Farankaa - ፈረንካ
Open in Telegram
The primary goal of this page is to enhance the financial literacy of Ethiopians by offering valuable insights on investment, banking, insurance, capital markets, and taxation.
Show more1 791
Subscribers
No data24 hours
+17 days
+630 days
Posts Archive
1 791
ወገኖቼ ትብብራችሁ ይፈለጋል!
አስቸኳይ የጠፋ ፓስፓርት የአፋልጉን ማስታወቂያ!
የቻይና ሀገር ቪዛ የተመታባቸው የ6 ሰዎች ፓስፖርቶች በድንገት በሚከተለው ሁኔታ ጠፍተዋል።
የፓስፖርት ባለቤቶች፦ 1. Abayneh Demeke 2. .Anteneh Tekalign 3. Engidu Tsegaye 4. Sara getu 5. Tizita Degu 6. Girma Tujo
ትናንት ዓርብ፣ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም፣ ከምሽቱ 12፡30 ሰዓት ከዘነበወርቅ ወደ ዓለም ባንክ በሚጓዝ ሰማያዊ ሚኒባስ ታክሲ ውስጥ ተሳፍረው ሲወርዱ ፓስፖርቶቹን በታክሲው ውስጥ ረስተው ወርደዋል። ፓስፖርቶቹን በታክሲው ውስጥ ያገኛችሁ ወይም ስለፓስፖርቶቹ መረጃ ያላችሁ ሰዎች፣ የጉዞው ቀን የቀረው አንድ ቀን ብቻ በመሆኑ በአስቸኳይ ከታች ከተዘረዘሩት ስልክ ቁጥሮች በአንዱ በመደወል እንድታሳውቁን በትህትና እንጠይቃለን።
ፓስፖርቶቹን ላገኘ ሰው ተገቢውን ወረታ የምንከፍል መሆኑን እናሳውቃለን።
📞 የመገናኛ ስልኮች፦
[ስልክ ቁጥር 1] 0912377272
[ስልክ ቁጥር 2] 0945353331
[ስልክ ቁጥር 3] 0924666904
እባካችሁ ይህን መልዕክት ለሌሎች በማጋራት እንድትተባበሩን በትህትና እንጠይቃለን።
1 791
አዲስ አበባ ገቢዎች
------
ሀገሪቱ በምትከተለውን የዲጂታይዜሽን ስትራቴጂ መሠረት የታክስ ስርዓቱን በማዘመን አብዛኞቹ ግብር ከፋዮች በኢ-ታክስ ስርዓት ግብራቸው አሳውቀው እንዲከፍሉ በኦንላይን ግብራቸውን ተደርጓል።
ይሄም በመሆኑ ደንበኞች የተለየ ነገር ካልተፈጠረ በቀር የግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እንዳይመላለሱ ሆኗል። በተለይ የፌደራል የታክስ ጽህፈት ቤቶች በእዚህ ጉዳይ ሊመሰገኑ ይገባል።
ይሁንና የአዲስ አበባ የግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ግብር ከፋዮች በኦንላይን ግብራቸውን አሳውቀው ከከፈሉ በኋላ የኢ-ታክስ ስርዐቱ ለግብር ከፋዩ ደረሰኝ በማይልክበት ጊዜ በተለይም ክፍያው የአዲስ አበባ ገቢዎች በውክልና የሚሰራው የጡረታ ክፍያ ከሆነ ግብር ከፋዩ ላይ ቅጣትና ወለድ ይይዛል። (አስቡት ግብር ከፋዩ በወቅቱ ነው አሳውቆ የከፈለው)
