en
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Open in Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Show more
1 158
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-130 days
Posts Archive
ለሐቅ: ለፍትሕ: ለነፃነት 2 ደቂቃ እንስጥ! "FEDERATION OF AFRICAN LAW STUDENTS!" - ተማሪዎች መብታቸውን አስመልክቶ በትምህርት ቤት ያላቸው ሁኔታ ምን ይመስላል የሚል የዳሰሳ
+2
ለሐቅ: ለፍትሕ: ለነፃነት 2 ደቂቃ እንስጥ! "FEDERATION OF AFRICAN LAW STUDENTS!" - ተማሪዎች መብታቸውን አስመልክቶ በትምህርት ቤት ያላቸው ሁኔታ ምን ይመስላል የሚል የዳሰሳ ጥናት እየሰራ ይገኛል:: ጥናቱ እንዳለቀም ለውጥ ይመጣ ዘንድ እንደሚተጋ አሳውቋል:: የተጠቀሱ ብዙ ጥያቄዎች ቢኖሩም "ዩኒቨርሲቲያችሁ የሀይማኖት ነፃነታችሁን ያከብራል?" - የሚል ጥያቄም አለው:: ስለሆነም እየደረሱብን ያሉት የሀይማኖት የመብት ጥሰቶች ለሁሉም ይደርሱ ዘንድ እውነታውን የሚገልፀውን ምርጫ ምረጡ:: በEMAIL Contact ካደረጓችሁ ዝርዝር ነገር አስቀምጡላቸው:: ለመሙላት https://forms.gle/YRjk2qqPqaNPHieX7 ይጠቀሙ:: ለእውነት ለፍትሕ ለነፃነት ... Share ይደረግ ! ! ! ©EHEMSU @aaumsu

sticker.webp0.34 KB

ትዕግስታችን እስከ መቼ ይፈተናል? ለዩኒቨርስቲያችን ሙስሊም ተማሪዎች፤ ላለፈው ሁለት ዓመታት ትልቅ ትዕግስት አሳይተናል። ሆኖም ግን፣ የእኛ በሰላማዊ መንገድ መጓዝ እንደ ፍርሃት፣ የሕግ አክባሪነታችን ደግሞ እንደ ደካማነት ተቆጥሮ ስልታዊ የሆነ ጥቃትና ንቀት እየደረሰብን ይገኛል። ትናንት ምሽት በ5 ኪሎ ግቢ በወንድሞቻችን እና በእህቶቻችን ላይ የደረሰው ድርጊት፤ ከተራዊህ ሲመለሱ በሩ ተዘግቶባቸው በብርድ አደባባይ ላይ እንዲቆዩ መደረጉ ተራ ስህተት አይደለም! ይህ በእምነታችን ላይ እየተሰነዘረ ያለ ግልጽ ንቀት ማሳያ ነው። በቅርቡ እንኳን የደረሱብንን ጥቃቶች ብንመለከት፦ 📌 እህቶቻችንን ከማንነታቸው ለመለየት ሞከሩ፤ በሰላማዊ መንገድ ታገልን! እየታገልንም እንገኛለን፤ ዓላማቸው እስካሁንም አልተሳካም፣ ወደፊትም አይሳካም! 📌 ላለፉት 5 ዓመታት አብሮን የሰራው ዩኒቨርሲቲ፤ የህብረቱን ተወካዮች እና ደብዳቤዎች እየፈረመ ሲቀበል የነበረ ዩኒቨርሲቲ፤ "ህጋዊ አይደላችሁም" በማለት ተቋሙን ለማዳከም ሞከረ፤ በዚያም የፈለጉትን ማሳካት ሳይችሉ ቀሩ! 📌 የተማሪዎችን ድምጽ ለማጥፋት በመሪዎቻችን ላይ የዲስፕሊን እርምጃ ለመውሰድ ሞከሩ፤ ይህም በሙስሊሙ ተማሪ ትዕግስትን በተላበሰ አካሄድ ያሰቡትን ሳያሳኩ ቀሩ! 📌 ከህብረቱ እና ከሙስሊም ተማሪዎች ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ቢቀርቡም፤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት እና የትምህርት ሚኒስቴር መመሪያ በጁሙዓ ቀን ትምህርት ከ5፡30 - 7፡30 እንዲቋረጥ በግልጽ እያዘዘ፣ ሆን ብለው እስከ 6፡30 በማራዘም ተማሪው በዲኑ እና በትምህርቱ መካከል እንዲዋዥቅ እያደረጉ ነው። 📌 ለረመዳን መሟላት ያለባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች የያዘውን ደብዳቤያችንን አንቀበልም በማለት ኃላፊነታቸውን ሽሽተዋል። በቃ ማለት አለብን! ትናንት ተማሪዎች በብርድ ሜዳ ላይ የወደቁት ሰላታቸውን ስለሰገዱ ብቻ ነው። ይህ ጉዳይ የአስተዳደር ጉዳይ ሳይሆን የሰብዓዊ ክብር ጉዳይ ነው። ሁሉንም ሰላማዊ እና ህጋዊ መንገዶች ተከትለናል፤ ሁሉንም ደብዳቤዎች ጽፈናል። የእስልምና እሴቶቻችን የሚያዙንን ሰላማዊነት ጠብቀናል። ነገር ግን መብታችንን አሳልፈን አንሰጥም! አቋማችን በፊትም አሁንም ግልጽ ነው። በተማሪዎቻችን ላይ ለደረሰው አካላዊና ስነ-ልቦናዊ ጉዳት የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ሙሉ ኃላፊነቱን ይወስዳል። እኛ የምንጠይቀው ችሮታ ሳይሆን በሀገሪቱ ህግ የተረጋገጠልንን መብታችንን ነው። ሁሉም ተማሪ ንቁ ሆኖ ይጠባበቅ! ቀጣዩን ሰላማዊ፣ ህጋዊ እና የተደራጀ ምላሻችንን እናሳውቃለን። መንፈሳችሁ እንዳይሰበር፣ ለትርምስም እድል እንዳትሰጡ። ጥንካሬያችን አንድነታችን እና ሰላታችን ነው። ጥያቄ አለን!! መልስም እንፈልጋለን!!! @aaumsu

