1 492
Subscribers
-224 hours
-87 days
+1630 days
Posts Archive
📢የ8ኛ ክፍል ፈተና የማለፊያ ውጤት ተወሰነ!
50% የማለፊያ ነጥብ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2017 የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን ወስኗል። የዘንድሮው ውጤት መሻሻል አሳይቷል! በተለይ የሂሳብ እና የእንግሊዘኛ ትምህርቶች ላይ ትኩረት ተደርጎ ነበር። ፈተናውን የወሰዱ ተማሪዎች ቁጥር 70,525 ነው። ውጤቱ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ይፋ ይሆናል። #አዲስአበባ #ትምህርት
ሰዓት ሲደርስ ዉጤት ለማየት 👉 Link
Share For Your Friend
+2
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት የ2017 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን በዛሬው እለት ወስነዋል።
(ሰኔ 17/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በከተማ አስተዳደሩ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት በየአመቱ መሻሻል እያሳየ መሆኑን ገልጸው ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራቱ ዘንድሮም ከአምናው የተሻለ ውጤት ለመመዝገብ ችላል ብለዋል።
ዶክተር ዘላለም አያይዘውም በ2017 ዓ.ም የሒሳብና እንግሊዘኛ ትምህርትን ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረገው ስትራቴጂ በተማሪዎች ውጤት መረጋገጡን ጠቁመው ፈተናውን በአጭር ጊዜ በማረም ውጤቱ ይፋ እንዲሆን ቀን ከሌት ሲሰሩ ለቆዩ የፈተና ክፍል ባለሙያዎችና ሂደቱን ሲደግፉ ለነበሩ አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል። በቀጣይ ጥቂት ቀናትም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ውጤት ይፋ እንደሚደረግ አስታውቀዋል። ውጤቱም ዛሬ ከሰዓት ይፋ ይደረጋል ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዲናኦል ጫላ በበኩላቸው በከተማ አስተዳደሩ በ2017 ዓ.ም 70,525 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡
የ2017 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት በነገው ዕለት ይፋ ይሆናል፡፡
(ሰኔ 16/2017 ዓ.ም) የ2017 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት በነገው ዕለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ነጥቡ ላይ ውይይት ካደረጉ በሃላ ይፋ ይደረጋል።
የ2017 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ ታርሞ ይፋ መደረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያስችል ሲሆን የ2017 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 3-4/2017 ዓ.ም ድረስ በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 194 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሁለት ቀናት መሰጠቱ ይታወሳል፡
ነገ ጉዞ እንሄዳለን የምትሉ ለሚፈጠረው ነገር እኔም ሁንኩኝ ት/ቤቱ ኃላፊነት አንወስድም# ወላጆችም ይህን አውቃችሁ በራሳቸው ፍላጎት መሄዳቸውን እንድታውቁ!!!! ያዘጋጆት ጉዞ በራሳቸው ፍላጎት መሆኑን እንድታውቁልኝ!!!!!!
በ15/10/17 በ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የተዘጋጀው ጉዞ #በተለያየ ምክንያት ለቀጣይ ቅዳሜ የተዘዋወረ መሆኑን #በ15/10/17 በዕለቱ ብዙ ትምህርት ቤቶችም በዛ ቀን ስለሚሂዱ መጨናነቅ ስለሚኖር በነዚህ ምክንያት ተዘዋውሯል አዘጋጆቹ !!!
📚 ነገ ሚኒስትሪ ፈተና ላይ ለምትቀመጡ ለ8ኛ ክፍል ተሪዎች አጠር ያለና አበረታች የሆነ መልዕክት 📚
📚 ውድ ተማሪዎች!
