ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
Open in Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
Show more3 309
Subscribers
-224 hours
-97 days
-3630 days
Posts Archive
✨✨✨#ቃና_ዘገሊላ✨✨✨
"የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ሁለትን የመጀመሪያ አንቀጽ መነሻ ያደረገችውና በሰርግ ቤቱ ስም ቃና ዘገሊላ በማለት የተሰየመ ይህ መጽሐፍ፥ እንደ ሰርግ ቤቱ ስድስት ጋኖች በስድስት ምዕራፎች የተከፈለ ነው። ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዝ እንደነበሩት እንደ ቃና ጋኖችም እነዚህ ምዕራፎች እያንዳንዳቸው ሦስት ወይም አራት የንዑስ ርዕስ እንስራን የያዙ ናቸው፡፡ ...
"ይህ መጽሐፍ በስድስቱ ጋኖች /ምዕራፎች/ ውስጥ በቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት ትርጓሜ መነሻነት በሰርግ ቤቱ ውስጥ ጥቂት እንድንቆይ ለማድረግ ይተጋል፡፡ .….
#መልካም_በዓል!!
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
📚#ፍኖተ_መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
JOIN US👇
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@fenotebooks1623
#ጥምቀት ዋዜማ የዝግጅት ቀን ነው። ምእመናን በጾምና በጸሎት ይዘጋጃሉ። ጾም ማለት ከምግብ መቆጠብ ብቻ አይደለም፤ ከኃጢአት፣ ከቂም፣ ከተንኮልና ከጥላቻ መራቅ ነው። ጸሎት ደግሞ ቃል ብቻ አይደለም፤ ልብን ለእግዚአብሔር መክፈት ነው።
💦ነገ ደግሞ ተወዳጁ ጥምቀት በዓል ነው። ይህ የዛሬው መጠባበቅ ፍሬ የሚታይበት ቀን ነው። ሕዝብ በደስታ ይሞላል፤ መንፈሳዊ ብርሃን ይበራል። የዚህ ቀን መሠረታዊ ትርጉም የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ ወንዝ በቅዱስ ዮሐንስ መጥምቁ የተጠመቀበትን ታላቅ ምስጢር ማስታወስ ነው። በዚያ ቀን ሰማይ ተከፈተ፤ መንፈስ ቅዱስ እንደ ርግብ ወረደ፤ የአብ ድምፅ “ይህ የምወደው ልጄ ነው” ተሰማ። ይህ ክስተት ብቻ የታሪክ ክፍል አይደለም፤ ለሰው ሁሉ የመዳን መንገድ የተገለጠበት ጊዜ ነው።
#እንኳን_አደረሳችኹ!!
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@fenotebooks1623
ጥር ፯
#በዓለ_ቅድስት_ሥላሴ በኃጢአት የተገነባውን የሰናዖር ግንብ ያፈረሱበት የሥሉስ ቅዱስ አንድነት ሦስትነትየተመሠጠረበት፤በግልጽ የታየበት ጥር ሰባት ቀን የከበረ በዓል እንደመሆኑ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡
ሰላም ለአጸብዒክሙ፦
❝#አብ_ወልድ_መንፈስቅዱስ ሆይ፤ ከጽፍሮቻቸው ላልተለዩ መለኮታዊ ጣቶቻችሁ ሰላምታ ይገባል። #ሥሉስ_ቅዱስ ሆይ፤ መለኮታዊ ባሕርይ አደራሻችሁ ንብረቱ የማይጎድልበት ገንዘብ የማያልቅበት ነውና ፤ በደሉ ኃጢአቱ ከድህነት ላይ ከጣለው በኋላ የሰውን ልጅ (አዳምን) ባበለጸጋችሁት (በአጸናችሁት )ጊዜ የሰማይ መላእክት ከአሁን በፊት ያላዩትን ችሮታ፣ አዩ። ስለሆነም መላእክት የሰው አገልጋዮች ተባሉ።❞
💧እንኳን አደረሰን !🙏
የቅድስት ሥላሴ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን !!!
