Sidama Region Electric Utility/የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት
Open in Telegram
Show more
702
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+830 days
Posts Archive
ተቋሙ በሲዳማ ክልል በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች ድጋፍ አደረገ
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን በወንሾ ወረዳ ሐምሌ 2016ዓ.ም በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች መስከረም 21/2017ዓ.ም በቦታው ድረስ በመሄድ ህብረተሰቡን በማፅናናት የአይነት ድጋፍ አደረገ።
በተደረገው የድጋፍ ፕሮግራም የሲዳማ ክልል ምክር ቤት የማህበራዊ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ አየለች ሌዳሞ፣ የሲዳማ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የማህበራዊ ጉዳይ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ባንታየሁ ቀፀላ፣ የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አበበ እድሉ፣ የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የማኔጅመንት ቡድን አባላት ተገኝተዋል።
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አበበ እድሉ ተቋሙ ለህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከመስጠት ጎን ለጎን ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የማህበረሰብ ክፍሎች የበጎ ተግባር ስራዎችን እየሰራ የሚገኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በመሆኑም በሲዳማ ብሄራዊ ክልል በተፈጥሮው አደጋ ከአካባቢያቸው ተፈናቅለው ለሚገኙ የወንሾ ወረዳ ነዋሪዎች ለአንድ አባወራ 20 ኪሎ ግራም ፉርኖ ዱቄት እና 3 ሊትር ዘይት በአጠቃላይ ለ112 ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች ለእያንዳንዳቸው በነፍስ ወከፍ ድጋፍ ማድረጉን፤ እንዲሁም በይርጋለም ከተማ እና በወንሾ ወረዳ ለሚገኙ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው 260 ተማሪዎች የትምህርት መርጃ መሣሪያ ድጋፍ ማድረጉን የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አበበ እድሉ ገልፀዋል።
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የስራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞች ከወር ደመወዛቸው በአጠቃላይ 268,000.00(ሁለት መቶ ስልሳ ስምንት ሺህ ብር) አዋጥተው በመሬት መንሸራተት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ ማድረጋቸውን፣ በተደረገው ድጋፍም እያንዳንዱ የስራ ኃላፊና ሰራተኛ ለወገናቸው በችግራቸው ወቅት በመድረሳቸው ከፍተኛ ደስታ የተሰማቸው መሆኑን አቶ አበበ እድሉ ገልፀዋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች የትምህርት መርጃ መሳሪያዎችን ድጋፍ እያደረገ የሚገኝ መሆኑን በመጥቀስ በሲዳማ ብሄራዊ ክልል በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን በይርጋለም ከተማ እና በወንሾ ወረዳ ለሚገኙ 260 ተማሪዎች በአጠቃላይ 3,143 የመማሪያ ደብተሮችን ድጋፍ ማድረጉን አቶ አበበ እድሉ ገልፀዋል።
