Addis Ababa Water & Sewerage Authority (AAWSA)
Open in Telegram
3 559
Subscribers
+824 hours
+207 days
+5030 days
Posts Archive
ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከኢቢሲ ጋር ባደረጉት ቆይታ ስለ ውሃና ፍሳሽ መሰረተ ልማት በተመለከተ የሰጡት ማብራሪያ 👆
የጽናት ቀን
ኢትዮጵያን ስናስብ፣ ሌት ተቀን በጽናት በመቆም ሀገርን ከጠላት ለመጠበቅ ወጥተው ለሚያድሩት ብርቱ የፀጥታ ኃይሎቻችን ቅድሚያ ሳንሰጥ ስለ ሁለንተናዊ ከፍታ ማሰብ ፈጽሞ አይቻልም፡፡ ለዚህም ነው በዚህ የጽናት ቀን፣ ለሀገረ-መንግሥታችን ዘላቂነትና ሉዓላዊነት ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን የከፈሉትን የጀግኖቻችንን ታሪካዊ መስዋዕትነት በከፍተኛ ሀገራዊ ክብር የምንዘክረው፡፡
ዛሬ ላይ ሀገራችን በራሷ ዕውቀትና በልጆቿ አቅም የላቀ የቴክኖሎጂ ብቃት ያላቸውን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን፣ ዘመናዊ የታጠቁ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን፣ ከባድ መሣሪያዎችንና መድፎችን፣ እንዲሁም ተተኳሽ ጥይቶችን በራሷ ወታደራዊ ኢንዱስትሪዎች ማምረት ችላለች፡፡
ይህ በራስ የመቆም አቅም፣ የሕዝባችን ሰላምና የሁለንተናዊ ኢኮኖሚ እድገታችን ጽኑ መሠረት በመሆኑ፣ ሀገራዊ ጽናታችንን በተጨባጭ ልማትና በጠንካራ የመጠበቅና የመከላከል አቅም እያረጋገጥን የኢትዮጵያን ዘላቂ ብልጽግና እናጸናለን!
ጠቅላይ ሚኒስትርአብይ አህመድ / ዶ/ር/
የማንሠራራት ቀን
ከቃል ባለፈ በተጨባጭ ስኬት የቆመችው ኢትዮጵያ!
ትናንት “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ስንል ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ ያረጋገጥነው እውነት ነው! ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል። ይህ ለውጥ በዜጎቻችን የኑሮ ደረጃ፣ በከተሞች መዘመንና የሥራ ዕድል ላይ እውነተኛ ብርሃን ከመሆኑም በላይ ለልጆቻችን የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ ነው። ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም! በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዶ/ር
#EthiopiaDelive
የእመርታ ቀን
አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል።
በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን።
እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው!
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የጎሮ ፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ
👉 በቀን 52ሺኅ ሜትር ኪዩብ ፍሳሽ ማጣራት አቅም አለው
👉 621 ሺ ሰዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ማጣሪያ ጣቢያ ነው
👉ቦሌ ወረዳ 11 ተብሎ የሚጠራ አካባቢ እየተሰራ ያለ ሲሆን
👉ለሚኩራ ክፍለ ከተሞችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው
👉 በ2019 በጀት አመት መጨረሻ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል
-----------------------------------
መረጃዎችን ለማግኘት ሊንኪን ይጫኑ
https://linktr.ee/AAWSA_Social_media
+2
በሀገራችን የመጀመሪያውን የተለየ የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም የሚያስችለውን ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) መካከል ስምምነት ዛሬ አከናውነናል።
በ100 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ካፒታል የተቋቋመው እና በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋፅኦ የሚያደርግበት ይህ ተቋም፤ በባንክ ዘርፋችን ውስጥ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠንን የሚቀርፍ እና በመላው ኢትዮጵያ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን የሚያስገኝ ይሆናል።
ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓታችን ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያስቀመጥነውን ግብ የሚያሳካ ወሳኝ እርምጃ ነው።
ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን ትቀጥላለች።
የማእከል ፎረም አባላት የ2019 በጀት አመት እቅድ እና በተጠናቀቀው በጀት አመት የተሰሩ አበይት ተግባራት ውይይት
ነሀሴ 27/2018 ዓ.ም (AAWSA)
የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎች
ጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”
ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”
ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”
ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”
ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”
የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ
የኪቲሜ ፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ
👉 በቀን 54ሺኅ ሜትር ኪዩብ ፍሳሽ ማጣራት አቅም አለው
👉 645ሺህ ሰዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ማጣሪያ ጣቢያ ነው
👉 ቦሌ ወረዳ 12 ኪቲሜ ተብሎ የሚጠራ አካባቢ እየተሰራ ያለ ሲሆን
👉 የካ እና ቦሌ ክፍለከተሞችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው
👉 በ2019 በጀት አመት መጨረሻ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል
+8
ቅርንጫፉ 600 አባወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የውሃ መስመር ዝርጋታ ስራ እያካሔደ ነው።
ነሀሴ 24/2018 ዓ.ም (AAWSA)
በባለስልጣኑ አዲስ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት መርካቶ አካባቢ እየተሰሩ ላሉ አዳዲስ ቤቶች የንጹህ ውሃ ተጠቃሚ ለማድግ የሚያስችል የመሰመር ዝርጋታ እያደረገ ነው።
የመስመር ዝርጋታው ባለ 4 ኢንች 200 ሜትር፣ ባለ 3 አንች 300 ሜትር መዘርጋት የሚፈልግ ነው። እስካሁን 350 ሜትር የተዘረጋ ሲሆን ቀሪውን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው።
+3
ገላን አሮጌው ኬላ አካባቢ የሚገኘው ባለ700 ሚ.ሜ የውሃ መስመርም ተጠግኖ ወደ ስርጭት ገብቷል፡፡
ነሀሴ 24/2018 ዓ.ም (AAWSA)
----------------------------------
መረጃዎችን ለማግኘት ሊንኪን ይጫኑ
https://linktr.ee/AAWSA_Social_media
