ ስነ ልቦናዊ፣ የባህሪ እና ሌሎች ድጋፎችን በሰለጠኑ ባለሙያዎች እንሰጣለን። 📲 0954842701 (ትዛዙ አበበ) በውስጥ ለማግኘት @Tizaabebe

Show more
2 078
Subscribers
+124 hours
+37 days
+1430 days
Posts Archive
8. የዓመቱ ምርጥ ሚዲያ
Anonymous voting

7. የዓመቱ ምርጥ ልዩ-ፍላጎት ያለው ግለሰብ
Anonymous voting

6. የዓመቱ ምርጥ እናት
Anonymous voting

5. የዓመቱ ምርጥ አባት
Anonymous voting

4. የዓመቱ ምርጥ ተቋም
Anonymous voting

3. የዓመቱ ምርጥ ቤተሰብ
Anonymous voting

2. የዓመቱ ምርጥ አድቮኬት
Anonymous voting

1. የዓመቱ ምርጥ ባለሞያ
Anonymous voting

በኢትዮጵያ ለ3ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም የ‘ሴሬብራል ፓልሲ’ ቀን አስመልክቶ በመጪው ጥቅምት ሀገር አቀፍ የእግር ጉዞ ሊካሄድ ነው ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ ለ3ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም የ‘ሴሬብራል ፓልሲ’ ቀንን ወይም በሕፃናት አዕምሮ ዕድገት ላይ በሚደርስ ጉዳት ምክንያት የሚከሰት፣ የእጅና እግር እንቅስቃሴን፣ የጡንቻን ጥንካሬ እና የሰውነት ሚዛንን የሚጎዳ የነርቭ ሕመም አስመልክቶ በመጪው ጥቅምት ወር ሀገር አቀፍ ንቅናቄና ታላቅ የእግር ጉዞ ሊካሄድ እንደሆነ የመርሃ-ግብሩ አዘጋጅ እዝነት አካል ጉዳተኛ ህፃናትና ወላጆች መርጃ ድርጅት አስታውቋል፡፡ ድርጅቱ ዛሬ ነሐሴ 18 ቀን 2019 ዓ.ም. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ሕዝባዊ የእግር ጉዞው ጥቅምት 8 ቀን 2019 ዓ.ም. "ለሲፒ ጉዳተኛ የነገ ተስፋ እጓዛለሁ" በሚል መሪ ቃል ይካሄዳል። የእግር ጉዞው መነሻውን ከፒያሳ ዓድዋ 00 በማድረግ እስከ ኩፓ ፓርክ ድረስ እንደሚዘልቅ ታውቋል። የድርጅቱ መሥራች እና ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ዘቢባ አሕመድ በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት፣ የ’ሴሬብራል ፓልሲ’ ጉዳተኞችን አስመልክቶ ድምፅ ለመሆን በቂ እንዳልሆነ እና ግንዛቤውም እንዳልተፈጠረ አብራርተዋል። ‘ሴሬብራል ፓልሲ’ በሕፃናት አእምሮ ዕድገት ወቅት በሚደርስ ጉዳት ምክንያት የሚከሰት፣ የእጅና እግር እንቅስቃሴን፣ የጡንቻን ጥንካሬ እና የሰውነት ሚዛንን የሚጎዳ የነርቭ ሕመም ሲሆን፤ ችግሩ በአብዛኛው ከፅንስ ጊዜ ጀምሮ እስከ ሁለት ዓመት ዕድሜ ባለው ጊዜ ውስጥ ይከሰታል። እንደ ሀገር በጉዳዩ ላይ በበቂ ሁኔታ ስላልተሰራበትና ጉዳቱ እየተባባሰ በመምጣቱ፣ የእግር ጉዞው ሰፊ ግንዛቤ ለመፍጠር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ሥራ አስኪያጇ ገልጸዋል። ሕብረተሰቡ ለዚሁ ተግባር የተዘጋጁ ቲሸርቶችን በመግዛትና በእግር ጉዞው በመሳተፍ ከተጎጂዎችና ከወላጆቻቸው ጎን እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።   በይስሐቅ ቀለመወርቅ ፌስቡክ ገጽ፡- https://web.facebook.com/ahadutelevision ቴሌግራም ገጽ፡- https://t.me/ahaduradio ቲክቶክ ገጽ፡- tiktok.com/@ahadutv.official ዌብሳይት፡- www.ahaduradio.com ኢንስታግራም ፡- www.instagram.com/ahaduradio/ #አሐዱ_ሬዲዮ_94.3 #አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

