en
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Open in Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Show more
1 157
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-130 days
Posts Archive
የዒልሙ መሐንዲስ - ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ ! ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ በ1945 አ.ል በዋድላ ደላንታ ተወለዱ ። የተወለዱባት መንደር ስያሜ አቃዱር ይሰኝ ነበር ። ከአባታቸው አህመድ ሸይኽ ሙስጠፋ እና ከእናታቸው ተዋበች አጋሽ ነበር የተገኙት ። ገና በለጋ እድሜያቸው በአካባቢያቸው በነበረ የመኖሪያ እና የእርሻ ቦታ እጥረት ምክንያትና የኑሮው ነገር ስላልገራላቸው ከመንደሩ ለቀው እንዲወጡ ግድ ሆነባቸው ። ከመንደራቸው የመኮብለል ጉዳይ ለእናታቸው ወ/ሮ ተዋበች አጋሽ እንዲህ በቀላል የሚታይ አልነበረም ። ከባለቤታቸው ጋር እስከመለያየት አደረሳቸው ። የኑሮ መላ ያስኮበለላቸው የሸይኽ ሰዒድ አባት ፣ ታላቅ ወንድምና አጎታቸው አካባቢውን ለቀው ወደመተከል ያቀናሉ ። ሸይኽ ሰዒድ ግን ከእናታቸው ጋር በመንደራቸው ጸኑ ። አባታቸው ለደረስነት እንዲሁም ልጃቸው በኢልሙ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ልዩ ፍላጎት ነበራቸው ። በርሳቸው ግፊትና ተፅዕኖ ሸይኽ ሰዒድ የደረስነት ህይወት ጀመሩ ። መሰረታዊውን የፊቅህን ስርዓተ እውቀት ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ቦረና ተጉዘው ለ3 ዓመታት ያክል የነህዉንና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነውም ቢሆን የተፍሲር ቂርዓታቸውን ቀጠሉ ። በሀገራችን ኢትዮጵያ የሚሰጡ ኪታቦችን ካጠናቀቁ ቡሀላ ወደ አዲስ አበባ መጡ ። እዚህም የመጡበት ምክንያት ከዚህ ሀገር ወተው ወደ አረብ ሀገራት ተጉዘው የሀዲስ እንዲሁም ሌሎች ቂርአቶችን ለመቅራት አስበው ነበር ። በወቅቱም ሀጂ ሙሐመድ ራፊዕ ከሳውድ አረቢያ ተመልሰው አንዋር መስጂድ ላይ ደረሶችን ሲያቀሩ የሚያቀሩበት ነበርና ያገኟቸዋል ። ሃሳባቸው ከሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ ዘንድ ለመቅራት ነበር ። ቆይተው ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ ወደትውልድ መንደራቸው ይሄዱ ነበርና አልተሳካም ። ሸይኽ ሰዒድ ግን ቂርዓታቸውን ከሐጂ ሙሐመድ ወሌ ዘንድ ይቀጥላሉ ። ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ እስኪመለሱ ድረስ . . .! ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕም የጥቅምት ማገባደጃ ላይ ወደአዲስ አበባ ይመለሳሉ ። ሸይኽ ሰዒድ ወትሮም ጊዜያቸውን በአግባቡ የሚጠቀሙ ነበሩ ። ኩቱቡ ሲታን እሳቸው ጋር ቀርተው ማጠናቀቅ ቻሉ ። በማለዳው ክፍለ ጊዜ ደግሞ ከሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ዘንድ ተፍሲርን ሙራጀዓ ሲያደርጉ ይቆያሉ ። አዲስ አበባ የነበራቸውን ቆይታ እንደጨረሱ ወደ ትውልድ ስፍራቸው ሄደው የማስቀራት ፍላጎት የነበራቸው ቢሆንም እዚሁ አንዋር መስጂድ የነበሩት 3 ታላላቅ ዑለሞች ፍቃደኛ ሳይሆኑ ይቀራሉ ።  ምክንያታቸው ደግሞ በወቅቱ የነበረው የደረሳ መጠን መብዛት ሸይኽ ሰዒድ እዚህ መቆየታቸውን ግድ ይል ነበር ። ትዕዛዙን ተቀብለው ሸይኽ ሰዒድ ዒልምን ማቅራት ጀመሩ ። በቆይታቸው የማረፍያ ስፍራና የእለት ጉርስ ማግኘት በጣም አስቸጋሪ ሆኖባቸው እንደነበር ይናገራሉ ። በዚያ ወቅትም ቀኑን ወሎ ሰፈር ድረስ በእግራቸው በመጓዝ ልጆችን ያቀራሉ ። እዚያው ቤትም ምሽቱን በጥበቃነት ማገልገል ይጀምራሉ ። በቀጣዩ የህይወት ምዕራፋቸው ለ15 አመታት አንዋር መስጂድ ዒልምን ሲያቀሩ ቆይተዋል ። ሸይኽ ሰዒድ በእድሜ ዘመናቸው በደማቁ ከሚወሱበት አበርክቷቸው