The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
الذهاب إلى القناة على Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
إظهار المزيد3 499
المشتركون
-124 ساعات
+187 أيام
+11130 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አለም አቀፍ ሚሲዮን ማህበር በየአመቱ ጥር ወር በሚያካሂደው የሚስዮን ቀን፤ እ.ኤ.አ በ2026 ልዩ በዓል ወቅት የ97% እድገት በማሳየት ከ23 ሚልየን ብር በላይ አሰባስቧል። በዚህም የሀብት ማሰባሰብ የላቀ አፈፃፀም ላሳዩ የሥራ ዘርፎች በ22ኛው የቤተ ክርስቲያኒቱ ካውስል እውቅና ተሰጥቷል።
የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዩናስ ይገዙ፤ የቀድሞ የክብር ፕሬዚዳንት ቄስ ኢተፋ ጎበና፤ የቀድሞ ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ዶ/ር መገርሳ ጉታ፤ የማህበሩ ዳይሬክተር ቄስ ዋኘው አንዳርጌ እና የቦርዱ ሰብሳቢ ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል ሽልማቶቹን ለሥራ ዘርፎች አበርክተዋል።
በነበረውም የአፈፃፀም እውቅና ሥነ ሥርዓት የሚስዮን ማህበሩ በከፍተኛ ንቃት በእንቅስቃሴ ላይ መሆኑ ተመላክቷል።
ቀጣይ የቤተ ክርስቲያኒቱን ዘገባዎች ለመከታተል የሚከተሉትን አካውንቶች ፎሎ በማድረግ ይከታተሉ:-
Facebook - https://www.facebook.com/share/1GDpuFoseh/
Telegram - https://t.me/EECMYeth
YouTube News- https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=cPuWOIVvHYDI01nd
YouTube Education - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=0XKpyBECeLaTIZFg
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ 22ኛው መደበኛ የካውንስል ስብሰባ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የአገልግሎት መደቦች መሪዎችን በመምረጥ በስኬት ተጠናቋል።
1. ቄስ ታምራት ታደለ የቤተ ክርስቲያኒቱ ጠቅላይ ጸሐፊ፤
2. ቄስ ወንድማገኝ ኡዴሳ የምሥራች ድምጽ ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ዳይሬክተር፤
3.ቄስ ታገሰች ዳኘው የሴቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር፤
4. አቶ ጋሉንዴ ዋኬታ የእስቲዋርድሽፕና ቸርች ኤኮኖሚ መምሪያ ዳይሬክተር፤
5. ወጣት ኤፍሬም ታሪኩ የልጆችና ወጣቶች መምሪያ ዳይሬክተር፤ በመሆን ለቀጣይ አራት አመታት ቤተ ክርስቲያኒቱን የሚያገለግሉ ይሆናል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ለተመረጡት መሪዎች መልካም ምኞቷን እየገለጸች ለአገልግሎታቸው ስኬት ትጸልያለች!
የመካነ ኢየሱስ ሴሚናሪዮም የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች፤ 22ተኛው የቤተ ክርስቲያኒቱ ካውንስል አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በርካታ አገልግሎቶችን የሚሰጥ ዘመናዊ የነዳጅ ማደያ አስመርቋል። ይህም ዘመናዊ ማደያ -- የነዳጅ፤ የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጂንግ፤ ዘመናዊ የመኪና ማጠቢያ፤ ሱፐርማርኬት እና የካፍቴሪያ አገልግሎት የሚሰጥ ይሆናል።
የዚህም ማደያ መጠናቀቅ ሴሚናሪዮሙ ለሚያካሂደው፤ አገልጋዮቹን ለቤተ ክርስቲያኒቱ የማዘጋጀት እና የማብቃት ሥራ፤ ጥሩ ፋይናንስ ድጋፍ የሚሰጥ እንደሆነ ተገልጿል። የፕሮቸክቱም በፍጥነት መጠናቀቅ ሴሚናሪው በልዩ ትኩረት የልማት ሥራዎችን በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ማሳያ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ዶ/ር ተሾመ አመኑ ለ22ተኛ የቤተ ክርስቲያኒቱ ካውንስል፤ የአንድ አመት የስራ ክንውን ሪፖርት አቅርበዋል።
* *
ከሁሉ በፊት ባሳለፍነው አመት በብዙ ምህረትና ቸርነት፤ በሰራናቸው የወንጌል እና የልማት ሥራዎች ረድቶናል ሲሉ እግዚአብሔርን አመስግነዋል። ቀጥለውም ከሁሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶች የመጡ የካውንስሉን ተሳታፊዎች፤ የጋራ ፕሮግራም ዳይሬክተሮች፤ የዋናው ጽሕፈት ቤተ ሰራተኞች እና ተጋባዥ እንግዶችን ሰላምታ ጠይቀዋል።
በሪፖርታቸውም የቤተ ክርስቲያኒቱ ነባራዊ እስታቲስቲካዊ መረጃዎች በዝርዝር ቀርቧል። በዚህም መሰረት የቤተ ክርስቲያኒቱ አጠቃላይ አባላት ብዛት 4.3% እድገት በማሳየት ከ13.12 ሚሊየን በላይ መድረሱን ገልጸዋል። በተያያዘ መልኩ የቁጥር እድገት ያሳያዩ የማኅበራነ ምዕመናን፤ የስብከት ጣቢያዎች፤ የቄሶች፤ የወንጌላዊያን እና የበጎ ፈቃድ አገልጋዮች ቁጥር በሪፖርቱ ተካቷል።
ከቀረቡትም የእስታቲስቲካዊ መረጃዎች ካለፈው የፈረንጆቹ 2025 ከፍተኛ እድገት ያሳየው የበጎ ፈቃድ አገልጋዮች ቁጥር እንደሆነ ተመላክቷል። ይህም እድገት የቤተ ክርስቲያኒቱ ምዕመናን በወንጌል አገልግሎቱ ላይ ያሳዩት ተሳትፎ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ እድገት ማሳየቱን መረጃዎቹ ተቁማል።
የቤተ ክርስቲያኒቱን እድገት ተከትሎ የትኩረት አቅጣጫ የሚሹ ጉዳዮች መካከል የመሪዎች እና አገልጋዮች አቅም ግንባታ እንደሆነ ይታወቃል። በዚህ ረገድም የአመራር ክህሎት ለማሳደግ በተደረጉ ጥረቶች ከ1.5 ሚልየን በላይ ለሆኑ አገልጋዮች ስልጠናዎች መሰጠቱን ቄስ ዶ/ር ተሾመ ገልጸዋል።
የአገልግሎት ትስስርና ስልታዊነትን ለማረጋገጥ፤ ቤተ ክርስቲያኒቱ የስትራቴጂክ ዕቅድ እና ክትትልን በመተግበር ላይ ትገኛለች። ይህንንም ከማረጋገጥ አንጻር በዋናው የቤተ ክርስቲያኒቱ ጽሕፈት ቤት በኩል ውጤታማ የክትትልና የግምገባ ስራዎች መካሄዳቸው በሪፖርቱ ተገልጿል።
ከዚም ባሻገር ሰፊ ጉዳዮችን የዳሰሰው ሪፖርት፤ በመምሪያዊች፤ ሲኖዶሶች፤ የጋራ ተቋማት እና ገቢ ማስገኛ የኢንቨስትመንት ተቋማት የተመዘገቡ ውጤቶችን፤ ተግዳሮቶች እና ያሉ እድሎችን በዝርዝር አካቷል።
ጠቅላይ ጸሐፊውም በማጠቃለያው የካውንስሉን ትኩረት የሚሹ ባለ 29 ነጥብ ጉዳዮችን ለተከበረው ካውንስል አቅርበዋል። በእነዚህ ነጥቦችም እውቅና ሊሰጣቸው የሚገቡ የተቋማት ስኬቶች፤ የቤተ ክርስቲያኒቱ ትምህርት እውቅና ሰጪ ኮሚሽን እንዲቋቋም፤ የቄሶችና አገልጋዮች ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ ሉተራዊነትን መሠረት ያደረጉ ስልጠናዎች በየአመቱ እንዲሰጡ፤ የቤተ ክርስቲያኒቱ የንብረት ልማት ፖሊሲ እንዲዘጋጅ እና የውስጥ ኦዲት ቁጥጥርን ማጠናከር ይገኙበታል።
በተጨማሪ ከቤተ ክርስቲያኒቱ የሥነ መለኮት ተቋማት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች የቀረቡ ሲሆን፤ ለቀጣይ አብይ ጉዳኤ ቀርበው የሚቋቋሙ አዳዲስ ሲኖዶሶችም በዝርዝር ቀርበዋል።
አክለውም ጊዜያቸወን ባጠናቀቁ የቤተ ክርስቲያኒቱን ጠቅላይ ጸሐፊ፤ የእስቲዋርድሺፕ እና የቤተ ክርስቲያን ኢኮኖሚ፤ የምሥራች ድምጽ ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት እና በተጨማሪ መምሪያ ቦታዎች ምርጫዎች እንዲደረጉ አቅርበዋል።
የጠቅላይ ጸሐፊውንም የሥር ክንውን ሪፖርት ያደመጠው ካውንስል፤ በዝርዝር በጉዳዮቹ ከመከረና ውሳኔ ካስተላለፈ በኋላ ሪፖርቱን በሙሉ ድምጽ ተቀብሏል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ ለ22ኛው የቤተ ክርስቲያኒቱ ካውንስል የመክፈቻ መርሐ ንግግር (Keynote Address) አቅርበዋል።
* * ***
ባሳለፍነው አንድ አመት እግዚአብሔር ያደረገልንን ምህረት ከ13 ሚልየን በላይ ከሚሆኑ ምዕመናን ጋር መለስ ብለን በምስጋና እናስባለን በማለት ፕሬዚዳንቱ አመስግነዋል። ይችም ከዓለም ሉተራዊያን አብያተ ክርስቲያናት በሁሉም ረገድ በቀዳሚነት የምትጠቀሰው ቤተ ክርስቲያናችን ለሌሎች ምሳሌ በምትሆንበት እና ተጽዕኖ መፍጠር በምትችለበት ቁመና ላይ እንደምትገኝ ገልጸዋል።
በአሁኑም ጊዜ ቤተ ክርስቲያኒቱ ከቆመችበት እውነት ያፈነገጡ ትምህርቶችና ልምምዶች የሚስተዋሉበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ፤ እነዚህን ጉዳዮች ለመከላከል እና ለማስቆም የሚያስችል የሥነ ቤተ ክርስቲያን አሰራሮች እንዲቀየሱ ጠቁመዋል።
ፕሬዚዳንቱም በሁለት ቋንቋዎች ባቀረቡት ሰፊ መርሐ ንግግር ባለፉት አስር ዓመታት የታየውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ፈጣን እድገት አስቀምጠዋል። በዚህም መሰረት ባለፉት 10 ዓመታት ከ5 ሚሊየን በላይ ምዕመናን የተጨመሩ ሲሆን ከ4 ሺህ በላይ ማኅበራነ ምዕመናን ተተክለዋል። ከዚህም በተጨማሪ 19 ተጨማሪ ሲኖዶሶች ተመሥርተው የአገልግሎት ተደራሽነት ዕድገት በቤተ ክርስቲያኒቷ በጉልህ ተመዝግቧል። ለዚህም ስኬት ከሁሉ በላይ እግዚአብሔርን፤ በመቀጠል የቤተ ክርስቲያኒቱን መሪዎችና አገልጋዮችን በሙሉ ያመሰገኑ ሲሆን፤ እድገቱ በሁሉም አቅጣጫ የተማከለ እንዲሆን በትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ከዚህም ጋር በተያያዘ ለዘብተኝነት (ሊብራሊዝም) ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችን እንዲሁም ዶግማዎችን የሚገዳደሩበት ጊዜ ላይ ስላለን፤ በቤተ ክርስቲያኒቱ የሉተራዊነት ማዕቀፍ ውስጥ ቤተ ክርስቲያን ራስዋን ለተቀረው አለም የምትገልጽበት እና ያላት ሥነ መለኮታዊ ማንነቷን በምርመራዊ ጥናት መሠረት እንዲሰራ ምክረ ሀሳብ ለግሰዋል።
በቀጣይ ዘመናትም ቤተ ክርስቲያኒቱ ሁለንተናዊ አገልግሎትን በስፋት ለመስጠት የሚያስችሏትና የቤተ ክርስቲያኒቱን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ የደንብ ማሻሻያ እንዲደረግ፤ በቤተ/ክን ደረጃ ሀገራዊ የሰላም ግንባታ ሥራ በኮምሽን መልክ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አቅርበዋል። አክለውም የቤተ ክርስቲያኒቱን ኢኮኖሚ ለማሳደግ የሚጠቅሙ ረቂቅ ሀሳቦች ተጠንተው ሊተገበሩ በሚችሉበት ይዘት በምክረ ሃሳብ መልክ ጠቁመዋል።
በዚሁም መሰረት መርሐ ንግግሩን ያደመጠው ካውንስል በሰፊው ከመከረ እና ውሳኔዎችን ካስተላለፈ በኋላ በሙሉ ድምጽ በምስጋና ተቀብሏል።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ፓስተር ዶ/ር ጌቱ ለማ በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ 22ኛ የካውንስል ስብሰባ በመገኘት የአብያተ ክርስቲያናት የካውንስሉን ሰላምታ አቅርበዋል።
* * ***
በመልዕክታቸውም የመካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን በአገራችን አንጋፈና ታሪካዊ ከሆኑት ወንጌላዊያን ቤተ እምነቶች አንዷ መሆኗን የጠቀሱ ሲሆን፤ ቤተ ክርስቲያኒቱም በረጅም የአገልግሎት ጉዞዋ ባካሄደቻቸው ጉባኤዎችዋና ስብሰባዎችዋ በሀገር እና በዓለም አቀፍ አገልግሎትዋ ላይ ጉልህ ድርሻን ያሳረፉ በርካታ ውሳኔዎችን ማሳለፏን አታውሰዋል።
ቤተ ክርስቲያንም ዛሬ ለደረሰችበት ሁለንተናዊ እድገት የቀደሙ አመራሮችን አስተዋጽዎ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው፤ ዛሬም ይህች አንጋፈ ቤተ እምነት ትውልድ፤ አገር እና ከሁሉ በላይ መለኮታዊ አደራ የሰጣት እግዚአብሔር ከእርሷ ብዙ እንደሚጠብቅ ተናግረዋል።
የዛሬዋም ቤተ ክርስቲያን መሪዎች ሃላፊነታችንን ስንወጣ፤ ትላንትን በመማስታውስ፤ ዛሬን በታማኝነት በማገልገል እና መሠረት በሚጥል መልኩ ነገን በራዕይ በመመልከት ሊሆን ይገባል ብለዋል።
ስብሰባውም መልካም እና የተሳካ ጉባኤ እንዲሆን የካውንስሉ ጠቅላይ ጽሐፊ ፓስተ ዶ/ር ጌቱ ለማ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ደረጀ ጀምበሩ መካነ ኢየሱስ በብዙ የታደለችና ብዙ መልካም ነገሮችን የያዘች አንጋፋ ቤተ ክርስቲያን መሆኗም ተናገሩ።
* * ***
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ 22ኛው መደበኛ ካውንስል የመክፈቻ መርሃግብር ላይ የተገኙት ቄስ ዶ/ር ደረጀ ጀምበሩ ለካውንስሉ መልዕክት አስተላልፋዋል። በመልዕክታቸውም መካነ ኢየሱስን እግዚአብሔር እራሱ እያሰፋት እና እየመራት እዚህ እንዳደረሳት የገለፁ ሲሆን ለሌሎች ምሳሌ መሆን የመቻል አቅምም እንደሰጣት ተናግረዋል።
የወንጌል አማኙንም ካውንስል ካቋቋሙ ቤተ እምነቶች መካከል መካነ ኢየሱስ አንዷ መሆኗን የጠቀሱ ሲሆን፤ ቤተ ክርስቲያኒቱ ከካውንስሉ ምስረታው ጊዜ ጀምሮ በነበራት እና አሁንም ባላት ተሳትፎ ካውንስሉ እየሰፋና ብዙ አገልግሎቶችን እየሰጠ እዚህ ደርሷል ብለዋል። ካውንስሉም ከቤተ ክርስቲያኒቱ ጋር አብሮ መስራት እና ማገልገሉን እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በ22ኛው መደበኛ ካውንስል ለሚሳተፉ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎችም ባስተላለፉት አባታዊ ምክር መሪዎች በአንድነት በመቆም ምሳሌ ሊሆኑ እንደሚገባ አሳስበዋል።
