cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ያህዌ ይርኤ ኪነ ጥበብ

ኢየሱስን መግለጥ

Show more
Advertising posts
253
Subscribers
No data24 hours
-27 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ነፍሴ ሆይ ስሚኝ #እንደ አንዱ ነሽ ከ8 ቢልዮን ህዝብ እንደ አንዱ ነኝ ከብዙ ዮሴፎች እንደ አንዱ ከሺህ ዘማሪ እንደ አንዱ ከሺህ አገልጋይ እንደ አንዱ ነኝ። ማህበራዊ ሚድያ ላይ ከሚገኙ ሚልየን ሰወች እንደ አንዱ ነኝ። በምንም ነገር አንድያ አደለሁም ምን ይተካቸዋል የተባሉ ግኝቶች አልፎባቸዋል ያልፍባቸዋልም አይነኬ የተባሉ ሪከርዶች ለጉድ ይሰባበራሉ #ኮከብ ነኝ ብዬ በማስብበት ቦታ እኔ ባልኖር ህይወት ትቀጥላለች የማልፍበትንም መንገድ ብዙ ሰው አልፎበታል። የምናገረውን ነገር አልተናገረውም እንጂ ብዙ ሰው ያውቀዋል እኔም ኑሮዬም አዲስ አደለንም ሳልወለድ አለም ነበረች ስሞትም አንድ ሰው እንዳጣች አስባ ትቀጥላለች ስሚኝ ነፍሴ ረጋ በይ #ብርቅ አደለሽም! Yosef Aschalew 🔥@Urim7🔥 🔥@Urim7🔥
Show all...
👍 3😁 2
ሰላም ቤተሰቦች አገልግሎታችን ብዙዎች ጋ እንዲደርስ share እያረጋችሁ እሺ😁
Show all...
👍 2
የ እግዚአብሄር አጠራር ግሩም ግሩም ግሩም ነው...ታራም 3 ልጆች ነበሩት...አብራም፣ሐራም እና ናኮር...ሐራም 3 ልጆችን ወለደ..ዮስካ ፣ ሚልካ እና ሎጥን...አብራም እና ናኮር ደግሞ ሚስቶች ነበሯቸው....ሁሉም ይኖሩ የነበረው ደግሞ በ ዑር ነበር ...ዑር በጣም የሰለጠነች ሀገር ነች ብዙ ስልጣኔ የጀመረባት ምድር....ከነዓን ደግሞ በተቃራኒው ከ ዑር የተሻለ ስልጣኔ አልነበራትም...እና የሚገርመው ታራም ከዚች ምድር ነው ሎጥ፣ አብራምንን እና ሚስቱን ወደ ከነዓን ለመሄድ ወደ ካራን ይዟቸው የሄደው...ቃሉን ስናነብ "ከእርሱም" ጋር ነው የሚለው...እና ቅድሚያ ራሱ ታራን ወደ ከነዓን የመሄድ ሀሳብ ነበረው....በጣም የገረመኝ ነገር...ታራም የተዋቸው ቤተ-ዘመዶች ነበሩ በ ዑር ...ልጁን ናኮር እና የ ሙት ሴት ልጆቹን ማለትም የ ሐራምን ልጆችን አልያዛቸውም ነበር።...ሐራም እዛው "ዑር" ነበር የሞተው...ዘፍ 12 ላይ እግዚአብሔር አብራምን ለሚጠራበት አጠራር መንገዶች ምቹ እየሆኑ ይመስላል🤷...ብቻ ህይወት እነ ታራም ቤት እንዲህ እየቀጠለ ያልተጠበቀ ነገር ተፈጠረ😱...ታራም በካራን ሞተ 😭..አብራም መጀመሪያ ሰምቶ የወጣ የሚመስለው የአባቱን ድምፅ ነበር...ሎጥ፣ አብራም እና ሚስቱ ሶራ ብቻቸውን በካራን ቀሩ 😔😭....እግዚአብሄርም መጣ 😎...አብራምን ጠራው በፉጨት .."አባትህ እንሂድ ብሎህ በካራን ካደህ፤ ያም የእኔ ፉጨት ነበር ..እና አብራም እግዚአብሔር እባላለው✋....ወደ ከነዓን እንሂድ" አለው....መንገድ አስጀምሮ እንደማይተው በዘላለም አባትነቱ አያስረገጠለት...ከዚያም ተነሱ ሎጥም አብሮት ነበር ነገር ግን መንገዱ የአብራም እና የ እግዚአብሄር ብቻ ስለነበር በአንዱ ክፍል ከሎጥም ተለዮ☹️🥺😊....ግን እሺ ታራም ባይሞት አብራም ያ መንገድ የማን ይመስለው ነበር🙄? እና እግዚአብሔር ነገሮችን ሲያስተካክል የመጣበት መንገድ ልዮ ነበር😊...የሐራም መሞት፤ የታራም እነ ናኮርን መተው፤ የ ታራም በካራን መሞት...ብቻ ይገርማል እናም እንደተለመደው ነው እግዚአብሔር አሻግሮ በ አብራም በኩል ኢየሱስን እያየ እንዴት እርፎ ይቀመጣል.....አህዛብ ልጆቹ ሲባሉ እና መንግስቱ ሲሰፋ እያስተዋለ እግዚአብሔር ከፍጥነቱ እንዴት ይዘገያል.....🙏አብራምን የሚያስቀርበትን መንገድ ይፈልጋል እንጂ።....እኛን ሊያተርፍ🥰... ከሲኦል አተረፍከን🙏 ዘፍ 11፥10-32, ዘፍ 12 እና ዘፍ 13 ይነበብ🙏 ✍️ Shall (Eyaned)
Show all...
🔥 4
Listan: The Name and The Gift | Abenezer Dejene and Mekdim Debebe https://youtube.com/watch?v=p8GStixFgJo&si=HtrwAxZeLW1ExGBh
Show all...

በፊደል አይደለም በሀጢያት ለነተብን ለቆሸሽን ለእኛ በራሳችን ጥፍት ከአምላክ ለሆንን ጠበኛ የፍቅርን ምንነት በውል ላላወቅን በፊደል ሳይሆን ሆኖ አስተማረን ድምጸት በሌለው ቃል ፍቅሩን አበሰረን በተግባር ተረከው ቃላት ሳያዋቅር እንዲህ ነው እንዲያ ነው ሳይል ስለፍቅር እኔ ነኝ አለና ወርዶ ገለጠልን እስከሞት መሆኑን ሙቶ አሳወቀን መውደድ ማለት ብሎ ሞተና ተረከው በመስቀል ሂደቱ ሁሉን ለኛ አበራው ምን ያህል እንደሆን የፍቅርን ርቀት በውርደቱ አሳየን የመውደዱን ብርታት ግና እየቻለ ማለት በአንደበት አልወደደም.. የኢየሱስ ፍቅር በፊደል አይደለም ሰላም✍ @jihovajrehartteam @jihovajrehartteam
Show all...
👏 4👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
Found this from our community, enjoy! መዝ 23(6) - እንዴት ነው ምህረቱና ቸርነቱ የሚከተሉን? Chad Bird የተባለ ፀሐፊ "ይከተሉኛል" የሚለውን ቃል የትኛውንም አይነት ተራ መከተልን ከማመልከት ያለፈ ትርጉም እንዳለው ያብራራል። "ይከተሉኛል" ተብሎ የተተረጎመው ቃል በእብራይስጥ "Radaph" ነው። ይኼም አንድን እጅግ ተፈላጊ ሰው እንዳይጠፋ ከኋላ ኋላው ማሳደድን ያመለክታል። እዚህ ጋር የሲ. አይ. ኤ ወይም ሞሳድ ወይም ኬጂቢ የስላለ ድርጅቶች አንድን እጅግ ተፈላጊ ሰው ጂፒኤስ፣ ድሮንና ዘመናዊ መሳሪያዎች ተጠቅመው ደብዛው እንዳይጠፋ የገባበት እየገቡ በጥብቅ መከታተልን የሚመስል ጥልቅ ትርጉም አለው። ይኼም ምናልባትም "ጥብቅ ክትትል ማድረግ" ከሚለው የስላላው ዓለም ሀሳብ ጋር ተስማሚ ነው!! እናም Chad ይላል፦ "ቸርነቱና ምህረቱ እንደ ተጎታች የቤት ውሻ ከኋላ ኋላችን አይከተሉንም። ወደየገባንበት ሰርጥና ጉራንጉር ሁሉ በእሳት ሰረገላ እያሳደዱ ይከተሉናል። ወንጀለኞችን ለማደን እንደ ሰለጠነ ውሻ በለያችን ያለውን ሰማያዊ ጠረን እያሸተቱ ያሳድዱናል። ከእግራችን ዱካ አይርቁም፤ ኮቴያችንን አይለቁም። ቸርነቱና ምህረቱ ወደ ሰማይ ደጅና አባታችን እቅፍ እስክንገባ ከኋላ ኋላችን ያሳድዱናል።" አንዳንድ ቅጂዎች ደግሞ "በእግዚአብሔር ቤት ለዘላለም እኖራለሁ" በሚለው ሀሳብ "እኖራለሁ" የሚለውን "ወደ መኖር እመለሳለሁ" ["Shall return to dwell" ESV Study Bible footnote] ይላሉ። ይኼም በቸርነትና ምህረቱ ክትትል ከተቅበዘበዘበት ተነድቶ በመመለስ ወደ ዘላለም ዕረፍት መግባትን ያመለክታል። Credits: @Mercysiuu #Spiritual #Lessons #Devotion @Dagmawi_Babi
Show all...
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
"ዲያኮኒያ" ልዩ የአምልኮ እና የኪነጥበብ ምሽት በቴፒ ቁ.1 ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ሰኔ 21 አርብ ከቀኑ 9:00 ሰዐት ጀምሮ በያህዌ ይርኤ የኪነጥበብ ህብረት የተዘጋጀ @jihovajrehartteam @jihovajrehartteam
Show all...
👍 6
Photo unavailableShow in Telegram
ተጋበዙልኝ @jihovajrehartteam
Show all...
ደርሶን ማሰብ ዘመን መሸከም እንደሆነ አለማወቅን ለመኖር መመለስ እንዲቻል የተፈጥሮን ትዕዛዝ መጣስ መገደድ ነው። ባለማወቅ ውስጥ ያለ ደስታ ሲቆይ ይመንናል ቢባል መንገዱ ራሱ ምስክር ነው።ለምን እንዳይባል የሀሳብን መንደር ሰብስቦ......ያላጠረው ይመስል....እየተሽከረከረ ቀዳዳ ይደፍናል ...ለቀዳዳው መስፋት እና መለጠጥ ከአትክልተኛው በላይ ማን ተጠያቂ አለ? ራሱን ለማወቅ መትጋት........ ✍️ሻሎም መልካሙ @jihovajrehartteam
Show all...
👍 4
እመነኝ ግዴለም ዛሬን ማረኝ እንጂ ዳግም አላጠፋም አልፈቅድም ከቀድሞው ምኞት እንዲፋፋም ቃል ገባለው እንዲ ምህረት ልገዛ ቋንቋን እያዛመድኩ መሸሽቆጥቆጥ ላበዛ ታዘብከኝ አይደለ ሁሉ እንደማታቅ ስሸነጋግልህ ሚገርመው ብታውቅም አዝኖ ለለመነህ መፅደቁ ነውና በሱቤት በራሱ ታነሳሳዋለህ ዝቅ ብለህ እንደሱ ወዳጄ ሆስ @jihovajrehartteam
Show all...
👍 1
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.