መሐል በኢትዮጵያ ታሪክ  የመጀመሪያውን የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ማህበር ወይም በተለምዶ ሙነዘማን ማቋቋም ነበር ። እጅግ ብዙ ጥረትና ልፋት የታየበት ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች መብታቸው የሚጠይቁበትና ማንነታቸውን የሚያስከብሩበት ተቋም መሆን የቻለ 165 ያህል ቅርንጫፍ ማዕከላትን ማቋቋም የቻለ ነበር ። በጊዜው መንግስት ለተቋሙ ሕጋዊ እውቅናና ፈቃድ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም የኋላ ኋላ ስጋት ይሆናል በሚል አደረጃጀቱ እንዲፈርስ የተለያዩ ስራዎች ተሰርተዋል ። ሸይኽ ሰኢድ አህመድ ሙስጠፋ በዚህ ሁኔታ ላይም ሆነው በ 5 መስጂዶች ላይ ተፍሲርን በማቅራት ሙሉ በሙሉ አጠናቀው የነበረ ሲሆን በኒ መስጂድ ፣ አንዋር መስጂድ ፣ ሀሺም መስጂድ ይገኙበታል ። በዚህ አጋጣሚ ኡምራ የማድረግ እድል ያገኙት ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ ዑምራቸውን ፈጽመው ከ15 ቀናት በኋላ የመመለስ እቅድ ነበራቸው ። ያ ግን በተለያየ ምክንያት ሊሰምር አልቻለም ። እርሳቸው ሄደው ቀናት ባስቀጠሩበት አጋጣሚ አገር ውስጥ ነገሮች ተቀያይረዋል ። ታዲያ በጊዜው አንድ ሁነት ይከሰትና ነገሮች መልካቸውን ይቀይራሉ ። የወቅቱ መንግስት በአንዋር መስጂድ እጅግ ብዙ ወጣቶችን ህይወት በመቅጠፍ እንዲሁም ሙስሊሞች ተለይተው ድብደባ እንደተፈጸማባቸው  ፣ የተለያዩ መሻዒኾች እየታሰሩ የግድያ ፍርድም እየተፈረደባቸው እንደሆነና እሳቸውም በጥብቅ እየተፈለጉ እንደሆኑ ይሰማሉ ። ሸይኽ ሰዒድም በነዚህና መሰል ምክንያቶች ሳዑዲ አረቢያ ይሰነብታሉ ። በዚህ ሁኔታ ቀናት ቀናትን እየተካ ወራትም ወራትን እየተኩ አመታት ተቆጠሩ ። ሸይኽ ሰዒድ የመኖሪያ ፍቃድ ስላልነበራቸው ከአደባባይ ተሸሽገው ከማንም ጋር ሳይገናኙ ለ 2 አመት ያክል ከቆዩ ቡሀላ ሳዑዲ አረቢያ ይኖሩ የነበሩት ሸይኽ አህመድ ሀዲ ሸይኽ ሰኢድን አፈላልገው ያገኟቸዋል ። ሸይኽ አህመድ ያላቸውን አቅም ያውቁ ስለነበር  ወደ አራት የሚጠጉ የዓቂዳ ኪታቦችን እንዲያቀሩና የድምፃቸውም ቅጂ ወደ ኢትዮጵያ በካሴት መልክ ተዘጋጅቶ እንዲሰራጭ ያማክሯቸዋል ። ሸይኽ ሰዒድም በጣም ደስተኛ እንደሆኑ በመናገር ስራቸውን ይጀምራሉ ። ቆይቶ ሙሉ ለሙሉ ስራቸውን በማጠናቀቅ ሸይኽ አህመድ ሙአሰተል ሀረመይን ከሚባል ድርጅት ጋር የነበራቸውን ትውውቅ ተጠቅመው የሸይኽ ሰዒድ አህመድ ድምፅ ተቀድቶ በካሴት መልክ ወደ ኢትዮጵያ እንዲሰራጭ ሆነ ። ስራቸው ተወዳጅነት ማትረፍ የቻለና በብዙዎች ዘንድ የሚወሳ መሆን ችሏል ። ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖች ጭምር ወደው ያደምጡት እንደነበር ይወሳል ። ሸይኽ ሰዒድ ሌላኛው ግዙፍ እድል ብለው የሚያነሱት አንጋፋው አፍሪካ ቲቪ ምስረታውን ያደርጋል ። እሳቸውም በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪው በሆነው ኢስላማዊ የሳተላይት የቴሌቭዥን ጣቢያ የቁርዓን ተፍሲርን ማስማር ጀመሩ ። የብዙዎች ዘንድ ተወዳጅ እና ተናፋቂ ሆኖ የብዙዎችን ልብ ከቁርዓን ጋር አዛምዷል ። በዚህ ሁሉ ውስጥ የ9 ልጆች አባት የሆኑት ሸይኽ ሰዒድ ቤተሰባቸውን አልዘነጉም ነበር ። ከቅርብ ዓመታት በፊት ለ23 ዓመታት ርቀዋት ወደቆዩት አገራቸው በመመለስ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ማገልገላቸውን ቀጥለዋል ። በአፍሪካ ቲቪ አል ፈታዋን ጨምሮ የተለያዩ ሸሪዓዊ መሰናዶዎች እያቀረቡ ያሉ ሲሆን አፍንጮ በር የሚገኘው የአቅሷ መስጂድ ዒማምና ኸጢብ በመሆን ከዚያን ባሻገር በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት የዑለሞች ምክር ቤት አባል በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ ። አላህ ( ሱ.ወ ) ከመልካም አበርክቷቸው ጋር አጽንቶ በረዥም እድሜ በበረታ አፍያ ያቆያቸው ። #አፍሪካ_ቲቪ #የህይወት_ጎዳና

Tutorial Session for Engineering Students! 🌟 As-salamu Alaikum wa Rahmatullahi wa Barakatuh 🌟 Dear brothers and sisters taking  Engineering Drawing course, 😊 The 5 Kilo Muslim Students’ Jem’a Academic Sector is delighted to announce a special tutorial session designed for all engineering students taking Engineering Drawing! This session is packed with intense practice to help you excel in your final exam, In shaa Allah. 🗓 Date: Tomorrow, Thursday, January 8 🕙 Time: 10:00 LT 📍 Venue: Will be announced. 🖊 Reminder: Don’t forget your drawing materials, and please arrive on time! ✨ Let’s strengthen our understanding and achieve success together, In shaa Allah! 📌 Don’t miss this opportunity! 📌 Invite your classmates too! 🔗 Stay updated via our Telegram channel: 👉 t.me/fivekjemaa

💥ለመላው የክርስቲያን እምነት ተከታይ    ወገኖቻችን በሙሉ 💥 ወደተፈጠራችሁበት እስልምና ኑ

ከበአሉ ጋር ተያይዞ በዩኒቨርሲቲዎች የሚዘጋጅ ምግብ ብይን - ባለፈው አመት ኡስታዝ አብዱናሲር እዚሁ ቻናል ላይ የፃፉት ====================== ቢስሚላህ! ብዙ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ዉስጥ በካፊሮች በአላት ስለሚዘጋጁ ምግቦች ውዝግቦች ይስተዋላሉ። ነገ በአላቸው እንደመሆኑ ትንሽ ልበል። የካህዲያንን በአላት ማክበርም ሆነ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ማስተላለፍ በጥብቁ የተከለከለ ነው። በዚያ እለት የሚያዘጋጁትን ምግብ መመገብም በተመሳሳይ ይከለከላል።   ነገር ግን ቤታቸው ሄዶ መካፈልና ገዝቶ መጠቀም የተለያዩ ናቸው። ብዙ ጊዜ ለሚፈጠሩ ዉዝግቦችም ምክኒያቱ በሁለቱ መካከል ያለዉን ልዩነት አለመረዳት ነው። በዩኒቨርሲቲ ካፌ የሚዘጋጀው ምግብ ሁኔታ በምሳሌ ብንገልጸው ሁልጊዜ የምትጠቀሙበት የካፊሮች ካፌ ካለ በነሱ በአል ቀን እዛ ሄዶ መጠቀም ማለት እንጂ ብዙዎች እንደሚሉት  የነሱን በአል ማክበር ማለት አይደለም። ሁኔታዉን በትክክል ብናስተዉል የሆነ ካፊር ለበአሉ ያዘጋጀልህ ሳይሆን በወጪ መጋራት (cost sharing) ሁልጊዜ የምትመገብበት ቦታ ሄደህ አገልግሎት እያገኘህ ነው። አማራጭ ያለው ሰው ራሱን ከዚህ ነገር ቢያርቅ ለጥንቃቄው ጥሩ ነው። ነገር ግን ሃራም ማለት አይቻልም። ይህን ጉዳይ ቀጥሎ ለሳዑዲ ቋሚ የፈታዋ ኮሚቴ(ሸይኽ ፈውዛንን ጨምሮ) ከቀረበው ጥያቄ ጋር ተመሳስሎ ስላገኘሁት ላጋራችሁ ወደድኩ። ጥያቄ፡ [በካህዲያን በአላት ቀን በተለምዶው የምንጠቀምበት ምግብ ቤት ዉስጥ መመገብ ይቻላልን? በበአላቸው ቀን የተለየ ምግብ እንደሚያዘጋጁ ታሳቢ ይደረግ። ] መልስ፡ [ይህ ምግብ የሚበላው ከነሱ ጋር በአልን ለመጋራት ከሆነ አይቻልም። እንደዚህ ካልሆነ ግን ለምሳሌ ተገጣጥሞ (ሁልጊዜ እንደምትሄደው ማለት ነው) ከሆነ እና ከአህለል ኪታቦች እርድ ከሆነ ይፈቀዳል። ሃራም እስከሌለበት ድረስ ለምሳሌ የአሳማ ስጋ። ከአህለል ኪታቦች ዉጭ ከሆነ ግን እነሱ ከሚያርዱት እርድ መብላት የተከለከለ ነው። ምክኒያቱም አላህ (ከካህዲያን መካከል) የአህለል ኪታቦችን ምግብ ብቻ ስለፈቀደልን። እዚህ ቦታ የተፈለገው እነርሱ የሚያርዱትን ምግብ ነው። ወቢላሂ ተውፊቅ ወሰለላሁ ዐላ ነቢዪና ሙሐመዲን ወአሊሂ ወሰህቢሂ ወሰለም።] አስተውሉ፡ እዚህ ቦታ የነርሱን እርድ ሁላ ነው ያካተተው። የዩኒቨርሲቲዎቹን ሁኔታ ስንመለከት ግን ከዚህ ይበልጥ የቀለለ ነው። 💥ከባለፈው አመት በድጋሜ የተፖሰተ @aau6kilojemea

🌙 5K Muslim Developers Circle Mentorship Program 📢 Mentorship has officially started! The Messenger of Allah ﷺ said: “The best of you are those who learn and teach.” With this intention, we have launched a tech mentorship program that brings together students eager to learn and developers willing to guide — built on sincerity, discipline, and brotherhood/sisterhood. 📌 If you are a interested and have not registered yet, this is your opportunity. 🌱 If you are a Student (Mentee) You will receive: ✨ Structured learning paths (Beginner → Advanced) 👨‍🏫 One-to-one guidance from experienced developers 🗺 Clear roadmaps with quality, halal learning resources 💻 Real-world project collaboration 🔥 Skill-focused bootcamps to strengthen your abilities. Seeking knowledge is an act of worship when done with the right intention — come learn with purpose, in shā’ Allāh. 📝 Register as a Mentee(student): 👉 https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSfN8copVNh7vIWeu9nKyQK_AWUDAHGBCqYpp2iUJbwQKdPF7A/viewform 🤝 If you are a Mentor You will have the opportunity to: 👨‍🏫 Teach and guide students with wisdom and patience 📖 Share your journey and lessons in development 🤝 Help shape the next generation of developers 🌱 Earn ongoing reward through spreading beneficial knowledge Teaching beneficial knowledge is ṣadaqah jāriyah — a reward that continues even after you step away. 📝 Register as a Mentor: 👉 https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSekqywkT-WEfdKwAGwyZgR7-L3OvA4yunSKm4sDLtgPfVatbQ/viewform 🌙 Our Intention To build a community where: 🤍 Knowledge is shared sincerely 🤝 Skills are strengthened together 📚 Learning is disciplined and purposeful 🤲 Growth is for the sake of Allah Whether you seek knowledge or share it, this journey is for you. Let’s learn ,Let’s teach. ,Let’s build — with ikhlāṣ and purpose. ✨ 👉 Join our Official Telegram Channel : 🔗 https://t.me/+i0_3C3tIO_45OWFk Stay connected, receive announcements, tech related news, and community.

የኡሱሉሲታ ኮርስ ተምራቹ ያጠናቀቃችሁ እና ሰርተፊኬት ያልወሰዳቹ ወንድሞች ነገ ከመግሪብ እስከ ዒሻ አል-አቅሷ መስጂድ ወንዶች ላይብረሪ መጥታቹ መውሰድ ትችላላቹ። ከ 4ቱ የኮርስ ቀናት 3 ቀን ለተገኙ ለሁሉም ሰርተፊኬት ተዘጋጅቷል!!

💥 ደርስ ማስታወሻ ::::::::::::::::::::::: 🗣🗣አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ 👋👋👋 ✅ ኢንሻአላህ  ዛሬ (📚الشمائل محمدية وحصآئل مصطفوية (ሸማኢሉ መሐመዲያህ) የተሰኘው የሲራ እና ሀዲስን የተመለከተ ኪታብ ደርስ ይኖረናል :: 📌የቂርዐት ቦታ ፦ 4 ኪሎ የተማሪዎች መስጂድ ⏰የቂርዐት ሰዐት፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻ ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/aau4kilomsj/1932 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/+Hr-I7ertvO00ZDQ0 @fivekjemaa

🗣🗣اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎👋👋 ✅ኢንሻአላህ ዛሬ (ማክሰኞ ) የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ደርስ ይኖረናል ።  6ኪሎ እና 5ኪሎ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች በጊዜ እንገኝ ሌሎችንም በማስከተል  ቡዙ እናተርፍለን። قَالَ رَسُولُ اللَّهِ : فَضْلُ الْعَالِمِ عَلَى الْعَابِدِ كَفَضْلِ الْقَمَرِ عَلَى سَائِرِ النُّجُومِ 📚 سنن أبي داود (٣ٌ٤٥) — حديث صحيح "የእውቀት ባለቤት የሆነ ሰው አሏህን ተገዢ በሆነ ሰው ላይ ያለው ብልጫ ፤ ጨረቃ በተቀሩት ከዋክብት ላይ ያላትን ብልጫ መሣይ ነው" ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ ቦታ፡ 6ኪሎ አቅሳ መስጅድ 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/durus_at_aqsa ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934 @fivekjemaa

Aselamu aleykum werahmetu'llahi weberekatuh Due to unavoidable matters, the Technical Drawing course tutorial that was going to be given today is postponed to a date that will be announced soon. We ask a big pardon for the inconvenience we may have created. Afwen

🚫🎄The Ruling on Congratulating Non-Muslims on Their Festivals. ሙስሊም ያልሆኑ ሰዎችን በሃይማኖታዊ በዓላቶቻቸው ላይ እንኳን ደስ አለዎት፣እንኳን አደረሳችሁ ወይም እነዚህን በዓላት በሚወክሉ ምልክቶችን ለምሳሌ እንደ የገና ዛፎች ወይም በምልክታቸው ያጌጡ ኬኮችን… ማዘጋጀት አይፈቀድም! እንደ ሙስሊም ተልእኳችን እስልምናን እንዲቀበሉ መጋበዝ እንጂ በሃይማኖታቸው ላይ ማሞገስ ወይም እንኳን አደረሳቹ ማለት አይደለም። ከሰዎች ሁሉ እጅግ በጣም አዛኝ እና ለጋስ የሆኑት ነብያችን ሙሐመድም (ﷺ)፣ሰሀባዎችም ሆኑ ተከታዮቻቸው እንዲሁም አንድም የሙስሊሙ ዑለማእ እንዲህ አላደረጉም። በል ከታላላቅ ዑለማኦች እንደ ኢብኑል ቀይም ያሉ ሊቃውንት የሌላ እምነት ተከታዮችን (በሀይማኖታቸው በዓላት ወይም ሌሎች የአምልኮ ሥርዓቶች ላይ) እንኳን አደረሳችሁ ማለትና ሃይማኖታዊ ምልክቶቻቸውን በማሳየት ረገድ አቋማቸው በጣም ጥብቅ ነበር። ስለዚህ የእንኳን አደረሳችሁም ሆነ ሌሎች ማንኛውም ኢስላምን የማይወክል እንዳውም ከኢስላም አስተምህሮት የሚፃረር ተግባራቶቻቸውን የሚያወድስ ነገሮችን ከመናገርም ከመተግበርም ልንርቅና ልንጠነቀቅ ይገባል!
Yunus 10:68 قَالُواْ ٱتَّخَذَ ٱللَّهُ وَلَدࣰاۗ سُبۡحَٰنَهُۥۖ هُوَ ٱلۡغَنِيُّۖ لَهُۥ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِۚ إِنۡ عِندَكُم مِّن سُلۡطَٰنِۭ بِهَٰذَآۚ أَتَقُولُونَ عَلَى ٱللَّهِ مَا لَا تَعۡلَمُونَ They have said, "Allah has taken a son." Exalted is He; He is the [one] Free of need. To Him belongs whatever is in the heavens and whatever is in the earth. You have no authority for this [claim]. Do you say about Allāh that which you do not know? «አላህ ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡ (ከሚሉት) ጥራት ተገባው፡፡ እርሱ ተብቃቂ ነው፡፡ በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ የርሱ ነው፡፡ እናንተ ዘንድ በዚህ (በምትሉት) ምንም አስረጅ የላችሁም፡፡ በአላህ ላይ የማታውቁትን ትናገራላችሁን?
ŠAAU6kilojemea @fivekjemaa