በድጋፍ ፕሮግራሙ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት የማህበራዊ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ አየለች ሌዳሞ የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች በሲዳማ ክልል በዜጎች የደረሰውን የተፈጥሮ አደጋ ተሰምቷቸው ድጋፍ ለማድረግ በመምጣታቸው፣ ለተጎዱት የህብረተሰብ ክፍሎችም ከደመወዛቸው አዋጥተው ድጋፍ በማድረጋቸው የተሰማቸው ደስታ ከፍተኛ መሆኑን በመግለፅ፣ የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የስራ ኃላፊዎችን እና ሰራተኞችን አመስግነዋል።
የሲዳማ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የማህበራዊ ጉዳይ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ባንታየሁ ቀፀላ በድጋፉ ፕሮግራም ባደረጉት ንግግር የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የክልላችን ነዋሪዎች ቢሮው ድጋፍ እንዲያደርግ በተጠየቀው መሠረት ለጥያቄው ፈጣን ምላሽ በመስጠት እያንዳንዱ ሰራተኛና የስራ ኃላፊ ከወር ደመወዙ በማዋጣት ለተጎዱት ነዋሪዎች ድጋፍ በማድረጉ ያደረገው በጎ ተግባር የሚያስመሠግነው መሆኑን፤ የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሰራተኞች ለህዝባችን ድጋፋችሁን በማሳየታችሁ፤ ለተማሪዎችም የትምህርት መርጃ መሣሪያ ድጋፍ በማድረጋችሁ የሚያስመሠግን ስራ ሰርታችኋል፤ ፈጣሪ ያክብራችሁ የሚል መልዕክትን አስተላልፈዋል።
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተፈጥሮ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ባደረገው የአይነት 268 ሺህ ብር፤ ለተማሪዎች በተደረገው የትምህርት መርጃ መሣሪያ ድጋፍ 168 ሺህ ብር ፤ በአጠቃላይ 436 ሺህ ብር ወጪ መደረጉን የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አበበ እድሉ ገልፀዋል።
በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን የወንሾ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አካሉ አደም የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያመጣውን የአይነት ድጋፍ ከሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳይሬተር አቶ አበበ እድሉ እጅ የተቀበሉ ሲሆን፣ ተቋሙ በወረዳቸው በመገኘት ላደረገው ድጋፍ ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።
ድጋፍ የተደረገላቸው የወንሾ ወረዳ ነዋሪዎች በተደረገላቸው ድጋፍ ደስታቸው ታላቅ መሆኑን በመግለፅ ድጋፍ ያደረገውን የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የስራ ኃላፊዎችን እና ሰራተኞችን አመስግነዋል።
#የሲዳማ_ክልል_ኤሌክትሪክ_አገልግሎት
Follow ሀs
Telegram
https://t.me/SIDAMAEU
Facebook
መስከረም /2017
ቆጣሪ በወቅቱ አለመነበብ በደንበኞች ላይ ምን ያህል ጫና እንደሚያሳድር ያውቃሉ? እንግዲያውስ እናሳውቅዎ የሚጠቀሙበት ቆጣሪ ካልተነበበ ቢል ስለማይዘጋጅልዎ ለተጨማሪ ወጪ ይዳረጋሉ፡፡ ስለሆነም ወድ #የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኞችን የሚጠቀሙበትን የኤሌክትሪክ ቆጣሪ በተቀመጠለት የማንበቢያ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በየወሩ መነበቡን ይከታተሉ፤ካልተነበበልዎትም ወዲያውኑ አገልሎት ወደሚያገሀኙበት ማዕከል በመሄድ ያሳውቁ፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ውድ#የድህረ ክፍያ ተጠቃሚ ደንበኛችን በመስከረም ወር የተጠቀሙበትን ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ እንዴት ማስላት እንዳለብዎ ያውቃሉ? ካለወቁ በምሳሌ እናስረዳዎ!!