#Ramadan 4 Daily Ramadan Virtue – Dua of Guidance & Character عن Ali ibn Abi Talib رضي الله عنه قال: كان رسول الله ﷺ يقول: «ا
#Ramadan 4 Daily Ramadan Virtue – Dua of Guidance & Character
عن Ali ibn Abi Talib رضي الله عنه قال: كان رسول الله ﷺ يقول: «اللَّهُمَّ اهْدِنِي لأَحْسَنِ الأَعْمَالِ وَأَحْسَنِ الأَخْلَاقِ، لَا يَهْدِي لأَحْسَنِهَا إِلَّا أَنْتَ، وَاصْرِفْ عَنِّي سَيِّئَهَا، لَا يَصْرِفُ عَنِّي سَيِّئَهَا إِلَّا أَنْتَ» رواه Sahih Muslim “O Allah, guide me to the best of actions and the best of character. None guides to the best of them except You. And turn away from me the evil of actions and character. None can turn them away from me except You.”
👉Ramadan is not only about fasting from food… It is about: * Better actions * Better manners * Better hearts We ask Allah not just to do good, but to be guided to the best good. And we admit something powerful: 👉 We cannot reach the best character without Allah. 👉 We cannot leave bad habits without Allah. This dua’ is a complete transformation request. Today’s Practice: Repeat this dua’ before Maghrib and in sujood. #DailyVirtue

