በወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር
Open in Telegram
እውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድምፅ!! በዚህ የቴሌግራም ቻናል የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዶግማን፡ቀኖናን እና ትውፍትን የጠበቁ ስርዓተ አምልኮ ትምህቶች እና ዝማሬዎች ይቀርቡበታል!!!
Show more326
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#ታላቅ_መንፈሳዊ _ጉዞ
👉ከክርስቶስ ልደት ከ200 ዓመታት በፊት የተቆፈረ ሰዉ ሰራሽ አሩጂያ ዋሻ አጠገብ የሚገኘዉ ሠሬ ባላካ አቡነ ተ/ሃይማኖት ቤ/ያን ሁሉ ነገር ተጠናቅቆ ልመረቅ ቀነ ቀጠሮ ቸይዟል!
ሁላችሁም እንዲትገኙ ተጋብዛቿል!!!
የማይቀርበት
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
"የአምላክ መንገድ ፍጹም ነው፤ የእግዚአብሔር ቃል የነጠረ ነው። መጠጊያ ለሚያደርጉት ሁሉ፣ እርሱ ጋሻ ነው።"
መዝሙር 18፥30
"ድንግል ሆይ በሁሉ አንደበት መመስገን የተገባሽ ስለሆነ። በሰማይ ካሉ መላእክትና በምድር ከሚኖሩ ደቂቀ አዳም፥ሁል ጊዜ ምስጋና ይቀርብልሻል።" /መልክአ ማርያም/
"በዕብራይስጥ ማሪሃም የተባለች የተመረጠች ድንግል ማርያምን ወደዳት ፤ አከበራት ፤ ከፍ ከፍ አደረጋት። በሁሉ ላይ አሰለጠናት። ሁሉን አስገዛላት። አምላክን በድንግልና የወለደች እርሷም የንጽሕና ፣ የቅድስና መሠረት ሆነች። አቤቱ ሆይ ! ክብሯን ፣ ገናናንነቷን በመረዳት አመሰግናት ዘንድ ለልቦናዬ ድምር እውቀትን ስጥ። አቤቱ ሆይ! ለአንደበቴ ኃይለ ቃሉን ስጥ። የማኅጸኗን መክበር ፣ የድንግልናዋን ነገር እናገር ዘንድ።"
አሜን በእውነት🙏🙏
አርጋኖን ዘሠሉስ
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥ በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥ የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፥ በጎች ከበረቱ ቢጠፉ፥ ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ፥
¹⁸ እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤ በመድኃኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ።
¹⁹ ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው፤ እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤ በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል።
ዕምባቆም 3:17-19
"ለቤተክርስቲያን የህልውና አደጋ የሆኑ ትርክቶችን ማስወገድ ይቻል ዘንድ የታሪክ ተመራማሪዎችን ያሳተፈ ሥራ ተግባራዊ እንዲሆን ተወስኗል።" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ
ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔዎችን በተመለከተ ዛሬ ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት መግለጫ ሰጥተዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በመግለጫቸው የጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የወሰናቸውን ውሳኔዎች የገለጹ ሲሆን እየተከሰቱ ስላሉት ውስጣዊ እና ውጫዊ ፈተናዎች ተነስተው ጠቃሚ ውሳኔዎች ተላልፈዋል ብለዋል።
ቅዱስነታቸው አክለውም ችግር የሚወገደው ለችግሩ መፈታት ሁሉም ድርሻ እንዳለው አውቆ በንስሐ ወደ ፈጣሪው ሲመለስ እና ሲጸጸት መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ያምናል በማለት ከኅዳር 15- ታኅሣሥ 27 ጸሎት እና ምህላ እንዲፈጸም እና ሁሉም በጸሎቱ መርሐ ግብር ላይ እንዲገኝ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።
ለቤተ ክርስቲያን የህልውና አደጋ የሆኑ ትርክቶችን ማስወገድ ይቻል ዘንድ የታሪክ ተመራማሪዎችን ያካተተ በቅዱስ ሲኖዶስ የሚመራ አካል ይኖራል በሥራውም የቤተክርስቲያንን ስም የሚያጎድፍ ትርክትን ይከላከላልም ነው ያሉት ቅዱስነታቸው።
ውጫዊ ፈተናዎችን በተመለከተ በችግሮቹ ዙሪያ ከሚመለከታቸው መንግሥታዊ ተቋማት ጋር በመወያየት መፍትሔ መፈለግ አስፈላጊ ነው ያሉት ቅዱስነታቸው በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች የተከሰቱት ጦርነቶች ፣ አለመግባባቶች እና ጥቃቶች አሳዝኖናልም ብለዋል።
የእምነት ነጻነት እና የምእመናን ደኅንነት እንዲሁም የቤተክርስቲያን ማኅበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ እና መዋቅራዊ ሥርዓቷ ይከበሩ ዘንድ በሁሉም ሀገረ ስብከቶች የህግ ባለሙያዎች ያሉት የህግ ክፍል እንዲኖር ተወስኗልም ሲሉ ገልጸዋል በመግለጫቸው።
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
ነጭም ቀይም አበባ የተባለ ልጅሽን እንዳቀፍሽው በተአምርና በንጽሕና ቀን ወደ ቤተ መቅደስ በገባሽ ጊዜ ርግቤ ድንግል ማርያም ሆይ ከልቅሶ ከሐዘን ታረጋጊኝ ዘንድ ነይ፤ መልካምና ውብ ሆይ ከደስተኛው ገብርኤልና እንዳንቺ ርኅሩኅ ከኾነው ከሚካኤል ጋር ነይ!
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተጠናቀቀ !
ጥቅምት 17 ቀን 2016 ዓ.ም
የጥቅምት 2016 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ለተከታታይ 6 ቀናት ማኅበራዊ ፣ መንፈሳዊ እንዲሁም አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ በማሳለፍ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።
ጉባኤው በዛሬ በ 6 ተኛ ቀን ውሎው አስተዳደራዊ ጉዳይን የያዘ የመሪ ዕቅድ ተመልክቶ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ ተጨማሪ ግብዓት ተጨምሮበት ለግንቦት ርክበ ካህናት እንዲቀርብ ወስኗል፡፡
በጸደቁ አጀንዳዎች ላይ ላለፈው አንድ ሳምንት ሲወያይ የቆየው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ መንፈስ ቅዱስን አጋዥ በማድረግ መግባባት በሰፈነበት ሁኔታ ጉባኤውን ማጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን በማጠናቀቂያው በሕግ ፣ በመሪ ዕቅድ ትግበራ እና በልዩ ልዩ ጉዳዮች ጥናት ላቀረቡ እና ማብራሪያ ለሰጡ ባለሙያዎች ብፁዕ ወቅዱስ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ምስጋና ማቅረባቸውን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ገልጸዋል።
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
#እስጢፋኖስም_ጸጋንና_ኃይልን_ተሞልቶ_በሕዝቡ_መካከል_ድንቅንና_ታላቅ_ምልክትን ያደርግ ነበር።
የሐዋርያት ሥራ 5 ፥ 2 - 8
#ቀዳሜ_ሰማዕት_ቅዱስ_እስጢፋኖስ
ጥቅምት 17 #ማዕረገ_ዲቁናን_በሐዋርያት_እጅ
በአንብሮተ እድ እንደተሾመ።
አሥራ ሁለቱም ደቀ መዛሙርት ሁሉን ጠርተው እንዲህ አሉአቸው፦ የእግዚአብሔር ቃል ትተን ማዕድን እናገለግል ዘንድ የሚገባ ነገር አይደለም።
ወንድሞች ሆይ፥ በመልካም የተመሰከረላቸውን መንፈስ ቅዱስና ጥበብም የሞላባቸውን ሰባት ሰዎች ከእናንተ ምረጡ፥ ለዚህም ጉዳይ እንሾማቸዋለን፤ እኛ ግን ለጸሎትና ቃሉን ለማገልገል እንተጋለን። ይህም ቃል ሕዝብን ሁሉ ደስ አሰኛቸው፤
እምነትና መንፈስ ቅዱስም የሞላበትን ሰው እስጢፋኖስን ፊልጶስንም ጵሮኮሮስንም ኒቃሮናንም ጢሞናንም ጳርሜናንም ወደ ይሁዲነት ገብቶ የነበረውን የአንጾኪያውን ኒቆላዎስንም መረጡ።
በሐዋርያትም ፊት አቆሙአቸው፥ ከጸለዩም በኋላ እጃቸውን ጫኑባቸው። የእግዚአብሔርም ቃል እየሰፋ ሄደ፥ በኢየሩሳሌምም የደቀ መዛሙርት ቍጥር እጅግ እየበዛ ሄደ፤ ከካህናትም ብዙ ሰዎች ለሃይማኖት የታዘዙ ሆኑ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
✝️በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ። አሜን።
✝️ጥቅምት ፲፮ ቀን
✝️፯ቱ ኪዳናት ወአባ ያቃቱ ሊቀ ጳጳሳት
✝️፯ቱ ኪዳናት
“ተካየደ” ማለት “ተስማማ፣ ተማማለ” እንደ ማለት ሲሆን “ኪዳን” በቁሙ “ውል፣ ስምምነት” እንደ ማለት ነው። ይኸውም እግዚአብሔር ከሰዎች ጋር፣ ሰዎችም ከሰዎች ጋር የሚያደርጉት ሊሆን ይችላል። ልዩነቱ የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ቅዱስና የማይለወጥ መሆኑ ነው።
እግዚአብሔር አምላክ ከሥነ ፍጥረት ጀምሮ በየጊዜው ከብዙ ወዳጆቹ ጋር ኪዳንን አድርጉዋል። ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም እነዚህን ኪዳናት ጥቅልል አድርጋ ፯ እንደሆኑ ታስተምራለች። ስለዚህም ዛሬ ፈጣሪ ቢረዳን እነዚሁን 7 ኪዳናት በጥቂቱ እንመለከታለን።
“ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ” “ከመረጥኳቸው ጋር ቃልኪዳንን አደረግሁ” (መዝ. ፹፰፥፫)
(፩) ✝️ኪዳነ አዳም
አዳም ማለት የእግዚአብሔር ድንቅ ፍጥረት፣ የፍጡራን አስተዳዳሪ፣ ነቢይ፣ ካህንና ንጉሥ ነው። እግዚአብሔር ከአዳም ጋር አስቀድሞ በእጸ በለስ አማካኝነት ቃል ኪዳን ነበራቸው። ነገር ግን አባታችን በዲያብሎስ ሴራ በመረታቱ ኪዳኑ ፈረሰ። (ዘፍ. ፫፥፩)