አንድ ደንበኛ በመኖሪያ ቤቱ 4 ባለ 60 ዋት አምፖሎች በቀን ለ6 ሰዓት በወር ለ30 ቀናት ቢያበራ፣ 3000 ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የሚጠቀም የእንጀራ ምጣድ በቀን ለ2 ሰዓት በወር ለ10 ቀናት ቢጠቀም እና 1000 ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የሚጠቀም ምድጃ በቀን ለ5 ሰዓት በወር ለ30 ቀናት ቢጠቀም ፤
በዚህም መሰረት፡-
1ኛ. 4 አምፑል X 60 ዋት x 6 ሰዓት x 30 ቀናት = 43,200 ዋት.ሰ፣
2ኛ. 3000 ዋት ኤሌክትሪክ የኃይል የሚጠቀም የእንጀራ ምጣድ x 2 ሰዓት x 10 ቀናት=60,000 ዋት.ሰ፣
3ኛ.1000 ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የሚጠቀም ምድጃ x 5 ሰዓት x ለ30 ቀናት = 150,000 ዋት.ሰ፣
ሶስቱም ሲጠቃለሉ 43,200 ዋት.ሰ + 60,000 ዋት.ሰ + 150,000 ዋት.ሰ = 253,200 ዋት.ሰ ይሆናል፡፡
ይህም ወደ ኪሎ ዋት ሰዓት ሲቀየር 1 ኪሎ ዋት ሰዓት = 1000 ዋት ሰዓት በመሆኑ፤ 253,200 ዋት ሰዓት = 253.2 ኪሎ ዋት ሰዓት ይሆናል፡፡
በዚህ ስሌት መሰረት ከላይ በምሳሌው የጠቀስነው ደንበኛ በወር 253.2 ኪ.ዋ.ሰ የኤሌክትሪክ ኃይል ቢጠቀም በተቀመጠው እርከን መሰረት በ2.46 ብር ይባዛል፡፡
በዚህ መሰረት 253.2 ኪ.ዋ.ሰ x 2.46 ብር= 622.872 ብር ይመጣል፡፡ የአገልግሎት ክፍያ ብር 42.95 እና የቴሌቪዥን አገልግሎት ክፍያ 10 ብር ሲደመርበት በአጠቃላይ የደንበኛው ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ 675 ብር ከ 80 ሳንቲም ይሆናል ማለት ነው፡፡
ይህ የፍጆታ ሂሳብ ስሌት የሚያገለግለው ለድህረ-ክፍያና ለመስከረም ወር ብቻ ነው፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
#እንኳን_ለመስቀል_ደመራ_በዓል_አደረሳችሁ
ከመስቀል ደመራ በዓል አከባበር ጋር ተያይዞ ሊከሰት የሚችለውን የኤሌክትሪክ አደጋ ለመከላከል ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለመስቀል በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ፤ ከመስቀል ደመራ በዓል አከባበር ጋር ተያይዞ የእምነቱ ተከታዮች በተለያዩ ቦታዎች ችቦ የማብራት ስነ-ስርዓት እንደሚያካሂዱ የሚታወቅ ነው፡፡
በዚህ ወቅትም ደመራ ሲለኮስ ከኤሌክትሪክ መስመሮች፣ ምሰሶዎች፣ ትራንስፎርመሮች በጣም በራቀ መልኩ ማከናወን እንዲሁም የእሳት አደጋ እንዳይከሰት ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል፡፡
በጥንቃቄ ጉድለት የኤሌክትሪክ ንክኪ ጋር በሚፈጠሩ አደጋዎች በሰውና ንብረት ላይ ጉዳት ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡
በመሆኑም ለአከባበሩ ድምቀት የኤሌክትሪክ ምሰሶዎችን በመጠቀም የሚደረጉ የማስዋብ ሥራዎች ለኤሌክትሪክ አደጋ ሊያጋልጥ ስለሚስችል ከፍተኛ ጥንቃቄ እንደሚገባው ተቋሙ ያሳስባል፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ በኤሌክትሪክ ማሰራጫ ምሰሶዎች ላይ በተሽከርካሪዎች አደጋ የማደርስ ተግባር በበዓላት የሚሰተዋል በመሆኑ አሽከርካሪዎች ጥብቅ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተቋሙ ጨምሮ ያሳውቃል፡፡
ስለሆነም ህብረተሰቡ መሰል አደጋዎች እንዳይከሰቱ የበኩልን ትብብር እንዲያደርግ እየጠየቅን፤ ሆኖም ድንገት ከኤሌክትሪክ ጋር በተገናኘ አደጋ ካጋጠመ ወይም ሌላ መረጃ ሲፈለግ ወዲውያኑ በአቅራቢያ በሚገኝ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ቀጥታ ስልክ በመደወል ወይም በአካል በመሄድ ማሳወቅ ያስፈልጋል፡፡
በበዓል ወቅት ድንገት ለሚፈጠር የኃይል መቆራረጥ ቀጥለው በቀረቡት ስልክ ቁጥሮች 0462200419 እና 0462124937 መደወል የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት
ለደንበኛው ተገቢ አገልግሎት በመስጠት የተሻለ አፈጻጸም ማምጣት በሚያስችሉ ነጥቦች ዙሪያ ከሰራተኛው ጋር ውይይት ተካሄደ