#ነፋሲያ 2
Al-'Ankabut 29:69 وَٱلَّذِينَ جَٰهَدُواْ فِينَا لَنَهۡدِيَنَّهُمۡ سُبُلَنَاۚ وَإِنَّ ٱللَّهَ لَمَعَ ٱلۡمُحۡسِنِينَ እነዚያም በእኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን፡፡ አላህም በእርግጥ ከበጎ ሠሪዎች ጋር ነው፡፡
👆ባለፈው ይሄን የቁርኣን አንቀፅ ጠቅሼ አቁሜ ነበር። ከአቆምኩበት ስቀጥል ኢብኑል ቀኝም (ረሂመሁሏህ) ይህችን አያህ አስመልክቶ አልፈዋኢድ በሚሰኘው ኪታባቸው እንዲህ ይላሉ:- ጥራት ለእርሱ የተገባ የሆነው(አሏህ) ትግልን ከሂዳያ ጋር አቆራኝቶታል። በመመራት (በሂዲያቸው) የተሟሉ ሰዎች፤ በጂሃድ የበለጠ ብርቱ የሆኑት ናቸው። ከጂሃድ ሁሉ ግዴታ ያለው ጂሃድ (ትግል)፦ ከነፍስ ጋር መታገል፣ ከፍላጎት (ሐዋ) ጋር መታገል፣ ከሸይጣን ጋር መታገል ና ከዱንያ (ዓለማዊ ሕይወት) ጋር መታገል ነው። ማንም እነዚህን አራት ነገሮች ለአላህ ብሎ ከታገለ፣ አላህ ወደ ገነት የምታደርሰውን የአላህ ውዴታ ያለባትን መንገድ  ይመራዋል። እንደ መታገሉ መጠንም ሂዳያን ያገኛል፤ እንደ መተውም መጠን ከሂዳያ ይቀራል። በሀዲሰል ቁድስ አሏህ (ዓዘወጀል) እንዲህ ይላል:-
إِذَا تَقَرَّبَ عَبْدِي مِنِّي شِبْرًا تَقَرَّبْتُ مِنْهُ ذِرَاعًا، وَإِذَا تَقَرَّبَ مِنِّي ذِرَاعًا تَقَرَّبْتُ مِنْهُ بَاعًا أَوْ بُوعًا، وَإِذَا أَتَانِي يَمْشِي أَتَيْتُهُ هَرْوَلَةً ባርያዬ ወደኔ በእጅ ስንዝር ርቀት ሲቀርብ አኔ በክንድ ርቀት እቀርበዋለሁ። ወደኔ በክንድ ርቀት ሲቀርብ ደግሞ እኔ በሁለት ክንድ ርቀት እቀርበዋለሁ። ወደኔ በእርምጃ ከመጣ እኔ ወደርሱ በፍጥነት እቀርባለሁ።
ሰሂህ ሙስሊም ይሄ ያለንበት የረመዳን ወር የትግሉ ሜዳ፤ ፃም ደግሞ መሣሪያው ነው። Take one Step. Seriously this time! አላህ ከአንተ ጋር ነው። © qirat_channel_5k

ተመልከቱት ••• ለሌሎችም Share አድርጉት ! ! ! AAU በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየፈፀፈ ያለው የመብት ጥሰት እንደቀጠለ ነው!   ይህ ትላንት ማታ ከተራዊህ መልስ የተፈጠረ ክስተት ነው:: ሙስሊም ተማሪዎች ተራዊህ ሰግደው ሲመለሹ አትገቡም ተብለው ለብዙ ደቂቃዎች ብርድ ላይ እንዲቆሙ ተደርገዋል:: ፆመኛን: ግቢው መብቴን ያከብርልኛል በክብር ያስተምረኛል ብሎ አምኖ የመጣን ተማሪ: ወጣት ልጆችን አትገቡም ብሎ በር ላይ ማቆም የተማሪዎቹን መብት የሚጥስ: ሀላፊነት የጎደለው እና ለአደጋ የሚያጋልጥ ተግባር ነው:: ዩኒቨርሲቲው ለአመታት ረመዷን ሲደርስ ለተራዊህ እና ተሐጁድ በር መግቢያ እና መውጫ ሰዓት ያስተካክል ነበር:: በዘንድሮው አመት ግን ጀመዓው ለረመዷን ማሳወቂያ ይሆን ዘንድ የላከውን ደብዳቤ አልቀበልም በማለት መልሶ ነበር:: እንደተፈራውም ተማሪዎችን በር ላይ አቁሞ እስከማንገላታት የሚያደርስ በደል ይፈፀም ጀመር:: በቶሎ መስተካከል አለበት:: ሀገራችን ብዙ ሊፈቱ የሚገቡ ጉዳዮች እያሉባት ሀላፊነት የጎደላቸው ሰዎች አጀንዳ እየፈጠሩ የሕዝቡን መብት ሲሸራርፉና ችግር ሲፈጥሩ ዝም መባል የለባቸውም:: ይህ የመጀመሪያቸው አይደለም:: ጤነኛም አይመስልም:: ኒቃብን በመመሪያ ደረጃ ከልክለው ችግር ለመፍጠር ቢሞክሩም ተማሪው በትዕግስት እና በጥበብ እየጠየቀ እስካሁን አለ:: የጀመዓውን ደብዳቤ አልቀበልም ብሎ በሙስሊም ተማሪዎች እና በግቢው መካከል ክፍተት ለመፍጠር ሲሞክር በጥበብ እየተጠየቀ እስካሁን አለ:: አሁን ደግሞ ተማሪዎችን በጨለማ ከበር አቁሞ አትገቡም ማለት ምን ማለት ነው? ምንድን ነው የተፈለገበት? ምንድን ነው የፈለጉት? ሁኔታዎች ወደአልተፈለገ አቅጣጫ ከማምራታቸው በፊት መፍትሔ ይፈልጋል:: የሚመለከተው የበላይ አካልም ይስተካከል ዘንድ አስቸኳይ እርምጃ ሊወስድ ይገባል:: ኒቃብን በመመሪያ የከለከሉትን በመመሪያ ያስተካክሉ ... ለሙስሊም ተማሪዎች እውቅናን አንሰጥም ማለታቸውን አቁመው እውቅና ይስጡ ... ለረመዷን መስጠት የሚገባቸውን ክብር ሰጥተው መስጠት ያለባቸውን አገልግሎት በአግባቡ ይስጡ! Share ይደረግ! ጥያቄ አለን!! መልስም እንፈልጋለን!!! Šaaumsu @fivekjemaa

#ነፋሲያ_1 ረመዳን አላህ ባሮቹ በአመት አንዴ ወዴት እየሄዱ እንደሆን ቆም ብለው እራሳቸውን በመገምገም በተውበት ወደርሱ እዲመለሱ እና በዚህ ወር መጥፎ ልምዳቸውን በመልካም ልምዶች ተክተው እንደመለማመዱ የዋለው ትልቅ ኒዕማ ነው። በዚህም ወር የሸይጧን መታሰር በርግጥ ትልቅ ኒዕማ ነው(keeping in mind ሁሉም ሸይጣን እደማይታሰር), it is such a great favour.  ግን ይሄ ማለት ምንም በመጥፎ የሚያዝህ ከመልካም የሚያሳንፋህ ውስዋስ የለም ማለት አይደለም። ነፋሲያ አለች! Yusuf 12:53
إِنَّ ٱلنَّفۡسَ لَأَمَّارَةُۢ بِٱلسُّوٓءِ إِلَّا مَا رَحِمَ رَبِّيٓۚ ነፍስ ሁሉ ጌታዬ የጠበቃት ካልሆነች በስተቀር በመጥፎ ነገር በእርግጥ አዛዥ ናት።
የረመዳን ወር በፃም መደንገግ ሂክማውም አንተና ነፋሲያህ 1 v 1 ተገናኝታችሁ ልክ እንድታስገባት ነው። ነፋሲያ ቀላል opponent አይደለችም፤ ሸይጣንን እራሱ ለአደም ከመስገድ እንዲኮራና ከአላህ ራህመት እንዲርቅ ያደረገችው ነፋሲያው ናት። So እንዴት ነው ምንዋጋት? 👉ፃም - The ultimate weapon!💪 ከምግብ፣ ከመጠጥና ከግንኙነት በቀኑ ክፋለ ጊዜ ብቻ መከልከሉ፤ 'መከልከል' ወይም ለአላህ ብሎና የሱንም ብቻ ምንዳ ፈልጎ መተው የሚለውን concept እንድትለማመድ ነው አንጂ መፃም ያለበት ሁለመናህ ነው። አይንህ፣ ጆሮህ፣ ምላስህ፣ እጅህና እግርህ በአጠቃላይ ሁሉ መናህ ነው ሚፃመው። በዚህ መልኩ ይችን 30ቀን እንደምንም ብለህ ነፋስያህን ስርአት አሲዛት! አለበለዚያ Nobody is coming to save you!🫵 Al-'Ankabut 29:69
وَٱلَّذِينَ جَٰهَدُواْ فِينَا لَنَهۡدِيَنَّهُمۡ سُبُلَنَاۚ وَإِنَّ ٱللَّهَ لَمَعَ ٱلۡمُحۡسِنِينَ እነዚያም በእኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን፡፡ አላህም በእርግጥ ከበጎ ሠሪዎች ጋር ነው፡፡
@qirat_channel_5k