አዳምና ሔዋን ተጸጽተው ቢያለቅሱ ግን አዲስ የኪዳን ተስፋ፣ “ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ” የሚል ኪዳንን ተቀበሉ። (ቀሌምንጦስ፣ ገላ. ፬፥፬)
(፪) ✝️ኪዳነ ኖኅ
ከአዳም እስከ ኖኅ ድረስ ባሉት 10 ትውልድ ዓለም በዓመፃ ተሞላች። ቅዱስ ኖኅ በደግነቱ መርከብ ሠርቶ ቤተሰቡን ሲያተርፍ ዓለም በማየ ሥራዌ ጠፋች። ከመርከቡ ከወጣ በኋላ ኖኅና እግዚአብሔር በቀስተ ደመና ምልክትነት ቃል ኪዳን ተጋቡ። “ኢያማስና ለምድር ዳግመ በማየ አይኅ” እንዲል። (ዘፍ. ፱፥፲፪)
(፫) ✝️ኪዳነ መልከ ጼዴቅ
መልከ ጼዴቅ የእግዚአብሔር ካህኑ፣ የክርስቶስም ምሳሌው የሆነ የሳሌም ንጉሥ ነው። በ15 ዓመቱ መንኖ፣ አጽመ አዳምን ይዞ: በቀራንዮ በሕብስትና በወይን ያስታኩት ነበር።
እግዚአብሔር ለመልከ ጼዴቅ፣ በሐዲስ ኪዳን ለምትሠራው ክህነትና ምሥጢረ ቁርባን ምሳሌ አድርጐ በቃል ኪዳን አትሞታል። በዚህም ተሰውሮ ይኖራል እንጂ ሞትን እስካሁን አልቀመሰም። ይህም ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከአብርሃም ጋር በተገናኙበት ጊዜ ተገልጧል። (ዘፍ. ፲፬፥፲፯, ዕብ. ፯፥፩)
(፬) ✝️ኪዳነ አብርሃም
ቅዱስ አብርሃም የሕዝብና የአሕዛብ አባት፣ ሥርወ ሃይማኖት፣ የጽድቅም አበጋዝ ነው። ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር ሲል ከርስቱና ከወገኖቹ ተለይቶ በቅድስና ኖሯልና እግዚአብሔር “በዘርሕ አሕዛብ ይባረካሉ” አለው። (ዘፍ. ፲፪፥፩) የቃል ኪዳን ምልክትም ይሆነው ዘንድ ግዝረትን ሰጠው። (ዘፍ. ፲፯፥፩-፲፬)
(፭) ✝️ኪዳነ ሙሴ
ቅዱስ ሙሴ የነቢያት አለቃ፣ የእሥራኤል እረኛ፣ የእግዚአብሔር ሰው እና ፍጹም ትሑት (የዋህ) ሰው ነው። በፈጣሪው ትዕዛዝ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አውጥቶ ለ40 ዘመናት በበርሃ ሲመራቸው ከእግዚአብሔር የኪዳንን ጽላትና አሠርቱን ትዕዛዛት ተቀብሏል። (ዘጸ. ፳፥፩፣ ፴፩፥፲፰)
(፮) ✝️ኪዳነ ዳዊት
ቅዱስ ዳዊት ሥርወ ነገሥት፣ ጻድቅ፣ የዋህና ቡሩ የሆነ አባት ነው። እግዚአብሔር ከእረኝነት ጠርቶ ንጉሥ አድርጐ ሹሞት “ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ አኖራለሁ” (መዝ. ፻፴፩፥፲፩) ሲል ምሎለታል። አክሎም ሰፊ ቃል ኪዳን ሰጥቶ "አልዋሰሽህም" ብሎ ሲምልለት እንመለከታለን። (መዝ. ፹፰፥፴፭)
(፯) ✝️ኪዳነ ምሕረት
በብሉይ ኪዳን የነበሩ ፮ቱ ኪዳናት በዘመናቸው ክቡርና ሕዝቡን ከመቅሰፍት ይታደጉ የነበሩ ቢሆንም ከሲዖል ማዳን ግን አልቻሉም። ስለዚህም አንድ ፍጹም ኪዳን ያስፈልግ ነበር። ይህን ፍጹም ኪዳን ይፈጽም ዘንድም ከቅድስት ሥላሴ አንዱ ወልድ ከሰማያት ወርዶ በድንግል ማርያም ማሕጸን አደረ።
በፍጹም ተዋሕዶም በሕቱም ድንግልና ተወልዶ፣ አድጎ፣ ተጠምቆ፣ አስተምሮ፣ ሙቶ፣ ተነስቶና ዐርጐ ሥጋ ማርያምን በዘባነ ኪሩብ አስቀመጠው። ኪዳነ ምሕረት (የምሕረት ኪዳን) የምንለው አንዱ ታዲያ ይሔው ነው።
