ያህዌ ይርኤ ኪነ ጥበብ
253
Subscribers
No data24 hours
-27 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
ነፍሴ ሆይ ስሚኝ #እንደ አንዱ ነሽ
ከ8 ቢልዮን ህዝብ እንደ አንዱ ነኝ ከብዙ ዮሴፎች እንደ አንዱ ከሺህ ዘማሪ እንደ አንዱ ከሺህ አገልጋይ እንደ አንዱ ነኝ። ማህበራዊ ሚድያ ላይ ከሚገኙ ሚልየን ሰወች እንደ አንዱ ነኝ። በምንም ነገር አንድያ አደለሁም ምን ይተካቸዋል የተባሉ ግኝቶች አልፎባቸዋል ያልፍባቸዋልም አይነኬ የተባሉ ሪከርዶች ለጉድ ይሰባበራሉ #ኮከብ ነኝ ብዬ በማስብበት ቦታ እኔ ባልኖር ህይወት ትቀጥላለች የማልፍበትንም መንገድ ብዙ ሰው አልፎበታል። የምናገረውን ነገር አልተናገረውም እንጂ ብዙ ሰው ያውቀዋል እኔም ኑሮዬም አዲስ አደለንም ሳልወለድ አለም ነበረች ስሞትም አንድ ሰው እንዳጣች አስባ ትቀጥላለች ስሚኝ ነፍሴ ረጋ በይ #ብርቅ አደለሽም!
Yosef Aschalew
🔥@Urim7🔥
🔥@Urim7🔥
👍 3😁 2
የ እግዚአብሄር አጠራር ግሩም ግሩም ግሩም ነው...ታራም 3 ልጆች ነበሩት...አብራም፣ሐራም እና ናኮር...ሐራም 3 ልጆችን ወለደ..ዮስካ ፣ ሚልካ እና ሎጥን...አብራም እና ናኮር ደግሞ ሚስቶች ነበሯቸው....ሁሉም ይኖሩ የነበረው ደግሞ በ ዑር ነበር ...ዑር በጣም የሰለጠነች ሀገር ነች ብዙ ስልጣኔ የጀመረባት ምድር....ከነዓን ደግሞ በተቃራኒው ከ ዑር የተሻለ ስልጣኔ አልነበራትም...እና የሚገርመው ታራም ከዚች ምድር ነው ሎጥ፣ አብራምንን እና ሚስቱን ወደ ከነዓን ለመሄድ ወደ ካራን ይዟቸው የሄደው...ቃሉን ስናነብ "ከእርሱም" ጋር ነው የሚለው...እና ቅድሚያ ራሱ ታራን ወደ ከነዓን የመሄድ ሀሳብ ነበረው....በጣም የገረመኝ ነገር...ታራም የተዋቸው ቤተ-ዘመዶች ነበሩ በ ዑር ...ልጁን ናኮር እና የ ሙት ሴት ልጆቹን ማለትም የ ሐራምን ልጆችን አልያዛቸውም ነበር።...ሐራም እዛው "ዑር" ነበር የሞተው...ዘፍ 12 ላይ እግዚአብሔር አብራምን ለሚጠራበት አጠራር መንገዶች ምቹ እየሆኑ ይመስላል🤷...ብቻ ህይወት እነ ታራም ቤት እንዲህ እየቀጠለ ያልተጠበቀ ነገር ተፈጠረ😱...ታራም በካራን ሞተ 😭..አብራም መጀመሪያ ሰምቶ የወጣ የሚመስለው የአባቱን ድምፅ ነበር...ሎጥ፣ አብራም እና ሚስቱ ሶራ ብቻቸውን በካራን ቀሩ 😔😭....እግዚአብሄርም መጣ 😎...አብራምን ጠራው በፉጨት .."አባትህ እንሂድ ብሎህ በካራን ካደህ፤ ያም የእኔ ፉጨት ነበር ..እና አብራም እግዚአብሔር እባላለው✋....ወደ ከነዓን እንሂድ" አለው....መንገድ አስጀምሮ እንደማይተው በዘላለም አባትነቱ አያስረገጠለት...ከዚያም ተነሱ ሎጥም አብሮት ነበር ነገር ግን መንገዱ የአብራም እና የ እግዚአብሄር ብቻ ስለነበር በአንዱ ክፍል ከሎጥም ተለዮ☹️🥺😊....ግን እሺ ታራም ባይሞት አብራም ያ መንገድ የማን ይመስለው ነበር🙄? እና እግዚአብሔር ነገሮችን ሲያስተካክል የመጣበት መንገድ ልዮ ነበር😊...የሐራም መሞት፤ የታራም እነ ናኮርን መተው፤ የ ታራም በካራን መሞት...ብቻ ይገርማል እናም እንደተለመደው ነው እግዚአብሔር አሻግሮ በ አብራም በኩል ኢየሱስን እያየ እንዴት እርፎ ይቀመጣል.....አህዛብ ልጆቹ ሲባሉ እና መንግስቱ ሲሰፋ እያስተዋለ እግዚአብሔር ከፍጥነቱ እንዴት ይዘገያል.....🙏አብራምን የሚያስቀርበትን መንገድ ይፈልጋል እንጂ።....እኛን ሊያተርፍ🥰...