የልዩ-ፍላጎት ረዳት መምህር ረዳት መምህር / ቴራፒስት (4 ቦታዎች) የስራ መደብ፦ ረዳት መምህር / ቴራፒስት (Assistance) የቅጥር ሁኔታ፦ በቋሚነት (Full-Time) ደመወዝ፦ በስምምነት የትምህርት ደረጃ፦ 10/12 ክፍል  ወይም በተዛማጅ መስክ የተሰጠ የምስክር ወረቀት (Certification) ያለው/ላት። የስራ ልምድ፦ ከተለያዩ ህጻናት ጋር አብሮ በመስራት፣ በመንከባከብ ወይም በማገዝ ዙሪያ የስራ ልምድ ያለው/ላት። በቴሌግራም ለማመልከት: @Tizaabebe በአካል መጥቶ ለማስገባት፦ ጦር-ሃይሎች ከሙሉ ወንጌል ቸርች ጀርባ https://t.me/gohcenters

የልዩ-ፍላጎት ረዳት መምህር ረዳት መምህር / ቴራፒስት (4 ቦታዎች) የስራ መደብ፦ ረዳት መምህር / ቴራፒስት (Assistance) የቅጥር ሁኔታ፦ በቋሚነት (Full-Time) ደመወዝ፦ በስምምነት የትምህርት ደረጃ፦ 10/12 ክፍል  ወይም በተዛማጅ መስክ የተሰጠ የምስክር ወረቀት (Certification) ያለው/ላት። የስራ ልምድ፦ ከተለያዩ ህጻናት ጋር አብሮ በመስራት፣ በመንከባከብ ወይም በማገዝ ዙሪያ የስራ ልምድ ያለው/ላት። በቴሌግራም ለማመልከት: @Tizaabebe በአካል መጥቶ ለማስገባት፦ ጦር-ሃይሎች ከሙሉ ወንጌል ቸርች ጀርባ https://t.me/gohcenters

ሶስት አባቶች ወግ እነዚህ ሶስት አባቶች ስለ አባትነት ልምዳተቸው ቢወያዩ፣ ውይይታቸው ምን ይመስል ይሆን ከሶስት በጣም የተለያዩ ዓለማት የመጡ ቢሆኑም፣ አንድ የሚያመሳስላቸው ነገር አለ፣ ልጆቻቸውን መጠበቅ፣ ለእነሱ መስዋዕት የመክፈል እና የመንከባከብ ተፈጥሯዊ  ስሜት። የመጀመሪያው- የሳንድግሩዝ ወፍ ይባላል፡ የሳንድግሩዝ ወፍ አባት ውሃ ለማግኘት በረሃውን በረጅም ርቀት በመብረር ሕይወቱን አደጋ ላይ ይጥላል። ልዩ የሆኑትን የሆድ ላባዎቹን በውሃ ያርሳል፤ ከዚያም ያንን ውድ ውሃ ወደ ጫጩቶቹ ይዞ ይመለሳል። ጫጩቶቹም ውሃውን በቀጥታ ከራሰው የአባታቸው ላባ ይጠጣሉ። እነዚህ ወፎች በሚኖሩበት ከባድና በደረቅ በረሃ፣ የጫጩቶቹ ህይወት በአባትየው የዕለት ተዕለት ውሃ የማመላለስ ተግባር ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ሁለተኛው- የባንጋይ ካርዲናል አሳ አባት የባንጋይ ካርዲናል አሳ አባት እንቁላሎቹን ከአዳኞች ለመጠበቅ በአፉ ውስጥ ተሸክሞ ይይዛቸዋል። አንድ ወር ለሚጠጋ ጊዜ ምግብ ሳይበላ እንቁላሎቹን በአፉ ይሆ ይቆያል። የሚያድጉትን ፅንሶች በትዕግስት ይጠብቃል፣ ኦክስጅን እንዲያገኙም ያደርጋል፤ በመጨረሻም በራሳቸው ለመኖር ዝግጁ እስኪሆኑ ድረስ ይንከባከባቸዋል። ሶስተኛው- የሰው ልጅ አባት ሶስተኛው አባት ናራያን ይባላል። ልጁ ኒምራን እ.ኤ.አ. በ2015 ኔፓልን በአስከፊ ሁኔታ በመታው የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት ተወለደ። ሁለተኛው የመሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰትና በዙሪያቸው ያሉ ሕንፃዎች ሲወድቁ፣ ናራያን ሳያመነታ ልጁን በልብሱ ስር ሸሽጎ በመሮጥ ህይወቱን አተረፈ። ሶስት አባቶች። ሶስት ዝርያዎች። ሶስት በጣም የተለያዩ ታሪኮች። ይሁን እንጂ በአንድ ነገር ላይ ይስማሙ ይሆናል፦ አባትነት በመልካም ጊዜ ብቻ ከልጅ ጋር አብሮ መሆን አይደለም። አባትነት ልጅዎ በጣም በሚፈልግዎት ጊዜ ከጎኑ መቆም፣ መጠበቅ፣ መስዋዕት መክፈል እና የሚያስፈልገውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆን ነው። እና ምናልባትም ታሪኮቻቸውን ከተካፈሉ በኋላ አንድ ነገር ይገነዘቡ ነበር፦ ምንም እንኳን የተለያዩ ቋንቋዎችን ቢናገሩም፣ የአባታዊ ፍቅር ቋንቋ ዓለም አቀፋዊ መሆኑን