Sidama Region Electric Utility/የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት
Open in Telegram
Show more
702
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+830 days
Posts Archive
አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ የቡና ጠጡ ፕሮግራም ተካሄደ።
የሪጅን ፅ/ቤት እና የሀዋሳ ቁጥር 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከል ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላት በአንድነት አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ የቡና ጠጡ ፕሮግራም አካሂደዋል። የሪጅኑ ሰራተኞች በአንድነት 2016 ዓመትን በማመስገን በመሸኘት፣ 2017 አመትን ተቀብለዋል።
መልካም አዲስ አመት
ለቅድመ-ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞቻችን በሙሉ
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የዘመን መለዋጫ በዓልን ምክንያት በማድረግ የቅድመ-ክፍያ (የካርድ) ተጠቃሚ ደንበኞቻችን በበዓሉ ዕለት በሀዋሳ ከተማ ካርድ መሙላት እንዲችሉ ሁኔታዎችን አመቻችቷል፡፡
በዚህ መሰረት በሀዋሳ ከተማ የምትገኙ የቅድመ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞቻችን በሙሉ በነገው በበዓሉ እለት በሀዋሳ ቁጥር 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከል ( መናኸሪያ ዋናው የተቋሙ ህንፃ ስር) በመገኘት አገልግሎቱን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት
ጳጉሜ/2016
በአርቤጎና ከተማ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተመልሷል
***
በአርቤጎና ከተማ አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ጳጉሜ 5/2016 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:00 ጀምሮ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት የኤሌክትሪክ ሽቦዎች በመበጣጠሳቸው አገልግሎቱ ለጊዜው ተቋርጦ ቆይቷል።
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባከናወነው የጥገና ስራ በአርቤጎና ከተማ እና በተወሰኑ አካባቢዎች ተቋርጦ የቆየው የኤሌክትሪክ ኃይል በመጠገኑ ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ መደበኛው አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን፤ ክቡራን ደንበኞቻችን መደበኛው አገልግሎት እስኪጀምር ድረስ በትዕግስት ስለጠበቃችሁ እናመሰግናለን፡፡
#የሲዳማ_ክልል_ኤሌክትሪክ_አገልግሎት
Follow ሀs
Telegram
https://t.me/SIDAMAEU
Facebook
ጳጉሜ /2016
ድንገተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥን ስለማሳወቅ
በአርቤጎና ከተማ እና አንዳንድ አካባቢዎች
በአርቤጎና ከተማ ዛሬ ጳጉሜ 5/2016ዓ.ም ንፋስ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት የኤሌክትሪክ ሽቦዎች በመበጣጠሳቸው በአርቤጎና ከተማ እና በአንዳንድ አካባቢዎች ከጥዋቱ 2 ሰዓት ጀምሮ የኤሌክትሪክ ኃይል የተቋረጠ በመሆኑ
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኃይለኛ ንፋስ እና ዝናብ ምክንያት የተፈጠረውን ችግር በማስተካከል በከተማው የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት መልሶ ለማስጀመር በስራ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ በትዕግሥት እንድትጠባበቁ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡
#የሲዳማ_ክልል_ኤሌክትሪክ_አገልግሎት
Follow ሀs
Telegram
https://t.me/SIDAMAEU
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61551030763514
ጳጉሜ /2016
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ስራ አስፈፃሚ አቶ አበበ እድሉ የ2017 አዲስ አመትን አስመልክተው ያስተላለፉት መልዕክት
እንኳን ለ2017 አዲስ ዓመት በሰላም በጤና አደረሳችሁ!!