ነገ የጥረታችሁን ፍሬ የምታዩበት ትልቅ ቀን ነው። ለዚህ ፈተና ስትዘጋጁ የነበራችሁበት ጊዜ፣ የደከማችሁበት ልፋት እና ያፈሰሳችሁት ላብ ሁሉ ነገ እንደ አላህ ፍቃድ ፍሬ ያፈራል።
✅ አሁን ማድረግ ያለባችሁ አንድ ነገር ብቻ ነው፤ በራሳችሁ መተማመን! በእውቀታችሁ እና በተማራችሁት ነገር ላይ ሙሉ እምነት ይኑራችሁ። አላህ ከእናንተ ጋር እንደሆነ እመኑ። ይህ ፈተና የእውቀታችሁ፣ የመረጋጋታችሁ እና የድፍረታችሁ መለኪያ ነው።
✅ ጭንቀትን አስወግዱ! ጭንቀት የሚያደናቅፍ እንጂ የሚረዳ አይደለምና። በጥሞና ተንፍሱ፣ አእምሮአችሁን አረጋጉ።
✅ ፈጣሪ ሁሉንም ነገር እንደሚያቀልላችሁ እመኑ። በቀ የቻላችሁትን ያህል ሰርታችኋልና፣ አሁን ደግሞ ውጤቱን ለፈጣሪያችሁ ስጡ።
መልካም ፈተናን እመኝላችኋለሁ!
ነገ የድል፣ የመረጋጋትና የጥሩ ውጤት ቀን ይሁንላችሁ!
✅ ሁላችሁንም አላህ ይርዳችሁ! መልካም የሆነን ውጤት ይስጠችሁ!!
✍️ በረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል
#ለ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ በተረጋጋ ሆኔታ ፈተናችሁን በመስራት ጥሩ ውጤት የምታመጡበት ይሁንላችሁ!!!!!
#መልካም ፈተና ይሁንላችሁ!!!!!
Repost from Yeka Education
✔️የተፈታኞች መብትና ግዴታ
✅ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብና ሥርዓት አከባበር እንዲሁም የመልስ ወረቀት አጠቋቆርና ተዛማጅ ሁኔታዎችን አስመልክቶ በሚሰጡ ገለፃዎች ላይ የመሣተፍ ግዴታ አለበት።
⭐️ተፈታኙ በገለፃው ላይ ባለመሳተፉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል።
✅ተፈታኙ/ኟ የሰራበትን የመልስ ወረቀት ለፈታኙ በመስጠት የጥያቄ ወረቀቱን ይዞ መውጣት ይችላል
✅ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ጥያቄዎቹን መስራት ከመጀመሩ በፊት በፈተና የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ የግል መለያ መረጃዎችን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ በቅደም ተከተል ጽፍ ማጥቆር ይኖርበታል (በተለይ የመለያ ቁጥር እና የትምህርት አይነት ኮድ)።
✅ማንኛውም ተፈታኝ የራሱን ችሎታና ዕውቀት ተጠቅሞ መስራት ይጠበቅበታል፡፡
⭐️የሚሠራባቸው የጥያቄና የመልስ መስጫ ወረቀቶች ለሌሎች ተፈታኞች ዕይታ የተጋለጡ እንዳይሆኑ ሸፍኖ መስራት ይኖርበታል
✅ማንኛውም ተፈታኝ ሞባይል፣ ካልኩሌተርና የመሳሰሉ ማንኛውንም ዓይነት የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው ።
⭐️እያንዳንዱ ተፈታኝ ይህንን አውቆ በቅድሚያ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ።
✅ይህንን ባለማድረጉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ተፈታኙ ራሱ ኃላፊነቱን ይወስዳል።
⭐️ማንኛውም ተፈታኝ በመፈተን ላይ እያለ ፈተናውን እንዳይሠራ የሚያውኩ ሁኔታዎች ቢያጋጥመው በፈታኙ ሲፈቀደለት ችግሩን በመግለጽ አስፈላጊውን እርዳታ ማግኘት ይችላል ይሁንና በማንኛውም ምክንያት ለባከነ ጊዜ ተጨማሪ ሰዓት አይፈቀድም
⭐️ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከሚጀመርበት ጊዜ ተኩል ሰዓት /30 ደቂቃ/ ቀደም ብለው ከመፈታኛው ቦታ በመገኘት መቀመጫቸውን መያዝ አለባቸው።
✅ፈተናው ከተጀመረ ከ15 ደቂቃ በኋላ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተናው አዳራሽ መግባት አይፈቀድለትም።
⭐️ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ፈተናውን ሠርቶ ቢያጠናቅቅም እንዲወጣ አይፈቀድለትም።
⭐️ይሁን እንጂ ፈተናው ከተጀመረ ከ45 ደቂቃ በኋላ ከፈተና አዳራሹ ለመውጣት እንዲፈቀድለት ሲጠይቅ የመልስ ወረቀቱን ለፈታኙ አስረክቦ በጸጥታ እንዲወጣ ይፈቀድለታል።
✅ፈተናው ሊጠናቀቅ ከ10 ደቂቃ ያነሰ ጊዜ ሲቀረው የሚጨርስ ተፈታኝ የሁሉም ተፈታኞች የመልስ ወረቀቶች እስኪሰበሰቡና ለፈተናው የተፈቀደው የጊዜ ገደብ አብቅቶ እስኪደወል ድረስ በቦታው ተቀምጦ እንዲቆይ ይደረጋል።
✅ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ ማንኛውም ተፈታኝ ትክክለኛ ያልሆነ የተቀደደ ወይም የተበላሸ የፈተና ጥያቄ ጥራዝ ከገጠመው ወይም የተሰጠው የመልስ ወረቀት የተበላሸ ከሆነ ወይም በራሱ እጅ ቢበላሽበት እጁን አንስቶ በመጠየቅ ሲፈቀድለት ሊያስቀይር ይችላል።
✅ለተፈታኞች የተፈቀዱ
✍️እርሳስ
✍️የቀን ተማሪዎች የደንብ ልብስ (UNIFORM)
✍️ADMISSION CARD
✍️ላጲስ፣ መቅረጫና ማስመሪያ
❌ለተፈታኞች የተከለከሉ
🔠 ስልክ ይዞ መግባት አይቻልም
🔠ካልኩሌተር
🔠የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን
🔠ሰዓት
🔠በሀኪም ከታዘዘ ውጪ የሆኑ መነጽሮች
🔠የሚነበቡ ጽሁፎች በሙሉ
✅የፈተና ኦረንቴሽን ቀን
✅የ8ኛ ክፍል በ2/10/2017 እና የ6ኛ ክፍል በ9/10/2017 ዓ፣ም
✅ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ
✅8ኛ ክፍል ሰኔ 3 እና 4 /2017 ዓ.ም
✅6ኛ ክፍል ከሰኔ10-12/2017 ዓ/ም ይሆናል
#Share for Others
🔠🔠🔠🅰️ 🔠🔠🔠
ቻናላችን ይህ ነው
👇👇👇👇👇
✅✅✅✅✅
https://t.me/dam76
ሕዝባዊ ሠራዊት ቅ/አ/አ/መ/ደ/ት/ቤት
ምክር ለተፈታኞች
ተፈታኝ ተማሪዎች እንኳን በጉጉት ስትጠብቁት ለነበረው ፈተና በሰላም አደረሳችሁ። ይህ ለእናንተ ወሳኝ ጊዜ ነው። እስካሁን ትምህርታችሁን እያጠናችሁ ቆይታችኋል። መልካም ነው። ነገር ግን በፈተና ወቅት የምታከናውኗቸው ተግባራትም የጥናታችሁን ያህል ውጤታችሁ ላይ ተጽዕኖ አላቸው። ስለዚህ በዚህ ወቅት ምን ማድረግ እንዳለባችሁና ምን ማድረግ እንደሌለባችሁ ጠንቅቃችሁ ማወቅ ይጠበቅባችኋል። ለዚህም ይረዳችሁ ዘንድ የሚከተሉትን ምክሮችን ከወዲሁ ተረድታችሁ ለመተግበር ዝግጁ ሁኑ!
