en
Feedback
የረሱል ﷺ መልእክት

የረሱል ﷺ መልእክት

Open in Telegram

በዚህ ቻናል በአሏህ ፍቃድ የረሱል ﷺ መልእክት ይተላለፍበታል በተቻለ መጠን የረሱል ﷺ መልእክት ተደራሽ እናደርጋለን ለአስተያየትወ ...................... @Abuhafss

Show more
470
Subscribers
No data24 hours
+67 days
+7730 days
Posts Archive
ዒኢሻ (ረ.ዐ) ነብዬ ﷺእንዲህ ብለዋል "አሏህ አዛኝ ነው።እዝነትን ይወዳል ። በመጥፎ ባህሪያት የማይሰጠውን /ስኬት/ በእዝነት ባህሪያት ሳቢያ ይሰጣል።"/ሙስሊም / @muhamedunresulullah

ዒኢሻ (ረ.ዐ) ነብዬ ﷺእንዲህ ብለዋል ስትል ዘግባለች።"አሏህ አዛኝ ነው።በሁሉም ጉዳዬች ላይ እዝነትን ይወዳል ።/ሁሉም የተስማሙበት / @muhamedunresulullah

ነብዬ ﷺ እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል:- "ለሌሎች የማያዝን ሰው አሏህ አያዝንለትም"/ሙስሊም / @muhamedunresulullah

ነብዬ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- '' ለታናናሾቻችን የማያዝን ታላላቆቻችንን የማያከብር ከኛ አይደለም'' /ቲርሚዚ/ @muhamedunresulullah

አነስ (ረ.ዐ) እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል :- "ከነብዬ ﷺ የበለጠ ለልጆች የሚያዝን ሰው አላየሁም " በድጋሚ አነስ በዘገቡት ሐዲስ ነብዩ ﷺ በመንገድ ላይ ሲያልፉ ልጆችን ካዬ ፈገግ ይሉና ሰላም ይሏቸው ነበር።/ቡኻሪና ሙስሊም/ @muhamedunresulullah

ጃቢር እንዳወሩት ነብዮ ﷺ ሐሰን እና ሁሴንንጀርባቸው ላይ በማስቀመጥ በእጆቻቸው እና በጉልበታቸው መሬት ላይ ተንበርክከው በመጓዝ እንዲህ ይሉ ነበር:-"እናንተ ጥሩ ጋላቢዎች ናቹህ ፤ ግመላቹህ ጥሩ ግመል ናት።" ሙስሊም ዘግበውታል @muhamedunresulullah

ኢብኑ አሳኪር እንደዘገቡት ነብዮ ﷺ እንዲህ ብለዋል :-"ህፃን ልጅ ያለው ሰው ልክ እንደ ህፃን መሆን አለበት።"/አልጃሚ አልሰጊር/ @muhamedunresulullah

ነብዬ ﷺ እንዲህ ብለዋል ''ከናንተ መካከል በላጩ ለቤተሰቡ ጥሩ የሆነ ነው እኔ ለቤተሰቦቼ ጥሩ ነኝ።''/አልጃሚ አልሰጊር/ @muhamedunresulullah

አቡሁረይራ  በዘገቡት ሀዲስ (አል አቅረእ ኢብን ሀቢስ የሚባል ቤድዊን ነብይ (ﷺ) የልጅ ልጃቸውን ሲስሙ አያቸውና ''እኔ አስር ልጆች አሉኝ። አንዳቸውንም ስሜያቸው አላውቅም'' አላቸው ። ነብዬ (ﷺ) ''አሏህ ለሌሎች ለማያዝን ሰው አያዝንም '' አሉት። /ሙስሊም/ @muhamedunresulullah

ነብዩ صلى الله عليه وسلم<<ይህች አለም ለአማኝ ሰው እስር ቤት ለከሀዲያን ደግሞ ጀነት ናት።>>ብለዋል። (ሙስሊም ዘግበውታል) @muhamedunresulullah