📚#ሲሎንዲስ📚
#ንጉሥ_ሰሎሞን በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ በታላቅ ጥበቡ፣ በልዩ ሁበቱ እና እግዚአብሔርን ለማምለክ በገነባው ድንቅ ቤተ መቅደስ ይታወቃል። ይህ መጽሐፍ የንጉሡን የሕይወት ውጣ ውረድ፣ የጻፋቸውን መጽሐፍት ምስጢር እና የቤተ መቅደሱን አሰራር ጥበብ በጥልቀት ይዳስሳል፡፡ መጽሐፉ እግዚአብሔር አምላክ ለሰው ልጆች የሰጠውን የጥበብ ምልአትን የሚያስረዳና ንጉሥ ሰሎሞን የጻፋቸውን አምስት የመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍትን ለማጥናት እንደ መግቢያ ሊያገለግል ይችላል፡፡
✍️[ሊቀ ሊቃውንት ዮሴፍ ደሳለኝ]
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
t.me/FinoteBooks1623
📚የዮሐንስ ወንጌል ማበብራሪያ📚
➾ስለዚህም የዮሐንስ ወንጌል ምንም እንኳ የዚህ መጽሐፍ አዘጋጅ መጋቤ ሐዲስ የንታ ስቡሕ እንዳሉት ለአኛ ቀርቶ ለቀደሙ ቅዱሳን ሊቃውንትም ሁልጊዜ ተርጉሙኝ፡ ገና አልተነካሁም የሚል ወንጌል ቢሆንም ለእኛ ዘመን ትውልድም በቀላሉ ልንረዳው በምንችለው በዚህ መንገድ መቅረቡ ታላቅ በረከትና ውድ ስጦታ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መሠረተ እምነትም ከዚህ ጥንታዊ፣ ሐዋርያዊና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትርጓሜና ከጌታና ከሐዋርያት አስተምህሮ አንድ ጋት እንኳ ፈቀቅ ያላለ እውነተኛ መሆኑን እንረዳበታለንና አንብበን እንጠቀምበት ዘንድ ቢታናሽነቴም ቢሆን እያስታወስኩ የኔታን እንዲደማመን ሌሎች ሊቃውንትንም እንዲከተሏቸው ከልብ እማጸናለሁ ።
✍️ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ
[በሥን ድርሳን ሁለተኛ ዲግሪ]
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
t.me/FinoteBooks1623ዠ
💧"ቃል ሥጋ ሆነ" ዮሐ.፩፥፲፬
፨ድንግል ፈጣሪዋን ወለደቸዉ።
እርሱም እናቱን ፈጠረ።
ከእርሷም እርሱ የፈጠረዉን ሥጋ ተዋኀደ። ሃ/አበዉ ዘቅ/ኤፍሬም ምዕ 47፣2 ገላ 4፣4
✨እንኳ ለተከበረው በዓል ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት አደረሳችሁ።
የተባረከ በዓል ያድርግልን ..!
💧አዕምሮን ሁሉ የእግዚአብሔር ሰላም በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምና ጸጋ ለእናንተ ይሁን..!
-ውድ ደንበኞቻችን እንደምታውቁት መጻሕፍት ቤታችን #ግዮን_መጻሕፍት በሚል ልዩ ስምና ሎጎ ስንንቀሳቀስ ዓመታትን ያሳለፍን የነበረ መኾኑ ይታወቃል። ይህ እየኾነ ባለንበት ወቅት በዚኽ ስም በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ያሉ መደብሮች #በአዲስ_አበባ እንዲኹም #በባህር_ዳር_ከተማ እንዳሉ በቅርብ ሰማን። ከእነርሱ በተቃራኒ ደግሞ በዚህ ስም በባዛርና በተለያዩ ቦታዎች ሰውን እያጭበረበሩ ያሉ ሰዎች እንዳሉ ሰማን። በዚህም ጉዳይ ከሚመለከታቸው ወንድሞች ጋር መከርን፥እኛም ለወንድም መተውን ከወንጌል በተማርነው መሠረት እንዲኹም እናንተ ደንበኞቻችንን ከመጭበርበር መታደግ ይገደናልና በመጭዎቹ የጌታችን ዐበይት በዓላት እንዲኹም ወቅቱ አስተርዕዮ [የመገለጥ] ነውና እኛም እናበስራችኹ ዘንድ አሰብን!