➊ በዋዜማው ስልክ መዝጋትና ከሚረብሹ ነገሮች ራስን ማራቅ ያስፈልጋል። ስልካችሁን መዝጋት ሀሳባችሁን ሊሰርቁ ከሚችሉ ማህበራዊ ሚዲያዎች መራቅ ይገባችኋል። በዚህ ወቅት ትኩረታችሁን ፈተናችሁ ላይ ብቻ አድርጉ፤
❷ በቂ እንቅልፍ ተኙ። በፈተና ዋዜማ ለማንበብ ብላችሁ በፍጹም አታምሹ። ባጭሩ በዚህ ቀን ተጨማሪ ሰዓት ከማንበብ ይልቅ ተጨማሪ ሰዓት መተኛት የተሻለ ዉጤት አለው። በቂ እንቅልፍ አለመተኛት በፈተና ወቅት ለድብርትና ለራስ ምታት ሊዳርግና ሥራችሁን ሊያበላሽ ይችላል። ጥሩ እንቅልፍ ለመተኛት ከባድ ምግቦችን አለመመገብ፤ ብዙ ቡና አለመጠጣት፤ እና ሌሎች አነቃቂ ነገሮችን አለመውሰድ ይመከራል፤
➌ ጠዋት ማልዶ መነሳት: በጊዜ ተነስቶ መዘጋጀት ከመቻኮል ጋር ተያይዞ ከሚመጣ መታወክ ያድናል። በተጨማርም ወደፈተናው አዳራሽ በጊዜ ለመድረስ ያስችላል፤
❹ ቁርስ በአግባቡ መብላት: በፈተና ወቅት ቁርስ አለመብላት አእምሮአችን የሚፈልገውን ያህል ኃይል እንዳያገኝ ስለሚያደርግ ለማሰብ አቅም እንዲያንስ ያደርጋል። ስለዚህ ቀለል ያሉ ምግቦችን ተመግባችሁ መሄድ ይኖርባችኋል። ከባድ ምግቦችን መመገብ ደግሞ አእምሮአችን ምግብ የመፍጨት ሥራ ላይ ብቻ እንዲወጠር ስለሚያደርግ ድካምና እንቅልፍ ያመጣል፤
❺ ወደ መፈተኛ ቦታው ፈተናው ከሚጀምርበት ሰዓት በፊት ቀድሞ መድረስ ያስፈልጋል። ይህም ለመረጋጋት ከፍተኛ አስተዋጽዖ አለው፤
❻ ከቤት ስትወጡ የፅህፈት መሳሪያዎቻችሁንና የመታወቅያ ካርዳችሁን መያዛችሁን እርግጠኛ ሁኑ። ይህም ከመንገድ ከመመለስና ከማርፈድ ያድናችኋል። ትርፍ እርሳሶችን እና የእርሳስ መቅረጫዎች መያዝ በጣም አስፈላጊ ነው፤
❼ ወደ ፈተና አዳራሽ ከመግባት በፊት ወደ መፀዳጃ ቤት መሄድ መልካም ነው። ምናልባት የፈተናው ሰዓት ረዥም ቢሆንና ሽንት ቢይዛችሁ መጨናነቅን ያመጣል። አቋርጣችሁ መውጣት ላይፈቀድላችሁ ይችላል፤
❽ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ላይ ስማችሁን በአግባቡ መጻፋችሁን እርግጠኛ ሁኑ። አንድ ፊደል እንኳን ብትሳሳቱ ኋላ የት/ት ማስረጃችሁ ላይ ስለሚቀመጥ ለማስቀየር ዋጋ ያስከፍላል፤
❾ መመሪያዎችን (instructions) በአግባቡ ማንበብና መተግበር ያስፈልጋል። በእያንዳዱ ፈተና ወረቀት ላይ ወይም የፈተናው ክፍሎች ላይ የሚሰጡትን መመሪያዎች በአግባቡ ማንበብና መተግበር ይኖርባችኋል፤
❿ አትደንግጡ! በደንብ ተንፍሱ! ብዙ ኦክስጂን ወደ ውስጣችን ማስገባት ብዙ ምግብ እንዲቀጣጠልና ኃይል እንዲመረት ስለሚያደርግ ጉልበትና ድፍረት ይጨምርላችኋል፤
⓫ መልስ መመለስ ከመጀመራችሁ በፊት እያንዳንዱ የፈተና ክፍል ስለያዛቸው የጥያቄ አይነቶች ገረፍ ገረፍ እያደረጋችሁ ብታዩ መልካም ነው። ይህም የተሰጣችሁን ሰዓት በጥያቄው ክብደት ልክ ከፋፍላችሁ ለመጠቀም ያግዛችኋል፤
