fa
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

رفتن به کانال در Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

نمایش بیشتر
3 496
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+157 روز
+11030 روز
آرشیو پست ها
የቤተ ክርስቲያኒቱ የቀድሞ የክብር ፕሬዚዳንት ቄስ ኢተፋ ጎበና እና የቀድሞ ጠቅላይ ​ጸሐፊ ቄስ ዶ/ር መገርሳ ጉታ ለተከበረው የ22ኛው የቤተ ክርስቲያኒቱ ካውንል ሰላምታ አቅርበዋል። ቄስ ኢተፋም በሰላታ ንግግራቸው መካነ ኢየሱስ እጅግ እያደገች እንደሆነ የገለጹ ሲሆን በዚህ መብዛቱ ከቤተ ክርስቲያን ብዙ እንደሚጠበቅ አሳስበዋል። ካውንስሉ መልካም እና ውጤታማ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን አስተላልፋዋል። ቤተ ክርስቲያን አገልግሎትዋን የምትመራው በመጽሐፍ ቅዱስ እና በቤተ ክርቲያኒቱ መተዳደሪያ ደንብ እንደሆነ የገለጹት ቄስ ዶ/ር መገርሳ፤ የመሰረተ እምነትና የደንብ ጉዳይ የዚህ ካውንስል አጀንዳ እንዲሆን አሳስበዋል። ቤተ ክርስቲያንም በታሪክ አጋጣሚ ለብዙዎች ምሳሌ የሚሆን አሰራር እና መመሪያን ከትውልድ ወደ ትውልድ ማሸጋገሯን አስታውሰዋል። ቀጣይ የ22ኛውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ካውንስል ዘገባዎች ለመከታተል የሚከተሉትን አካውንቶች ፎሎ በማድረግ ይከታተሉ:- Facebook - https://www.facebook.com/share/1GDpuFoseh/ Telegram - https://t.me/EECMYeth YouTube News- https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=cPuWOIVvHYDI01nd YouTube Education - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=0XKpyBECeLaTIZFg

የ21ኛው የቤተ ክርስቲያኒቱ ካውንስል ተሳታፊዎች የጌታን እራት በጋራ ተካፍለዋል። ቀጣይ የ22ኛውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ካውንስል ዘገባዎች ለመከታተል የሚከተሉትን አካውንቶች ፎሎ በማድረግ ይከታተሉ:- Facebook - https://www.facebook.com/share/1GDpuFoseh/ Telegram - https://t.me/EECMYeth YouTube News- https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=cPuWOIVvHYDI01nd YouTube Education - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=0XKpyBECeLaTIZFg

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ 22ኛው መደበኛ የካውንስል ስብሰባ ዛሬ ማለዳ በጸሎት መርሃግብር ተጀምሯል። * * *** በትንቢተ ኤርሚያስ 6፥16 “የቀደመችውንም መንገድ ፈልጉ” የሚለውን ጥቅስ መሪ ቃል ያደረገው የቤተ ክርስቲያንቱ 22ኛ መደበኛ የካውንስል ስብሰባ፤ ዛሬ በጉዲና ቱምሳ ሁለገብ የስልጠና ማዕከል ጅማሬውን አድርጓል። ስብሰባውም ለቀጣይ ዓራት ቀናት እስከ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን በርካታ ጉዳዮችን እንደሚዳስስ ይታመናል። በማለዳውም የጸሎት መርሃገብር፤ በመሪ ጥቅሱ መሰረት የእግዚአብሔር ቃል ትምህርት፤ በካየር አገልግሎትም ዝማሬዎች የቀረቡ ሲሆን፤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶች በተነሱ የጸሎት ጥያቄዎች ዙሪያ በጋራ ተጸልዬአል። በጸሎቱም የቤተ ክርስቲያንን አንድነት፤ የሀገራችንን ሰላም፤ በመካሄድ ላይ የሚገኘውን አገራዊ የምክክር ጉባኤው፤ በወንጌል ማዳረስ አገልግሎት እና ሌሎች ተጨማሪ አርዕስቶች ዙሪያ ጸሎት ተደርጓል። በመደበኛ የስብሰባ ጊዜውም ካውንስሉ ባለፉት 12 ወራት የተከናወኑ ተግባራትንና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ከሚቀርበው መርሃ ንግግርና ሪፖርቶች አድምጦ የሚመክር እና ውሳኔዎችን የሚያስተላልፍ ይሆናል።

የኢ/ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ የልጆች በዓል ሳምንት ነሐሴ 11-17/2018ዓ.ም መሪ ጥቅስ: ''ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም።'' ምሳሌ 22:6 ርዕስ: ''ጠንካራ ቤተሰብ: ስኬታማ ትውልድ'' በሁሉም ማኀበራነ ምዕመናን * * Kabaja Torbaan Ayyaana Ijoollee WWWMakaana Yesuus Itoophiyaa Hagayya 11-17, 2018ALI 👉Luqqisii Duree: ''Akka itti jiraachuun ta'u mucaa barsiisi! Innis yommuu dulloomu iyyuu irraa hin kaatu/goru.'' Fakk. 22:6 👉Mata Duree: 'Maatii Jabaa : Dhaloota Milkaa'aa' 👉Waldaa Amantootaa Hundumaatti * * EECMY Children's Week- August 17-23/2026 👉Leading Verse: ''Train children in the right way, and when old, they will not stray.'' Prov. 22:6 👉Theme: 'Strong Family: Successful Generation' 👉In all congregations of the EECMY EECMY Children Ministry - MY Sunday School

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ለ15 አገልጋዮች የቅስና ሃላፊነት ሰጠች። *** የቤተ ክርስቲያኒቱን የቃል እና የቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት እንዲያግዝ ለ15 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት የመስጠት ሥነ ሥርዓት በጀሞ ቤቴል ማህበረ ምዕመናን በትላንትናው ዕለት ተካሂዷል። እጩ ቀሳውስቱም ከማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ኢሉባቦር ቤቴል፣ ከደቡብ፣ ከጅማ ቤቴል፣ ከአዲስ አበባ እና ከፊንፊኔና አከባቢው እጩ ቤቴል ሲኖዶሶች የመጡ ናቸው። ቅስና የመስጠት ሥነ ሥርዓቱን የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የመሩና ሀላፊነቱንም ሰጡ ሲሆን፤ የቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶሎሳን ጨምሮ በመርሃግብሩ እጩ ቀሳውስትን የላኩ ሲኖዶስ ፕሬዚዳንቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በዚህም መልክ በርካታ ሲኖዶሶች ቀሳውስትን በጋራ የማቀሰስ የቀድሞ ልማድን ያስታወሰ ሥነ ሥርዓት እንደነበር የተገለፀ ሲሆን በጋራ አገልጋዮችን የማሰማራት ምሳሌ ሆኖ የተስተዋለት የማቀሰስ መርሃግብር ነበር። ለእረኝነት አገልግሎቱ አገልጋዮችን የጨመረልን የእግዚአብሔር ስም ብሩክ ይሁን! 📷 Jemo Betel Congregation