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመላው ደንበኞቻችን፣ ለኢትዮጵያ ህዝብ እንዲሁም ለመላው ለተቋማችን ሰራተኞች በሙሉ እንኳን ለ2017 አዲስ ዓመት በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት አዲሱ ዓመት የሰላም የፍቅር እና የስኬት እንዲሆን መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡
በዋዜማውና በዕለቱ በኤሌክትሪክ መቋረጥ ምክንያት የበዐል አከባበሩ እንዳይታጎል በሪጅናችን በሐዋሳ ከተማ እና ከሐዋሳ ከተማ ውጪ በሚገኙ የደንበኞች አገልግሎት መስጫ ማዕከላቶቻችን ጊዜያዊ ግብረ ኃይል በማቋቋም በቂ ዝግጀት ተደርጓል፡፡
ደንበኞቻችን በዋዜማውና በዕለቱ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍጆታ ስለሚኖር የኤሌክትሪክ ኃይል የሚፈልጉ ስራዎች የኃይል ጭነት በማይበዛባቸው ሰዓታት በመጠቀም በመስመሮችና በትራንስፎርመሮቻችን ላይ ጫና እንዳይፈጠር በማድረግ የበኩላችሁን አስተዎጾ እንድታደርጉ እያሳሰብኩ መጪው አዲስ ዓመት ለአገራችን ሰላምና ለህዛባችን አንድነት የምናገኝበት እንዲሆንልን ልባዊ ምኞቴን እየገለጽኩ በድጋሚ መልካም አዲስ ዓመት ይሁንልን፡፡
አቶ አበበ እድሉ
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ
#የሲዳማ_ክልል_ኤሌክትሪክ_አገልግሎት
Follow ሀs
Telegram
https://t.me/SIDAMAEU
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61551030763514
ጳጉሜ/2016
በስራ ምክንያት የሚቋረጥ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ስለማሳወቅ
***
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቅድመ መከላከል ስራ ለማከናወን
በሀዋሳ ከተማ መነኃሪያ አካባቢ፣ አዲሱ ስታዲየም አካባቢ፣ ወልደ አማኑኤል አካባቢ፣ ሮሪ ሆቴል አካባቢ ፣ እና ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በከፊል
ጳጉሜ 1 /2016 አርብ እለት ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ እስከ 12፡00 ድረስ የኤሌክትሪክ አገልግሎት የሚቋረጥ በመሆኑ
በተጠቀሰው አካባቢ የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡
#የሲዳማ_ክልል_ኤሌክትሪክ_አገልግሎት
Follow ሀs
Telegram
https://t.me/SIDAMAEU
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61551030763514
ጳጉሜ/2016
አዲስ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማሻሻያ ተግባራዊ ሊደረግ ነው
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ሽፈራው ተሊላ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አዲስ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማሻሻያ ተግባራዊ ሊደረግ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ተግባራዊ የሚደረገው የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማስተካከያ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ሰኔ 13/2016 ዓ.ም መፅደቁን ያስታወሱት ዋና ስራ አስፈጻሚው፤ ከመስከረም 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል፡፡
ዋና ስራ አስፈጻሚው በመግለጫቸው የታሪፍ ማሻሻያው በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ደንበኞችን እንዳይጎዳ ድጎማ መደረጉንና በህብረተሰቡ ሊያሳድረው የሚችለውን ጫና ለመቀነስ ድጎማ ከማድረጉም በተጨማሪ በየሩብ አመቱ ተከፋፍሎ ለአራት አመታት የሚተገበር መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የሃገራችን የኤሌክትሪክ ታሪፍ ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሃገራት የኤሌክትሪክ ታሪፍ ጋር ሲነጻጸር በጣም ዝቅተኛ መሆኑን የገለፁት ዋና ስራ አስፈጻሚው፤ አሁን ተግባራዊ የሚደረገው ማሻሻያ ከሁለት ዓመት በፊት መሻሻል የነበረበት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
እንደ ዋና ስራ አስፈጻሚው ገለፃ ተግባራዊ የሚደረገው ታሪፍ ማሻሻያ የተቋሙን የመልሶ ግንባታና ሌሎች ወጪዎችን ለመሸፈንና ጥራት ያለውና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመስጠት ያለመ ነው፡፡
የታሪፍ ማሻሻያው የመኖሪያ ቤት፣ የንግድ ተቋማት፣ ዝቅተኛ ኢንዱስትሪ፣ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ እንዲሁም የመንገድ መብራት ተጠቃሚ ደንበኞች በሚል መከፋፈሉንም አስታውቀዋል።
የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚዎችን በተመለከተ እንደ አጠቃቀማቸው አሁን ከሚከፍሉትና ማስተካከያ ከተደረገበት መካከል ያለውን ልዩነት ሲከፍሉ እንደ አጠቃቀማቸው ድጎማ ተደርጓል፡፡
በዚህም ከ0 እስከ 200 ኪዋት/ሰ የሚጠቀሙ ደንበኞች የድጎማው ተጠቃሚ የሚሆኑ ሲሆን፤ ድጎማውም የመጨረሻው የትግበራ ዓመት ድረስ ይተገበራል ብለዋል፡፡
👉 ከ50 ኪዋት/ሰ በታች ለሚጠቀሙ ደንበኞች ያለውን ልዩነት 75 በመቶ የሚሆነውን ይደጎማሉ፣
👉 ከ50 ኪዋት/ሰ እስከ 100 ኪዋት/ሰ ለሚጠቀሙ ደንበኞች ያለውን ልዩነት 40 በመቶ የሚሆነውን ይደጎማሉ፣
👉 ከ200 ኪዋት/ሰ እስከ 300 ኪዋት/ሰ ለሚጠቀሙ ደንበኞች ያለውን ልዩነት 4 በመቶ ይደጎማሉ፣
👉 ከ400 ኪዋት/ሰ እስከ 500 ኪዋት/ሰ የሚሆነውን ማሻሻያውን ያለምንም ድጎማ የሚከፍሉ ይሆናል ብላዋል፡፡
እንዲሁም ከ500 ኪዋት/ሰ በላይ የሚሆነውን ደግሞ ሌላውን ተጠቃሚ የሚደግፉበት የጎንዮሽ ድጎማ ሥርዓት ተግባራዊ እንደሚደረግ አንስተዋል።
እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ ይህ የተደረገው የታሪፍ ማስተካከያ የሚከፈለው በአንድ ጊዜ ሳይሆን በ16 ዙር በሚደረግ የሂሳብ ማስተካከያ [ከመስከረም 1/2017 ጀምሮ] በአራት ዓመት ጊዜ ውስጥ ተፈፃሚ ይሆናል።
ኢንጂነር ሽፈራው ይሄንን ሲያስረዱ 50 ኪዋት/ሰ የሚጠቀሙ ደንበኞች አሁን የሚከፍሉት 27 ሳንቲም እንደሆነ ገልጸው፤ ከመስከረም ጀምሮ የሚከፍሉት 35 ሳንቲም ይሆናል ብለዋል።
ከአራት ዓመታት በኋላ ደግሞ [በ16 ዙሮች በሚደረግ ማስተካከያ] 1.56 ብር መክፈል ይጀምራሉ ሲሉ አስረድተዋል።
ይህ አዲሱ የኤሌክትሪክ የታሪፍ ማስተካከያ አፈጻፀም ትግበራ የሚመለከታቸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ሃይል እና የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
አዲሱን የታሪፍ ማስተካከያ የሚገልፅ መረጃ ለማግኘት ተከታዩን ሊንክ ይጫኑ፡-
http://www.eeu.gov.et/contents/electricity-tariff?lang=am
በክልሉ አራት የገጠር ቀበሌዎችን እና 1980 አባወራዎችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ ተቻለ
****
በሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሀገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራም በ2016 በጀት አመት በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በ4 ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ አራት የገጠር ከተሞች ውስጥ 1040 አባወራዎችን ፤ እንዲሁም ቀደም ባሉ አመታት ኤሌክትሪክ ባገኙ 18 የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ የሚኖሩ 940 አባወራዎችን በአጠቃላይ በበጀት አመቱ 1980 አባወራዎችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ ተቻለ።
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጀክት ማኔጅመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሀነ ዘርአይ አራት የገጠር ከተሞቹን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ 31.96 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ፣ 87.15 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ዝርጋታ እና የተለያየ አቅም ያላቸው የ16 ትራንስፎርመሮች ተከላ ስራዎች መከናወኑን ገልፀዋል።
የገጠር ቀበሌዎቹን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ የማቴርያል(የእቃ) ዋጋ እና የኮንስትራክሽን ወጪ ጨምሮ በአጠቃላይ 76,141,456.03 ብር ወጪ መደረጉን የክልሉ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ቢሮ አስታውቋል።
በክልሉ በዳራ ኦቲልቾ፣ በብላቴ ዙርያ፣ በዳሌ እና በአርቤጎና ወረዳዎች በሚገኙ የገጠር ቀበሌዎች ጋጀባ፥ሎያና ሾእቾ፥ጋሰራ ኩዌ እና ቦሬሻወላ፥ ርቃሜና ሙችቾ ቀበሌ የሚገኙ ከ1040 በላይ አባወራዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል።
የሲዳማ ክልል የፕሮጀክት ማናጅመንት ቢሮ በ2017 በጀት አመት ስድስት የገጠር ቀበሌዎችን የ24 ሰዓት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ እቅድ ይዞ በስራ ላይ የሚገኝ መሆኑን የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጀክት ማኔጅመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሀነ ዘርአይ አስታውቀዋል።
