The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
Open in Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
Show more3 493
Subscribers
+324 hours
+97 days
+11030 days
Posts Archive
የኢ/ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ የልጆች በዓል ሳምንት
ነሐሴ 11-17/2018ዓ.ም
መሪ ጥቅስ: ''ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም።'' ምሳሌ 22:6
ርዕስ: ''ጠንካራ ቤተሰብ: ስኬታማ ትውልድ''
በሁሉም ማኀበራነ ምዕመናን
* *
Kabaja Torbaan Ayyaana Ijoollee WWWMakaana Yesuus Itoophiyaa
Hagayya 11-17, 2018ALI
👉Luqqisii Duree: ''Akka itti jiraachuun ta'u mucaa barsiisi! Innis yommuu dulloomu iyyuu irraa hin kaatu/goru.'' Fakk. 22:6
👉Mata Duree: 'Maatii Jabaa : Dhaloota Milkaa'aa'
👉Waldaa Amantootaa Hundumaatti
* *
EECMY Children's Week-
August 17-23/2026
👉Leading Verse: ''Train children in the right way, and when old, they will not stray.'' Prov. 22:6
👉Theme: 'Strong Family: Successful Generation'
👉In all congregations of the EECMY
EECMY Children Ministry - MY Sunday School
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ለ15 አገልጋዮች የቅስና ሃላፊነት ሰጠች።
***
የቤተ ክርስቲያኒቱን የቃል እና የቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት እንዲያግዝ ለ15 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት የመስጠት ሥነ ሥርዓት በጀሞ ቤቴል ማህበረ ምዕመናን በትላንትናው ዕለት ተካሂዷል።
እጩ ቀሳውስቱም ከማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ኢሉባቦር ቤቴል፣ ከደቡብ፣ ከጅማ ቤቴል፣ ከአዲስ አበባ እና ከፊንፊኔና አከባቢው እጩ ቤቴል ሲኖዶሶች የመጡ ናቸው።
ቅስና የመስጠት ሥነ ሥርዓቱን የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የመሩና ሀላፊነቱንም ሰጡ ሲሆን፤ የቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶሎሳን ጨምሮ በመርሃግብሩ እጩ ቀሳውስትን የላኩ ሲኖዶስ ፕሬዚዳንቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በዚህም መልክ በርካታ ሲኖዶሶች ቀሳውስትን በጋራ የማቀሰስ የቀድሞ ልማድን ያስታወሰ ሥነ ሥርዓት እንደነበር የተገለፀ ሲሆን በጋራ አገልጋዮችን የማሰማራት ምሳሌ ሆኖ የተስተዋለት የማቀሰስ መርሃግብር ነበር።
ለእረኝነት አገልግሎቱ አገልጋዮችን የጨመረልን የእግዚአብሔር ስም ብሩክ ይሁን!
📷 Jemo Betel Congregation
በአባታችን ቄስ ስምዖን ሞቻ ዜና ዕረፍት የተሰማንን ሀዘን እንገልጻለን።
* * ***
“ከሰማይም፦ ከእንግዲህ ወዲህ በጌታ የሚሞቱ ሙታን ብፁዓን ናቸው። መንፈስ፦ አዎን፥ ከድካማቸው ያርፉ ዘንድ፥ ሥራቸውም ይከተላቸዋል ይላል ብለህ ጻፍ የሚል ድምፅ ሰማሁ።” ራእይ 14፥13
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስን በብሔራዊ ደረጃና በበርካታ የሲኖዶስ ሀላፊነቶች በቅንነትና ታማኝነት ሲያገለግሉ የነበሩት፤ የቄስ ስምዖን ዜና እረፍትን በታላቅ ሀዘን ሰምተናል።
አባታችን ቄስ ስምዖን የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስን በምክትል ፕሬዚዳንት፤ ዋና ኮሚቴ አባልነት፤ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባልነት፤ እንዲሁል በማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ በምክትል ፕሬዚዳንትነት፤ የወንጌል ተልዕኮና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተርነት የአገልግሎት ሀላፊነቶች ቤተ ክርስቲያንን አገልግለዋል።
በተጨሪም አባታችን የአማሮና አከባቢው ሲኖዶስ የመጀመሪ ፕሬዚዳንት በመሆን ያገለገሉ ሲሆን፤ በጡረታ ጊዜያቸውም በምክርና አቅጣጫን በማሳየት የአባትንት ሀላፊነታቸውን እየተወጡ በነበሩበት ጊዜ ባጋጠማቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ወደሚወዱትና ወዳገለግሉት ጌታ ሄደዋል።
ቄስ ስምዖኝ በአማሮ፤ በቡርጂ እና በበርካታ የደቡብ ኢትዮጵያ አከባቢዎች የእግዚአብሔር ቃል ያስተናሩ የወንጌል አርባኛ ነበሩ።
የቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ነገ በኬሌ ከተማ መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን የሚፈጸም ይሆናል።
ለቤተሰባቸው፤ ወዳጅ ዘመዶች፤ ላገለገሏቸው ምዕመናን እና ለሁላችን እግዚአብሔር መጽናናቱን ይስጠን!
ሁሉን አቀፍ የናቪሽን የሂሳብ አስተዳደር ስልጠና ተሰጠ።
* * * * * *
የኢትዮጲያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በአስተዳደር እና ፋይናንስ መምሪያ የተዘጋጀው የናቬሽን የሂሳብ አስተዳደር ስልጠና በስኬት ተካሂዷል። በስልጠናውም ከቤተ ክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶች እና የጋራ ተቋማት የመጡ የሂሳብ ባለሙያዎች እና የመምሪያ ዳይሬክተሮች ተካፍለዋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱ የአስተዳደር እና ፋይናንስ መምሪያ ዳይሬክተ ወ/ሮ ሰብለ ገመችስ በመዝጊያ ንግግራቸው የሥልጠናው ዋና አላማ የሂሳብ ባለሙያዎቹ የሂሳብ ነክ መረጃዎችን በአግባቡ እንዲመዘግብ፤ የቁጥጥርና ጊዜውን የጠበቀ ሪፓርቲንግን ክህሎትን እንዲያዳብሩ መሆኑን የገልፀዋል። አያይዘውም የስልጠናውን ውጤት ማረጋገጥ እንዲያስችል ተግራዊ የሶፍትዌር አጠቃቀም ስልጠና መሰጠቱን አክለዋል።
ሰልጣኞቹም በስልጠናው ከወሰዱት እውቀት ባሻገር በውይይት እና የጥያቄና መልስ ክፍለ ጊዜ ብዙ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልፀዋል።
በመካነ ኢየሱስ ሴሚናሪዮም ቻፕል በተካሄደው ስልጠና ማጠቃለ ለስልጠናው ተካፋዮች የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምክክር አውደ ጥናት ዛሬ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
* * * * * *
የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥነ መለኮት አቋም ማስጠበቅ፤ የአምልኮ ሥርዓተ ጥንቃቄ፤ ሐሰተኛ ትምህርቶችን እና ልምምዶችን መከላከል ላይ ያተኮረው የመሪዎች አውደ ጥናት በጉዲና ቱምሳ ሁለገብ የሥልጣና ማዕከል ባሳለፍነው ዕለት መካሄድ ጀምሯል። በዚህም አውደ ጥናት የሲኖዶስ ፕሬዚዳንቶች፤ ዋና ፀሐፊዎችና የወንጌል ተልዕኮና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተሮች እና ከጋራ ተቋማት የመጡ መሪዎች እየተሳተፉበት ይገኛል።
አውደ ጥናቱን ያዘጋጀው የቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌል ተልዕኮና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ጥላዬ ከበደ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የምክክር አውደ ጥናቱን አላማ የገለፁ ሲሆን ይህንን የጋራ ጊዜ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች እና አገልጋዮች እያጋጠሙ ባሉ ውጫዊ ተፅዕኖዎች እና ሊደረጉ በሚገቡ ጥንቃቄዎች ዙሪያ የሚመክሩበት ሰፊ እድል እንደሆነ ገልጸዋል።
በአውደ ጥናቱ ወቅታዊነትና ጠቀሜታ ዙሪያ አጽንዖት በመስጠት ተሳታፊዎች በትኩረት በመከታተል ግብአት በመስጠት አስተዋፆ እንዲያደርጉ ፣ እስከ ማህበረ ምዕመናን በማዉረድ የምክክሩ ዉጤቶች እንዲተገበሩ የቤተ ክርስቲያኒቱ ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ዶ/ር ተሾመ አመኑ አሳስበዋል።
አዉደ ጥናቱ በተለያዩ ርዕሶች ላይ ከመምሪያዉ ባልደረቦች ለዉይይት መነሻ የሚሆኑ ፁሑፎች የሚቀርቡ ሲሆን በማለዳውም ክፍለ ጊዜ የቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶሎሳ "የብልጽግና ወንጌል በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ እያደረሰ ያለዉ ተጽዕኖ" በሚል ርዕስ ሰፊ ጽሑፍ አቅርበዋል።
በተያያዘ መልኩ በዚህ አውደ ጥናት ለመካፈል በአሜሪካ ሐገር ኪንታኪ ከተማ ከምትገኘዉ የሄብሮን ሉተራዊት ማህበረ ምዕመናን የመጡ አገልጋዩች ሰላምታ አቅርበዋል።
አውደ ጥናቱም በተዘጋጀለት የፕሮግራም ሰሌዳ እንደሚቀጥል ከመምሪያው ለመረዳት ተችሏል።