አሏህ ዝምድናን ስለመቀጠል ሲናገር<< እኔ ረህማን(አዛኙ ነኝ) ። ረሂምን (ማህጸንን) የፈጠርኩ እኔ ነኝ ። ከስሜም ረሒም ወጣ። እሷን የቀጠለውን እቀጥላለሁ እሷን የቆረጠውን እቆርጠዋለሁ።> ብሏል። (ኢማም እህመድ ዘግበውታል) @muhamedunresulullah

በሀዲስል ቁድስ አሏህ (ሱ.ወ) ለጀነት እንዲህ ብሏል <<አንች እዝነቴ ነሽ ። ከባሮቼ መካከል የፈለኩትን ባንች አማካኝነት እዝነቴን እሰጠዋለሁ። ብለዋል። ቡኻሪ ዘግበውታል @muhamedunresulullah

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦<<አንድም ሰው በአሏህ እዝነት ቢሆን እንጅ ጀነት አይገባም።>> አሉ።<< አንቱም ቢሆኑ የአሏህ መልእክተኛ ሆይ!>> አሏቸው። <<አወን እኔም ብሆን አሏህ በእዝነቱ ውስጥ ቢነክረኝ እንጅ።>> አሉ። አጥጦበራኒ ዘግበውታል @muhamedunresulullah

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ <<ሀያሉ አሏህ አለ-የኔን ወዳጅ የሚተናኮል ጦርነት አውጄበታለሁ። ባሪያዬ ከኔ ጋር በአንድ ነገር ሊቃረብ የሚችለው ግዴታ ያደረኩበትን ነገር ሲፈጽም ነው። ባሪያዬ ወደኔ (ነዋፊል) ትርፍ በሆኑ ነገሮች በሚቃረብበት ወቅት በጣም እወደዋለሁ። ከወደድኩት ደግሞ የሚሰማበት መስሚያ፣ የሚያይበት አይን፣ የሚዳስስበት እጅ፣የሚሄድበት እግር እሆነዋለሁ ።ቢጠይቀኝ እሰጠዋለሁ ጠብቀኝ ካለም እጠብቀዋለሁ።>>(ቡኻሪ ዘግበውታል ) @muhamedunresulullah

ከተዘነጉ ሱናዎች ውስጥ በህይወት ለሌሉ ወላጆቻችን ዱዓ ማድረግ! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ “ሰውዬው በጀነት ውስጥ ደረጃው ከፍ ብሎ ያያል። ይህ ለኔ ነው? ሲል ይጠይቃል። ‘ልጅህ ላንተ በሚጠይቅልህ ምህረት (ዱዓ) ነው’ ይባላል።” 📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ: 1598 ጆይን፦ @muhamedunresulullah

የረሱል ﷺ ልጆች ስንት ናቸው?
Anonymous voting

ሸሪዓዊ ህክምና! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል “ሦስት ነገሮች ፈውስ ሊያስገኙ ይችላሉ። በዋግምት መወጋት፣ ማር መጠጣትና በእሳት መተኮስ። ተከታዮቼን በእሳት እንዳይተኮሱ እከለክላለሁ።” 📚 ቡኻሪ ዘግበውታል: 5681 ጆይን፦ @muhamedunresulullah

«እናንተ ሰዎች ሆይ! ሰላምታን አብዙ፣ የተራበን አብሉ፣ ዝምድናን ቀጥሉ፣ ሰዎች በሚተኙበት የሌሊት ሰዓት ተነስታችሁ ስገዱ፣ በሠላም ጀነት ትገባላችሁ»። ረሱል (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) 📒ቲርሚዚይ ዘግበውታል @muhamedunresulullah

ዛሬ ጁምዓ ነው ሶለዋት አብዙ

የሙሐረም ወር ፆም! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ “ከረመዳን በመቀጠል በላጩ ፆም የአላህ ወር የሆነው የሙሐረም ወር ፆም ነው።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1123 ማስታወሻ፦ የሙሀረም ወር ፆም በኢትዮጵያ አቆጣጠር አርብ ሐምሌ 21 ላይ ይሆናል። ከበፊቱ ወይም ከበስተኋላው ያለውን አንድ ቀን ጨምሮ መፆም መዘንጋት የለበትም። @muhamedunresulullah