➥ተወዳጆች ስማችንን #ፍኖተ_መጻሕፍት ብለን ሰይመናል።
--
➥የተለያዩ ቻናልና ግሩፖች ያላችኹ መምህራንና ምዕመናንን በማስተዋወቅ[shareበማድረግ] አጋርነታችኹን ትገልጹልን ዘንድ እናሳስባለን....!
-በዚኹ አጋጣሚ ውድ ደንበኞቻችን ከእኛ ጋር ላላችኹ ያልተቋሰጠ ቤተሰባዊነት ከልብ አክብሮታችንን እንገልጻለን።
https://t.me/FinoteBooks1623
📚#ጉዞ_ወደ_እግዚአብሔር📚
#ጠንካራ እምነት ሊመጣ የሚችለው የእምነት ጀግኖች አባቶቻችን የሠሩትን አብነት በማድረግ ነው፡፡ እስከ ሞት ድረስ ለሃይማኖት የታመኑ ሲሆኑ፣ በፆም በፀሎት ተወስነው ሲኖሩ፣ የሚደርስባቸውን መከራ ሁሉ በትዕግስትና በደስታ ሲቀበሉ ስናነብ የምናገኘው እጅግ ብዙ ነው፡፡ ባላቸው ኃይል እና እውቀት ሁሉ ቤተክርስቲያንን ጠብቀዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ለሚመጣባቸውም ምንም አይነት መከራ ፅኑዎች ሆነው በግዞትና በእስር ቤት ፈጣሪያቸውን እያመሰገኑ ኖረዋል፡፡ ቤት አልባ ሆነው ማረፊያ እንዳጡ በስደት በየሀገሩ ተንከራተዋል
“ለረጅም ጊዜያት ፀንተህ በመታገስ ለፍፃሜ የማታደርሰው እቅድ ሁሉ ፍሬ ቢስ ነው፡፡” ማር ይስሐቅ
[ከመጽሐፉ የተወሰደ]
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
➯ላሊበላ ከተማ ዝግጅቷን አጠናቅቃ እንግዶቿን በመጠባባቅ ላይ ትገኛለች..
♱♱♱♱♱♱♱
#ላሊበላ ከተማ ዝግጅቷን አጠናቅቃ እንግዶቿን በመጠባባቅ ላይ ትገኛለች..