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በክልሉ የሚገኙ 15 አገልግሎት ሰጪ ማዕከላትን ማዕከል በማድረግ የ2016ዓ.ም የስራ አፈጻጸም ግምማን እና የ2017 እቅድ የተመለከተ ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል።
በሪጅኑ የሚገኙ ማዕከላትን በአራት ቡድን በማድረግ የጀመረው ስብሰባ በሦስተኛው ቡድን የሰራተኞች የስራ አፈጻጸም ግምገማ በክልሉ በአራት የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት የሚገኙ ሰራተኞችን በአንድ ቡድን በማካተት መስከረም 7/ 2017 ዓ.ም ማክሰኞ እለት በይርጋለም ከተማ አከናውኗል።
በውይይቱም በወንዶ ገነት፣ በይርባ፣ ለኩ እና በይርጋለም አገልግሎት መስጫ ማዕከላት የሚገኙ ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል።
በእለቱ በነበረው ግምገማና የእቅድ ውይይት የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አበበ እድሉ፣ የክልሉ የማኔጅመንት ቡድን አባላት፣ የአራቱ ማዕከላት ስራ አስኪያጆች፣ የሰራተኛ ማህበር ተወካይ እና የአገልግሎት መስጫ ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል።
በ2016 ዓ.ም አመት የተሰሩ ዋና ዋና ስራዎችን እና የ2017 በጀት አመት እቅድን የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕላኒንግ ክፍል ስራ አስኪያጅ አቶ ደጀን ገረመው አቅርበዋል።
የግምገማና የ2017 የእቅድ ውይይትን የመሩት የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አበበ አድሉ ሲሆኑ በቀረበው ሪፓርት መሰረት ከሰራተኛው ጋር ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
ማዕከላቱ ደንበኞችን በአግባቡ በማገልገል ተገቢ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር፣ የተቋሙን ገቢ በአግባቡ መሰብሰብ በሚያስችሉ ነጥቦች ዙሪያ፣ ለደንበኛው አዲስ ቆጣሪ ከመስጠት አንጻር፣ እንዲሁም በሪጅኑ በ2016 በጀት አመት የተገኘውን የተሻለ አፈጻጸም ማስቀጠል በሚቻልበት ዙሪያ ከሰራኛው ጋር ውይይት ተካሂዷል።
በሰራተኞች ለተነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎች በክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አበበ እድሉ እና በሚመለከታቸው የሪጅን የስራ ክፍሎች እና በማዕከላቱ ስራ አስኪያጆች ምላሽ ሰጥተዋል።
የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አበበ እድሉ በውይይቱ መጨረሻ ባስተላለፉት መልዕክት ተቋሙ ደንበኛው የተሸለ አገልግሎትን ማግኘት ይችል ዘንድ ምቹ የሆኑ አዳዲስ አሰራችን በመዘርጋት ላይ የሚገኝ መሆኑን በመጥቀስ እያንዳንዱ ሰራተኛ ለተሸለ ስራ ራሱን ማዘጋጀት ያለበት መሆኑን ተናግረዋል።
ተቋሙ ደንበኞችን በአግባቡ፣ በጥሩ ስነምግባር የሚያገለግሉ ሰራተኞችን ብቻ ይዞ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸው፤ ይህም በመሆኑ የተቋሙን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ ተቋሙን ማሳደግ እንደሚገባ፣ በተጨማሪም የኤሌክትሪኩን ኔትወርክ በማሻሻል ለደንበኛው ያልተቆራረጠ ኤሌክትሪክ ለመስጠት በቁርጠኝነት መስራት የሚያስፈልግ መሆኑን ገልጸዋል።
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2016 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ ያገኘውን የተሻለ ውጤትና አፈጻጸም በማስቀጠል በ2017 በጀት አመት በሁሉም የስራ መስክ ከፍተኛ ውጤት ለማምጣት ሁሉም ሰራተኛ የቻለውን ሁሉ ማድረግ እንዳለበት የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አበበ እድሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
