የረሱል ﷺ መልእክት
Open in Telegram
በዚህ ቻናል በአሏህ ፍቃድ የረሱል ﷺ መልእክት ይተላለፍበታል በተቻለ መጠን የረሱል ﷺ መልእክት ተደራሽ እናደርጋለን ለአስተያየትወ ...................... @Abuhafss
Show more470
Subscribers
No data24 hours
+67 days
+7730 days
Posts Archive
470
ዒኢሻ (ረ.ዐ) ነብዬ ﷺእንዲህ ብለዋል "አሏህ አዛኝ ነው።እዝነትን ይወዳል ። በመጥፎ ባህሪያት የማይሰጠውን /ስኬት/ በእዝነት ባህሪያት ሳቢያ ይሰጣል።"/ሙስሊም /
@muhamedunresulullah
470
ዒኢሻ (ረ.ዐ) ነብዬ ﷺእንዲህ ብለዋል ስትል ዘግባለች።"አሏህ አዛኝ ነው።በሁሉም ጉዳዬች ላይ እዝነትን ይወዳል ።/ሁሉም የተስማሙበት /
@muhamedunresulullah
470
አነስ (ረ.ዐ) እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል :- "ከነብዬ ﷺ የበለጠ ለልጆች የሚያዝን ሰው አላየሁም "
በድጋሚ አነስ በዘገቡት ሐዲስ ነብዩ ﷺ በመንገድ ላይ ሲያልፉ ልጆችን ካዬ ፈገግ ይሉና ሰላም ይሏቸው ነበር።/ቡኻሪና ሙስሊም/
@muhamedunresulullah
470
ጃቢር እንዳወሩት ነብዮ ﷺ ሐሰን እና ሁሴንንጀርባቸው ላይ በማስቀመጥ በእጆቻቸው እና በጉልበታቸው መሬት ላይ ተንበርክከው በመጓዝ እንዲህ ይሉ ነበር:-"እናንተ ጥሩ ጋላቢዎች ናቹህ ፤ ግመላቹህ ጥሩ ግመል ናት።" ሙስሊም ዘግበውታል
@muhamedunresulullah
470
ኢብኑ አሳኪር እንደዘገቡት ነብዮ ﷺ እንዲህ ብለዋል :-"ህፃን ልጅ ያለው ሰው ልክ እንደ ህፃን መሆን አለበት።"/አልጃሚ አልሰጊር/
@muhamedunresulullah
470
ነብዬ ﷺ እንዲህ ብለዋል ''ከናንተ መካከል በላጩ ለቤተሰቡ ጥሩ የሆነ ነው እኔ ለቤተሰቦቼ ጥሩ ነኝ።''/አልጃሚ አልሰጊር/
@muhamedunresulullah
470
አቡሁረይራ በዘገቡት ሀዲስ (አል አቅረእ ኢብን ሀቢስ የሚባል ቤድዊን ነብይ (ﷺ) የልጅ ልጃቸውን ሲስሙ አያቸውና ''እኔ አስር ልጆች አሉኝ። አንዳቸውንም ስሜያቸው አላውቅም'' አላቸው ። ነብዬ (ﷺ) ''አሏህ ለሌሎች ለማያዝን ሰው አያዝንም '' አሉት። /ሙስሊም/
@muhamedunresulullah
470
ነብዩ صلى الله عليه وسلم<<ይህች አለም ለአማኝ ሰው እስር ቤት ለከሀዲያን ደግሞ ጀነት ናት።>>ብለዋል። (ሙስሊም ዘግበውታል)
@muhamedunresulullah
470
አሏህ ዝምድናን ስለመቀጠል ሲናገር<< እኔ ረህማን(አዛኙ ነኝ) ። ረሂምን (ማህጸንን) የፈጠርኩ እኔ ነኝ ። ከስሜም ረሒም ወጣ። እሷን የቀጠለውን እቀጥላለሁ እሷን የቆረጠውን እቆርጠዋለሁ።> ብሏል። (ኢማም እህመድ ዘግበውታል)
@muhamedunresulullah
470
በሀዲስል ቁድስ አሏህ (ሱ.ወ) ለጀነት እንዲህ ብሏል <<አንች እዝነቴ ነሽ ። ከባሮቼ መካከል የፈለኩትን ባንች አማካኝነት እዝነቴን እሰጠዋለሁ። ብለዋል። ቡኻሪ ዘግበውታል
@muhamedunresulullah
470
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦<<አንድም ሰው በአሏህ እዝነት ቢሆን እንጅ ጀነት አይገባም።>> አሉ።<< አንቱም ቢሆኑ የአሏህ መልእክተኛ ሆይ!>> አሏቸው። <<አወን እኔም ብሆን አሏህ በእዝነቱ ውስጥ ቢነክረኝ እንጅ።>> አሉ። አጥጦበራኒ ዘግበውታል
@muhamedunresulullah
470
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
<<ሀያሉ አሏህ አለ-የኔን ወዳጅ የሚተናኮል ጦርነት አውጄበታለሁ። ባሪያዬ ከኔ ጋር በአንድ ነገር ሊቃረብ የሚችለው ግዴታ ያደረኩበትን ነገር ሲፈጽም ነው። ባሪያዬ ወደኔ (ነዋፊል) ትርፍ በሆኑ ነገሮች በሚቃረብበት ወቅት በጣም እወደዋለሁ። ከወደድኩት ደግሞ የሚሰማበት መስሚያ፣ የሚያይበት አይን፣ የሚዳስስበት እጅ፣የሚሄድበት እግር እሆነዋለሁ ።ቢጠይቀኝ እሰጠዋለሁ ጠብቀኝ ካለም እጠብቀዋለሁ።>>(ቡኻሪ ዘግበውታል )
@muhamedunresulullah
470
ከተዘነጉ ሱናዎች ውስጥ በህይወት ለሌሉ ወላጆቻችን ዱዓ ማድረግ!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
“ሰውዬው በጀነት ውስጥ ደረጃው ከፍ ብሎ ያያል። ይህ ለኔ ነው? ሲል ይጠይቃል። ‘ልጅህ ላንተ በሚጠይቅልህ ምህረት (ዱዓ) ነው’ ይባላል።”
📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ: 1598
ጆይን፦ @muhamedunresulullah
470
ሸሪዓዊ ህክምና!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል
“ሦስት ነገሮች ፈውስ ሊያስገኙ ይችላሉ። በዋግምት መወጋት፣ ማር መጠጣትና በእሳት መተኮስ። ተከታዮቼን በእሳት እንዳይተኮሱ እከለክላለሁ።”
📚 ቡኻሪ ዘግበውታል: 5681
ጆይን፦ @muhamedunresulullah
470
«እናንተ ሰዎች ሆይ! ሰላምታን አብዙ፣ የተራበን አብሉ፣ ዝምድናን ቀጥሉ፣ ሰዎች
በሚተኙበት የሌሊት ሰዓት ተነስታችሁ ስገዱ፣ በሠላም ጀነት ትገባላችሁ»።
ረሱል (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
📒ቲርሚዚይ ዘግበውታል
@muhamedunresulullah
470
የሙሐረም ወር ፆም!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
“ከረመዳን በመቀጠል በላጩ ፆም የአላህ ወር የሆነው የሙሐረም ወር ፆም ነው።”
📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1123
ማስታወሻ፦ የሙሀረም ወር ፆም በኢትዮጵያ አቆጣጠር አርብ ሐምሌ 21 ላይ ይሆናል። ከበፊቱ ወይም ከበስተኋላው ያለውን አንድ ቀን ጨምሮ መፆም መዘንጋት የለበትም።
@muhamedunresulullah