..የመምሪያው ኃላፊ ገነት ሙልጌታ እንደገለጹት፤ በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ታኅሣሥ 29 ቀን የሚከበረውን በዓል በድምቀት ለማሳለፍ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቅቀዋል።
➥እንግዶችን በከተማዋ አራቱም የመግቢያ በሮች ተቀብሎ የማስተናገድና የማረፊያ ቦታዎችን የማመቻቸት ሥራ እንደሚከናወን የገለጹት ኃላፊዋ፤ ሆቴሎች ዝግጅታቸውን አጠናቅቀው እንግዶችን መያዝ መጀመራቸውን ጠቁመዋል።
➥#በበዓሉ ወቅት እንግዶች የመብራት፣ የውኃና የመንገድ መጥፋት ችግር እንዳይገጥማቸው የሚያግዝ ኮሚቴ መቋቋሙን ወይዘሮ ገነት አስረድተዋል።
፨እንዲኹም ተከታታይ ዝግጅቱ እንግዶች በቆይታቸው ተደስተው ለቀጣይ #በዓላት ሌሎች ጎብኚዎችን ይዘው እንዲመጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑንም አክለው ገልጸዋል።
─━━━━━━⊱✿⊰━━━━━━─
➮ምንጭ ፦የሰሜን ወሎ ዞን ባሕል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ
💧አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
📚#ዜና_አበው_ቅጽ_፪📚
➥#በመጽሐፍ ቅዱስ በትእዛዝና በመመሪያ መልክ የተጻፈው የቅድስና ሕይወት በዜና አበው በኀልዮ፣ በነቢብ፣ በገቢር፣ በኑሮ ተገልጾ እናገኘዋለን። ይህ ለኦርቶዶክሳውያን ወደ ጽድቅ የሚመራ የሕይወት ፍኖተ ካርታ ነው። ወንድማችን መ/ር አብርሃም ፈቃዴ ደግሞ በቋንቋ የተደበቀውን በትርጓሜ ገላልጠውና በመጽሐፈ ገነት ውስጥ የሚገኙትን ፍሬያት ለመንፈሳዊ አመጋግብ እንዲመቹ በማድረግ አጣፍጠውና ቀምመው እንዳቀረቡልን ዛሬም ሁለተኛውን ክፍል አዘጋጅተው አቅርበውልናልና ዓይናችንን ከፍተን አእምሯችንን አስፍተን እንመገብ እላለሁ።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
📚#መጽሐፈ_ሐዊ📚
ስለ መጽሐፉ ሊቃውንት ይህን ብለዋል.....👇
➥#ይህ መጽሐፈ ሐዊ ለእኛ ከተላኩ መላእክት መካከል አንዱ ሲሆን ተሰውሮ ከሚኖርበት ቦታ ለሕዝቡ ልትገለጥ ይገባሃል ብለው ያመጡት ሊቀ ጠበብት መሠረት ናቸው። ዜማን ከዜማ መሣሪያ ጋር ማስማማት የማይሳናቸው የአቁቋሙ ሊቅ የትርጓሜው መምህር ሊቀ ጠበብት መሠረት የተሰወረ የፊቱን መልክ እንድናየው የቋንቋ መጋረጃውን አንስተው ኑ በብርሃኑ ተመላለሱ እያሉን ነው።
በቀኖና ቤተ ክርስቲያን በሥርዐተ ሃይማኖት ጸንቶ ለመኖር ለሚፈልግ ክርስቲያን ሁሉ እጅግ ጠቃሚ መጽሐፍ ነው። የምዕመናን፣ የመምህራን፣ የመነኮሳት ሕይወት በዚህ መጽሐፍ ተዳሷል። የጥንት አባቶቻችን ምን ብለው አስተማሩ? ብሎ የሚጠይቅ ሰው ካለ አንዱ የአባቶቻችንን ትምህርት ከያዙ መጻሕፍት አንዱ ይህ መጽሐፈ ሐዊ ስለሆነ መመልከት ይገባዋል።
ክቡር ሊቀጠበብት መሠረት ምሕረቱ በክፍል አንድ መጽሐፍዎ የጀመሩትን በጎሥራ በክፍል ሁለት ስላስቀጠሉልን እጅግ እያመሰገንን እኛም የመምህራኑን ትምህርት አንብበን የመምህራንን እግር ተከትለን የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመውረስ ያብቃን እላለሁ። አሳትማ ያቀረበችልን ኢትዮ ፋጎስን ግሪክ ድረስ ሳንወርድ ያገኘናት አርዮስፋጎሳችን {መካነ ጥበባችን} ነሽ ብለናታል።
መልካም ንባብ!!
✍️ሊቀሊቃውንት ስምዐኮነ መልአክ
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
➥#ሌላኛው ረዘም ላለ ጊዜ ከገበያጠፍቶ የነበረው ተወዳጁ📚#ብሉይ_ኪዳን_ለሕፃናት📚 በድጋሚ ለ5ኛ ታትሟል....
