en
Feedback
Don Bosco Catholic First and Middle level School (1-8) A.A

Don Bosco Catholic First and Middle level School (1-8) A.A

Open in Telegram
3 702
Subscribers
+424 hours
+437 days
+16130 days
Posts Archive
20/12/2018 ዓ.ም ለ 2019 ዓ.ም መደበኛ ትምህርት ላለስመዘገባችሁ የዶን ቦስኮ  ካቶሊክ  አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ነባር ተማሪዎች ወላጆች / አሳዳጊዎች ጉዳዩ:- የመመዝገቢያ ቀን መጠና ቀቁን ስለማሳወቅ ከላይ በርዕሱ እንደተጠቀሰው የነባር ተማሪዎች የ2019 ዓ.ም መደበኛ ትምህርት መመዝገቢያ ቀን እስከ ነሐሴ 12 / 2019 ዓ.ም ድረስ እንደነበር በማስታወቂያ መገለፁ ይታወቃል። ሆኖም ግን ጥቂት ተማሪዎች በተሰጠው የጊዜ ገደብ አለመመዝገባቸው ከምዝገባ ክፍል ከተገኘው መረጃ ለማወቅ ተቸሏል። ስለሆነም እስከአሁን በተለያዩ ምክንያቶች ምዝገባ ያላከናወናችሁ ወላጆች / አሳዳጊዎች ለመጨረሻ ጊዜ እስከ ዓርብ ( ነሐሴ 22 / 2018 ዓ.ም ) ድረስ ብቻ በት/ቤቱ ውስጥ በአካል ተገኝታችሁ እንድታስመዘግቡና መመዝገባቸውንም እንድታረጋግጡ እየገለፅን በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ያልተመዘገቡ ተማሪዎች በራሳቸው ፈቃድ ት/ቤቱን እንደለቀቁ እንደሚቆጠርና ለሚፈጠረው ማንኛውም ክፍተት ተጠያቂነቱን ት/ቤቱ የማይወስድ መሆኑን ከወዲሁ በጥብቅ እናሳውቃለን። ት/ቤቱ

03/12/2018 ዓ.ም . . ለ ዶን ቦስኮ  ካቶሊክ  አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት የመደበኛ ተማሪዎች ወላጆች / አሳዳጊዎች ነገ (ነሐሴ 4 2019 ዓ.ም) የሚጀመረውን የቀጣይ ዓመት የመደበኛ ተማሪዎች የመመዝገቢያ ቀንና የአመዘጋገብ ሂደቱን በተመለከተ በማስታወቂያ መግለፃችን ይታወቃል። በዚህም መሠረት ክፍያውን ከዚህ በፊት በተላከላችሁና እየተጠቀማችሁብት ባለው የባንክ የመክፈያ ኮድ ከከፈላችሁ በኋላ በት/ቤቱ የሂሳብ ክፍል በአካል በመገኘት መከፈሉን ማረጋገጥና በት/ቤቱ የተዘጋጀው የተማሪዎች ህግና ደንብ ላይ መፈረም ይኖርባችኋል :: ጥብቅ ማሳሰቢያ 1ኛ) ወላጆች ክፍያውን በኮዱ መሠረት መክፈላቸውን በት/ቤቱ የሂሳብ ክፍል ተገኝተው ካላረጋገጡና በተማሪዎች ህግና ደንብ ቅፅ ላይ ካልፈረሙ ተማሪዎች እንዳልከፈሉ ተቀጥሮ ለ 2019 ዓ.ም በሚደረገው የክፍል ደልድል ዉስጥ አይካተቱም :: 2ኛ) በ 2018 ዓ.ም የት/ቤት ቆይታቸው ከባህሪይ (ፀባይ) ጋር ተያይዞ ክፍተት ያለባቸው ተማሪዎች ወላጆቻቸው በአስተባሪዎች ቢሮ ተገኝተው የሚጠበቅባቸውን ቅድመ ሁኔታ ካላሟሉና በተማሪዎች ህግና ደንብ ቅፅ ላይ ካልፈረሙ ለ 2019 ዓ.ም በሚደረገው የክፍል ደልድል ዉስጥ አይካተቱም :: 3ኛ) ወላጆች ወደ ት/ቤት ለማስመዝገብ ሲመጡ የተማሪውን / ዋን የ2018 ዓ.ም ካርድ መያዝ ይኖርባቸዋል :: ካርድ ይዘው ካልተገኙ የምዝገባ ሂደቱን ማከናወን አይችሉም። ት/ቤቱ

03/12/2018 ዓ.ም . . ለ ዶን ቦስኮ  ካቶሊክ  አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት የመደበኛ ተማሪዎች ወላጆች / አሳዳጊዎች ነገ (ነሐሴ 4 2019 ዓ.ም) የሚጀመረውን የቀጣይ ዓመት የመደበኛ ተማሪዎች የመመዝገቢያ ቀንና የአመዘጋገብ ሂደቱን በተመለከተ በማስታወቂያ መግለፃችን ይታወቃል። በዚህም መሠረት ክፍያውን ከዚህ በፊት በተላከላችሁና እየተጠቀማችሁብት ባለው የባንክ የመክፈያ ኮድ ከከፈላችሁ በኋላ በት/ቤቱ የሂሳብ ክፍል በአካል በመገኘት መከፈሉን ማረጋገጥና በት/ቤቱ የተዘጋጀው የተማሪዎች ህግና ደንብ ላይ መፈረም ይኖርባችኋል :: ጥብቅ ማሳሰቢያ 1ኛ) ወላጆች ክፍያውን በኮዱ መሠረት መክፈላቸውን በት/ቤቱ የሂሳብ ክፍል ተገኝተው ካላረጋገጡና በተማሪዎች ህግና ደንብ ቅፅ ላይ ካልፈረሙ ተማሪዎች እንዳልከፈሉ ተቀጥሮ ለ 2019 ዓ.ም በሚደረገው የክፍል ደልድል ዉስጥ አይካተቱም :: 2ኛ) በ 2018 ዓ.ም የት/ቤት ቆይታቸው ከባህሪይ (ፀባይ) ጋር ተያይዞ ክፍተት ያለባቸው ተማሪዎች ወላጆቻቸው በአስተባሪዎች ቢሮ ተገኝተው የሚጠበቅባቸውን ቅድመ ሁኔታ ካላሟሉና በተማሪዎች ህግና ደንብ ቅፅ ላይ ካልፈረሙ ለ 2019 ዓ.ም በሚደረገው የክፍል ደልድል ዉስጥ አይካተቱም :: 3ኛ) ወላጆች ወደ ት/ቤት ለማስመዝገብ ሲመጡ የተማሪውን / ዋን የ2018 ዓ.ም ካርድ መያዝ ይኖርባቸዋል :: ካርድ ይዘው ካልተገኙ የምዝገባ ሂደቱን ማከናወን አይችሉም። ት/ቤቱ

በተማሪዎች ህግና ደንብ ቅፅ ላይ ካልፈረሙ

ለ2018ዓ.ም የሚንስትሪ ተፈታኝ  የ 2019 ዓ.ም የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችና ወላጆች ውድ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች የዶን ቦስኮ ካቶሊክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ የሚለቀቅበት የቴሌግራም ቻናል ከታች የተያያዘው ሊንክ መሆኑን እየገለፅን join በማለት (የቴሌግራም አባል ) በመሆን የሚለቀቁ አዳዲስ መረጃዎችን እንድትከታተሉ ለማሳሰብ እንወዳለን።👇👇👇 https://t.me/donbosco2021

ውድ የዶን ቦስኮ ካቶሊክ ት/ቤት ተማሪዎች / ወላጆች / አሳዳጊዎች እንኳን ደስ አላችሁ !!! በ2018 ዓ.ም የክልላዊ ፈተና የወስዱ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን በከፍተኛ ውጤት ወደ 7ኛ ተዘዋውረዋል !!! ለዶን ቦስኮ ካቶሊክ ት/ቤት ተማሪዎች ፣ መምህራን፣  ወላጆች፣ የተቋማችን ማህበረሰብና  ባለድርሻ አካላት በሙሉ ለተመዘገበው   የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላደረጋችሁት ጥረትና ላበረከታችሁት አስተዋፅኦ ከልብ እናመሰግናለን::    የዶን ቦስኮ ካቶሊክ    ሳሊዚያን ማኅበር እና ት/ቤት

የ2018ዓም የት/ቤት ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ የተማሪ ወላጆች በሙሉ የ2018ዓም የተማሪዎች ሪፖርት ካርድ ለወላጅ የሚሰጠው እሁድ ሃምሌ 05/2018ዓም መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ከፍላችሁ ያላጠናቀቃችሁ ወላጆች ነገ ከ ረቡዕ ሃምሌ 01 እስከ አርብ ሃምሌ 03/2018ዓም ከፍላችሁ እንድታጠናቅቁ እያሳስብን  ያላጠናቀቁ ተማሪዎችን ሪፖርት ካርድ የመለየት ስራ የምንሰራ  እና እሁድ ሪፖርት ካርዱን የምንይዝ(የማንሰጥ) መሆኑን እያሳወቅን ማንኛውንም ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ በአፋጣኝ(ከላይ በተጠቀሱት ቀናት ብቻ) ከፍላችሁ እንድታጠናቅቁ በጥብቅ እናሳስባለን። ማሳሰቢያ 👉ክፍያ ላላጠናቀቁ ተማሪዎች ካርድ የማንሰጥ መሆኑን እያሳወቅን ሪፖርት ካርድ ባለመውሰዳችሁ  ከምዝገባ ጋር ለሚፈጠር ማንኛውም ችግር ኃላፊነቱን ወላጅ የሚወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።                             ት/ቤቱ