#የሲዳማ_ክልል_ኤሌክትሪክ_አገልግሎት
Follow ሀs
Telegram
https://t.me/SIDAMAEU
Facebook
https://www.facebook.com/profile.php?id=61551030763514
መስከረም/2017
ስለ አዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ በአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃንና የማህበራዊ ሚዲያ የትስስር ገፆች እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ የተሳሳተ ነው
ከመስከረም ወር 2017 ዓ.ም ጀምሮ የኤሌክትሪክ አገልግሎት በኪሎ ዋት እስከ 95 ብር ድረስ ጭማሪ ሊደረግበት ነው በሚል በአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃንና በማህበራዊ የትስስር ገፆች እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ የተሳሳተ ነው፡፡
ደንበኞች በታሪፍ ማሻሻያው ምክንያት ለኑሮ ጫና እንዳይጋለጡ፣ የገበያ ዋጋ እንዳይንር፣ ታሪፉን በየሩብ ዓመቱ ሸንሽኖ ተግባራዊ ከማድረጉም ባሻገር ከ0 እስከ 200 ኪዋት/ሰ የሚጠቀሙ የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚዎ ድጎማ ተደርጓል፡፡
በዚህም ከ0 እስከ 200 ኪዋት/ሰ የሚጠቀሙ ደንበኞች የድጎማው ተጠቃሚ የሚሆኑ ሲሆን፤ ድጎማውም የመጨረሻው የትግበራ ዓመት ድረስ ይቀጥላል፡፡
▶️ከ50 ኪዋት/ሰ በታች ለሚጠቀሙ ደንበኞች 75 በመቶ ይደጎማሉ፣
▶️ከ50 ኪዋት/ሰ እስከ 100 ኪዋት/ሰ ለሚጠቀሙ ደንበኞች 40 በመቶ ይደጎማሉ፣
▶️ከ200 ኪዋት/ሰ እስከ 300 ኪዋት/ሰ ለሚጠቀሙ ደንበኞች 4 በመቶ ይደጎማሉ፣
▶️ከ400 ኪዋት/ሰ እስከ 500 ኪዋት/ሰ የሚሆነውን ማሻሻያውን ያለምንም ድጎማ የሚከፍሉ ይሆናል ፡፡
ለምሳሌ በወር 50 ኪዋሰ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የሆነ አንድ ደንበኛ ቀድሞ በነበረው ታሪፍ በአንድ ወር ውስጥ 24 ብር ብቻ ይከፍል ነበር፡፡ አዲሱ ታሪፍ በሚጀምርበት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የአንድ ወር ክፍያው 28 ብር ነው፡፡ በ2ኛው ሩብ ዓመት የአንድ ወር ክፍያው 32 ብር ሲሆን፣ በ3ኛው ሩብ ዓመት የአንድ ወር ክፍያው 37፣ በ4ኛው ሩብ ዓመት 41 ብር ይከፍላል፡፡
ስለሆነም ህብረተሰቡ መሰል ከተሳሳቱና ከሚያደናገሩ መረጃዎች እራሱን ማራቅና ስለታሪፉ መረጃ ማወቅ ካስፈለገ ከዚህ በታች ያስቀመጥነውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ማንበብ የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን፡፡
http://www.eeu.gov.et/contents/electricity-tariff?lang=am
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ለመላዉ የእስልምና እምነት ተከታይ ደንበኞቻችን በሙሉ እንኳን ለ1499ኛው የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ !!
በዓሉ የሰላም፣ የጤናና የደስታ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን፡፡
ኢድ-ሙባረክ
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት
መስከረም /2017
ውድ ደንበኞቻችን እንኳን አደረሳችሁ!!
አዲሱን አመት ከውድ ደንበኞቻችን ጋር ተቀብለነዋል። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታ እና የስኬት አመት ይሁንልን።
የቅድመ ክፍያ ደንበኞቻችን በዛሬው በበዓሉ እለት በሀዋሳ ቁጥር 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከል የካርድ መሙላት አገልግሎት በመስጠት ላይ እንገኛለን።
የሲዳማ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት
መስከረም/2017ዓ.ም