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
#ታኅሣሥ_ገብርዔል እንኳን አደረሳችሁ
=====
"አሕለፍከነ ማዕከለ እሳት ወማይ፣
ወአውፃእከነ ውስት ዕረፍት።
ትርጉም
=====
"በእሳትና በውኃ መካከል አለፍን (አሳለፍኸን)፣
ወደ ዕረፍትም አወጣኸን።"
(መዝ ፷፭÷፲፪ || መዝ 65(66)÷12)
#ታኅሣሥ_ገብርዔል እንኳን አደረሳችሁ
=====
"አሕለፍከነ ማዕከለ እሳት ወማይ፣
ወአውፃእከነ ውስት ዕረፍት።
ትርጉም
=====
"በእሳትና በውኃ መካከል አለፍን (አሳለፍኸን)፣
ወደ ዕረፍትም አወጣኸን።"
(መዝ ፷፭÷፲፪ || መዝ 65(66)÷12)
#ታኅሣሥ_ገብርዔል እንኳን አደረሳችሁ
=====
"አሕለፍከነ ማዕከለ እሳት ወማይ፣
ወአውፃእከነ ውስት ዕረፍት።
ትርጉም
=====
"በእሳትና በውኃ መካከል አለፍን (አሳለፍኸን)፣
ወደ ዕረፍትም አወጣኸን።"
(መዝ ፷፭÷፲፪ || መዝ 65(66)÷12)
💧#አስደሳች ዜና ለልጆቻችን
📚#ሐዲስ_ኪዳን_ለሕፃናት📚
➥#ከስመ ጥሩ ካህን ቀሲስ ታድሮስ ማላቲ ላቅ ያለ ጠቀሜታ ያላቸው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትረካዎች ባማረ ሁኔታ ተጠናቅረው በዚህ መጽሐፍ ቀርበዋል።
#ይህ_መጽሐፍ ከሕፃናት ጀምሮ እስከወላጆች እንዲሁም በወጣቶች ሃይማኖታዊ ትምህርት ላይ አደራና ሓላፊነት እስካለበት ማንኛውም ሰው ድረስ ሐዲስ ኪዳንን እና በውስጡ የተካተቱትን እጅግ ወሳኝ ታላላቅ ክስተቶች በአስደናቂ ሁኔታ የያዘ በሁሉም እድሜዎች ለሚገኙ ሁሉ የሚጠቅም ነው፡፡ይህ የከበረ መጽሐፍ አማርኛው ለሁሉም በሚገባ መልኩ የተዘጋጀና በቅዱስ መጽሐፍ ውስጥ በደስታ እንድንጓዝ የሚጋብዝ ሲሆን ለበርካታ ቀጣይ ትውልዶችም ትልቅ ዋጋ ያለው ሐብት ነው።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
📚#ፍኖተ_እግዚአብሔር📚
➥#በምሥጢረ_ሥላሴ ዙሪያ በኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ከተጻፉ መጻሕፍት ቁጥር #፩ ምርጫዬ ነው። #ፍኖተ_እግዚአብሔር። መጋቤ ሐዲስ ልዑለ ቃል አካሉ Leulekal Alemu ምንባባቱን ከመጻሕፍት፣ በተለይ ከሃይማኖተ አበው ያቆራኙበት መንገድና የሊቁን ታሪክ ሰፋ አድርገው ማቅረባቸው የሚያስመሰግን ተግባር ነው። በመታተሙ ደስ ብሎኛል። መጋቤ ሐዲስንም ያሳትሙልን ብዬ ደጅ የጠናሁ ይመስለኛል።
...መጽሐፉ ረዘም ላለ ጊዜ በሊቃውንቱ በቅብብል እየዳበረ መጥቶ በአለቃ ኅሩይ ፍጽምና እንዳገኘ አስባለሁ። ከምደነቅባቸውና ከአባቶቼ የማመሥጠር ጸጋ የተነሣ እግዚአብሔርን ከማመሰግንባቸው መጻሕፍት አንዱ ነው።
✍️በአማን ነጸረ
[ደብተራና የሕግ ባለሙያ]
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