#የሲዳማ_ክልል_ኤሌክትሪክ_አገልግሎት
Follow ሀs
Telegram
https://t.me/SIDAMAEU
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61551030763514
ነሃሴ/2016
ሰራተኛው ተቋሙ የጣለበትን ኃላፊነት በአግባቡ በመወጣት፣ ደንበኛውን በቅንነት ማገልገል እንዳለበት ተገለጸ
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በክልሉ የሚገኙ 15 አገልግሎት ሰጪ ማዕከላትን ማዕከል በማድረግ የ2016ዓ.ም የስራ አፈጻጸም ግምማን እና የ2017 እቅድ የተመለከተ ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል።
በሪጅኑ የሚገኙ ማዕከላትን በአራት ቡድን በማድረግ የጀመረው ስብሰባ በሁለተኛው ቡድን የሰራተኞች የስራ አፈጻጸም ግምገማ በክልሉ በአራት የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት የሚገኙ ሰራተኞችን በአንድ ቡድን በማካተት ነሃሴ 23/ 2016 ዓ.ም ሐሙስ እለት በአለታወንዶ ከተማ አከናውኗል።
በውይይቱም በሀገረሰላም፣ በቀባዶ፣ በጩኮ እና በአለታወንዶ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት የሚገኙ ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል።
በእለቱ በነበረው ግምገማና የእቅድ ውይይት የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ አቶ አበበ እድሉ፣ የክልሉ የማኔጅመንት ቡድን አባላት፣ የአራቱ ማዕከላት ስራ አስኪያጆች፣ የሰራተኛ ማህበር ተወካይ እና የአገልግሎት መስጫ ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል።
በ2016 ዓ.ም አመት የተሰሩ ዋና ዋና ስራዎችን እና የ2017 በጀት አመት እቅድን የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕላኒንግ ክፍል ስራ አስኪያጅ አቶ ደጀን ገረመው አቅርበዋል።
የግምገማና የ2017 የእቅድ ውይይትን የመሩት የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ስራ አስፈፃሚ አቶ አበበ አድሉ ሲሆኑ በቀረበው ሪፓርት መሰረት ከሰራተኛው ጋር ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
ማዕከላቱ ለደንበኛው ተገቢ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር፣ የተቋሙን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ በሚያስችሉ ነጥቦች ዙሪያ፣ ለደንበኛው አዲስ ቆጣሪ ከመስጠት አንጻር፣ እንዲሁም በሪጅኑ በ2016 በጀት አመት የተገኘውን የተሻለ አፈጻጸም ማስቀጠል በሚቻልበት ዙሪያ ከሰራኛው ጋር ውይይት ተካሂዷል።
በሰራተኞች ለተነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎች በክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ አቶ አበበ እድሉ እና በሚመለከታቸው የሪጅን የስራ ክፍሎች በማዕከላቱ ስራ አስኪያጆች ምላሽ ሰጥተዋል።
የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ አቶ አበበ እድሉ በውይይቱ መጨረሻ ባስተላለፉት መልዕክት ተቋሙ ደንበኞችን በአግባቡ፣ በጥሩ ስነምግባር የሚያገለግሉ ሰራተኞችን ብቻ ይዞ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸው፤ ይህም በመሆኑ የተቋሙን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ ተቋሙን ማሳደግ እንደሚገባ፣ በተጨማሪም የኤሌክትሪኩን ኔትወርክ በማሻሻል ለደንበኛው ያልተቆራረጠ ኤሌክትሪክ ለመስጠት በቁርጠኝነት መስራት የሚያስፈልግ መሆኑን ተናግረዋል።
እያንዳንዱ የስራ ኃላፊና ሰራተኛ ተቋሙ የጣለበትን ኃላፊነት በአግባቡ በመወጣት፣ ደንበኛውን በቅንነት ለማገልገል ሁሌም ዝግጁ መሆን እንዳለበት ይህን በማድረግ ሪጅኑ በ2016 ያገኘውን የተሻለ ውጤትና አፈጻጸም በማስቀጠል በ2017 በጀት አመት በሁሉም የስራ መስክ ከፍተኛ ውጤት ለማምጣት ሁሉም ሰራተኛ የቻለውን ሁሉ ማድረግ እንዳለበት የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ አቶ አበበ እድሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በቀጣይም በሰራተኛው መካከል የሚካሄደው ውይይት በቀሩት የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት የሚቀጥል ይሆናል።
#የሲዳማ_ክልል_ኤሌክትሪክ_አገልግሎት
Follow ሀs
Telegram
https://t.me/SIDAMAEU
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61551030763514
ነሃሴ/2016