የጌታችን መጸነሱ፣ መወለዱ፣ መሰደዱ፣ መጠመቁ፣ ማስተማሩ፣ ሥጋውንና ደሙን መስጠቱ፣ መሰቀሉ፣ መሞቱና መነሳቱ፣ ማረጉና መንፈስ ቅዱስን መላኩ በአንድ ላይ ኪዳነ ምሕረት ይባላል። ታዲያ ይህ ሁሉ የተደረገው በሥጋ ማርያም ነውና የኪዳኑ ባለቤት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት።
የእርሷ ኪዳን የ፮ቱን አበው ኪዳናት ፍጹም በማድረጉ
“የኪዳናት ማሕተም” ይባላል። የድንግል ማርያም ኪዳኗ ከሲዖልና ከገሃነም ሊታደገን አቅሙ አለውና።
መድኃኒታችን ክርስቶስ ለድንግል እናቱ ቃል ኪዳኑን
ያጸናላት ደግሞ ካረገ ከዓመታት በሁዋላ ጐልጐታ ላይ ነው።
እመ ብርሃን በዚያ ቁማ ስለ ኃጥአን ስታለቅስ “እናቴ
ሆይ! በስምሽ ያመነውን፣ በቃል ኪዳንሽ የተማጸነውን እምርልሻለሁ” ብሎ ደስ አሰኝቷታልና። ይሔው በእመ ብርሃን ምልጃና ቃል ኪዳን ምዕመናን ከመቅሰፍትና ከገሃነመ እሳት ማምለጥ ከጀመሩ 2ሺ ዓመታት ሆኑ። ዛሬም እኛ ኃጥአን ልጆቿ ከእሳት እንደምታድነን አምነን በጥላዋ ሥር እንኖራለን።
“ኢትዝክሪ ብነ አበሳነ፣ ኃጢአተነ: ወጌጋየነ።
ማርያም እሙ ለእግዚእነ። በኪዳንኪ፣ ወበስደትኪ ድንግል ተማሕጸነ።”
“ድንግል ሆይ! ኃጢአታችን፣ አበሳችንና በደላችንን
አታስቢብን ዘንድ በስደትሽና በኪዳንሽ ተማጽነናል።”
ቸሩ ልጇ ከበረከተ ኪዳኗ አይለየን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።
ማቴ. 19፥27-ፍ.ም
27. በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ መልሶ። እነሆ፥ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ፤ እንኪያስ ምን እናገኝ ይሆን? አለው።
28. ኢየሱስም እንዲህ አላቸው። እውነት እላችኋለሁ፥ እናንተስ የተከተላችሁኝ፥ በዳግመኛ ልደት የሰው ልጅ በክብሩ ዙፋን በሚቀመጥበት ጊዜ፥ እናንተ ደግሞ በአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ ስትፈርዱ በአሥራ ሁለት ዙፋን ትቀመጣላችሁ።
29. ስለ ስሜም ቤቶችን ወይም ወንድሞችን ወይም እኅቶችን ወይም አባትን ወይም እናትን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን ወይም እርሻን የተወ ሁሉ መቶ እጥፍ ይቀበላል የዘላለምንም ሕይወት ይወርሳል።
30. ነገር ግን ብዙዎቹ ፊተኞች ኋለኞች፥ ኋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ።
“በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ።”
ኢሳይያስ 56፥5
✝️እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ የተሰወሩበት መታሰቢያ ዓመታዊ ታላቅ የንግስ ክብረ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን፤ አደረሳችሁ።
✝️“ከዚህም በኋላ በእግዚአብሔር ጸጋ እንደ ሔኖክና ኤልያስ ከሞት ፊት ተሸሸገ (ተሰወረ)።”
✝️ጻድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ✝️
-ሀገራቸው ሮም(ጣሊያን) ሲሆን አባታቸው ይስሐቅ የሮም ንጉሥ ነበሩ ፤ እናታቸው ደግሞ እድና ይባላሉ። ቀዳሚ ስማቸው ዘሚካኤል ነው።