ግብር ከፋዩ በወቅቱ ለከፈለው ክፍያ የታክስ ሲሰተሙ ደረሰኝ ባለመላኩ ምክንያት ግብር አልከፈልክም ተብሎ ደብዳቤ ይጻፍበታል፣ በአካል ቀርቦ declaration እና የባንክ ደረሰኝ ቢያቀርብም በተለይ ክፍያው የጡረታ ከሆነ ግብር ከፋዩን ወደሚመለከተው የጡረታ ቢሮ ሄዶ ቅጣቱን እንዲያስነሳ ይጠየቃል። አስቡት ግብር ከፋዩ ወቅቱን ጠብቆ ነው የከፈለው። ይሁንና የግብር ሲሳተሙ በፈጠረው ችግር ግብር ከፋዩ በየወሩ ጡረታ ሚንስቴር እንዲሄድ አሊያም ሲስተሙ የያዘበትን የግብር ቅጣትና ወለድ እንዲከፍል ይገደዳል። በጣም የሚገርመው የግብር ከፋይ ጽ/ቤቶች ሠራተኞች ችግሩ የሲስተሙ መሆኑን እያወቁ፣ ሲስተሙን ለማስተካከል ከመሞከር ይልቅ ችግሩን ወደ ግብር ከፋዩ ለማላከክ የሚሞክሩበት መንገድ ነው። ይሄንኑ ችግር በአንድ የግብር ከፋይ ጽህፈት ቤት በጠራው ስብሰባ ላይ አንስቼው ነበር። በሚቀጥለው ወር ስሄድ ችግሩ እንዳለ ነው።
መንግስት ሙስና የሚበሉ የግብር ከፋይ ጽ/ቤት ሠራተኞችን ብቻ ሳይሆን ሥራን የሚበድሉና ግብር ከፋዮችን ያለአግባብ የሚያጉላሉ ሠራተኞችን፣ ሲስተም ከማስተካከል ይልቅ ግብር ከፋዩ የsystem inefficiency እንዲሸከም የሚጥሩ ሠራተኞችም ሀይ ሊል ይገባል ብዬ ጽሀፌን እደመድማለሁ።
1 791
"የሰጠኸው ሁሉ በቂ ካልሆነ፣ ከአጠገባቸው ጥፋ። ጨው በምግብ ዝርዝር ውስጥ አይጻፍም፣ ይሁንና ጨው ሲያንስ ነው ያለመኖሩ የሚታወሰው።
1 791
ማህበራዊ ድረ-ገጽን፣ በተለይ ፌስቡክን፣ ለበጎ ዓላማ ያዋለች ወጣት በጎ ፈቃደኛ ናት።
ሜላት ካከናወነቻቸው ተግባራት መካከል፣
- ከአምስት ሺ በላይ ለሚሆኑ ወጣት ስራ ፈላጊዎች ስራ እድል አመቻችታለች
- የተስፋ አዲስ የካንሰር ህሙማን መርጃ ማእከል ለሚገኙ ህፃናት የማያቋርጥ ድጋፍ እያደረገች ትገኛለች፤ ለድርጅቱም ህፃናት ሆስፒታል የሚመላለሱበት መኪና አስገዝታለች ።
በተለያዩ መልኩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ያላት ተሳትፎ እና ድጋፍ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ባገኘችው ተቀባይነት እና ድጋፍ የቅን ልቦች የማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪ እና የቅን ልቦች የወርቅ ሜዳሊያ እጩ እንድትሆን አስችሎታል።
የሚከተለውን ሊንክ ተጭነን ድምጻችንን በመስጠት ማህበራዊ ድረ-ገጽን በኃላፊነት በመጠቀም ማህበረሰባችን ላይ የሚታይ ለውጥ ለማምጣት የሚተጉ ወጣቶችን እናበርታ!
https://lnkd.in/ekDU3sKY
1 791
አስመሳይነትን ስለማታውቅ፣ በሁሉም ሰው ዘንድ ተወዳጅና ተመራጭ ላትሆን ትችላለህ።
በሰዎች ፊት በማስመሰል ፈገግ ብለህ፣ ከጀርባቸው ስማቸውን ማጥፋት፣ ማታለልና ማዋረድ፣ ከዚያም እጆችህ ንጹሕ እንደሆኑ ማስመሰል አትችልበትም።
ሁሉም ሰው ላይወድህ ይችላል፤ ይሁን እንጂ እውነተኛ ሆነህ ትኖራለህ።
1 791
🥊 Adwa Fight Night: Beyond the Win or the Loss
___
The big news from Adwa Fight Night is either Johi’s impressive win or Seido’s painful loss—depending on which side you were supporting.
