en
Feedback
በወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር

በወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር

Open in Telegram

እውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድምፅ!! በዚህ የቴሌግራም ቻናል የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዶግማን፡ቀኖናን እና ትውፍትን የጠበቁ ስርዓተ አምልኮ ትምህቶች እና ዝማሬዎች ይቀርቡበታል!!!

Show more
326
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
"ኦ ሚካኤል ኦ መተንብል፣ ካህነ አርያም ትሰመይ ቢጸ ሱራፌል፣ ዘእምርዑሳን ርዑስ ወዘእምልዑላን ልዑል፣ ጊዜ ጸዋዕኩከ ቅረበኒ በምሕረት ወሣህል፡፡" "አማላጃችን ሚካኤል ሆይ ፈጥኖ ደራሻችን ሚካኤል ሆይ የጌታን ዙፋን ከሚያጥኑ ሱራፌል ካህናት አንዱ ሰማያዊ ካህን አንተ ነህ ። የሰማያውያን ሊቃነ መላእክት ሁሉ አንተ አለቃቸው ነህ ይልቁንም የልዑላንም ልዑል አንተ ነህና በጠራሁህ ጊዜ ሁሉ በይቅርታና በቸርነት ድረስልኝ አትራቀኝ አሜን።" መልክአ ሚካኤል

"አኩርፈው የተለዩንን ወደ እኛ እንመልሳቸው እኛም ከሚያስኮርፍ ነገር እንራቅ አንድነታችንን እናጠናክር።" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አ
+3
"አኩርፈው የተለዩንን ወደ እኛ እንመልሳቸው እኛም ከሚያስኮርፍ ነገር እንራቅ አንድነታችንን እናጠናክር።" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማኅበራዊ እና  መንፈሳዊ ችግሮችን አጥንቶ ውሳኔ የሚሰጠው ምልዓተ ጉባኤ መከፈቱን ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ አበሰሩ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ቀዳማዊ  ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል። ቅዱስነታቸው በንግግራቸው ቤተክርስቲያን ከፈተና አልተለየችም ወደፊትም አትለይም ያሉ ሲሆን የደረሰብን ጫና ምን ያህል እንደሆነ የሚታወቅ ነው አንድ መሆን አለመቻላችንም ፈተና ሆኖብን ክፍተትን ፈጥረናል ብለዋል። የቀደምት አባቶቻችን የሰሩትን ልንደግም ይገባል ፤ ኃላፊነት አለብን ኃላፊነትታችንንም በሚገባ ልንወጣ ይገባል ፤ ለቤተክርስቲያን ክብር ከወገኝተኝነት የጸዳ እንከን የለሽ አንድነትን ልንፈጥር ይገባናል ነው ያሉት ቅዱስነታቸው። በርካታ ተከታይ ያላት ቤተክርስቲያን ልጆቿን በቅዱስ ወንጌል ከገነባች ሀብቷን በሚገባ ከጠበቀች እንኳን ለገንዘቡ ለሕይወቱ የማይሳሳ ምእመናን አሏት ፤ ዘመኑ የሚጠይቀውን አሰራር በመጠቀም የምንሰራው አሁን ነው ብለዋል። በመጨረሻም የሥራዎቻችን ዋስትና በሀገር እና በቤተክርስቲያን ዘላቂ ሰላም ሲኖረው ነው ፤ ቤተክርስቲያን ለሀገር ሰላም የአንበሳው ድርሻም እንዳላት ይታወቃል ድርሻዋንም ለመወጣት ትሠራለች ብለዋል ቅዱስነታቸው። የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መክፈቻ የጸሎት ስነ ሥርዓት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተካሄደ። ጥቅምት 11 ቀን 2016 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መክፈቻ የጸሎት ስ
+4
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መክፈቻ የጸሎት ስነ ሥርዓት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተካሄደ። ጥቅምት 11 ቀን 2016 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መክፈቻ የጸሎት ስነ ሥርዓት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተካሂዷል! በቤተ ክርስቲያናችን በዓመት ሁለት ጊዜ ከሚካሄዱት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤያት አንዱ የሆነው የጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤም ከነገ ጀምሮ ጉባኤውን የሚያከናውን ይሆናል። ፎቶ ፦ EOTC TV የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif

#ስብሐት_ለከ_ኢየሱስ_በአፈ_ኲሉ_ውዱስ፤ በኹሉም አፍ የተመሰገንኽ ኢየሱስ ሆይ ምስጋና ላንተ ይገባል ስብሐት ለከ ኢየሱስ ቀዳሴ ሥጋ ወነፍስ፤ ሥጋንና ነፍስን ያከበርኽ ኢየሱስ ሆይ ምስጋና ላንተ ይገ
#ስብሐት_ለከ_ኢየሱስ_በአፈ_ኲሉ_ውዱስ፤ በኹሉም አፍ የተመሰገንኽ ኢየሱስ ሆይ ምስጋና ላንተ ይገባል ስብሐት ለከ ኢየሱስ ቀዳሴ ሥጋ ወነፍስ፤ ሥጋንና ነፍስን ያከበርኽ ኢየሱስ ሆይ ምስጋና ላንተ ይገባል ስብሐት ለከ ኢየሱስ ለዕሩቃን ልብስ፤ [በኃጢአት] ለተራቆቱት [የጸጋ] ልብስ የኾንኽ ኢየሱስ ሆይ ምስጋና ላንተ ይገባል ስብሐት ለከ ኢየሱስ ዘኢትሠዐር ንጉሥ፤ የማትሻር ንጉሥ ኢየሱስ ሆይ ምስጋና ላንተ ይገባል ስብሐት ለከ ኢየሱስ ቃለ አብ ቅዱስ ቅዱስ የአብ አካላዊ ቃል ኢየሱስ ሆይ ምስጋና ላንተ ይገባል። (መቅድመ ተአምረ ኢየሱስ)

ባሕረ ጥበባት ካህን ቅዱስ ያሬድ
ባሕረ ጥበባት ካህን ቅዱስ ያሬድ

"ደስ ብሰኝ በአንቺ ደስ እሰኛለሁ ። ባዝንም ባንቺ እጽናናለሁ ።መከራና ችግር ቢያገኘንም ወደ አንቺ እጮኻለኹ ፤ የአመጸኛ ምላስ ቢያስከፋኝ ወደ አንቺ ፊት እማልላለኹ።ሰውነቴም የወደደችው ነገር ቢኖ
"ደስ ብሰኝ በአንቺ ደስ እሰኛለሁ ። ባዝንም ባንቺ እጽናናለሁ ።መከራና ችግር ቢያገኘንም ወደ አንቺ እጮኻለኹ ፤ የአመጸኛ ምላስ ቢያስከፋኝ ወደ አንቺ ፊት እማልላለኹ።ሰውነቴም የወደደችው ነገር ቢኖር አንቺን እለምናለኹ። በመታመን ያሻሁትንና የተመኘኹትን ባንቺ አገኛለኹ።" (መጽሐፈ አርጋኖን ዘአባ ጊዮርጊስ)

ለሰ/ት/ቤቶች መማሪያነት የተዘጋጀውን ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ ለማድረግ የሁሉም ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በኩል ተዘጋጅቶ ወደ እንቅሰቃሴ እየገ
ለሰ/ት/ቤቶች መማሪያነት የተዘጋጀውን ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ ለማድረግ የሁሉም ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በኩል ተዘጋጅቶ ወደ እንቅሰቃሴ እየገባ በሚገኘው የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ዙሪያ ለ አጠቃላይ ዓለም አቀፍ  ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች ማብራሪያ ቀርቧል። ማብራሪያውን የሰጡት የአገር አቀፍ ሰ/ት/ቤት አንድነት ም/ሰብሳቢ ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው እንደተናገሩት የሰ/ት/ቤች ሥርዓተ ትምህርትን ለመቅረጽ እጅግ በርካታ ሥራዎች ተሠርተዋል። አሁን ተቀርጾ ወደ ተግባር እንዲገባ የሚጠበቀው ሥርዓተ ትምህርት 6 ዋና ርእሶች እና አንድ ደጋፊ ርእስ ያለው ሲሆን ለዘንድሮው ዓመት ትግበራ እንዲሆን 42 መጽሐፍት ታትመው እና በሊቃውንት ጉባኤ ተገምግሞ ዝግጁ ሆኗል። አቅራቢው በተጨማሪ እንደገለጹት ሥርዓተ ትምህርቱ አሁን ያለው ትውልድ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ተረድቶ መንፈሳዊ ወጣት እንዲሆን የሚያስችል ዕውቀትን የያዘ በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለተግባራዊነቱ እንዲረባረቡ ጥሪ አቅርበዋል። ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቃ ጳጳስ እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እንዳሉት አሁን ያለውን ትውልድ ለማዳን ሰ/ት/ቤትን ማጠናከር የግድ ይለናል ብለዋል። በተጨማሪም ሁሉም አኅጉረ ስብከቶች ሥርዓተ ትምህርቱ ተግባራዊ እንዲሆን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ መልእክት አስተላልፈዋል። የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif

" ሐናም ስትጸልይ እንዲህ አለች። ልቤ በእግዚአብሔር ጸና፥ ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ፤ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ፤ በማዳንህ ደስ ብሎኛል።" (መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 2:1)

" አትታበዩ፥ በኩራትም አትናገሩ፤ እግዚአብሔር አዋቂ ነውና፥ እግዚአብሔርም ሥራውን የሚመዝን ነውና፥ ከአፋችሁ የኵራት ነገር አይውጣ።" (መጽ ሳሙ ቀዳማዊ 2:3)

"በዕብራይስጥ ማሪሃም የተባለች የተመረጠች ድንግል ማርያምን ወደዳት ፤ አከበራት ፤ ከፍ ከፍ አደረጋት። በሁሉ ላይ አሰለጠናት። ሁሉን አስገዛላት። አምላክን በድንግልና የወለደች እርሷም የንጽሕና ፣ የቅድስና መሠረት ሆነች። አቤቱ ሆይ ! ክብሯን ፣ ገናናንነቷን በመረዳት አመሰግናት ዘንድ ለልቦናዬ ድምር እውቀትን ስጥ። አቤቱ ሆይ! ለአንደበቴ ኃይለ ቃሉን ስጥ። የማኅጸኗን መክበር ፣ የድንግልናዋን ነገር እናገር ዘንድ።" አሜን በእውነት -አርጋኖን ዘሠሉስ- የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif