en
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Open in Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Show more
1 160
Subscribers
-124 hours
+27 days
-130 days
Posts Archive
አላሁ አክበር!!!🔥 አላሁ አክበር!!!🔥 አላሁ አክበር!!!🔥 አልሀምዱሊላህ! ምስጋና የምንሰጠው ለሰጠን የአለማቱ ጌታ የተገባ ይሁን!!! ምርጥ የአሏህ ባሮች 100 ብር (pre engineerin
+3
አላሁ አክበር!!!🔥 አላሁ አክበር!!!🔥 አላሁ አክበር!!!🔥 አልሀምዱሊላህ! ምስጋና የምንሰጠው ለሰጠን የአለማቱ ጌታ የተገባ ይሁን!!! ምርጥ የአሏህ ባሮች 100 ብር (pre engineering) + 100 ብር + 400 ብር (ማኔጅመንት) + 50 ብር ገቢ አድርገዋል! አላህ በዚህች ቀን በሰጣችሁት ከጀሀነም እሳት ነጃ ይበላችሁ፣ የቲምን የረዳ ከነብያችን  ጋር የተጎራበተ ነውና አሏህ በጀነት ከሳቸው ጉርብትናን ይወፍቃችሁ!!! 🤲አሚን ያረበል አለሚን🤲 ቀጣይ አመት ረመዷን ለመድረሳችን ምንም ዋስትና የለንምና ይህችን ምናልባትም የመጨረሻዋን ለሊት ባማረ ኸይር ሾል ያሸበረቀች እናደርጋት ዘንድ ጥሪያችን ነው!  ያ ጀማዓ እኛ ለወንድም እህቶቻችን ዱዓ ስናደርግ መላኢኮች ደግሞ ''አሚን ላንተም/ላንቺም " ይላሉና ለይል ስንቆም በዱዓ እናስባቸው! 📌ዛሬ ለይሉ 29ኛ ነው! በኸይር ሾል እንበረታ!! አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን

🔥ተክቢር! አሏሁ አክበር!!! 🔥ተክቢር! አሏሁ አክበር!!! 🔥ተክቢር! አሏሁ አክበር!!! የቲሞችን እና መሳኪንን ለማስደሰት እና ዒድን ከትካዜ ወጥተው እንዲያሳልፉ በማሰብ በጀመርነው ሰደቃ ሁሉ
🔥ተክቢር! አሏሁ አክበር!!! 🔥ተክቢር! አሏሁ አክበር!!! 🔥ተክቢር! አሏሁ አክበር!!! የቲሞችን እና መሳኪንን ለማስደሰት እና ዒድን ከትካዜ ወጥተው እንዲያሳልፉ በማሰብ በጀመርነው ሰደቃ ሁሉም አሏህ ባገራለት ልክ እየተሳተፈ ይገኛል። "እኔስ ለምን እቀራለሁ" በማለት አንድ ወንድማችን 1,400 ብር አስገብቷል ያጀምዐ!!! አሏሁ አክበር!!! አሻሽለን ያስቀመጥነው ሪከርዳችን ደግሞ ይህን ይመስላል ፡ 🥇10,000 ብር 🥈7000 ብር 🥉 5500 ብር 4ኛ 5000 ብር 🏅 5ኛ 2500 ብር 🏅 6ኛ 1550 ብር 🏅 7ኛ 1500 ብር 🏅 8ኛ 1400 ብር 🏅 9ኛ 1000 ብር 🏅 አላሁ አክበር⚡️ ! አላሁ አክበር ⚡️! አላሁ አክበር⚡️ ! በመጀመሪያ ሁሉን ያስቻለውን ጌታችንን አላህ እናመሰግናለን! አልሀምዱሊላሂ ረቢል ዓለሚን! በመቀጠል ደግሞ ለ ሰደቃ ጥሪያችን መልካም ምላሽ የሰጣችሁ እህት ወንድሞችን ጀዛኩሙላሁ ኸይረል ጀዛእ እንላለን! 📌 እስካሁን በተለያዩ ምክንያቶች ሰደቃችሁን ያላስገባችሁ ወይም ደግሞ ድጋሜ ማስገባት  እንዲሁም በየትኛውንም ደረጃ ያለን ሪከርዳችንን ማደስ የምትሹ እህቶች እና ወንድሞች ፣ እስከ ነገ ጠዋት ድረስ የኸይር ጥሪው በር ክፍት ነው!! {ያ ለአላህ መልካም ብድርን የሚያበድር ለእርሱም (አላህ) የሚያነባብርለት ሰው ማነው? ለእርሱም መልካም ምንዳ አልለው፡፡} (ቁርአን 57፡11) አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !

አላሁ አክበር 🔥! ወሊላሂል ሐምድ🔥 !! አላሁ አክበር 🔥! ወሊላሂል ሐምድ 🔥!! ሰደቃው እንደቀጠለ ነው! ኸይር ፈላጊ እህት "አደራ አደራ በዱአ አትርሱኝ" ትላለች 100 ብር ካስገባች በኋላ
አላሁ አክበር 🔥! ወሊላሂል ሐምድ🔥 !! አላሁ አክበር 🔥! ወሊላሂል ሐምድ 🔥!! ሰደቃው እንደቀጠለ ነው! ኸይር ፈላጊ እህት "አደራ አደራ በዱአ አትርሱኝ" ትላለች 100 ብር ካስገባች በኋላ። አሏህ በልብሽ የሻትሽውን ላንቺ ኸይር ከሆነ ይወፍቅሽ ፣ ከክፉ ሁሉ ያርቅሽ ፣ በመጨረሻም በጀነት ያበሽርሽ🤲 ያ ሙተሰዲቂን አላህ ኸይር ስራችሁን ይቀበል ! የመልካም ስራችሁን ምንዳ በብዙ እጥፍ ተባዝታ አግኟት! ጀነቱንም ያውርሳችሁ!! በዚያም የነብያችን ሰ.ዐ.ወ ጎረቤት ያርጋችሁ! 🤲አሏሁመ አሚን🤲 የኸይር ስራ ጥሪያችን ሊጠናቀቅ ይህች ለሊት ብቻ ትቀረናለች ፣ አደራ እንበርታ ፣ በተሰጠን ኒዕማ አጅርን እንሸምትበት። የምትወዱትን እስከምትለግሱ ድረስ በጎን ሥራ (ዋጋውን) አታገኙም፡፡ ከምንም ነገር ብትለግሱ አላህ ያውቀዋል፡፡ (ቁርኣን 3:92) አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !

🌴ምናልባት ዛሬ የረመዳን የመጨረሻ ሌሊታችን ትሆናለች፤ ይህ ታላቅ ወር ጥሎን ሊሄድ ነው:: ግን አሁንም ሌሊቱ አላበቃም ታላቁ ነቢይ  ስራዎች የሚመዘኑት በፍፃሜያቸው ነው!Âť á‹­áˆ‹áˆ‰á˘ ምናልባት ዛሬ 29'ኛ ሌሊት ለይለተል ቀድር የምንወፈቅበት ሌሊት ትሆናላች! እንሰድቅ እንጂ የምን መቀዛቀዝ ነው??? «الدالُّ على الخيرِ كفاعلِهِ» (Whoever guides to good is like the one who does it) ለቤተሰቦቻችን: ዘመድ: ጉአአአደኛ...እናስነይት ይሄን የመሰለ አጅር የሚታፈስበት ሾል ለዛውም በዚ ሌሊት መልሶ አይገኝም 😌! 💭 Imagine This… A child smiling on Eid… because of you. A family eating peacefully… because of you. A دؚا rising to Allah… mentioning you. ምንእየተበቅን ነው ለአይታሞች፣ ምስኪኖች መደሰት ሰበብ ከመሆን በላይ ደስታ አለ እንዴ ያ ሸባብ ??? 📌ሰደቃችንን በመጨረሻው ለይል ላይ ይገኛል ... ከእውነተኞች ሁሉ እውነተኛ የሆኑት ከስሜታቸውም የማይናገሩት ረሱል () እንዲህ ብለዋል፦ "ስራዎች የሚለኩት በመጨረሻቸው ነው!" 🌼 አጀማመራችን ቢያምርም አጨራረሳችን ካላመረ ፤ ልፋታችን ከንቱ ነው! አጨራረሳችንን ከሚያሳምሩ ነገሮች ደግሞ አንዱ የየቲሞች እና ሚስኪኖችን ቀልብ በደስታ መሙላት ነው ። አላህ ያግዘንና! አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !

አላሁ አክበርርርር!! አላሁ አክበርርርር!! አላሁ አክበርርርር!! 100 ብር + 200 ብር + 50 ብር ገቢ ለሰደቃችን ገቢ ሆኗል !! አላህ ይቀበላችሁ !! ✨ አሁን ላይ ሰደቃችን 54, 600 ብር
+2
አላሁ አክበርርርር!! አላሁ አክበርርርር!! አላሁ አክበርርርር!! 100 ብር + 200 ብር + 50 ብር ገቢ ለሰደቃችን ገቢ ሆኗል !! አላህ ይቀበላችሁ !! ✨ አሁን ላይ ሰደቃችን 54, 600 ብር ደርሷል✨ 🌴 የ ወሩ 29ኛ ለይል .. የመጨረሻው ጎዶሎ ለይል ... ምናልባትም የዘንድሮ ረመዳን የመጨረሻ ለይል ...ተናፋቂው እንግዳችን ሳንጠግበው ተገቢውንም መስተንግዶ ሳናደርግለት ሊሰናበተን ተዘጋጅቷል ። 📌ታዲያ የመጨረሻውን ስንብት እንዴት እናድርግ ካልን ... ✨በዱዓ ችክ ማለት ፣ ደግሞ ደጋግሞ ማድረግ እና ✨ኢኽላስ የተሞላበትን ፣ለአላህ የተባለን ሰደቃ በመስጠት ✨ የየቲሞችን ራስ በማበስ እና ካለን ላይ ለሚስኪኖች በማካፈል አላህ የስራዎቻችንን መጨረሻ ያሳምር !አሚን! አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !

አላሁ አክበር 🔥!! አላሁ አክበር🔥!! አላሁ አክበርርር🔥 !! ከሰፈረ ሰላም መንደር አንድ እህታችን ሰደቃችንን በ 200 ብር ተቀላቅላለች !! " ለኔም ለቤተሰቤም ዱዓ አድርጉልኝ " ስትልም አ
አላሁ አክበር 🔥!! አላሁ አክበር🔥!! አላሁ አክበርርር🔥 !! ከሰፈረ ሰላም መንደር አንድ እህታችን ሰደቃችንን በ 200 ብር ተቀላቅላለች !! " ለኔም ለቤተሰቤም ዱዓ አድርጉልኝ " ስትልም አክላለች ። መርሃበን እህታችን .. አላህ ለቤተሰቦችሽ ረጅም እድሜ እና ዓፊያ ይስጣቸው🤲 ፤ ትምህርቱንም ገር በገር ያድርግልሽ🤲 ፤ ፆማችሁንም ሰደቃችሁንም ይቀበል🤲 ፤ ዱኒያ አኺራችሁን ያሳምር 🤲! አሚን! 📌ሰደቃችንን በመጨረሻው ለይል ላይ ይገኛል ... ከእውነተኞች ሁሉ እውነተኛ የሆኑት ከስሜታቸውም የማይናገሩት ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ "ስራዎች የሚለኩት በመጨረሻቸው ነው!" 🌼 አጀማመራችን ቢያምርም አጨራረሳችን ካላመረ ፤ ልፋታችን ከንቱ ነው! አጨራረሳችንን ከሚያሳምሩ ነገሮች ደግሞ አንዱ የየቲሞች እና ሚስኪኖችን ቀልብ በደስታ መሙላት ነው ። አላህ ያግዘንና! አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !

ከዚህ ቀደም 200 ብር አስገብቶ ለአያቶቹ ሂዳያ እንዲሰጣቸው ዱዓ እንድናደርግለት ጠይቆ የነበረዉ ወንድማችን 100 ብር ሰደቃውን ገቢ አድርጓል ። በጣም እንደተጨነቀ እና በደንብ ዱዓ እንዲደረግለትም
ከዚህ ቀደም 200 ብር አስገብቶ ለአያቶቹ ሂዳያ እንዲሰጣቸው ዱዓ  እንድናደርግለት ጠይቆ የነበረዉ ወንድማችን 100 ብር ሰደቃውን ገቢ አድርጓል ። በጣም እንደተጨነቀ እና በደንብ ዱዓ እንዲደረግለትም ጠይቋል! አላህ የአያቶቹን ልብ ለኢስላም ብርሃን ይግለጥ 🤲!! መጨረሻቸውንም በኢስላም ያድርገው 🤲!! ለወንድማችንም አላህ ሰብር እና ፅናት ይስጠው 🤲!! ከጭንቀትም ይገላግለው 🤲!! አሚን ያ ጀማዓ እኛ ለወንድማችን ዱዓ ስናደርግ መላኢኮች ደግሞ ''አሚን ላንተም " ይላሉና ለይል ስንቆም በዱዓ እናስበው! 📌ዛሬ ለይሉ 29ኛ ነው! በኸይር ሾል እንበረታ!! አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን

ሰደቃው እንደቀጠለ ነው! ኸይር ፈላጊ እህት ወንድሞቻችን እያንዳንዳቸው 50 + 200 + 200 + 2ዐዐ ብር ገቢ አድርገዋል ! በአጠቃላይ 53850 ብር ደርሰናል ! አላሁ አክበር 🔥! ወሊላሂል ሐ
+3
ሰደቃው እንደቀጠለ ነው! ኸይር ፈላጊ እህት ወንድሞቻችን እያንዳንዳቸው 50 + 200 + 200 + 2ዐዐ ብር ገቢ አድርገዋል ! በአጠቃላይ 53850 ብር ደርሰናል ! አላሁ አክበር 🔥! ወሊላሂል ሐምድ🔥 !! አላሁ አክበር 🔥! ወሊላሂል ሐምድ 🔥!! 54000 ለመሙላት 150 ብር ብቻ ነው የቀረን .. ማን የኸይር ሥራ አርበኛ ነው ይቺን የሚሞላልን ? ያ መተሰዲቂን አላህ ኸይር ስራችሁን ይቀበል ! የመልካም ስራችሁን ምንዳ በብዙ እጥፍ ተባዝታ አግኟት! ጀነቱንም ያውርሳችሁ!! የኸይር ስራ ጥሪያችን ሊገባዳድ 1 ቀን ነው የቀረን እና እንጠቀምበት። ✨የምትወዱትን እስከምትለግሱ ድረስ በጎን ሥራ (ዋጋውን) አታገኙም፡፡ ከምንም ነገር ብትለግሱ አላህ ያውቀዋል፡፡✨ (ቁርኣን 3:92) አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !

السلام عليكم ورحمت الله وبركاته 👉በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት በይበልጥ ደግሞ የኒቃብ መብት መነካት የአንዲት እህት ብቻ ሳይሆን የእምነታችን ድንበርና የሁላችንም የጋራ መብት መነካት ስለሆነ ሁሉም ይመለከተኛል በሚል እሳቤ  የተቻለውን የማድረግ ሰብዓዊ ሀላፊነት አለበት:: 👉በመሆኑም ሙስሊም ተማሪዎች መብታቸው ሲጣስ ፤ ኒቃብ የለበሱ እህቶቻችን ዩኒቨርሲቲ በር ፤ካፌ ሌላም ቦታ ላይ መብት ጥሰት ሲደርስባቸው ስናይ ባፋጣኝ ለግቢው አሚሮች እናሳውቅ:: 5 ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች ጀምዓ አሚር መሐመድ ኢድሪስ 0953439949 ኢንሻአላህ በጋራ ሙተነቂብ እህቶቻችን በሰላም ገብተው በሰላም የሚወጡበትን ከባቢ እንፈጥራለን!!!

السلام عليكم ورحمت الله وبركاته 👉በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት በይበልጥ ደግሞ የኒቃብ መብት መነካት የአንዲት እህት ብቻ ሳይሆን የእምነታችን ድንበርና የሁላችንም የጋራ መብት መነካት ስለሆነ ሁሉም ይመለከተኛል በሚል እሳቤ  የተቻለውን የማድረግ ሰብዓዊ ሀላፊነት አለበት:: 👉በመሆኑም ሙስሊም ተማሪዎች መብታቸው ሲጣስ ፤ ኒቃብ የለበሱ እህቶቻችን ዩኒቨርሲቲ በር ፤ካፌ ሌላም ቦታ ላይ መብት ጥሰት ሲደርስባቸው ስናይ ባፋጣኝ ለግቢው አሚሮች እናሳውቅ:: 5 ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች ጀምዓ አሚር መሐመድ ኢድሪስ 0953439949 -በተጨማሪ የመብት ጥሰቱ ሲደርስ ባካባቢው ሆናችሁ ማንኛውም የቀረፃችሁት photo አልያም video ካለ     👇በዚ bot ላኩልን!!!! @fivekjemaa_bot ኢንሻአላህ በጋራ ሙተነቂብ እህቶቻችን በሰላም ገብተው በሰላም የሚወጡበትን ከባቢ እንፈጥራለን!!!

ዓለም አቀፍ የኢስላሞፎብያ መከላከያ ቀን (March 15, 2026) !   በተባበሩት መንግስታት መሪነት በአለምአቀፍ ደረጃ እየተሰራጨ ያለውን ሙስሊም ጠልነት ለመግታት ያለመ ፕሮግራም በድርጅቱ አዳራሽ በየአመቱ March 15 ላይ ይካሄዳል። ከትላንት ወዲያም ቀኑ ነበርና በአዳራሹ የተገኙ ሰዎች መልዕክቶችን አስተላልፈዋል። እኛም በአሁኑ ሰዓት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊሞችን የሚያገል መመሪያ ከማውጣት ጀምሮ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚፈፅመውን በደል ታሳቢ በማድረግ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ካስተላለፉት መልዕክቶች ጥቂቱን ለማስፈር ወደድን። መልዕክቱ በቀጥታ ለዩኒቨርሲቲው የተላለፈ ይመስላልና እንደወረደ አንብቡት። መልዕክት 1:- "...አድሎአዊ ትረካዎች በስልጣን ላይ ባሉ አካላት ሲስተጋገቡ፣ ጥላቻ እንደ ተለመደ ነገር ይቆጠራል። የተዛቡ አመለካከቶች (Stereotypes) ሳይታገሉ ሲቀሩ፣ ወደ ፖሊሲነት ይጠነክራሉ። ፍርሃት ውሳኔዎችን እንዲመራ ሲፈቀድ ደግሞ ኢፍትሃዊነት ይከተላል...” ዋና ጸሐፊው አክለውም  በእያንዳንዱ ሰው፣ በሁሉም ቦታ ለሚገኝ እኩልነት፣ ሰብአዊ መብትና ክብር” አዲስ ቁርጠኝነት እንዲኖር አሳስበዋል፤ እንዲሁም እየናረ የመጣውን ሙስሊም ጠልነትና ለሙስሊሞች ያለ ክፉ አመለካከትን ማዕበል ለማጥፋት እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጥሪ አቅርበዋል። እኛም የሚከተለውን እንላለን:- በስልጣን ላይ ባሉ ሰዎች አድሏዊ ትረካ፣ በእነርሱ የተዛባ አመለካከት እና በሌሎች ፍርሐት የወጣው አድሏዊ መመሪያ የሚሻርበት ጊዜ አሁን ነው። ለዚያ ደግሞ የእኛ የተስተካከለ ግንዛቤ፤ የተቀናጀ አካሄድ እና ቁርጠኝነት ያስፈልጋል። በዚህም የተስተካከለ እና ፍትሐዊ ከባቢን ለመጪው ትውልድ የምናወርስ ይሆናል። @aaumsu

🌼السلام عليكم ورحمت الله وبركاته🌼 የቲሞችን እና መሳኪንን ለማስደሰት እና ዒድን ከትካዜ ወጥተው እንዲያሳልፉ በማሰብ በጀመርነው ሰደቃ ከእናንተ ቅን ልቦች በ 3 ቀናት ውስጥ ከ53,000 ብር በላይ ለማሰባሰብ በቅተናል! ብዙ እህት ወንድሞች ከአባ ጅፋሯ ጅማ ሀ ብለው ጀምረውልን ተመርቀው የወጡ ወንድሞች እና እህቶችም ተሳትፈው  ከ50 ብር ጀምረው እስከ 10,000 ብር ድረስ ገቢ አድርገውልናል ። አሻሽለን ያስቀመጥነው ሪከርዳችን ደግሞ ይህን ይመስላል ፡ 🥇10,000 ብር 🥈7000 ብር 🥉 5500 ብር 4ኛ 5000 ብር 🏅 5ኛ 2500 ብር 🏅 6ኛ 1550 ብር 🏅 7ኛ 1500 ብር 🏅 8ኛ 1000 ብር 🏅 አላሁ አክበር⚡️ ! አላሁ አክበር ⚡️! አላሁ አክበር⚡️ ! በመጀመሪያ ሁሉን ያስቻለውን ጌታችንን አላህ እናመሰግናለን! አልሀምዱሊላሂ ረቢል ዓለሚን! በመቀጠል ደግሞ ለ ሰደቃ ጥሪያችን መልካም ምላሽ የሰጣችሁ እህት ወንድሞችን ጀዛኩሙላሁ ኸይረል ጀዛእ እንላለን! 📌 እስካሁን በተለያዩ ምክንያቶች ሰደቃችሁን ያላስገባችሁ ወይም ደግሞ ድጋሜ ማስገባት  እንዲሁም በየትኛውንም ደረጃ ያለን ሪከርዳችንን ማደስ የምትሹ እህቶች እና ወንድሞች ፣ እስከ ነገ ጠዋት ድረስ የኸይር ጥሪው በር ክፍት ነው!! {ያ ለአላህ መልካም ብድርን የሚያበድር ለእርሱም (አላህ) የሚያነባብርለት ሰው ማነው? ለእርሱም መልካም ምንዳ አልለው፡፡} (ቁርአን 57፡11) አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !

#Ramadan28 ዘካተል ፊጥርን የሚመለከቱ ነጥቦች ~ 👉የሚስሰጡ የእህል / የምግብ አይነቶች፦ ተምር፣ ዘቢብ፣ አይቤ እንዲሁም በሃገር በአካባቢው ለቀለብነት የሚውሉ፣ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይበላሹ መቆየት የሚችሉ እንደ ስንዴ፣ ገብስ፣ ጤፍ፣ ወዘተ. ያሉ የእህል / የምግብ አይነቶች ሁሉ ይገባሉ። ምክንያቱም "ከምግብ አንድ ቁና" የሚል ሐዲሥ አለና። [አልቡኻሪይ፡ 1508] [ሙስሊም፡ 985] በዒዱ እለት መመገብ የሚችሉት አይነት ቢሆን ተመራጭ ነው። 👉 መጠኑ፦ አንድ ቁና (ሷዕ) ነው። በአራቱ ኸሊፋዎች ዘመን በዚህ መልኩ ነው ሲፈፀም የኖረው። በራስ ፈቃደኝነት ጨምሮ መስጠት ይቻላል። የሚስሰጠው መጠን በኪሎ ግራም:- በሐዲሥ የመጣው በስፍር ስለሆነ የክብደት መለኪያ ስንጠቀም እንደ እህሉ አይነት መጠኑ ይለያያል። ወደ ኪሎ ሲቀየር ዱቄት ላይ 2.5 ኪሎ አቅራቢያ ይመጣል። ይሄ የአንድ ሰው መጠን ነው። 10 ቤተሰብ ያለው ሰው 25 ኪሎ ማለት ነው። 👉ጊዜው፦ ግዴታ የሚሆነው የረመዷን ወር የመጨረሻ እለት ተጠናቆ የዒዱ ሌሊት ሲገባ ነው። ልብ በሉ! በኢስላማዊው አቆጣጠር የአንድ እለት ቀዳሚው ክፍል ቀኑ ሳይሆን ሌሊቱ ነው። 👉 ከቤተሰብ ርቃችሁ ለምትገኙ ተማሪዎች ወላጆቻችሁ ዘካተል ፊጥር የማያወጡላችሁ ከሆነና የማውጣት አቅሙ ካላችሁ ዘካተል ፊጥር ማውጣት እንዳትረሱ። 🌙  Ramadan Daily Virtue – Day 28 🤲 Give Sadaqah Tonight is the 29th night- the last odd night of the last ten. Don’t let it pass empty… Put something in your account of Akhirah. “Charity extinguishes sins just as water extinguishes fire.” Sunan al-Tirmidhi, Hadith 614,                                                                                                                                      💛 Give today. It could be Laylatul Qadr. #FiqhusiyyamiRamadan #DailyVirtue

አላሁ አክበርርርር💥 አላሁ አክበርርርር💥 አላሁ አክበርርርር💥 መተሰዲቆች አሁንም ቀጥለዋል ! 200 ብር + 200 ብር ገቢ ሆኗል !! ተቀበለላሁ ሚንኩም !! ✨ሰደቃችን 53,200 ብር ደርሷል✨
+1
አላሁ አክበርርርር💥 አላሁ አክበርርርር💥 አላሁ አክበርርርር💥 መተሰዲቆች አሁንም ቀጥለዋል ! 200 ብር + 200 ብር ገቢ ሆኗል !! ተቀበለላሁ ሚንኩም !! ✨ሰደቃችን 53,200 ብር ደርሷል✨ ሊገባደድ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት ለቀሩት የተከበረው እንግዳችን ምርጥ ሽኝት እናድርግ !! 📌 ስንት እህት ወንድሞቻችን ይሄን ረመዳን ሳያገኙ ቀርተዋል ?? እኛስ ቀጣዩን መወፈቃችንን ምን ያህል እርግጠኞች ነን? በእጃችን ባለው እንጠቀም !! የየቲሞችን እና ሚስኪኖችን ቤት ለዒድ በፌሽታ እንሙላ !! አላህ በተከበረ ቃሉ እንዲህ ይለናል :- {አንዳችሁንም ሞት ሳይመጣውና ጌታዬ ሆይ! እንድመጸውትና ከደጋጐቹም ሰዎች እንድኾን ወደ ጥቂት ጊዜ ብታቆየኝ ኖሮ እመኛለሁ ከማለቱ በፊት ከሰጠናችሁ ሲሳይ ለግሱ፡፡} ( ቁርአን 63፡10) አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !

🔥ከ ሙተነቂቦች መንደር ~ 2🔥 ኒቃብ ተከልክሏል በተባለው ወቅት የሁለተኛ አመት ተማሪ ነበርኩ። ኒቃብ ከለበስኩ ወራትን አስቆጥሬ ነበር። ፈተና ላይ ስለነበርኩና ወደ ውጭ ወጣ ገባ ስል ስላልነበር ዋናው ግቢ ላይና FBE በር ላይ የሚከሰቱ ነገራቶች በቻናል ላይ ከማንበብ ባለፈ ስሜቱን ብዙም አልተጋራሁም፤ እውነት ነው ብዬ ከውስጤ አላመንኩም ነበር ልበለው። አንድ ቀን ወደ ካፌ እየሄድኩ እያለ አንድ ወንበር ላይ ቁጭ ብሎ የሚገባውና የሚወጣውን ሲቆጣጠር የነበረ አመራር ይመስለኛል ጠራኝ። ወደሱ ጠጋ አልኩኝ። ይሄ አለባበስ እንደማይፈቀድ አላወቅሽም ነው? አለኝ። ያው እኔም ነገሩ ላይ ከአሚሮቻችን ጋር ውይይት ላይ እንደሆነ ስላነበብኩኝ ጥያቄ አቅርበናል፣ ውይይት ላይ ያለ ጉዳይ እንደሆነ ለማስረዳት ነገር ሞከርኩ። የሱ ምላሽ «አይ በፍጹም! ይሄኮ መመሪያ የጸደቀ ነው እስካሁንም ወደ ትግበራ ስላልገባ እንጂ መመሪያው ከወጣ ቆይቷል!» አለኝ። ምንም አላልኩም ዝም ነበር ያልኩት። ከአነጋገሩ ዩኒቨርሲቲው እንደዚህ አይነት አለባበስ ቀድሞውኑ አይቀበልም፤ ወይ አንቺ ወይ ኒቃቡ ከግቢው ውልቅ ማለት አለባቹ በሚል ነበር የተረዳሁት። ከዚያም ቀጠል አድርጎ እነሱ ከደግነታችን የመነጨ ነው ብለው የሚያስቡትን ንግግር አስከተለ። « ለዛሬ ፈቅጄልሻለሁ ግቢ፤ ከነገ ጀምሮ ግን ይህንን ለብሰሽ ካፌም ብቻ ሳይሆን ግቢ ውስጥ እንዳትንቀሳቀሺ» አለኝ። ምንም አላልኩም ዝም እንዳልኩኝ ወደ ካፌ ገባሁ! ምግቡን ጠረቤዛ ላይ አድርጌ እምባዬን ማስቆም አልቻልኩም። ከረሜላውን እንደተነጠቀ ህጻን አለቀስኩ። በዛ ሰአት ሳስብ የነበረው መብቴ ነው የሚለውን አልነበረም። ግቢው ውስጥ በህግ ደረጃ ግልጽ እስከሚወጣ እኔን ለግቢው እንደማልመጥን እንደሚታሰብ እና ኒቃቤን ማጣት ምን ያህል እንደሚከብደኝ ነበር ሳስብ የነበረው። ነፍስያዬንና ሌሎች ተጽዕኖዎች ታግዬ ለበስኩ ያልኩትን ኒቃብ ነጥቆ ያወለቀብኝ ያህል ነበር የተሰማኝ ሃቂቃ። የያዝኩትም ምግብ የሆነ ሰው ስለፈቀደልኝ ያገኘሁት እንጂ የሚገባኝ እንዳልሆነ እንደሚታሰብ ማሰቡ ራሱ ያስከፋል!! ዋናው ግቢ ላይ የተደረጉ ነገራቶች even እንደተከለከሉ ራሱ ሰምቼ ነበር እኮ!! ግን ቦታው ላይ ስሆን ነበር በጣም የተሰማኝ!! ህግ እንደጣስን እንዲሰማን ለማድረግ ሁሉም ከጥበቃ ጀምሮ፣ ጽዳት ሰራተኞች፣ የግቢው ማህበረሰብ፣ መምህራኖች፣ ተማሪዎች የራሱ ድርሻ መወጣት ይፈልጋል። አንዷ በአይኗ ከመሬት አንስታ ስትጥልሽ ሌላው ደግሞ በበር በገባሁና በወጣሁ ቁጥር ምክንያት እየፈለገ ያጉረመርማል። አንዷ ተማሪ ትመጣና ቆይ አሁን ከኒቃብሽና ከትምህርትሽ ብትባዪ የቱን ትመርጪያለሽ ትላለች። እህህህህ ለምን እመርጣለሁ ቆይ?? ሰው ከእምነትህ እና ከትምህርትህ ምረጥ ይባላል እንዴ?? ይሄ የሁሉም ኒቃቢ እህቶች ታሪክ ነው። መብቷ ተጥሶ ሳለ እሷን ህገ ወጥ ያደርጓታል!! የሁሉንም ተግባር ህጋዊ ያደረገላቸው ግን ያ አንቀጽ ነው!! አላህ መመሪያቸውን ይሻርልን፣ ሸራቸውንም ይመልስልንና እኛስ አላህ አይተወንም!! በዚህ ነገር ውስጥ ግን ከሒጃብ ጋር ያለኝ ትስስር እየጨመረ፣ ለኒቃቤ ያለኝ ዋጋ እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ አልሄደም፤ ወልሃምዱሊላህ!! @aaumsu

አላሁ አክበር !! አላሁ አክበር !! አላሁ አክበር !! ከ ባዮሜዲካል አንዲት እህት 300 ብር ፤ ሌላኛዋ እህታችን ከሶፍትዌር 2ዐዐ ብር ለሰደቃችን ገቢ አድርገዋል !! ዱዓ አድርጉልንም ብለዋል!
+1
አላሁ አክበር !! አላሁ አክበር !! አላሁ አክበር !! ከ ባዮሜዲካል አንዲት እህት 300 ብር ፤ ሌላኛዋ እህታችን ከሶፍትዌር 2ዐዐ ብር ለሰደቃችን ገቢ አድርገዋል !! ዱዓ አድርጉልንም ብለዋል! አላህ ሰደቃችሁን ይቀበል ! ያሰባችሁትንም ያሳካላችሁ! ሰደቃችንም  52800ብር ደርሷል ! አላሁ አክበር ወሊላሂል ሓምድ !! 🌴 ጉዟችን ረጅም ናት ፤ አላማችንም ሰፊ ! ሁላችንም የአቅማችንን ለሰደቃው እናበርክት!! {የመጸወቱ ወንዶችና፣ የመጸወቱ ሴቶች፣ ለአላህም መልካምን ብድር ያበደሩ ለእነርሱ መልካም ምንዳ አልላቸው፡፡} ( ቁርኣን 57:18) አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !

📌ዛሬ ትንሽ መቀዛቀዝ አለ! የትላንቱ ድካም ነው መሰል ጠፍታችሁብናል  .. ነቃ እንበል እንጂ ያ ጀማዓ ! ✨ግባችን 100,000 ብር መሆኑን አንዘንጋ!✨ ነቢያችን ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም የየቲሞችን ልሾ ማበስ ያለዉን ፈድል ሲገልፁ እንዲህ ይሉናል :- “እኔና የቲምን ‘ወላጁ በህፃንነቱ የሞተበትን’ ልጅ ተንከባካቢ በጀነት ውስጥ እንዲህ ነን✌️። በማለት ጠቋሚ እና መካከለኛ ጣታቸውን አሳዩ።” አላህ! አላህ! ስማቸውን አንስተን ሰለዋት ከማውረድ ፤ ሁሌም እሳቸውን  ከመናፈቅ አልፈን ፤ በአኺራ የሁለቱ ጣቶችን ያህል የሚያቀራርበን ሾል ነው ለየቲሞች መሰደቅ ... አላህ ይወፍቀን 🤲 ነቢያችንንም (ሰ.ዐ.ወ) ከሚጎራበቱት ያድርገን🤲 ነፍስያችንን አሸንፈን account ላይ ያለችንን ረመዳአናችን ስይገባደድብን እንሰድቃት አላህ ዘንድ ያለው የላይኛው ካዝና በላጭ ነው!!!!!! ሀያ ያ ጀመዓ ! ዳይ ወደ ሰደቃ ! አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !

"አላህ የአያቴን ልብ ለእስልምና እንዲከፍትላት ፣ ለኔም ንጹህ የሆነችን ልብ እንዲሰጠኝ ዱዓ አርጉልኝ " ይህን ያለችው 300 ብር ለየቲሞች የሰደቀች እንስት ናት! ቀልብ ከተስተካከለ ሁሉም ሰዉነት
"አላህ የአያቴን ልብ ለእስልምና እንዲከፍትላት ፣ ለኔም ንጹህ የሆነችን ልብ እንዲሰጠኝ ዱዓ አርጉልኝ " ይህን ያለችው 300 ብር ለየቲሞች የሰደቀች እንስት ናት! ቀልብ ከተስተካከለ ሁሉም ሰዉነት ይስተካከላል እና አላህ  ንፁህ የሆነችን ፣ ለተውበት የምትቸኩልን ቀልብ ይወፍቃት! አያቷንም አላህ ልባቸውን ለኢስላም ብርሃን ይክፈትላቸው! ኻቲማቸውንም ያሳምር!! ረሱል () እንዲህ ብለዋል፦ ከናንተ አንዳችሁ በሀላል ካገኝው ገንዘቡ አንዲትን ቴምር ብትሆን ሰደቃ አይሰጥም፤ አላህ በቀኝ እጁ ተቀብሎ የሚይዛትና ልክ አንዳችሁ የፈረሱን ወይም የግመሉን ግልገል ተንከባክቦ እንደሚያሳድጋት ትልቅ ወይም ተራራ እስከሚያክል ድረስ ተንከባክቦ የሚያሳድገው ቢሆን እንጂ። (ሙስሊም ዘግበውታል) 📌 ለሰደቃ እንቻኮል!! 📌 ለውዱን እንግዳችን ያማረ ሽኝትን እናድርግ አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !

ተክቢር !!አላሁ አክበርርር🔥! ተክቢር !!አላሁ አክበርርር🔥! ተክቢር !!አላሁ አክበርርር🔥! 52,000 ለመሙላት ቀርታን የነበረችውን 50 ብር አንድ እህት/ወንድማችን ሞልተውልናል !! አላህ
ተክቢር !!አላሁ አክበርርር🔥! ተክቢር !!አላሁ አክበርርር🔥! ተክቢር !!አላሁ አክበርርር🔥! 52,000 ለመሙላት ቀርታን የነበረችውን 50 ብር አንድ እህት/ወንድማችን ሞልተውልናል !! አላህ ይቀበላቸው! እንዲህ ለኸይር ስራ ስትጠሩ ለምላሽ የምትቸኩሉ የእናንተን አይነት ያብዛልን !! በዱዓ ሁላችንም እናስባቸው !! ✨የተቀረነውም ለኸይር ስራ እንሽቀዳደም✨ አካውንት፡ 1000626274718 (Abdulfetah Y. / Umer A. / Hayat F.) ዲፓርትመንታችሁን እና ያስገባችሁበትን Screenshot በ @fivekjemaa_bot ላኩልን !