Addis Ababa Water & Sewerage Authority (AAWSA)
Ir al canal en Telegram
3 472
Suscriptores
+124 horas
+217 días
+5030 días
Archivo de publicaciones
+4
የውሃ መሰረተ ልማትን በተመለከተ
በ2013 በጀት አመት ማብቂያ የውሃ ምርት አቅም 570,000 ሜትር ኪዩብ/በቀን የነበረ ሲሆን የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ እና ወደ ስርጭት በማስገባት የምርት አቅማችንን ወደ 850,000 ሜትር ኪዩብ/በቀን ማድረስ ተችሏል። ከዚህም ተጨማሪ በቀን 280,000 ሜትር ኪዩብ ውሃ የማምርት አቅም ተፈጥሯል።
የዘመናዊ ፍሳሽ ማስወገድ ስርአትን የማሻሻል ስራዎችን በተመለከተ ከዚህ ቀደም ከነበረበት 36 በሞቶ ወደ 42 በሞቶ ማድረስ ተችሏል። ከዚህ ቀደም በከተማችን የነበረው ፍሳሽ ማጣሪያ አንድ ብቻ ሲሆን፣ በአሁኑ ጊዜ ወደ 44 ማጣሪያዎች ማድረስ ተችሏል፡፡ የለገዳዲን የውሃ ግድብን በመጠገን እና በማሻሻል ግድቡ ለተጨማሪ 50 አመታት እንዲያገለግል የማስቻል ስራ ተሰርቷል።
የከተማዋን የውኃ አቅርቦት ሽፋን በበጀት ዓመቱ ማብቂያ በቀን በ60 ሺህ ሜ.ኩብ ለማሳደግ በቁጥር እስከ 20 የሚደርሱ አዳዲስ ጉድጓዶች በመቆፈርና ወደ ስርጭት በማስገባት በቀን 60,000 ሜ.ኩብ ውሃ መጨመር ችለናል።
በተመሳሳይ 100ሺህ ሜ.ኩብ ውኃ ማምረት ከሚያስችለው የጭቋላ ዌል ፊልድ የውሃ ልማት ፕሮጀክት ጋር ተያይዞ የተቆፈሩ ጉድጓዶችን ወደ ስርጭት ለማስገባት የግንባታ ሥራውን 30 በሞቶ ማድረስ ተችሏል። በሌላ በኩል ከገጸ ምደር ውሃ ልማት አንጻር በቀን እስከ 73 ሺህ ሜ.ኩብ ውሃ መስጠት የሚያስችለው የገርቢ መጠጥ ውሃ ግድብ ግንባታ ተጀምሯል፡፡
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት አመታት አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትን ከ6ዐ በመቶ በላይ ያሳደግን ሲሆን፣ የዘመናዊ የፍሳሽ አወጋገድና የፍሳሽ ማጣራት ስርአትንም በከፍተኛ ደረጃ አድጓዋል፡፡
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ያለአፈር አትክልቶችን የማልማት ቴክኖሎጂ( Hydroponics ) በውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ሊተገበር በዝግጅት ላይ ነው
ሀምሌ 4/2018 ዓ.ም (AAWSA)
-----------------------------------
መረጃዎችን ለማግኘት ሊንኪን ይጫኑ
https://linktr.ee/AAWSA_Social_media
በቦሌ አራብሳ አካባቢ እየተሰሩ ያለ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክቶች
ሀምሌ 2/2018 ዓ.ም (AAWSA)
-----------------------------------
መረጃዎችን ለማግኘት ሊንኪን ይጫኑ
https://linktr.ee/AAWSA_Social_media
+2
የደንበኞች ተሳትፎ ለአገልግሎት ጥራት መሻሻል መሠረት መሆኑ ተገለጸ
ሰኔ 27/2018 ዓ.ም (AAWSA)
የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የመገናኛ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከደንበኞች ፎረም አባላት ጋር ባካሄደው የውይይት መድረክ፣ የደንበኞች ጥቆማና ተሳትፎ የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል ወሳኝ መሆናቸው ተገልጿል።
በመድረኩ የፎረም አባላት የቅርንጫፉ የአገልግሎት አፈጻጸም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን በማድነቅ፣ የውሃ መፍሰስ፣ የውሃ ፈረቃ፣ የብረት መስመሮችን በፕላስቲክ መተካት፣ የፍሳሽ ማንሆል ክዳኖችን ማሟላት እና ሌሎች የአገልግሎት ማሻሻያ ጉዳዮችን በተመለከተ ጥቆማዎችን አቅርበዋል።
የቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ደበሬ ቱጆ በበኩላቸው የቀረቡትን ሀሳቦች እንደ ቀጣይ የሥራ ግብዓት እንደሚጠቀሙባቸው በመግለጽ፣ የውሃ መፍሰስ ችግሮችን በአፋጣኝ እንደሚያስተካክሉ፣ የውሃ አቅርቦትን በፈረቃ ክለሳ እንደሚያሻሽሉ እና ግልጽነትንና ተጠያቂነትን ለማጠናከር የዲጂታል አሠራርን በስፋት እየተገበሩ መሆኑን ገልጸዋል።
በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ የደንበኞች ፎረምና የባለስልጣኑ አመራሮች በጋራ በመስራትና የደንበኞችን ጥቆማ በተግባር በመተግበር የውሃና የፍሳሽ አገልግሎትን የበለጠ ቀልጣፋና ጥራት ያለው ለማድረግ እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል።
አጎዛ ገበያ ወደ አትላስ የሚወስደው የወንዝ ዳርቻ የፍሳሽ መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክት
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ መሃሙድ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ
AAWSA - ሰኔ 22/2018 ዓ.ም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ የትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ መሃሙድ ጋር በኢኮኖሚያዊ ትስስር፣ ደኅንነት እና የቀጠናዊ መረጋጋት ዙሪያ በመተማመንና በመከባበር ላይ የተመሠረተ የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደናል ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ኢትዮጵያና ሶማሊያ ከድንበር በላይ የሚጋሩት ነገር አለ፤ እሱም እጅግ ውድ የሆነውን ህዝባችንን እና የጋራ እጣ ፈንታችንን ነው በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
-----------------------------------
መረጃዎችን ለማግኘት ሊንኪን ይጫኑ
https://linktr.ee/AAWSA_Social_media
See less
+8
በመዲናዋ የሚከናወነው የልማት ስራ ዘመናዊ የውሃና ፍሳሽ መስመር ዝርጋታ ስራ ለመስራት ትልቅ እድል ፈጥሯል።
ሰኔ 18, 2018ዓ.ም (AAWSA)
የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የመገናኛ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የደንበኞች መረጃ ማዘመን እና የኮሪደር ስራ ላይ ያከናወናቸውን ተግባራት ለቦሌ ክ/ከተማ መሰረተ ልማትና መዘጋጃቤታዊ ቋሚ ኮሚቴ አባላት ፤ ለፎረም ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴዎች እና ለቅርንጫፉ ፕሮሰስ ካውንስል አባላት አስጎብኝተዋል፡፡
በጉብኝቱም ወቅት የቅርንጫፉ ስራ አስኪያጅ አቶ ደበሬ ቱጂ የውሃና የፍሳሽ መስመር ዝርጋታዎች በባህሪያቸው በመሬት ውስጥ ለውስጥ የሚዘረጉ እና ለከተማዋ ውበት የራሳቸው ሚና የሚጫወቱ መሆናቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ምንም እንኳን ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት ላይ ከዋለ በኋላ በአይን የሚታይ ነገር ባይሆንም በመሬት ውስጥ የተከናወነው ድንቅ ስራ ከላይ ለሚታየው የከተማዋ ዘመናዊነት እና ውበት የራሱ የሆነ የማይናቅ አስተዋፅኦ አድርጓል ብለዋል
በተጨማሪም የኮሪደር ልማት መኖሩ በራሱ የውሃና ፍሳሽ መሰረተ ልማትን በጥራት ለመዘርጋት ጥሩ አጋጣሚ ሆኖልናል ብለዋል፡፡
ከአደይ አበባ እስታዲየም አካባቢ የተጀመረው ጉብኝት የአያት - ኤድናሞልን፤ የሲግናልን ፤ የቺቺኒያ፤ የፒኮክ መናፈሻን ፤ ከቦሌ መድኃኒአልም እስከ 22 እና የቀበና ወንዝን ተከትሎ የተሰራውን የወንዝ ዳርቻ የካለለ ሲሆን ፤
በእነዚህ አካባቢዎች ላይ ኮሪደር ልማቱን ተከትሎ በመንገዱ ሁለቱም አቅጣጫ ላይ ቋሚ የሆነ የውሃና የፍሰሽ መሰረተ ልማት ከመዘርጋቱ በተጨማሪ ነዋሪዎች በጊዚያዊነት ውሃ እንዳያጡ ለማድረግ ከስር ከስር ጊዚያዊ የውሃ መስር ዝርጋታዎች ጭምር ይከናወኑ እንደነበር ተገልጿል፡፡
ባለስልጣኑ በውሃ መገኛ እና ሌሎች ቦታዎች ላይ 150ሺህ ችግኝ ለመትከል ተዘጋጅቷል
የለገዳዲ ግድብን እድሜ ለማራዘም የተሰራ የማሻሻያ እና ጥገና ስራ የት ደረሰ ?
ቪዲዮውን ይመልከቱ
ሰኔ 15/2018 ዓ.ም (AAWSA)
-----------------------------------
መረጃዎችን ለማግኘት ሊንኪን ይጫኑ
https://linktr.ee/AAWSA_Social_media
ግድብ በደለል እንዳይሞላ
ሰኔ 13/1018 ዓም
-----------------------------------
መረጃዎችን ለማግኘት ሊንኪን ይጫኑ
https://linktr.ee/AAWSA_Social_media
ሌትን እንደ ቀን ፤ ያለ እንቅልፍ
7/24 ምርጡ የከተማችን የስራ ባህል ! 👆
ጽዱ አካባቢ ለመፍጠር ዘመናዊ የፍሳሽ አወጋገድ ስርዓት መዘርጋት የግድ ነው ። ይህ አሁን ትልቁ ፖስታ ቤት አካባቢ እየተዘረጋ ያለው ፍሳሽ መስመር ብዙ መንደሮችን የሚያሳርፍ እና ፍሳሽ ቆሻሻን ይዞ ወደ ቃሊቲ ማጣሪያ ጣቢያ የሚወስድ መስመር ነው ።
ሰኔ 6/2018 ዓ.ም
+9
"ባለስልጣኑ ከላይ እስከ ታች የተናበበ ተቋም መገንባቱን አይተናል" የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት መሰረተ ልማትና ማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ግዛቸው አይካ ፡፡
ሰኔ 5/2018 ዓ.ም (AAWSA)
የቋሚ ኮሚቴው አመራሮች እና አባላት ዛሬ የባለስልጣኑን አቃቂ እና ንፋስ ስልክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጎብኝተዋል፡፡
በጉብኝታው ደንበኞች የሚስተናገዱበትን ሁኔታ፣ የደንበኛ መረጃ አያያዝ ፣ ቅርንጫፎቹ ለአገልግሎት ምቹነት፣ ህጻናት መዋያ አገልግሎት ፣የንብረት አያያዝና መረጃ ለማዘመን የተጀመሩ ስራች መመልከት ችለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ምክር ቤት መሰረተ ልማትና ማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ግዛቸው አይካ "በቅርንጫፎቹ ተዘዋውረን የተመለከትናቸው አሰራር ስርዓቶች ባለስልጣኑ ተቋም መገንባቱን የሚያመላክት እና ደስ የሚያሰኝ ነው "ብለዋል፡፡
በመስክ ምልከታው ላይ የነበሩ የቋሚ ኮሜቴው አባላትም የቅርንጫፎቹ አመራሮች እና ሰራተኞች ቅንጅት እና ተናቦ መስራት እንዲሁም አሰራር ስርዓትን ለማቀናጀት የሄዱበት መንገድ የሚደነቅ ነው ብለዋል፡፡
በአቃቂ ቅርንጫፍ ያለው የህጻናት ማቆያ ወላጆች ያለ ሰቀቀን ስራቸውን እንዲሰሩ ከማድረግ ባሻገር በንጽህና የተያዘበት መንገድ የሚበረታታ ነው ብለዋል፡፡
ባለስልጣኑም ከጊዜ ወደ ጊዜ የአሰራር ስርዓቱን ለማዘመን እና ለማሻሻል እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀዋል፡፡
አባላቱ ከውሃ ስርጭት አኳያ የሚታየውን የግፊት ማነስ ችግር እና የሚፈስ ውሃ ሲጠቆም ቶሎ ያለመጠገን ችግር ሊፈታ እንደሚገባውም አመላክተዋል፡፡
