ዳኒ ህትመት እና ማስታወቂያ ሥራ
Closed channel
ዳኒ ህትመት ማስታወቃያ ሥራ This Is Your Happy PIace Let Us Be Beautiful ::: ::: 0907748876 0986677077 @GEORGG23
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
1 304
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 304
አድ ላደረጋችሁ ፋጣሪ ያክብርልን
ይሄንን ግሩፕ አጋሩት ዛሬ ላይ ዝም ካልናቸው ነገ ደግሞ ተስፉፍተው ወንድ ልጅክ ወንድ እየጎተተመቶ ፍቅረኝዬ ሲልክ ሴቷ ልጅክ ሴት እየጎተተች መታ ፍቅረኝዬ ስትልክ እንደማየት ሞት የለም።🌈🌈🌈🌈🌈🌈👊👊👊
1 304
#ስም የሌለው ኃጢአት #
*እግዜር ሰውና እንስሳን ጾታ ለገሳቸው ግብረ ሰዶምነት ግን ጾታ የሌለውን ተፈጥሮ ስም የሌለውን ኃጢአት ይዞ የተገኘ ነው፡፡ ይህ ግብር ለምንም የማይመች ነው ፡፡ በትንሣኤ ጊዜ ወንዶች የ30 ዓመት ሴቶች የ15 ዓመት ሆነን ስንነሳ ግብረ ሰዶማዊ የሆነ / የሆነች በየትኛም ጾም ዕድሜ ሊነሱ ነው ??? ይህ ስም የሌለው ኃጢአት ነው ፡፡ እንኳን ለምድሩ ለሰማዩም የሚቸግር፡፡
የሚደንቀው ሁሉ ጾታውን ሲጠብቅ ከሰው ወገን ግን ስም የሌለው ኃጢአትን ይፈጽማሉ፡፡ይህም ግብረ ሰዶማዊነት ነው ፡፡ ግብረ ሰዶማዊነት ማለት.....
1.ባሕርይን መልቀቅ ነው
ግብረ ሰዶምነት ኃጢአት ብቻ አይደለም ባሕርይንም መልቀቅ ተፈጥሮን ማዛባት ነው፡፡
*በቤ/ክ ትምህርት ወንድ ዘር አቀባይነቱ ባህርያዊ ነው ሴት ዘር ተቀባይነቷ ባህርያዊ ነው፡፡ ነገር ግን የሰዶም ሰዎች ወንዶቹ ዘር አቀባይነትን ትተው ዘር ልቀበል አሉ ባህርያቸውንም አጡ ሴቷም የዘር ተቀባይነት ባህርይዋን ትታ ዘር ላቀብል አለች ባህርየ አንስትነቷን በባህርየ ተባዕት ለወጠች ይህን አይቶ ቅ/ጳውሎስ ለባህርያቸው የሚገባውን ትተው ለባህርያቸው የማይገባውን አደረጉ" ሮሜ1:27 አለ፡፡ባሕርያዊ ነው ስንልም እግዜር ሰው ከመባላችንንና ከአካላችን ያለመቀዳደም ፈጥሮና " " እግዚአብሔርም አለ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር"
(ኦሪት ዘፍጥረት 1:26) ሰውን እንፍጠር ከማለቱ ና ከአካሉ መገኘት ሳይቀዳደም ነው፡፡ ሰው መባል የሚገኘው በጽንሰት ጊዜ ነው ፡ ከዚያም አልፍ እግዜር ወንድ ሴት መባልን የሚሰጠው በጽንሰት ጊዜ ነው፡እንጂ ከቆይታ በኀላ የሚመጣ አይደለም፡፡ኢዮብ "ወንድ ልጅ፡ተጸነሰ የተባለባት ሌሊት የተረገመች ትሁን" ኢዮብ 3:3 ያቺ ሌሊት ኢዮብ የተጸነሰባት ሲሆን ወንድ ጾታነቱን ያኔ እንደተሰጠ አስረዳ፡፡ግብረ ሰዶማዊነት ግን በተፈጥሮ የተሰጠን ባሕርያዊ ግብር ለወጡ ስም የሌለው ተፈጥሮን ገንዘብ አደረጉ
2.ከእንስሳም ማነስ ነው
# ቅዱስ ጳውሎስ "ሥጋ ሁሉ አንድ አይደለም የሰው ሥጋ ግን አንድ ነው የእንስሳ ሥጋ ሌላ ነው የወፎችም ሥጋ ሌላ ነው የአሳም ሥጋ ሌላ ነው " በማለት ሲናገር ይሁዳ በመልእክቱ "ሌላን ሥጋ የተከተሉ ሰዶምና ገሞራ " ይላቸዋል ይሁ1:7 (ሌላ ሥጋ ) ብሎ ከሰው አልፈው ከእንስሳ ሥጋነት ተፈጥሮነት እንዳነሱ ያስረዳል፡፡ስም ቢያጣለት "ሌላ ሥጋ" አላቸው፡፡ከእንስሳት ወገን በተመሳሳይ ጾታ የሚዛመዱ የሉም ፡ ይሄኔ ነው እንስሳ ከሰው ተሽሎ፡የሚታየው፡፡
3.ብዙ ተባዙ ምድርን ሙሏት"ዘፍ የሚለውን ሕግ ይጻረራል፡፡ እንኳንስ ባሕርይን ቀይሮ ጾታን ማምታታት ቀርቶ በተቃራኒ ጾታ እንኳን ዘር እንዳይያዝና የሚያዝበትን ማጨናገፍ በደል ነው፡፡ ለምሳሌ በኦሪቱ
(ኦሪት ዘዳ 25:11)"ሁለት ሰዎች እርስ በርሳቸው ቢጣሉ፥ የአንደኛውም ሚስት ባልዋን ከሚመታው ሰው እጅ ታድነው ዘንድ ብትቀርብ፥ እጅዋንም ዘርግታ ብልቱን ብትይዝ እጅዋን ቍረጥ፥ ዓይንህም አትራራላት"#ለምን? ቢባል ብዙ ተባዙ የሚለውን ሕግ ስለተደፋፈረች ነው፡፡ ግብረ ሰዶማዊነት ደግሞ ከዚህ የባሰ ስም የሌለው ኃጢአት ነው፡፡
# በፍትሐ ነገስት አንድምታ ትርጓሜም "በእንተ ተፍኅሮት" ላይ ሊቃውንቱ ሲያትቱ ባልና ሚስት ሚስት በእርግዝናዋ ወቅት ሩካቡ አያርጉ ፡ የተጸነሰችው ሴት ብትሆን ከልጅቷ እንደመድረስ ነው የተጸነሰው ወንድ ቢሆን ግበረ ሰዶምነት ነው " በማለት አስቀምጠውታል፡፡ከዚህ ባለፈ መከላከያ መዳኒቶች ኮንዶም መጠቀም ፡ ሴት በወር አበባዋ ጊዜ ሩካቤ ማድረግ፡ ውርጃ ና የመሳሰሉት የመባዛትን ሕግ ስለሚጻረሩ ቤ/ክ አትፈቅድም:: *** +++:
ከእነዚህ የባሰውና የከፋው ግብረ ሰዶምነት የመባዛትን ሕግ የሚጻረር ስም የሌለው ኃጢአት ነው፡፡ * +++:
4.ክፉ ደዌ ሕማም ነው
#ቅ/ጳውሎስ "በፍትወት ተቃጠሉ " እንዳለው ይህ ግብር የማይበርድና የሚወራረሱት ከመርዝ የከፋ ደዌ ነው፡፡በመጽሐፈ ጥበብ 9;24 "ወይገብሩ ኅቡዕ ምሥጢር " የሚለውን ሊቁ ሲፈታው ግብረ ሰዶምንም ይሠራሉ ፡ከሕጋቸው ወጥተው በሌላ ሥራ እየተቅበዘበዙ ያስባሉ፡፡ ቁ.25 ላይ "ወኢሰብሳቦሙ ዓቀቡ እንከ -ሕገ ሰብሳባቸውን ፈጽመው አልጠበቁም ፡ "ዳዕሙ ካልዕ ይቀትሎ ለካልዑ - ባልንጀራውን ይገድላል(በነፍስ):: አንድም በሴት አካል የሚዘራው በወንድ አካል ሲዘራ በሥጋው ቅሉ ደዌ ሆኖ ይገድለዋልና ይቀትሎ አለ፡፡ "ወእመ አኮ ይየውሆ ወያስተሴፍዎ በዘያደውዮ- ይህም ባይሆን በሽተኛ በሚያደርገው ገንዘብ ይህን እሰጥሀለሁ ብሎ ይለዋል፡፡ አንድም በሴት አካል የሚዘዘራው በወንድ አካል ሲዘራ በሥጋ ቅሉ በሽተኛ ያደርገዋልና "ያደውዮ" አለ በማለት አትተዋል፡፡
* +++:
### እናም ይህ የከፋ ኃጢአት ነው ይህ ሲባል ግን በዚህ ሕይወት፡ያሉ ሰዎችን የምንጠቅማቸው በመግደል በመደብደብ ወይስ የሚወጡበትን መንገድ በማዘጋጀት ??? ይህ በጣም አቅምና ሕብረትን፡የሚፈልግ ነው፡፡እንደኔ
1.ማገገሚያ ተቋም ቢዘጋጅላቸው
2.ሐኪሞቻችን በዚህ በሽታ ላይ የተሻለ የማከም ስልጠናዎች ቢሰጣቸው
3.ቅድስት ቤ/ክ ከዚህ ሕይወት፡የሚመጡ ሰዎችን የምትሰጠው ትምህርት ማዘጋጀትና ካህናት መምህራኖቿን ማሰልጠን
4.እንደ ሕግ መንግስት ኢትዮጵያ እንደማትቀበለው ማስቀመጥ
5.ይህን የሚያስፋፉ ት/ቤቶች ; ጭፈራና መዝናኛ ቤቶች የመሳሰሉት ላይ የሕግ ቅጣት መጣል (እስከ ማዘጋት)
# በአጠቃላይ ግብረ ሰዶምነት ስም የሌለው ኃጢአት ነው ከዚህ ሕይወት መውጣት ለሚፈልጉ ደግሞ ድጋፍ አድርጎ ነጻ ማውጣት የሁላችንም ግዴታ ነው፡፡ ከዚህ አልፍ ለማስፋፋትና እንደ ሕይወት አድርጎ ለሚቀጥለው በሕግ ቅጣት ሊኖረው ይገባል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
አሜን
https://t.me/Gbre_Sedom
1 304
ከፈጣሪ ህግ አንወጣም ለዘለዓለም❗️
የነገው ትውልድህ የሚያሳስብህ ከሆነ ዛሬ ላይ መልካም ነገር ዝራ ኢትዮጵያ በታሪኳ ተቀብላ አታውቅም መቼም አትቀበልም
እኔ ግብረ ሰዶማውያንን እቃወማለሁ‼️❌
እኔ ግብረ ሰዶምን አወግዛለሁ‼️❌
እናንተስ❓❓❓
https://t.me/Gbre_Sedom
1 304
Repost from ዳኒ ህትመት ማስታወቃያ ሥራ
ስልኬ አልሰራ ላላችሁ ውድ ደንበኞቼ ወደ ክፍለሃገር ስለወጣው ነው ነገ ሐሙስ እገባለሁኝ ሸገር ከአርብ ጀምሮ መደወል ትችላላችሁ በአካልም መምጣት ትችላላችሁ ፓያሣ ባለው ቢሯችን
ስትሞክሩት ከሰራላችሁ ደውሉ ሞክሩ ኔቶርክ ስላስቸገረኝ ነው
☎️ 09 86 67 70 77
☎️ 09 07 74 88 76
☎️ 09 41 74 71 70
oR @DANI_2 👈አግኙኝ
1 304
ሁላችንም ይሄን ሊንክ ለ5 ሰው ሼር ብናደርግ ሀገራዊ ግዴታችን ተወተናል ማለት ነው!! 👇 Add አድ ያድርጉ
እናቃወማለን፣ እናጠፋቸዋለን!! ✊
https://t.me/Gbre_Sedom
1 304
የዋይታና የመራራ ልቅሶ ድምፅ በኢትዮጵያ [በትግራይ] ተሰማ...!!
👉 ባያድለን ነው እንጂ ይሄ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያውያን ሁሉ ኀዘን፤ የምድሪቱ ልቅሶ መሆን ነበረበት!!
በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)
"ኢትዮጵያ ሆይ፥ ምን እመሰክርልሻለሁ? በምንስ እመስልሻለሁ? አጽናናሽ ዘንድ በምን አስተካክልሻለሁ? ስብራትሽ እንደ ባሕር ታላቅ ነውና፤ የሚፈውስሽ ማን ነው. . . ?!"
እንደ መግቢያ፤
"የኢትዮጵያ ሀገሬ ታጠቂ በገመድ፤
የወንድ ልጅ እናት ታጠቂ በገመድ፤
ያም ልጅሽ ያም ልጅሽ፤
ያም ዘመድ ያም ዘመድ፤
ለማን ታድያለሽ ... ለማንስ ይፈረድ?!
(የባህል ሙዚቃ ንግሥቷ ማሪቱ ለገሠ/እንደው ዘራፌዋ)
የኢትዮጵያና የኢትዮጵያን የታሪክና የሥልጣኔ እምብርት፤ የክርስትና እና የኢስላም ሃይማኖቶች (የርዕሰ አድባራት አክሱም ጽዮን እና የአልነጃሺ) መሠረት/መነሻ ምድር ኢትዮጵያ/አክሱም/ትግራይ፤
ኢትዮጵያውያን ከሰሜን እስከ ደቡብ፤ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ጫፍ ተጠራርተው ብሔርና ጎሳ፤ ሃይማኖትና ቋንቋ ሳይለያቸው በአጥንታቸው ብዕርነት በደማቸው ቀለምነት የነጻነትን ክቡር መንፈስ ከፍ ባደረጉበት፤ ለአፍሪካና ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት ሰንደቅ በተውለበለበባት፤ የኢትዮጵያዊነት የቃልኪዳን ውሉ በተቋጠረባት በዐድዋ/በትግራይ ምድር፤
በወንድማማች ጦርነት በአንድ ጀምበር ለወሬ ነጋሪ አንዱ እንኳን ሳይተርፉላት አምስቱም ልጆቿ/ሁሉም ማለቃቸውን ሰምታ ራስዋን ስላጠፋች፤ ኀዘን አቅሏን ስላሳታት የትግራይ/የኢትዮጵያ ምስኪን እናት ምን ምላሽ፤ ምንስ የማጽናኛ ቃል አለን...?!
በአማራ፣ በአፋር፣ በቤሻንጉል ጉሙዝ፣ በወለጋ... በሁሉም ኢትዮጵያ ምድር በጦርነት ነዲድ እየተለበለቡ በገፍና በግፍ ስላለቁትና እያለቁ ስላሉት የኢትዮጵያ ልጆች ምን እያልን፤ ምን እያሰብን ይሆን...?!
በቤተ መቅደሱ ደጃፍ ስለታረዱት ካህናት፣ ደማቸውን ውሻ ስለላሰው፣ በድናቸውን ለአውሬና ለአሞራ ሲሳይ ስለዳረግናቸው ወገኖቻችን፤ ስለተደፈሩ መነኮሳት፤ የሴትነታቸው ክብር በአደባባይ ስለተዋረደባቸው፣ ስለተጎሳቆለባቸው ምስኪን እናቶቻችና እህቶቻችን ምን ቃል፤ ምንስ አንደበት ይኖረን ይሆን...?!
የጦርነት ነጋሪት ስንጎስም፣ በወንድማማች ሕዝብ፤ በኢትዮጵያውያን መካከል የጥላቻን፤ የመለያየትን ዘር ስንዘራ የነበርን ነፍሰ-ገዳዮች/ቃኤላውያን ሆይ አሁን ገና የደም ግብራችን አልረካ ይሆን...?!
የዋይታና የመራራ ልቅሶ ድምፅ በኢትዮጵያ [በትግራይ] ተሰማ...!!
እነዚህ ኃይለ-ቃላት ከመጽሐፍ ቅዱስ የተወሰዱ ጥቅሶች ሲሆኑ፤ በተለያዩ ጊዜያት የእግዚአብሔር ነቢያት ስለ እስራኤል፣ ስለ ኢየሩሳሌም/ስለጽዮን ውርደት፣ መከራና ሰቆቃ የተናገሯቸው ናቸው። ጥቅሶቹ የእናት ምድራችንን የኢትዮጵያን ኀዘን፤ የኢትዮጵያውያን እናቶችን ሰቆቃ/ታላቅ ስብራት የሚገልጽ መስሎ ስለተሰማኝ ነው- ኢትዮጵያ የሚለውን ስም በመተካት አካፍላችሁ ዘንድ የወደድኹት።
"እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። የዋይታና የመራራ ልቅሶ ድምፅ በራማ [በትግራይ] ተሰማ፤ ራሔል [ኢትዮጵያ] ስለ ልጆችዋ አለቀሰች፤ የሉምና ስለ ልጆችዋ መጽናናትን ፈጽሞ እንቢ አለች።"
(ትንቢተ ኤርምያስ ፴፩፤፲፭)።
"ድምፅ በኢትዮጵያ ተሰማ፥ ልቅሶና ብዙ ዋይታ፤ የትግራይ እናት ስለ ልጆችዋ አለቀሰች፥ መጽናናትንም አልወደደችም።"
ኢትዮጵያ አለቀሰች፥ ደጆችዋም ባዶ ሆኑ በምድርም ላይ ጨለሙ፤ የእናቶች ጩኸት ከፍ ከፍ ብሎአልና፤
የኢትዮጵያ ሽማግሌዎች ዝም ብለው በመሬት ላይ ተቀምጠዋል፤ ትቢያን በራሳቸው ላይ ነሰነሱ፥ ማቅም ታጠቁ፤ ደናግላን ራሳቸውን ወደ ምድር አዘነበሉ።
ወደ ዓመት በዓልም የሚመጣ የለምና የጽዮን መንገዶች [የአክሱም መንገዶች] አለቀሱ፤ በሮችዋ ሁሉ ፈርሰዋል ካህናቶችዋም እየጮኹ ያለቅሳሉ፤ ደናግሎችዋም ተጨነቁ፤ እርስዋም በታላቅ ምሬት ውስጥ አለች።
በኢትዮጵያ ሴቶችን፥ በከተሞቿም ደናግልን አጐሰቈሉ፤ አለቆች በእጃቸው ተሰቀሉ፤ በመቅደሱ የካህናት፣ በአደባባይም የሽማግሌዎች ፊት አልታፈረም።
ጕልማሶች ወፍጮን ተሸከሙ፥ ልጆችም ከእንጨት በታች ተሰናከሉ። ሽማግሌዎች ከአደባባይ፥ ጕልማሶች ከበገናቸው ተሻሩ።
አቤቱ፥ ተጨንቅናል፥ አንጀታችም ታውኮብናልና፤ ተመልከት፤ ልባችን በውስጣችን ተገላበጠብን፤ በሜዳ ሰይፍ ልጆቻችንን አጠፋ በቤታችንም ሞት አለ።
ድንጋጤና ቍጣ፥ ጥፋትና ቅጥቃጤ ሆነብን። ስለ ወገናችን ሴት ልጆች ቅጥቃጤ ዓይናችን የውኃ ፈሳሽ አፈሰሰች። እግዚአብሔር ከሰማይ እስኪጐበኝና እስኪመለከት ድረስ ዓይናችን ሳያቋርጥ ዝም ሳይሉ እንባን ያፈሳሉ።
የልባችን ደስታ ቀርቶአል፤ ዘፈናችን ወደ ልቅሶ ተለውጦአል፤ ዓይናችን በእንባ ደከመች፥ አንጀታችንም ታወከ፤ ስለ ኢትዮጵያ ወገኖቼ ቅጥቃጤ ጉበታችን በምድር ላይ ተዘረገፈ።
ኢትዮጵያ ሆይ፥ ምን እመሰክርልሻለሁ? በምንስ እመስልሻለሁ? አጽናናሽ ዘንድ በምን አስተካክልሻለሁ? ስብራትሽ እንደ ባሕር ታላቅ ነውና፤ የሚፈውስሽ ማን ነው?
ነቢያቶችሽ ከንቱና ሐሰተኛ ራእይ አይተውልሻል፤ ምርኮሽንም ይመልሱ ዘንድ በደልሽን አልገለጡም፤ ከንቱና የማይረባ ነገርንም አይተውልሻል።
እንደ መውጫ፤
አንጋፋው ፖለቲከኛ፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁሩ፣ አዛውንቱ ዶክተር ኃይሉ አርዓያ- በዛን ጊዜው የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ/የአሁኑ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ በነበሩበት በ1950 ዎቹ ስለኢትዮጵያ የቋጠሩት ስንኝ ለአሁኗ ኢትዮጵያም የሚስማማት ይመስለኛል። እንሆ ከዶ/ር ኃይሉ አርዓያ እንጉርጉሮ/ስንኞች፤
"... ይኸው ትታያለች ለሕዝብ በይፋ፣
ጥቁር ተከናንባ ጥቁር ተጎናጽፋ፡፡
እኔስ መስሎኝ ነበር ዘመድ የሞተባት፣
የእናት ሞት የአባት ሞት፣
የልጅ ሞት ያጠቃት፣
ለካ እሷስ ኖራለች ዘመን የሞተባት...!!
(ሰቆቃው ኤርምያስ ምዕ. ፭)
----------
፲፯፤ አቤቱ፥ የሆነብንን አስብ፤ ተመልከት ስድባችንንም እይ። ርስታችን ለእንግዶች፥ ቤቶቻችን ለሌሎች ሆኑ።
፲፰፤ ድሀ አደጎችና አባት የሌለን ሆነናል፤ እናቶቻችን እንደ መበለቶች ሆነዋል።
፲፱፤ አቤቱ፥ አንተ ለዘላለም ትኖራለህ፤ ዙፋንህ ከትውልድ እስከ ትውልድ ነው።
፳፤ ስለ ምን ለዘላለም ትረሳናለህ? ስለ ምንስ ለረጅም ዘመን ትተወናለህ?
፳፩፤ አቤቱ፥ ወደ አንተ መልሰን እኛም እንመለሳለን፤ ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድስ።
፳፪፤ ነገር ግን ፈጽመህ ጥለኸናል፤ እጅግ ተቈጥተኸናል።
ሰላም ለኢትዮጵያ፤ ሰላም ለምድራችን🕊🕊