#Ramadan3 መንገድ ሊወጣ ያሰበ ሰው መቼ ነው ማፍጠርን መነየት ያለበት? ጉዞውን ጀምሮ ከሚኖርበት ሃገር ከወጣ በኋላ ነው። እንጂ መጓዝን ስለወሰነ ብቻ ገና ካገር ሳይወጣ በፊት ማፍጠርን ሊወስን አይገባም። "ነገ መንገድ እወጣለሁ" በሚል ሰበብ ማፍጠርን ከወዲሁ ወስኖ ማደር ከባድ ጥፋት ነው። ምክንያቱም የጉዞው ውሳኔ ሊቀየር ይችላልና። ጉዞ ዑዝር የሚሆነው በተግባር ሲከሰት ነው። እንጂ በኒያ ብቻ ሙሳፊር (መንገደኛ) አይኮንም። አንድ ሰው "ነገ መንገድ እወጣለሁ" ብሎ ማፍጠርን ወስኖ ካነጋ በኋላ ሃሳቡን ቀይሮ ጉዞውን ቢሰርዝ መፆም አይችልም። ኒያውን ከሌሊት ጀምሮ አላሳደረምና። በረመዷን ወር ያለ ተጨባጭ ምክንያት አለመፆም ደግሞ ከባድ ወንጀል ነው። ስለዚህ በረመዷን ወር ጉዞ ያሰበ ሰው ማፍጠርን ሊወስን የሚገባው ጉዞውን በተግባር ጀምሮ ከመኖሪያው ሲወጣ ነው። ጥያቄ፡- በጾም ቀን ጸጉርን መላጨት ወይም ጥፍርን ማሳጠር ጾምን ያበላሻል? መልስ፡- ጸጉርን መቆረጥ ጥፍርን ማሳጠር የብብትን ጸጉር መንጨት የብልትን ጸጉር መላጨት ጾመኛን አያስፈጥርም፡፡ Daily Ramadan Virtue
عن أنس بن مالك رضي الله عنه قال: قال رسول الله : ﴿من ŘľŮ„ّى ŘšŮ„يَّ ŘľŮ„ا؊ً ŮˆŘ§Ř­ŘŻŘŠŮ‹ŘŒ صلّى اللهُ عليه عشرَ صلواتٍ، وحطَّ عنه بها عشرَ سيئاتٍ، ورفعَه بها عشرَ درجاتٍ.ď´ž The Messenger of Allah  said: “Whoever sends one blessing upon me, Allah will send ten blessings upon him, erase ten sins from him, and raise him ten دع؏ات (ranks).”
Today's Daily Virtue: Send at least 100 Salawat upon the Prophet ﷺ. On Jumu‘ah, we are encouraged to increase in Salawat. In Ramadan, every good deed is multiplied. You may say one sentence with your tongue… But in the heavens, your ranks are rising. Let our tongue stay moist with: Allahumma salli wa sallim ‘ala Nabiyyina Muhammad «اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ وَبَارِكْ عَلَى نَبِيِّنَا مُحَمَّدٍ #RamadanQA #FiqhusiyyamiRamadan #DailyVirtue

🎉የረመዳን የመጀመሪያ ጁምአ በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آ
🎉የረመዳን የመጀመሪያ ጁምአ በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّو عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ ﷺ 🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟 ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት "ሱረቱል ካህፍን በጁምዓ ቀን መቅራት፤ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል የሚበራ ብርሃን (ኑር) ይሆንልሃል/ ይሆንልሻል።" ይህ ማለት አላህ እስከሚቀጥለው አርብ ድረስ ልብአችንን በብርሃን ይሞላዋል፣ ትክክለኛውንና ስህተቱን የምንለይበትን ጥበብ ይሰጠናል ማለት ነው። ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ ‣ በመጨረሻው ሰአት ዱዓ ማድረግ (ማለትም ከአስር በኋላ ኡማውን በዱዓ እናስታውስ) በውዱ ነብያችን ላይ ሶለዋት ማብዛትንም አንርሳ❤️ اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً ﷺ 🌟 መልካም ጁምአ🌟 @fivekjemaa

Aselamualeykum werehmetulahi weberekatuh, Dear Brothers and Sisters😍, We kindly invite you to fill out this short survey regarding the Jemma program. Your response will help us understand the reasons for low participation and improve future programs according to students' needs and interests. Please use the link below to complete the survey: https://form.svhrt.com/69972fc82ac0ef04c548ffea Jazakumullahu Khairan for your time and cooperation.

Assalamu Alaikum dear brothers, Alhamdulillah, Ramadan has begun — a month of mercy, forgiveness, and light. Don’t let these
Assalamu Alaikum dear brothers, Alhamdulillah, Ramadan has begun — a month of mercy, forgiveness, and light. Don’t let these blessed days pass without sitting with the Words of Allah. The Qur’an One-to-One Session is still open — an opportunity to: * Improve your recitation * Strengthen your Tajweed * Memorize or revise Hifz * Build consistency with your Ustadh 📅 Registration extended until this Sunday 👤 For brothers only Make this day count. The Qur’an is your companion — let it illuminate your heart from the very start of Ramadan. 📝 Register now via the Google Form below.      https://forms.gle/uQqJ9GTmwhQYKtdz6

#Ramadan2 ጥያቄ፡- አንድ ሰው ፈጅሩ መውጣቱን ቢጠራጠር መብላት መጠጣት ይችላል? መልስ፡- ፈጅሩ ለእርሱ ግልጽ እስኪሆንለት ድረስ መብላት እና መጠጣት ይችላል፡፡ አላህ እንዲህ ብሏል፡- ﴿فَٱلۡئَٰنَ بَٰشِرُوهُنَّ وَٱبۡتَغُواْ مَا كَتَبَ ٱللَّهُ لَكُمۡۚ وَكُلُواْ وَٱشۡرَبُواْ حَتَّىٰ يَتَبَيَّنَ لَكُمُ ٱلۡخَيۡطُ ٱلۡأَبۡيَضُ مِنَ ٱلۡخَيۡطِ ٱلۡأَسۡوَدِ مِنَ ٱلۡفَجۡرِۖ ثُمَّ أَتِمُّواْ ٱلصِّيَامَ إِلَى ٱلَّيۡلِۚ ď´ž ٥٨٧ : البقرة  “(ሚስቶቻችሁን) አሁን ተገናኙዋቸው፡፡ አላህም ለናንተ የጻፈላችሁን ነገር (ልጅን) ፈልጉ፡፡ ከጎህ የሆነው ነጩ ክርም ከጥቁሩ ክር (ከሌሊት ጨለማ) ለእናንተ እስከሚገለጽላችሁ ድረስ ብሉ፤” (አል`በቀራህ፡ 187) በጸሐይ መጥለቅ በተጠራጠረ ሰው ተቃራኒ ፈጅሩ መውጣቱን የተጠራጠረ ሰው እርግጠኛ እስከሚሆን ድረስ መብላት ይችላል፡፡ የጸሐይን መጥለቅ የተጠራጠረ ሰው ግን መጥለቋን እስከሚያረጋግጥ ወይም ጥርጣሬው አመዛኝ እስከሚሆን ድረስ እንዳይባላ፡፡ Daily Ramadan Virtue عن Aisha رضي الله عنها قالت: كان رسولُ اللهِ  يُصلِّي صلاةَ الضُّحى، ويقولُ فيها: اللَّهُمَّ اغفِع لي وتُبْ عليَّ، إنَّكَ أنتَ التَّوَّابُ الرَّحيمُ مائةَ مرَّةٍ. — رواه Al-Adab Al-Mufrad، وصححه al-Albani Aisha (رضي الله عنها) reported: The Messenger of Allah  used to pray Duha prayer, and he would say in it: “O Allah, forgive me and accept my repentance. Indeed, You are the Accepter of repentance, the Most Merciful” — one hundred times. Salat ad-Duha (Salat al-Awwabin) Pray Duha (2–8 rak‘ahs), then say 100x: اللهم اغفع لي وتب علي إنك أنت التواب الرحيم ✔ Charity for all 360 joints ✔ 100 doors of forgiveness ✔ Multiplied reward in Ramadan A few minutes. Massive ajr. #RamadanQA #DailyVirtue

📢 ACADEMIC SECTOR UPDATE 📚✨ Asselamu Aleykum Werahmetu'llahi weberekatuh 🌙 We are pleased to announce that dedicated Telegram group links have been created for each department under the academic sector of the Muslim jemma'ah to strengthen collaboration, share academic resources, and support one another in both dunya and akhirah 🤝📖 Please join your respective department group using the links below: Main channel: https://t.me/fivekjemaa 💻 Software Engineering: https://t.me/+bUv8Yyj8bvVhMDRk 🧪 Chemical Engineering: https://t.me/+QZE_9Wdk28Q1ZTJk 🧬 Biomedical Engineering: https://t.me/+Syg1aAUjtOZhYzFk ⚡ Electrical Engineering: https://t.me/+MvU0oK75kexiNDhk 🏗️ Civil Engineering: https://t.me/+G4bHIHi__v1iYjU0 ⚙️ Mechanical Engineering: https://t.me/+zl-9s_sjFPY0ZDE0 The Prophet  said: "Whoever follows a path in pursuit of knowledge, Allah will make easy for him a path to Paradise."  May Allah make your journey an easier one. Let’s make these platforms beneficial spaces for knowledge sharing, reminders, and academic growth for the sake of Allah  🌱 Jazakumullahu Khairan 🤍 Academic Sector – Muslim Jemma’ah

#Ramadan1 የፆም ጥቅሞች(ፋኢዳዎች) ፆም ከተቅዋ (አላህን ከመፍራት) ጋር የተሳሰሩ ብዙ ጥቅሞችን ያዘለ ነዉ ፆም ሰይጣንን ለማሸነፍ ፣ስሜትን ለመስበር የሰዉነትን ክፍል ለመቆጣጠር መንገድ ነዉ፡፡ ከመጥፍ ስሜትና ወንጀል የመራቅ ፍላጎትን ያዳብራል እንዲሁም ከስርዓቶች ና ከቃልኪዳን ጋር መላመድን  ያስተምራል፡፡ ጥያቄ . ጥርስን በሳሙና (Toothpaste) መቦረሽ ይቻላል? መልስ:- ሸይኽ ኢብኑ ባዝ እንዲህ ብለዋል፦ "በጥርስ ሳሙና መቦረሽ ጾምን አያበላሽም፤ ነገር ግን ሳሙናው ወደ ውስጥ እንዳይገባ መጠንቀቅ ግዴታ ነው። ሚስዋክ መጠቀም ግን ይበልጥ የተወደደ ነው።" ነቢዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦ "በአፍንጫችሁ ውሃ ስታስገቡ (ለውዱእ) አጥብቃችሁ ሳቡ፤ ጾመኛ ካልሆናችሁ በስተቀር።" (አቡ ዳውድ — ይህ የሚያሳየው ወደ ውስጥ እንዳይገባ ጥንቃቄ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ነው። Today's Task
عَنْ زَيْدِ بْنِ خَالِدٍ الْجُهَنِيِّ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏"‏ مَنْ فَطَّرَ صَائِمًا كَانَ لَهُ مِثْلُ أَجْرِهِ غَيْرَ أَنَّهُ لاَ يَنْقُصُ مِنْ أَجْرِ الصَّائِمِ شَيْئًا ‏"‏ ‏.‏ قَالَ أَبُو عِيسَى هَذَا حَدِيثٌ حَسَنٌ صَحِيحٌ ‏.‏   Zaid bin Khalid Al-Juhani narrated that: The Messenger of Allah said: "Whoever provides the food for a fasting person to break his fast with, then for him is the same reward as his (the fasting person's), without anything being diminished from the reward of the fasting person." Jami` at-Tirmidhi (no. 807) وصححه الألباني
ďťż #RamadanQA #FiqhusiyyamiRamadan #Dailytask1

RAMADAN PLANER.pdf4.22 MB

ለ 5 ኪሎ ግቢ ተማሪዎች በሙሉ በግቢያችን ውስጥ የምትገኙ የ እስልምና እምነት ተከታይ የሆናችሁ እህት ወንድሞቻችን እንኳን ለ1447ኛው የረመዳን ወር በሰላም አደረሳችሁ እያልን ዶርማችሁ 5 ኪሎ የሆናችሁ እና ማታ ላይ ለመስገድ መስጊድ ሄዳችሁ ወደ ግቢ በጊዜ(እስከ ምሽት 4 ሰዓት ) መመለስ የማትችሉ ተማሪዎች ከ አሁን ሰዐት ጀምሮ የተማሪዎች አገልግሎት ቢሮ በመሄድ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እና ወደ ግቢ የመግቢያ የሰዓት ገደብ የሚስተካከል መሆኑን ልናሳውቃችሁ እንወዳለን:: የተስተካከለውን የሰዓት ገደብ እና ተግባራዊ የሚደረግበትን ቀን የምናሳውቃችሁ ይሆናል :: ማሳሰቢያ:- 1 ካልተመዘገባችሁ በር ላይ ያሉት የጥበቃ አካላት እንደማያስገቧችሁ እንድታውቁ እና ለሚፈጠረው ማንኛውም ነገር ኃላፊነቱን እራሳችሁ ናችሁ የምትወስዱት 2 ይህ ማስታወቂያ ለሙስሊም እህት ወንድሞቻችን ብቻ ነው ! መልካም የረመዳን ወር እንዲሆንላችሁ ተመኘን::

🥀 የረመዷን ትውስታ ለእህቴ 🥀 ☆ ዛሬ የቀጠሯችን መጀመሪያ ቀን ነው! ☆ ሰአቱም አፍጥር ሰአት ነው‼️ ምስጋና ለአለማቱ ጌታ ይሁንና የተከበረው የአላህ ወር አንድ ብሎ ጀምሯል:: ይህን ተከትሎ ከዚህ ቀደም በተባባልነው መሰረት ዶርማችን ተበታትነን ከምናፈጥር ለምን አንድ ቦታ አንሰባሰብም? የሚለውን አስበን... 🕌 አል-አቅሷ መስጂድ ለአፍጥር የሚሆነን ቦታ ጠይቀን እናንተን በሚመጥን መልኩ በረመዷን ድባብ አጅበን ዝግጅታችንን አጠናቀናል!! ✨️ ያንቺ መቅረት ስብስባችንን ያልተሟላ ያደርግብናልና: የኛም ስብስብ መድመቅ ባንቺም መገኘት ጭምር ነውና: አፍጥርሽን ይዘሽ በጊዜ ወደ መስጅድ ኢንሻአላህ!! 🌸 ለ ውዷ እህቴ 🌸

👉ከዛሬ ጀምሮ የሰሁር አግልግሎት ይሰጣል።ካፌ የሚከፈትበት ሰዓት (10:00 - 11:30) ነው:: meal card መያዝ አትርሱ ከዛሬ ጀምሮ ለተራዊህ ሰላት ሲባል የግቢ መግቢያ በሮች እስከ 04፡30 ድረስ ክፍት ሆነው ይቆያሉ። ለተራዊህ በምትወጡበት ጊዜ ሰብሰብ ብላችሁ ለመውጣት ሞክሩ፤ የግቢ መታወቂያ መያዛችሁንም አትርሱ።