-በ480 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ መጡ።
-ወደ ሀገራችን ወደ ኢትዮጵያ በአራተኛው ክፍለ ዘመን ከመጡት ከዘጠኙ ቅዱሳን አንዱ ናቸው። የቀሩት ስምንቶቹ ዘመዶቻቸው ሲሆኑ ከስምንቱም አንዷ እናታቸው እድና ናቸው።
-ተሰዓቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ የመጡበት ምክንያት በጉባኤ ኬልቄዶን የሁለት ባሕርይ እምነትን አንቀበልም ብለው ነው።
-ገዳማቸው ደብረ ዳሞ ከአክሱም በስተምስራቅ ፸ ኪ.ሜ ያህል ርቆ ይገኛል።
-ወደ ዳሞ ደብር ፷ ክንድ በሚረዝም ከጌታ በታዘዘ ዘንዶ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሰይፈ እሳት ይዞ እየጠበቃቸው ወጥተዋል።
-ደብረ ዳሞ የሀገራችን የመጀመሪያው ስመ ጥር ገዳም ሲሆን ዙሪያው ገደል ሲሆን ገዳሙ ላይ ለመድረስ ከላይ የሚለቀቀውና ፲፮ ሜትር የሚረዝመውና ወገብ ላይ ታስሮ የሚጎተተውን የተጎነጎነ የጠፈር ገመድ መታገዝ ያስፈልጋል።
-አቡነ አረጋዊ ከዐፄ ገብረ መስቀልና ከቅዱስ ያሬድ ጋር በደቡብ የሀገራችን ክፍል እየተዘዋወረ ወንጌልን ሲያስተምር ጋሞ ጎፋ ውስጥ ውኃ ከሌለበት ቦታ ደርሶ መሬቱን በመስቀል ባርኮ በአንድ ሥፍራ ላይ በተአምር ፵ ምንጮችን አፍልቋል። በዚህም ምክንያት ከተማው አርባ ምንጭ በመባል ይጠራል። እዚያው አካባቢ የምትገኘውን ደብረ ማርያም ብርብር ገዳምን በመጎብኘት ወንጌልን በመስበክ አካባቢውን ባርኳል።
-፺፱ ዓመት ሲሆናቸው በጌታ ፈቃድ ልክ እንደ ሔኖክና ኤልያስ ተሰውረዋል። የዛሬው በዓል ምክንያትም ይህ ነው። የመሠወራቸው ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል።
-የጻድቁ አባታችንን ረድኤት በረከት ያሳድርብን፣ የዓመት ሰው ይበለን! አሜን።
ዋቢ መጻሕፍት: መዝገበ ታሪክ ፣ ፍኖተ ስብከት ፣ መድብለ ታሪክ
ጥቅምት 14 ቀን 2016 ዓ.ም
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ 25 አጀንዳዎችን አጽድቆ ውይይት ጀመረ::
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ 25 አጀንዳዎችን በማጽደቅ ውይይቱን ጀምሯል ።
ምልዓተ ጉባኤው ዛሬ ጠዋት ባደረገው ስብሰባ አጀንዳ አርቃቂ ሰባት ብፁዓን አባቶችን መሰየሙ የሚታወቅ ሲሆን ለምልዓተ ጉባኤው ቀርበው ከጸደቁት 25 አጀንዳዎች መካከል በቅዱስ ፓትርያርኩ መልእክት እና በ 42 ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ በቀረበው የአቋም መግለጫ ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።
በቀጣይም ምልዓተ ጉባኤው የሚወያይባቸው አጀንዳዎች በየዕለቱ ለምእመናን እንደሚገለጹ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የኒውዮርክና አካባቢው አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አሳውቀዋል።
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif
