cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Abdu Tube Ethiopia

Focus on Student information #dish and #mobile and #Apps YouTube channel https://youtube.com/channel/UCT3rOhyQxk7W_93M8ZtcrDA

Show more
Advertising posts
1 000
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1630 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

⭕️የተፈጥሮ ሳይንስ የአምና የሪሚዲያል ኮርስ pdf ይሄንን ይመስላል አዲስ ነገረ የማይኖር ከሆነ ይሄንኑ ኮርስን የምትማሩ ይሆናል❗️❗️❗️ SHARE SHARE ለሁሉም ይዳረስ🙏🙏🙏🙋‍♂️ @EthioUniversty1 @EthioUniversty1 @EthioUniversty1 @EthioUniversty1
Show all...
#JimmaUniversity ጅማ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ አዲስ ገቢ አንደኛ ዓመት ተማሪዎች ምዝገባ ታህሳስ 01 እና 02/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። የምዝገባ ቦታ፦ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በጅማ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ፤ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ግቢ የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች ምዝገባ እንደየትምህርት መስካችሁ በተገለፁት ቀናት፣ በተጠቀሱት ካምፓሶች እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ወደ ተቋሙ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፡- ➢ የ12ኛ ክፍል ፈተና ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ አራት ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ፣ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ጨርቅ፣ ➢ የስፖርት ትጥቅ፡፡ [ዝርዝር መረጃ ከምስሉ ያንብቡ] ➡️ናቹራል ፍሬሽማን ተማሪዎች ይህን #Ad ቼክ አድርጉት 👉 Click
Show all...
👏 1
Repost from ATC NEWS
#JimmaUniversity ጅማ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ አዲስ ገቢ አንደኛ ዓመት ተማሪዎች ምዝገባ ታህሳስ 01 እና 02/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። የምዝገባ ቦታ፦ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በጅማ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ፤ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ግቢ የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን በጅማ ዩኒቨርሲቲ ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች ምዝገባ እንደየትምህርት መስካችሁ በተገለፁት ቀናት፣ በተጠቀሱት ካምፓሶች እንደሚከናወን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ወደ ተቋሙ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፡- ➢ የ12ኛ ክፍል ፈተና ሰርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ አራት ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ፣ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ጨርቅ፣ ➢ የስፖርት ትጥቅ፡፡ [ዝርዝር መረጃ ከምስሉ ያንብቡ] ➡️ናቹራል ፍሬሽማን ተማሪዎች ይህን #Ad ቼክ አድርጉት 👉 Click ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news
Show all...
ቀብሪደሀር ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም የመጀመሪያ ዓመት (Freshman) ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው መደበኛ የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ህዳር 13 እና 14/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል። በ2014 ዓ.ም የአንደኛ ሴሚስተር ትምህርታችሁን በቀብሪደሀር ዩኒቨርሲቲ ጀምራችሁ በተለያዩ ምክንያቶች Withdrawal የሞላችሁ ተማሪዎችን የሞላችሁበትን ቅፅ በመያዝ በተገለፁት ቀናት ሪፖርት አድርጉ ተብሏል፡፡
Show all...
👍 3
#RayaUniversity በ2016 ዓ.ም በራያ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ህዳር 17 እና 18/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦ ➢ የ8ኛ፣ 10ኛ እና 12ኛ ክፍል ሰርትፍኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ የ12ኛ ክፍል ፈተና ሰርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ አራት 4×4 ፎቶግራፍ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ።
Show all...
👍 1
#ማስታወቂያ፡- በረመዲያል ምደባ አዎንታዊ ድጋፍ ለምትሹ ............................................. በ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ እና በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ ለምትሹ ተማሪዎች ማመልከቻችሁን በ https://student.ethernet.edu.et በኩል ብቻ እስከ ህዳር 12/2016 ዓ.ም እንድታመክቱ እየገለጽን ምንም አይነት ማመልከቻ በአካል የማንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን። ትምህርት ሚኒስቴር በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ ይፈልጋሉ ብሎ የለያቸው ጉዳዮች፦   የአካል ጉዳት ያለባቸው ተማሪዎች:- የምደባ ሲስተሙ የአካል ጉዳት ላለባቸው ተማሪዎች እኩል እድሎችን የሚሰጥ ሲሆን ልዩ ፍላጎቶቻቸውን እና ለምደባ መስፈርቶቻቸውን ግምት ውስጥ በማስገባት የሚሰራ ይሆናል።  አስፈላጊ ማስረጃዎች፦ ከትምህርት ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ እና የአካል ጉዳት ያለበትን የሰውነት ክፍል የሚያሳይ ፎቶግራፍና ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣   ትክክለኛ የሕክምና ቦርድ ማስረጃዎች፡- በምደባ ወቅት የጤና ችግር ኖሮባቸው ትክክለኛ የሕክምና ማስረጃ ላላቸው ተማሪዎች ምደባው በተለየ መልኩ ሊታይ ይችላል፡፡ 
Show all...
👍 2
በአዲሱ የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት የተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ክፍል ዝውውር መመሪያ መሠረት 💥የ12ኛ ክፍል ተማሪ በሚሰጠው አገር አቀፍ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና ወስዶ ወደ ከፍተኛ ትምህርት የሚገቡት፡- ⚡️ትምህርት ሚኒስቴር ሚያስቀምጠውን ዝቅተኛ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብ ያሟሉ ⚡️ በሂሳብ እና በእንግሊዝኛ የትምህርት ዓይነቶች ከ50% በታች #ያላገኙ ⚡️ ዓይነ ስውራን ተማሪዎች ከሒሳብ በስተቀር እንደማንኛውም ተማሪ ዝቅተኛ ማለፊያ ነጥብ ያሟሉ ⚡️ በልዩ ክህሎት ብቁ የሚሆኑ [ ምስሉን ይመልከቱ ‼️] ➡️መመሪያው ከዚህ ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል የተባለ ሲሆን ትምህርት ሚኒስቴር መመሪያው ተግባራዊ መደረግ የሚጀምርበትን ወር እና ቀን ለጊዜው አልተገለፀም።
Show all...
🤔 1
በአዲሱ የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት የተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ክፍል ዝውውር መመሪያ መሠረት 💥የ9ኛ እና የ10ኛ ክፍል የተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ክፍል ዝውውር ሁኔታ ⚡️ በሁሉም የትምህርት አይነቶች 40% በተከታታይ ምዘና እና 60% በትምህርት ዘመኑ ግማሽ ዓመት እና ማጠቃለያ ላይ በሚሰጥ የማጠቃለያ ፈተና በአጠቃላይ ከ100% የሚያገኙትን ውጤት በማስላት በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች 50% እና #በላይ ያገኘ ወደ ቀጣዩ ክፍል ይዛወራል፡፡ ⚡️ በ1 አንኳር ያልሆነ የትምህርት ዓይነት ከ50% በታች ውጤት ያመጣ ተማሪ አማካይ ውጤት 51% ካገኘ ወደ ቀጣዩ ክፍል ይዛወራል፡፡(አንኳር የሚባሉት English and Mathematics ናቸው) ⚡️ በ2 አንኳር ያልሆኑ የትምህርት ዓይነቶች ከ50% በታች ውጤት ያመጣ ተማሪ አማካይ ውጤት 52% ካገኘ ወደ ቀጣቀዩ ይዛወራል፡፡ ⚡️ በ3 አንኳር ያልሆኑ የትምህርት ዓይነቶች ከ50% በታች ውጤት ያመጣ ተማሪ አማካይ ውጤት 55% ካገኘ ወደ ቀጣቀዩ ይዛወራል፡፡ ⚡️ በአንኳር የትምህርት አይነቶች 50% እና በላይ #ያላመጣ ተማሪ ወደ ቀጣዩ ክፍል አይዛወርም፡፡ [ ምስሉን ይመልከቱ ‼️] ➡️መመሪያው ከዚህ ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል የተባለ ሲሆን ትምህርት ሚኒስቴር መመሪያው ተግባራዊ መደረግ የሚጀምርበትን ወር እና ቀን ለጊዜው አልተገለፀም።
Show all...
👍 1