🗣🗣اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎👋👋 ✅ኢንሻአላህ ዛሬ (ሰኞ ) የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ደርስ ይኖረናል ።  6ኪሎ እና 5ኪሎ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች በጊዜ እንገኝ ሌሎችንም በማስከተል  ቡዙ እናተርፍለን። قَالَ رَسُولُ اللَّهِ : فَضْلُ الْعَالِمِ عَلَى الْعَابِدِ كَفَضْلِ الْقَمَرِ عَلَى سَائِرِ النُّجُومِ 📚 سنن أبي داود (٣ٌ٤٥) — حديث صحيح "የእውቀት ባለቤት የሆነ ሰው አሏህን ተገዢ በሆነ ሰው ላይ ያለው ብልጫ ፤ ጨረቃ በተቀሩት ከዋክብት ላይ ያላትን ብልጫ መሣይ ነው" ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ ቦታ፡ 6ኪሎ አቅሳ መስጅድ 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/durus_at_aqsa ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934 @fivekjemaa

🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣🗣 بِسۡمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحۡمٰنِ ٱلرَّحِيۡم           اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎👋👋        🗣🗣 የማይቀርበት ሳምንታዊ የዳዕዋ ፕሮግራም !!!!! 🍀 ለቀልባችን ስንቅ ለሳምንታችን መነቂያቂያ የሆነው ተናፋቂው እና ተወዳጁ ሳምንታዊ የዳዕዋ ፕሮግራማችን እነሆ ዛሬም የሚቀጥል ይሆናል። ሾለ ደጃል ይቀጥላል 👌 ሁላችንም ከጓደኞቻችን ጋር ከመሆን በቦታው ላይ በመገኘት ተጠቃሚ እንሁን። 👉 መልዕክቱን ላልሰሙት እናሰማ!!!!!! 🕰 ሰዓት: መግሪብ-ኢሻ 🗓 ቀን: ሰኞ ታህሳስ 20/2018 🕌 ቦታ: 4ኪሎ ተማሪዎች መስጂድ Šaau4kilomsj @fivekjemaa

የ "ኢቅራዕ" ትውልድ ሆይ... የብዕሩ ክብደት ይሰማሃልን? ወንድሜ... እንዴት ነህ? እህቴስ... ሁሉ ሰላም? እንግዲህ ወደ Final የፈተና ሳምንት እየገባን ነው። እናንተ የዚህ ግቢ ምርጥ ተማሪዎች እንደሆናችሁ እናውቃለን፤ ስለዚህ ሾለ ውጤት ብዙ አንሰጋም። ግን አንድ ሀቅ እንነጋገር... እኛ እኮ ተራ ተማሪዎች አይደለንም። እኛ የዚያ የ "አንብብ" ትውልድ አካል ነን! እኛ እኮ "የአንቢያዎች ወራሽ" ነን። የአንቢያዎች ወራሽ ደግሞ ሥራው በሙሉ ጥራት ያለው ነው። "ከሰራችሁ አሳምራችሁ ሾሊ" ተብለን ታዘናለና። ስለዚህ እኛ የምናጠናው ለ "A" ብቻ አይደለም፤ የያዝነውን የነብያት ውርስ (እውቀት) አክብረን ለመያዝ፣ በዛውም በኒያችን ኢባዳን ለመሸመት መሆን አለበት። ታድያ ምንድነው  ማድረግ ያለብን? 1️⃣ ኒያህ ከፍ ይበል፦ ወንድሜ... ለራስህ ብቻ የምትኖር ከሆነ በጣም ትንሽ ነህ። ኒያህን አድስ፤ "ጌታዬ ሆይ... ይህን የምማረውን እውቀት ለልሴ መጥቀሚያ ብቻ ሳይሆን፣ ለዚህች የተከበረች ኡምማ ጋሻና መከታ እንድሆንበት አግዘኝ" ብለህ አስብ። ትልቅ አላማ ያለው ሰው፣ ትልቅ ጉልበት ያገኛል። 2️⃣ የአንቢያዎች ወራሽ ሁን፦ ወራሽ ንብረቱን አይበታትንም። ጊዜህን በአግባቡ ተጠቀም። ስልክህን እና አልባሌ ወሬዎችን ወደ ጎን አድርገህ፣ እንደ "አንቢያዎች ወራሽ" በጥልቀት እና በረጋ መንፈስ አንብብ። ጭንቀትን ለተራው ሰው ተወው፤ ላንተ የሚመጥንህ እርጋታ ነው። አላህ ያግዛችሁ! ŠAAU6kilojemea @fivekjemaa

Advice of Luqman al-Hakim to his son يَا بُنَيَّ، إِذَا امْتَلَأَتِ الْمَعِدَةُ نَامَتِ الْفِكْرَةُ وَخَرِسَتِ الْحِكْمَةُ وَقَعَدَتِ الْأَعْضَاءُ عَنِ الْعِبَادَةِ ሆድ ዕቃ በሞላች ጊዜ ማሰቢያህ ትተኛለች: ጥበብ ዲዳ ትሆናለች: ሰውነት ከኢባዳ ትቀመጣለች!!!!

ከሰለፎች አንደበት! አል‐ኢማሙ ሻፊዒይ (رحمه الله) እንዲህ ይላሉ፦ ﴿من أحب أن يفتح الله قلبه ويرزقه العلم فعليه بالخلوة وقلة الأكل وترك مخالطة السفهاء وبعض أهل العلم الذين ليس معهم إنصاف ولا أدب﴾ “አላህ ልቡን እንዲከፍትለትና እውቀትን እንዲለግሰው የሚወድ ሰው በብቸኝነት፣ ምግብ በማቅለል እንዲሁም ከቂላቂሎችና አንዳንድ ሚዛናዊነትና አደብ ከሌላቸው የእውቀት ሰዎች ጋር ከመቀላቀል በመራቅ ላይ ያተኩር አደራውን።” 📙ቡስታኑል ዓሪፊን፡ 1/53 © atwhiddcom

Tutorial Session for Engineering Students! 🌟 Aselamu Aleykum werahmetullahi waberekatuh 🌟 Dear brothers and sisters taking  Engineering Drawing course, 😊 The 5 Kilo Muslim Students’ Jema’ah Academic Sector is delighted to announce a special tutorial session designed for all engineering students taking Engineering Drawing! This session is packed with intense practice to help you excel in your final exam, In shaa Allah. 🗓 Date: Tuesday, January 6 🕙 Time: 10:15 LT 📍 Venue: Will be announced. 🖊 Reminder: Don’t forget your drawing materials, and please arrive on time! ✨ Let’s strengthen our understanding and achieve success together, In shaa Allah! 📌 Don’t miss this opportunity! 📌 Invite your classmates too! 🔗 Stay updated via our Telegram channel: 👉 t.me/fivekjemaa

«ኒዕመቱል ኢስላም».m4a53.85 MB

ልዩ ምክር ለግቢ ተማሪዎች👇👇👇👇👇 ወንጀልን እየደጋገምን በመጣን ቁጥር ውርደት ውድቀት ያመጣል : በሕይወታችን ላይ ብዙ ተፅእኖ እያያቹ ትመጣላችሁ በትምህርታቹ ላይ ምናልባት acadamy ላይ በፊት እኮ high school, elementary ላይ ጎበዝ የነበረ ተማሪ ወደ campus ሲመጣ ሰነፍ የሆነ ብዙ አለ "አእምሮው እንደልብስ ተቀይሮ አይደለም" ወንጀል አደከመው አእምሮውን, ደረጃ ይዘው ሲመጡ የነበሩ campus ሲገቡ ወደታች 👇, ቤተሰብ ለስንት ነገር ሲጠብቃቸው የነበሩ ልጆች university ላይ ውጤታቸው ባዶ ይሆናል ""ወላሂ ምንም አዲስ ነገር ተፈጥሮ አይደለም ከቤተሰብ ሲርቁ ወንጀልን ይዳፈራሉ ኢብኑ ቀዩም ረ.አ ሲናገሩ ነብዩላህ ዩሱፍ ያንን ወንጀል ሲቁአቁአሙ እሱን ወደ ወንጀል የሚገፉ ብዙ ነገራቶች ነበሩ ከነዛ ውስጥ አንዱ እንግዳ ነበሩ የማያቁት አካባቢ ነበር የሄደው ይሄ ለምን ጠቀሱት አንድ ሰው የማያውቀው አካባቢ ሲሄድ " ያ የሚከለክለው ነገር አእምሮውን የሚወቅሰው ነገር ይነሳል ማንም የሚያውቀው የለም እዛ የሚያውቀው አላህ ሱ.ወ ብቻ ነው......... ..... እኔ እዚ ካአንዱአ ጋር ተቃቅፌ ብሄድ አላህን ካልፈራሁኝ "እንዴ የከሌ ልጅ ብሎ የሚያስጠነቅቀኝ የለም "..... ሱሪ ለብሳ ሴቷ ብትሄድ : ፀጉሬን እንደፈለኩኝ አድርጌ ቆርጭኤ ብሄድ ላባቴ ይናገራል የምንለው የለም............

ከትላንቱ የዳዕዋ ፕሮግራም የተወሰደ 🛡«ወንጀል እና ቀልብ» 🎙በ ኡስታዝ አቡ ሱፍያን حفظـہ اللـہ تعـالـﮯ بِقَدْرِ الكَدِّ تُكْتَسَبُ المَعَالِي وَمَنْ طَلَبَ العُلَا سَهِرَ اللَّيَالِي وَمَنْ رَامَ العُلَا مِنْ غَيْرِ كَدٍّ أَضَاعَ العُمْرَ فِي طَلَبِ المُحَالِ تَرُومُ العِزَّ ثُمَّ تَنَامُ لَيْلًا؟ يَغُوصُ البَحْرَ مَنْ طَلَبَ اللَّآلِي 👉የሰው ልጅ ስኬቱ በልፋቱ በጥረቱ ልክ ነው, ስኬትን ከፍታን የፈለገ( በ ዲንም ሆነ በዱንያ) ለይሉን ያነጋል, ያለ ልፋት ግን ስኬትን የፈለገ የማይሆን ነገርን በመፈልግ እድሜውን ጨረሰ, ከፍታን ትፈልጋለህ ከዛ ደግሞ ለሊቱን ተኝተህ ታድራለህ? ጉዳዩ እንደዚ አይደለም ባህር ውስጥ ያሉ እንቁዎችን የፈለገ ባህር ውስጥ ሰጥሞ መግባት አለበት:: Imam al-Ghazali رحمه الله إِنَّ مَنْ طَالَتْ أَمَانِيُّهُ ثَقُلَتْ عَلَيْهِ الطَّاعَةُ وَتَأَخَّرَتْ تَوْبَتُهُ وَقَسَا قَلْبُهُ لِأَنَّهُ يُمَنِّي نَفْسَهُ بِالتَّوْبَةِ غَدًا 👉ምኞቱ የረዘመችበት የሆነ ሰው በሱ ላይ አምልኮ ይከብደዋል, ተውበቱ ይዘገኛል, ቀልቡ ይደርቃል ምክንያቱም ነገ እቶብታለው እያለ ነፍሱን ይነግራታልና:: 👆 በተለይ university ያለ ወጣት life campus ላይ ካልሆነ የት ይሆናል ስለዚህ enjoy ማድረግ ያለብኝ እዚ ነው የሚል ዱንያ: አሂ ራውን ያበላሻል "فَقَدْ خَسِرَ الدُّنْيَا وَالْآخِرَةَ"