5killo Jem'a official Channel
Open in Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Show more1 160
Subscribers
-124 hours
+17 days
+530 days
Posts Archive
Repost from AAU - Muslim Students Union
Update!
ከመጅሊስ በኩል ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ፣ ኡስታዝ አዩብ ደርባቸው፣ ኡስታዝ ሸሃቡዲን ሸኑራን ጨምሮ 5 ልዑካን አባላት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተገኝተው ከጀማዓው ተወካዮች እንዲሁም ከአጠቃላይ ተማሪዎች ጋር ውይይት ካደረጉ በኃላ በነገው ዕለት ከዩኒቨርሲቲው ጋር ውይይት እንደሚደረግ፤ ይህንንም ጉዳይ በኃላፊነት እንደሚይዙት በመናገር ተማሪዎች እንዲበተኑ ሆኗል።
አሁንም የመጅሊስ አመራሮች ለተማሪዎች የገባችሁትን ቃል አክብሩ! ተማሪው እናንተን አምኖ ጥያቄየን ታሳካላችሁ ብሎ አማና ሰጥቷችኃል። ይህን አማና መብላት አላህ ፊት፤ ተማሪው ፊት፤ ህዝብ ፊት እንዲሁም ታሪክ ፊት ተጠያቂ ያደርጋችኃልና አማናችሁ ተወጡ!
ተጨማሪ በቅርቡ የምንመለስ ይሆናል።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ከቀኑ 7:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ አሁን ምሽት 2:40 ሰዓት ድረስ፣ ተማሪዎቻችን በብርዱና በጨለማው ውስጥ ቁጭ ብለው ለጥያቄዎቻችን ምላሽ እየጠበቁ ይገኛሉ። መብትንና ክብርን ለማስከበር የሚደረግ ጉዞ መራራና ዋጋ የሚያስከፍል ቢሆንም፣ የእነዚህ ወጣቶች ጽናት ግን የፍትሃዊነታቸው ትልቁ ማረጋገጫ ነው።
📌 ለተማሪዎቻችን፦ በዚህ ብርድ በበዛበት ምሽት እያሳያችሁት ያለው ተስፋ አለመቁረጥና ቁርጠኝነት ታሪክ የማይረሳው ታላቅ የጽናት መዝገብ ነው። ቅስናችሁ አይሰበር፣ ሞራላችሁ አይውረድ። በዚህ አስቸጋሪ ሰዓት የምታሳዩት ትዕግስት (ሰብር) እና አንድነት ለነገው ድላችሁ መሰረት ነው። አላህ እውነተኞችንና መብታቸውን በሰላማዊ መንገድ የሚጠይቁትን መቼም ቢሆን አይጥልም።
📌 ለሚዲያ አካላት፦ እነዚህ ወጣቶች የነገዋ ሀገር ተስፋዎች እንጂ የሁከት አራማጆች አይደሉም። ሰላማዊ በሆነ መንገድ፣ ህጋዊና ሰብአዊ መብቶቻቸውን ይዘው መልስ ፍለጋ በብርድ ላይ ተቀምጠዋል። ለነዚህ ተማሪዎች ድምጽ በመሆን ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እናሳስባለን።
📌 ለዩኒቨርሲቲው አመራሮችና ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት፦ ተማሪዎች በሰላማዊ መንገድ ላነሷቸው ጥያቄዎች አፋጣኝ፣ ግልጽና ፍትሃዊ ምላሽ መስጠት የሀላፊነት ሁሉ መጀመሪያ ነው። ጉዳዩን በቸልተኝነት መመልከት ወይንም ማዘግየት መፍትሄ አይሆንም። አሁንም ጥያቄያችን ግልጽ ነው! ከምላሹ መሸሽ አይቻልም!
📌 ለመጅሊስ፦ የናንተ የመጀመሪያ ኃላፊነት የሙስሊሙን መብት ማስጠበቅ ነው። ሰላማዊው ጥያቄያችን በፍትሐዊ መንገድ ይመለስ ዘንድ ስሩ። ሴት ልጅ ብርድ ላይ አትደር፤ ተማሪዎች እንቅልፍ አጥተው ሜዳ ላይ አይደሩ። ስለፍትሕ ቁሙ! ታሪክ እየተፃፈ ነው!!
