en
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

Open in Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

Show more
3 491
Subscribers
+324 hours
+97 days
+11030 days
Posts Archive
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶ/ር ጌቱ ለማ በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ 22ኛ የካውንስል ስብሰባ በመገኘት የአብያተ ክርስቲያናት የካውንስሉን ሰላምታ አቅርበዋል። * * *** በመልዕክታቸውም የመካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን በአገራችን አንጋፈና ታሪካዊ ከሆኑት ወንጌላዊያን ቤተ እምነቶች አንዷ መሆኗን የጠቀሱ ሲሆን፤ ቤተ ክርስቲያኒቱም በረጅም የአገልግሎት ጉዞዋ ባካሄደቻቸው ጉባኤዎችዋና ስብሰባዎችዋ በሀገር እና በዓለም አቀፍ አገልግሎትዋ ላይ ጉልህ ድርሻን ያሳረፉ በርካታ ውሳኔዎችን ማሳለፏን አታውሰዋል። ቤተ ክርስቲያንም ዛሬ ለደረሰችበት ሁለንተናዊ እድገት የቀደሙ አመራሮችን አስተዋጽዎ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው፤ ዛሬም ይህች አንጋፈ ቤተ እምነት ትውልድ፤ አገር እና ከሁሉ በላይ መለኮታዊ አደራ የሰጣት እግዚአብሔር ከእርሷ ብዙ እንደሚጠብቅ ተናግረዋል። የዛሬዋም ቤተ ክርስቲያን መሪዎች ሃላፊነታችንን ስንወጣ፤ ትላንትን በመማስታውስ፤ ዛሬን በታማኝነት በማገልገል እና መሠረት በሚጥል መልኩ ነገን በራዕይ በመመልከት ሊሆን ይገባል ብለዋል። ስብሰባውም መልካም እና የተሳካ ጉባኤ እንዲሆን የካውንስሉ ጠቅላይ ጽሐፊ ፓስተ ዶ/ር ጌቱ ለማ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ደረጀ ጀምበሩ መካነ ኢየሱስ በብዙ የታደለችና ብዙ መልካም ነገሮችን የያዘች አንጋፋ ቤተ ክርስቲያን መሆኗም ተናገሩ። * * *** በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ 22ኛው መደበኛ ካውንስል የመክፈቻ መርሃግብር ላይ የተገኙት ቄስ ዶ/ር ደረጀ ጀምበሩ ለካውንስሉ መልዕክት አስተላልፋዋል። በመልዕክታቸውም መካነ ኢየሱስን እግዚአብሔር እራሱ እያሰፋት እና እየመራት እዚህ እንዳደረሳት የገለፁ ሲሆን ለሌሎች ምሳሌ መሆን የመቻል አቅምም እንደሰጣት ተናግረዋል። የወንጌል አማኙንም ካውንስል ካቋቋሙ ቤተ እምነቶች መካከል መካነ ኢየሱስ አንዷ መሆኗን የጠቀሱ ሲሆን፤ ቤተ ክርስቲያኒቱ ከካውንስሉ ምስረታው ጊዜ ጀምሮ በነበራት እና አሁንም ባላት ተሳትፎ ካውንስሉ እየሰፋና ብዙ አገልግሎቶችን እየሰጠ እዚህ ደርሷል ብለዋል። ካውንስሉም ከቤተ ክርስቲያኒቱ ጋር አብሮ መስራት እና ማገልገሉን እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በ22ኛው መደበኛ ካውንስል ለሚሳተፉ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎችም ባስተላለፉት አባታዊ ምክር መሪዎች በአንድነት በመቆም ምሳሌ ሊሆኑ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የቤተ ክርስቲያኒቱ የቀድሞ የክብር ፕሬዚዳንት ቄስ ኢተፋ ጎበና እና የቀድሞ ጠቅላይ ​ጸሐፊ ቄስ ዶ/ር መገርሳ ጉታ ለተከበረው የ22ኛው የቤተ ክርስቲያኒቱ ካውንል ሰላምታ አቅርበዋል። ቄስ ኢተፋም በሰላታ ንግግራቸው መካነ ኢየሱስ እጅግ እያደገች እንደሆነ የገለጹ ሲሆን በዚህ መብዛቱ ከቤተ ክርስቲያን ብዙ እንደሚጠበቅ አሳስበዋል። ካውንስሉ መልካም እና ውጤታማ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን አስተላልፋዋል። ቤተ ክርስቲያን አገልግሎትዋን የምትመራው በመጽሐፍ ቅዱስ እና በቤተ ክርቲያኒቱ መተዳደሪያ ደንብ እንደሆነ የገለጹት ቄስ ዶ/ር መገርሳ፤ የመሰረተ እምነትና የደንብ ጉዳይ የዚህ ካውንስል አጀንዳ እንዲሆን አሳስበዋል። ቤተ ክርስቲያንም በታሪክ አጋጣሚ ለብዙዎች ምሳሌ የሚሆን አሰራር እና መመሪያን ከትውልድ ወደ ትውልድ ማሸጋገሯን አስታውሰዋል። ቀጣይ የ22ኛውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ካውንስል ዘገባዎች ለመከታተል የሚከተሉትን አካውንቶች ፎሎ በማድረግ ይከታተሉ:- Facebook - https://www.facebook.com/share/1GDpuFoseh/ Telegram - https://t.me/EECMYeth YouTube News- https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=cPuWOIVvHYDI01nd YouTube Education - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=0XKpyBECeLaTIZFg

የ21ኛው የቤተ ክርስቲያኒቱ ካውንስል ተሳታፊዎች የጌታን እራት በጋራ ተካፍለዋል። ቀጣይ የ22ኛውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ካውንስል ዘገባዎች ለመከታተል የሚከተሉትን አካውንቶች ፎሎ በማድረግ ይከታተሉ:- Facebook - https://www.facebook.com/share/1GDpuFoseh/ Telegram - https://t.me/EECMYeth YouTube News- https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=cPuWOIVvHYDI01nd YouTube Education - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=0XKpyBECeLaTIZFg

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ 22ኛው መደበኛ የካውንስል ስብሰባ ዛሬ ማለዳ በጸሎት መርሃግብር ተጀምሯል። * * *** በትንቢተ ኤርሚያስ 6፥16 “የቀደመችውንም መንገድ ፈልጉ” የሚለውን ጥቅስ መሪ ቃል ያደረገው የቤተ ክርስቲያንቱ 22ኛ መደበኛ የካውንስል ስብሰባ፤ ዛሬ በጉዲና ቱምሳ ሁለገብ የስልጠና ማዕከል ጅማሬውን አድርጓል። ስብሰባውም ለቀጣይ ዓራት ቀናት እስከ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን በርካታ ጉዳዮችን እንደሚዳስስ ይታመናል። በማለዳውም የጸሎት መርሃገብር፤ በመሪ ጥቅሱ መሰረት የእግዚአብሔር ቃል ትምህርት፤ በካየር አገልግሎትም ዝማሬዎች የቀረቡ ሲሆን፤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶች በተነሱ የጸሎት ጥያቄዎች ዙሪያ በጋራ ተጸልዬአል። በጸሎቱም የቤተ ክርስቲያንን አንድነት፤ የሀገራችንን ሰላም፤ በመካሄድ ላይ የሚገኘውን አገራዊ የምክክር ጉባኤው፤ በወንጌል ማዳረስ አገልግሎት እና ሌሎች ተጨማሪ አርዕስቶች ዙሪያ ጸሎት ተደርጓል። በመደበኛ የስብሰባ ጊዜውም ካውንስሉ ባለፉት 12 ወራት የተከናወኑ ተግባራትንና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ከሚቀርበው መርሃ ንግግርና ሪፖርቶች አድምጦ የሚመክር እና ውሳኔዎችን የሚያስተላልፍ ይሆናል።