But for me, the bigger story is what this fight can inspire.
Ethiopian youngsters are watching. They are seeing that boxing, martial arts and other sports can be a path to discipline, excellence and international recognition.
Ethiopia has produced world-class athletes, particularly in athletics. It is time to expand our horizon and nurture talent in boxing, martial arts, wrestling, swimming and other sports.
The spirit of Adwa was about courage, determination and believing that seemingly impossible victories are possible.
May Adwa Fight Night inspire a new generation to step into the ring—not only to fight, but to pursue excellence. 🇪🇹🥊
#AdwaFightNight #Boxing #Ethiopia #Youth #Sports #Excellence
1 791
"ክቡር ፕሬዚደንት" ከሚለው ማዕረጋቸው ይልቅ "ምዋሊሙ" አሊያም "መምህር" በሚለው ማዕረጋቸው የሚታወቁት አፍሪቃዊ መሪ...
__
ጁሊዩስ ኔሬሬ እ.ኤ.አ. በ1964 የታንዛኒያ መሪ ሆኑ። ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በአፍሪቃ ውስጥ ተጽእኖ ፈጣሪ መሪ ለመሆን ቻሉ። ኔሬሬ የፖለቲካ ስልጣን ከመቆናጠጣቸው አስቀድሞ አስተማሪ ነበሩ። ታንዛኒያውያንም በፍቅር "መምህር" አሊያም በስዋሂሊ ቋንቋቸው "Mwalimu/ምዋሊሙ" ሲሉ ይጠሯቸው ነበር።
እጅግ የሚገርመው ነገር ኔሬሬ እንደአብዛኞቹ አፍሪቃዊያን መሪዎች በኩዴታ አሊያም በሞት ሳይሆን እ.ኤ.አ. በ1985 በገዛ ፈቃዳቸው ስልጣናቸውን ለቀቁ። እንደሌሎች አፍሪቃዊያን መሪዎች 'ሞቴን ቤተመንግስት ያድርገው፤ እኔ ከሞትኩ አገሬን ምን ይውጣታል" አላሉም። ማዕረጋቸው ሳያሳሳቸው ከስልጣናቸው ወረዱ።
ብዙዎች በስልጣን ጥም በሚቃጠሉበት አህጉር መምህሩ ትልቁን ፈተና አልፉ።
__
ስንቶቻችን ማንነታችንን ሳንተው ስልጣናችንን ለመልቀቅ ዝግጁ ነን?
ኔሬሬ ብዙ አመራሮችና ባለሙያዎች ሊያስቡት የማይፈቅዱትንና ሊዋጥላቸው የማይችሉትን ነገር ተረድተው ነበር።
ስልጣን ጊዜያዊ መሆኑን።
ዛሬ ላይ ብዙዎቻችሁ በስልጣን ማማ ላይ የተቀመጣችሁ ፕሬዚዳንት ፣ ጠቅላይ ሚንስትር፣ ሚንስትር፣ ምክትል ሚንስትር፣ ገዢ፣ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ ዳይሬክተር ወይም በሌላ ማዕረግ የምትጠሩ መሪ ልትሆኑ ትችላላችሁ።
ነገ ደግሞ ሌሎች የእናንተን ሥፍራ፣ የእናንተን ወንበር በያዙበት ስብሰባ ላይ ታዳሚ ልትሆኑ ትችላላችሁ። ይሁን እንጂ ያ እናንተን የሚያሳንስ አይሆንም። ምክንያቱም ማዕረጋችሁ በወቅቱ የነበራችሁበትን ሥፍራ የሚያሳይ እንጂ ዋጋችሁን የሚበይን አይደለምና።
ኔሬሬ "ምዋሊሙ" ወይም መምህር ነበሩ፣ ከስልጣናቸው በኋላም መምህር እንደተባሉ ኖረዋል። የስልጣን ዘመናቸው አክትሟል፣ መምህርነታቸው ግን ሁሌም አብሯቸው ኖሯል።
ሁላችንም ከኔሬሬ ታሪክ አንድ ነገር እንማራለን እርሱም ዛሬ ላይ በቢዝነስ ካርዳችን ላይ ከምናትመው፣ በየሚዲያው ከምንጠራበትና የሊንክዲን ፕሮፋይላችን ላይ ከምንጽፈው ስልጣን የሚዘልል ማንነትን ስለመገንባት።
አንድ ቀን ሁሉም ማዕረግ ጥሎን ይጠፋል። አብሮን የሚኖረውና በሌሎች የምንታወሰው ለሌሎች ባስማርነው፣ በሌሎች ውስጥ በገነባነው እንዲሁም ሰዎችን ባከበርነው መንገድና በፈጠርነው ተጽእኖ ብቻ ነው።
___
1 791
የኢትዮጵያውያን የማካበድ ጥግ!
__
ገዱ አንዳርጋቸው ኢትዮጵያ ከኢህአዴግ ወደ ብልጽግና ባደረገችው የሽግግርና የለውጥ መንግስት ውስጥ ከፍተኛ ሚና የተጫውቱ ጉምቱ ባለስልጣን ነበሩ፣ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ከጠሚ ዐቢይ አህመድና ከለማ መገርሳ ጋር ፖስተራቸው ተለጥፈው የሚወደሱ። ከእዛ ከዐብይ ጋር ያልተሰማሙባቸው ጉዳዮች ነበሩ ፣ ልክ እንደኦሮሚያው ለማ መገርሳ።
So ሀገር ጥለው ወጡ፣ አሜሪካ ሄዱ፣ የፓርኪንግ ሠራተኛ ሆኑ። ጥያቄው አሜሪካ ሲሄዱ የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር እንዲሆኑ ነበር የጠበቅነው? ልክ አቶ ተወልደ የህንድ አየር መንገድን እንደመሩት? ሲያምራችሁ ይቅር!
በነገራችሁ ላይ የአፍጋኒስታን የገንዘብ ሚንስትር ታሊባን ሀገሪቱን ሲቆጣጠር አሜሪካ ሄደው የኡበር ታክሲ ነጂ ነው የሆኑት።
ይሄ በሆነው ባልሆነው የምነፋረቀውንና እዬዬ የምንለውን ነገር እናቁም!
From Afghanistan's finance minister to cab driver in the US https://lnkd.in/eH6Tj9q4
1 791
ሰዎች ስለእግዚአብሔር ፣ ስለዓለም፣ ስለእድገት፣ ስለገንዘብ፣ ስለራእያቸው እና ግባቸው የሚወያዩበት ጠረጴዛ ዙሪያ ተቀመጥ።
ሰዎች ስለ "ሰው" ከሚያወሩበት ጠረጴዛ ራቅ!
1 791
ምስጋና - በAddis Ababa University የAdmission Team Leader ለሆኑት ለወ/ሮ Meaza Getachew
_
በቢሮአቸው ለጉዳይ በተገኘሁባቸው ሁለት ቀናት የተመለከትኩት፣
📚 የእያንዳንዱን ባለጉዳይ ችግር በጥሞና እና በትእግስት በማዳመጥ መፍትሔ ለመሻት በዩንቨርሲቲው ወደሚገኙ የተለያዩ ክፍሎች በአካል ጭምር በመሄድ ችግሮቻቸውን ሊፈቱላቸው ሲሞክሩ አስተውያለሁ።
📚 "የስኮላርሺፕ ደብዳቤ አልደረሰልኝም መማር አፈልጋልሁ፣ ስኮላርሺፕ ተፈቅዶልኝ ዲኑ አልፈረሙልኝም ምን ይሻለኛል?" ለሚሉ ጥያቄዎች ወደ ዩንቨርስቲዎች በግል ስልካቸው ደውለው "የስኮላርሺፕ ደብዳቤው እስኪደርስ ድረስ እንድንመዘግባቸው የትብብር ደብዳቤ ጻፉላቸው" በማለት ተማሪዎችን ወክለው ሲከራከሩና ችግሮቻቸውን ሲፈቱ ተመልክቻለሁ። ሌሎች ተማሪዎችም ሲያመሰግኗቸው ሰምቻለሁ።
📚 በግሌ የክሊራንስ ሂደት ባለማለቁ ምክንያት ለገጠመኝ ችግር በኮሜርስ ከሚገኙ የሬጅስራር ሠራተኞች ጋር በተደጋጋሚ በመደዋወል ችግሬን ፈትተውልኛል።
ከሁሉም በላይ የገረመኝ አንድ ወጣት "የCost sharing ሙሉ ለሙሉ አልከፈልኩም መማር ፈልጌ ነበር" ብሎ ላቀረበው ጥያቄ ክፍያው ሳይፈጸም ምዝገባ እንደማይቻል ከነገሩት በኋላ ወጣቱ አዝኖ እንደወጣ "ሰው መማር ፈልጎ፣ መማር እንደማይችል መንገር እንዴት የሚያም ነገር ነው?!" በማለት የተናገሩት ነገር በውስጤ ቀርቶ ይሄንን ጽሁፍ እንድጽፍ አነሳስቶኛል።
ጉዳዬን ጨርሼ ወ/ሮ መዓዛን ከልብ አመስግኜ ስወጣ አምላክ በየተቋሙ "አይቻልም፣ አይሆንም!" ከሚሉ ቃላት ውጪ ከአፋቸው ደግ የማያወጡትን ቀንሶ እንዲህ የየሰዉን ችግር በትእግስት አዳምጠው ሰው ለመርዳት ረጅም ርቀት በሚሄዱ፣ ቀኑን በሙሉ ባለጉዳይን በቅንነት ለመርዳት በሚታትሩና የሰው ችግር በሚያማቸው ሰዎች እንዲባርከን ከልቤ እየተመኘሁ ነበር።
___
Dear W/o Meaza,
Thank you for your excellent service, humanity, and enthusiasm. I truly appreciate your dedication and the warmth with which you carry out your work.
1 791
When Ethiopia Exports Its Best Professionals...
__
When an Ethiopian professional is appointed to a senior international position, we should see it as more than an individual career achievement, it is a national achievement.
The career of Tewolde Gebremariam, former CEO of Ethiopian Airlines, is a powerful example of how Ethiopian professionals can compete and lead at the highest international level.
For years, we have talked about brain drain as a challenge. But perhaps we should also recognize another side of the story: when our best professionals are sought after by international organizations and companies, it can be a sign of excellence.
A country that starts to export its best professionals is demonstrating that its human capital is becoming globally competitive.
Let us celebrate Ethiopians who take their expertise beyond our borders,not because we are losing them, but because they are showing the world what Ethiopian talent can deliver.
Our professionals are not just looking for international opportunities. Increasingly, the world is looking for Ethiopian professionals.
That is something worth celebrating. 🇪🇹🌍
1 791
Ethiopia’s richest billionaire, Mohammed Al-Amoudi returns to the $10 billion club after a $1.7 billion wealth surge | Business Insider Africa https://share.google/ZxC5KeJCo65eQpKmJ
1 791
Ethiopia’s richest billionaire, Mohammed Al-Amoudi returns to the $10 billion club after a $1.7 billion wealth surge | Business Insider Africa https://share.google/ZxC5KeJCo65eQpKmJ