📌 ለሙስሊም ማህበረሰብ፦ እነዚህን በብርድና በጨለማ ውስጥ ያሉ ልጆቻችሁን በዱዓና በሞራል ከጎናቸው ቁሙ።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
እናት አባቶች ዱዓችሁ መሳሪያችን ነውና በዱዓ አስታውሱን። ይህ የትውልድ አማና ነው። ሁሉም በያለበት በሚችለው ማገዝ ግዴታው ነው። ኡስታዞች፣ የመጅሊስ አካላት፣ የሚዲያ ሰዎች፣ የመንግስት አካላት ሀላፊነታችሁን ትወጡ ዘንድ ጥያቄያችን ነው።
አደራ ! አደራራራ!!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+1
"እናንተም የበላዮች ስትኾኑ ምእመናን እንደኾናችሁ አትስነፉ፤ አትዘኑም፡፡" (ኣሊ-ዒምራን 139)
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ከፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ከተሰባሰብን 5 ሰዓታት አልፈዋል። ጀምበር አዘቅዝቃም ምሽት ገብቷል። እኛ መቶዎችን ሆነን ለጥያቄያችን መልስ ስጡን እያልን ባለበት ሰዓት ፕሬዚዳንቱ ልደታ ካምፓስ ዶርም እያስመረቁ ነበር። አሁን ደግሞ ምግብ አታስገቡም ብለው በሆድ ሊደልልን፣ ከውጪ ያሉትን ደግሞ እንገባለን ካላችሁ እንደበድባችሗለን በማለት እያስፈራሩ ነው።
ዳግም ለማስቀመጥ ያክል፦
ጥያቄያችን ሰላማዊ ነው። ሰላማዊ ነው ማለት ግን በሆድ ወይንም በዱላ ይሸጣል ማለት አይደለም። ለጥያቄያችን መልስ እስክናገኝ ድረስ እናድራለን፣ እንውላለን፣ እንራባለን፤ መስዋዕትነትም እንከፍላለን።
መጅሊስ እና የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት፦ ሰላማዊው ጥያቄያችን በፍትሐዊ መንገድ ይመለስ ዘንድ ስሩ። ሴት ልጅ ብርድ ላይ አትደር፤ ተማሪዎች እንቅልፍ አጥተው ሜዳ ላይ አይደሩ። ስለፍትሕ ቁሙ! ታሪክ እየተፃፈ ነው!!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
ግቢው እብደቱን ቀጥሏል!
ምግብም ወደግቢ እንዳይገባ ከልክሏል! ውጭ ያሉ ተማሪዎችም አትገቡም ብሎ እያስፈራራ ነው። መጾም ለኛ አጅር እና ክብር እንደሆነ አላወቁም!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+1
አይደለም እንቅልፉን፤ ጉልበቱን፤ ጊዜውን ይቅርና ህይወቱንም ለዲኑ ለመሰዋት የተዘጋጀ ትውልድ እንዳለ አልገባቸውም!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
እዚያ ያለውን ተማሪ ማስነሳት ሲያቅታቸው ተማሪዎች ወደግቢው እንዳይገቡ እየከለከሉ ይገኛሉ።
አሁንም መፍትሄው የተማሪን ድምጽ ማፈን ሳይሆን ለተጠየቀው ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ መስጠት ነው።
ጥያቄ አለን! መልስም እንፈልጋለን!
Video: አሁን ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ፊት ለፊት
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+2
ፌደራል ፖሊሶች ተማሪውን እንዲበተን ለማድረግ እየሞከሩ ቢሆንም ተማሪው አሁንም በእምቢታው ቀጥሏል።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
FBE፣ Main፣ 5 ኪሎ እና 4 ኪሎ ያላችሁ ወንድም እና እህቶች ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ያሉ ወንድሞቻችሁን በፍጥነት ተቀላቀሉ!!!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+1
ፕሬዝዳንቱ ልደታ ካምፓስ ነው ያለው!
ይህ ንቀት ነው! መልስ እስኪሰጠን ድረስ የትም አንቀሳቀስም!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+1
ፕሬዝዳንቱ ልደታ ካምፓስ ነው ያለው!
ይህ ንቀት ነው! መልስ እስኪሰጠን ድረስ የትም አንቀሳቀስም!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+1
"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ታገሱ ተበራቱም፡፡ (በጦር ኬላ ላይ) ተሰለፉም፡፡ ትድኑም ዘንድ አላህን ፍሩ፡፡" (ኣሉ-ዒምራን 200)
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+1
"ከነቢይም ብዙ ሊቃውንት ከርሱ ጋር ኾነው የተዋጉ ብዙ ናቸው፡፡ በአላህም መንገድ ለሚደርስባቸው ነገር አልፈሩም፤ አልደከሙምም፡፡ (ለጠላት) አልተዋረዱምም፡፡ አላህ ትዕግስተኞችን ይወዳል፡፡" (አሉ ዒምራን 146)
@aaumsu