⓬ አንዱ ጥያቄ ከከበዳችሁ ዝለሉት፤ አንድ ጥያቄ ላይ ተጠምዳችሁ ብዙ ጊዜ የምታጠፉ ከሆነ ቀጥለው ለሚጠብቋችሁ ጥያቄዎች ጊዜ ሊያጥራችሁ ይችላል። ስትዘሉት ግን የጥያቄ ወረቀቱ ላይ ምልክት ማድረጋችሁን እንዲሁም መልስ መስጫ ወረቀቱ ላይ ከተሰጡት አማራጮች አንዱን መልስ በግምት ማጥቆራችሁን አትርሱ። አጥቁሮ ማለፍ ምናልባት በኋላ የተሰጠው ጊዜ ቢያልቅና ወደ ጥያቄው መመለስ ቢያቅታችሁ መልስ መስጫ ቦታው ባዶ ሆኖ እንዳይቀር ያደርጋል፤
⓭ ቶሎ ለመውጣት አትቸኩሉ፤ ምንም አይጠቅማችሁም፤ ሰዓታችሁን አሟጥጣችሁ መጠቀማችሁን፤ ሁሉንም ጥያቄዎች በአግባቡ መመለሳችሁንና ማጥቆራችሁን አረጋግጡ። ጊዜ ቢተርፋችሁ ጥያቄዎቹን ለመከለስ ተጠቀሙበት፤
⓮ ያልገባችሁ ማንኛውንም ነገር ሲኖር ፈታኞችን ለመጠየቅ አትፍሩ (ከመልስ በስተቀር 🤔)፤
⓯ ልክ የፈተና ወረቀቱን ከመለሳችሁበት ጊዜ ጀምሮ የዚያ ትምህርት (subject) ነገር ማክተሙን በመገንዘብ ለቀጣዩ ፈተና እራስን ማዘጋጀት ይገባል። እንጂ፤ ስላለፈው ፈተና እያሰላልሰሉ መጨነቅ ለቀጣዩ ፈተና በምታደርጉት ዝግጅት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራል።
📚 መልካም የፈተና ጊዜ!
an 8 Students
▬▬▬▬▬▬
➤ የፈተና ቀናት እየደረሱ ስለሆነ አንዘናጋ!!
✍️ ተፈታኞች በሞዴል ፈተና ማለቅ ሳትዘናጉ በቀሪ ቀናት አስፈላጊውን ክለሳ ማድረግ ይጠበቅባቹሀል
✅ 8ኛ ክፍል
📚የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ሰኔ 3 እና 4/2017 ዓ.ል ይሰጣል
✅ 6ኛ ክፍል
📚 የ6ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ከሰኔ 10-12/2017 ዓ.ል የሚሰጥ ይሆናል
✅ አንዘናጋ!!
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
የሚኒስትሪ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች
➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡
❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡
➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡
❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡
❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡
❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡
❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል።
❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
✅ Second Semester Grade 8 Model Exam Answer key 2017 E.C
📚 ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION EDUCATION BUREAU