ከሲኦል አተረፍከን🙏
ዘፍ 11፥10-32, ዘፍ 12 እና ዘፍ 13 ይነበብ🙏
✍️ Shall (Eyaned)
🔥 4
Listan: The Name and The Gift | Abenezer Dejene and Mekdim Debebe
https://youtube.com/watch?v=p8GStixFgJo&si=HtrwAxZeLW1ExGBh
በፊደል አይደለም
በሀጢያት ለነተብን ለቆሸሽን ለእኛ
በራሳችን ጥፍት ከአምላክ ለሆንን ጠበኛ
የፍቅርን ምንነት በውል ላላወቅን
በፊደል ሳይሆን ሆኖ አስተማረን
ድምጸት በሌለው ቃል ፍቅሩን አበሰረን
በተግባር ተረከው ቃላት ሳያዋቅር
እንዲህ ነው እንዲያ ነው ሳይል ስለፍቅር
እኔ ነኝ አለና ወርዶ ገለጠልን
እስከሞት መሆኑን ሙቶ አሳወቀን
መውደድ ማለት ብሎ ሞተና ተረከው
በመስቀል ሂደቱ ሁሉን ለኛ አበራው
ምን ያህል እንደሆን የፍቅርን ርቀት
በውርደቱ አሳየን የመውደዱን ብርታት
ግና እየቻለ ማለት በአንደበት
አልወደደም..
የኢየሱስ ፍቅር በፊደል አይደለም
ሰላም✍
@jihovajrehartteam
@jihovajrehartteam
👏 4👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
Found this from our community, enjoy!
መዝ 23(6) - እንዴት ነው ምህረቱና ቸርነቱ የሚከተሉን?
Chad Bird የተባለ ፀሐፊ "ይከተሉኛል" የሚለውን ቃል የትኛውንም አይነት ተራ መከተልን ከማመልከት ያለፈ ትርጉም እንዳለው ያብራራል።
"ይከተሉኛል" ተብሎ የተተረጎመው ቃል በእብራይስጥ "Radaph" ነው። ይኼም አንድን እጅግ ተፈላጊ ሰው እንዳይጠፋ ከኋላ ኋላው ማሳደድን ያመለክታል። እዚህ ጋር የሲ. አይ. ኤ ወይም ሞሳድ ወይም ኬጂቢ የስላለ ድርጅቶች አንድን እጅግ ተፈላጊ ሰው ጂፒኤስ፣ ድሮንና ዘመናዊ መሳሪያዎች ተጠቅመው ደብዛው እንዳይጠፋ የገባበት እየገቡ በጥብቅ መከታተልን የሚመስል ጥልቅ ትርጉም አለው። ይኼም ምናልባትም "ጥብቅ ክትትል ማድረግ" ከሚለው የስላላው ዓለም ሀሳብ ጋር ተስማሚ ነው!!
እናም Chad ይላል፦ "ቸርነቱና ምህረቱ እንደ ተጎታች የቤት ውሻ ከኋላ ኋላችን አይከተሉንም። ወደየገባንበት ሰርጥና ጉራንጉር ሁሉ በእሳት ሰረገላ እያሳደዱ ይከተሉናል።
ወንጀለኞችን ለማደን እንደ ሰለጠነ ውሻ በለያችን ያለውን ሰማያዊ ጠረን እያሸተቱ ያሳድዱናል። ከእግራችን ዱካ አይርቁም፤ ኮቴያችንን አይለቁም።
ቸርነቱና ምህረቱ ወደ ሰማይ ደጅና አባታችን እቅፍ እስክንገባ ከኋላ ኋላችን ያሳድዱናል።"
አንዳንድ ቅጂዎች ደግሞ "በእግዚአብሔር ቤት ለዘላለም እኖራለሁ" በሚለው ሀሳብ "እኖራለሁ" የሚለውን "ወደ መኖር እመለሳለሁ" ["Shall return to dwell" ESV Study Bible footnote] ይላሉ። ይኼም በቸርነትና ምህረቱ ክትትል ከተቅበዘበዘበት ተነድቶ በመመለስ ወደ ዘላለም ዕረፍት መግባትን ያመለክታል።
Credits: @Mercysiuu
#Spiritual #Lessons #Devotion
@Dagmawi_Babi
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
"ዲያኮኒያ"
ልዩ የአምልኮ እና የኪነጥበብ ምሽት
በቴፒ ቁ.1 ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ሰኔ 21 አርብ ከቀኑ 9:00 ሰዐት ጀምሮ
በያህዌ ይርኤ የኪነጥበብ ህብረት የተዘጋጀ
@jihovajrehartteam
@jihovajrehartteam
👍 6
ደርሶን ማሰብ ዘመን መሸከም እንደሆነ አለማወቅን ለመኖር መመለስ እንዲቻል የተፈጥሮን ትዕዛዝ መጣስ መገደድ ነው። ባለማወቅ ውስጥ ያለ ደስታ ሲቆይ ይመንናል ቢባል መንገዱ ራሱ ምስክር ነው።ለምን እንዳይባል የሀሳብን መንደር ሰብስቦ......ያላጠረው ይመስል....እየተሽከረከረ ቀዳዳ ይደፍናል ...ለቀዳዳው መስፋት እና መለጠጥ ከአትክልተኛው በላይ ማን ተጠያቂ አለ?
ራሱን ለማወቅ መትጋት........
✍️ሻሎም መልካሙ
@jihovajrehartteam
👍 4
እመነኝ
ግዴለም
ዛሬን ማረኝ እንጂ ዳግም አላጠፋም
አልፈቅድም ከቀድሞው ምኞት እንዲፋፋም
ቃል ገባለው እንዲ ምህረት ልገዛ
ቋንቋን እያዛመድኩ መሸሽቆጥቆጥ ላበዛ
ታዘብከኝ አይደለ ሁሉ እንደማታቅ ስሸነጋግልህ
ሚገርመው ብታውቅም አዝኖ ለለመነህ
መፅደቁ ነውና በሱቤት በራሱ
ታነሳሳዋለህ ዝቅ ብለህ እንደሱ
ወዳጄ
ሆስ
@jihovajrehartteam
👍 1
Choose a Different Plan
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.