en
Feedback
በወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር

በወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር

Open in Telegram

እውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድምፅ!! በዚህ የቴሌግራም ቻናል የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዶግማን፡ቀኖናን እና ትውፍትን የጠበቁ ስርዓተ አምልኮ ትምህቶች እና ዝማሬዎች ይቀርቡበታል!!!

Show more
326
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥንተ ስቅለት ዓመታዊ ክብረ በዓል በወላይታ ሀ/ስብከት በዳሞት ሶሬ ወረዳ አንጩቾ ደ/ሰላም መድሃንአለም ገዳም በድምቀት ተከብሮ ውሏል።
+4
የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥንተ ስቅለት ዓመታዊ ክብረ በዓል በወላይታ ሀ/ስብከት በዳሞት ሶሬ ወረዳ አንጩቾ ደ/ሰላም መድሃንአለም ገዳም በድምቀት ተከብሮ ውሏል።

"የሚሰዋ በግ እርሱ ነው፤ የሚሰዋ ካህን እርሱ ነው፡፡ ከባሕርይ አባቱ ከአብ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም መስዋዕት የሚቀበል እርሱ ነው፡፡ በፈቃዱ መከራን በሥጋው የተቀበለ መከራንም ሁሉ የታገሠ እርሱ ነው፡፡ እንደ በግ ሊሰዋ መጣ፤ በግ በሚሸልተው ሰው ፊት እንዳይናገር አልተናገረም፤ በአንደበቱ ሐሰት አልተገኘበትም፡፡" ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ

​​በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን፡፡ ጥቅምት ፳፯ ✞✞✞ እንኳን ለፈጣሪያችን "መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ" እና ለቅዱሳኑ "አባ መቃርስ": "አቡነ መብዓ ጽዮን" "ወአባ ጽጌ ድንግል" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ለእኛ ሲል በፈጸመው የማዳን ሥራ ክፉዎች አይሁድ ከምሽቱ 3:00 ጌቴሴማኒ ውስጥ ያዙት:: ሙሉውን ሌሊት ከቀያፋ ወደ ሐና: ከሐና ወደ ቀያፋ ሲያመላልሱት: አስረው ሲደበድቡት አድረዋል:: ዝም ቢላቸው ዓይኑን ሸፍነው በጥፊ መቱት:: ምራቃቸውን ተፉበት:: ዘበቱበት:: ራሱንም በዘንግ መቱት:: እርሱ ግን ሁሉን ታገሰ:: በጧት ከገዢው ዘንድ ሞት እንዲፈረድበት አቀረቡት:: በሠለስት (3:00 ላይ) አካሉ እስኪያልቅ እየተዘባበቱ 6,666 ገረፉት:: ሊቶስጥሮስ አደባባይ ላይ እርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት:: 6:00 ላይ በረዣዥም ብረቶች 5 ቦታ ላይ ቸንክረው ሰቀሉት:: 7 ታላላቅ ተአምራት በምድርና በሰማይ ታዩ:: ዓለም በጨለማ ሳለች ጌታ በመስቀል ላይ 7 ቃላትን ተናገረ:: ከቀኑ 9:00 አካባቢ በባሕርይ ስልጣኑ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ:: +በዚያች ሰዓትም ወደ ሲዖል ወርዶ የታሠሩትን ሁሉ ፈታ:: 11:00 ላይ ደጋጉ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር በአዲስ መቃብር ቀበሩት:: በዚአች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተቃጠለ:: ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍፁም ለቅሶን አለቀሰ:: ቅዱሳት አንስት በዋይታ ዋሉ:: ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለው መጋቢት 27 ቀን ቢሆንም በዓሉ ወደ ጥቅምት እንዲመጣ ያደረጉት አበው ሊቃውንት ናቸው:: ምክንያቱም ብዙ ጊዜ መጋቢት 27 የሚውለው ዓቢይ ጾም ውስጥ በመሆኑና የንግሥ በዓላት በዓቢይ ጾም ስለማይፈቀዱ ነው:: ምንም እንኩዋ በቅርብ ጊዜ በዓቢይ ጾም የሚያነግሡ አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ቢኖሩም አባቶቻችን ግን እንዲህ ያለውን ሥርዓት አላቆዩልንም:: ከበሮና የቸብቸቦ ዝማሬም በወቅቱ የተፈቀደ አይደለም:: በዚህም ምክንያት የበዓለ ስቅለት ንግሡ ወደ ጥቅምት 27 ሲመጣ: የመጋቢት 5 ገብረ መንፈስ ቅዱስ ንግሥ ወደ ጥቅምት 5: የመጋቢት 10 መስቀል ወደ መስከረም 17 መጥቶ እንዲከበር ሆኗል:: የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif

በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የገለምሶ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ህንፃ ቤተ ክርስቲያን ተመረቀ። ህንፃ ቤተክርስቲያኑ በብፁዕ አቡነ እንጦንስ የምዕራብ ሐረርጌና የአፋር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
+2
በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የገለምሶ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ህንፃ ቤተ ክርስቲያን ተመረቀ። ህንፃ ቤተክርስቲያኑ በብፁዕ አቡነ እንጦንስ የምዕራብ ሐረርጌና የአፋር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጸሎትና ቡራኬ ተባርኮ ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ።

ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወደ ሚኒሶታ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተዘዋወሩ ። ጥቅምት 25 ቀን 2016 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የምዕራብ አርሲ
ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወደ ሚኒሶታ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተዘዋወሩ ። ጥቅምት 25 ቀን 2016 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰሜን አሜሪካ ወደሚገኘው የሚኒሶታ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ተዘዋውረው እንዲያገለግሉ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል። ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ጥቅምት 21 ቀን 2016 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ተፈርሞ የወጣ የብፁዕነታቸውን የዝውውር ደብዳቤ ተመልክቷል። ለብፁዕነታቸው መልካም የአገልግሎት ጊዜን እንመኛለን። የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif

የአቡነ ኤርሚያስ መልዕክት ለማኅበራዊ ሚዲያ ማድመቂያ በማኅሌቱ የሚታየው የሥርዓተ ቤተክርስቲያ ጥሰት ሊቆም ይገባል ሲሉ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ለኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ተናገሩ አቡነ ኤርሚ
የአቡነ ኤርሚያስ መልዕክት ለማኅበራዊ ሚዲያ ማድመቂያ በማኅሌቱ የሚታየው የሥርዓተ ቤተክርስቲያ ጥሰት ሊቆም ይገባል ሲሉ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ለኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ተናገሩ አቡነ ኤርሚያስ እንዳሉት ከበሮ ይዞ የሚሽከረከሩ፣ ጭፈራ የሚመስል በፍፁም ከኃይማኖታዊ የማይመስሉ ድርጊቶች በቤተክርስቲያን ላይ እየታዩ ነው ይህን ድርጊት ለማስቆም ሊቃውት መናገር ፈርቷል አሁን ደፍረን መናገር አለብን ይህ ድርጊት መቆም አለበት ብሏል። አሁን አላዋቂዎች እና ደጋፊዎቻቸው እየበዙ አዋቂዎች እያነሱ መጥቷል፣ እነዚህ ከእምነቱ ውጪ የሆኑ ድርጊቶች ሲከናወኑ ማህሌቱ ደመቀ ይባል መሆን የለበትም ሊቃውት ይህን ማስቆም አለባቸው ብለዋል።

#እጄን_ለአዴቻ_ኢየሱስ_ቤ/ያን_እንዘርጋ!! “አቤቱ አምላካችን ሆይ፥ ለቅዱስ ስምህ ቤት እንሠራ ዘንድ ይህ ያዘጋጀነው ባለጠግነት ሁሉ ከእጅህ የመጣ ነው፥ ሁሉም የአንተ ነው።” 1 ዜና 29፥16 በወ
+2
#እጄን_ለአዴቻ_ኢየሱስ_ቤ/ያን_እንዘርጋ!! “አቤቱ አምላካችን ሆይ፥ ለቅዱስ ስምህ ቤት እንሠራ ዘንድ ይህ ያዘጋጀነው ባለጠግነት ሁሉ ከእጅህ የመጣ ነው፥ ሁሉም የአንተ ነው።” 1 ዜና 29፥16 በወላይታ ሀገረ ስብከት በዳሞት ወይዴ ወረዳ ቤተክህነት ጽ/ቤት ሥር የሚገኝ ለአዴቻ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን የበኩላችን እንዲንወጣ ለታላቁ ማህበራችን ሕጋዊ ደብዳቤ ደርሶናል! በብዙ ድካም በገጠር መንደር እንዲህ ያለ አስደናቂ ግንባት በዚህ ደረጃ ካደረሱ ቡኃላ ለማስመረቅ ስሉ እጅ አጠሯቸዋል😥 አስተውሉ በገጠር አከባቢ አንድ ቤተክርስቲያን ሲመረቅ ስንት ስሁታን እንደሚመለሱ የሚታውቁት የአደባባይ ሚስጢር ነው። በአጭሩ :-2000 ብር የሚለግስ 60 በጎ አድራጊ እንፈልጋለን በተጨማሪ በዝርዝር ከተጻሐፉት 1ዱን እኔ እሸፍለው የሚል ከተገኘ ደስታችን ወደር የለውም ።ውድ ኦርቶዶክሳዊያን አቅማችሁ የፈቀደውን ለበረከት እጃችሁን ዘርጉ!!! 👉አካውንት ቁጥሩ እነሆ:-1000227657016 የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif

“ብንጸና፥ ከእርሱ ጋር ደግሞ እንነግሣለን፤ ብንክደው፥ እርሱ ደግሞ ይክደናል፤” 2ኛ ጢሞቴዎስ 2 ፥ 12