en
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Open in Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Show more
1 157
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-130 days
Posts Archive
قال القائل رحمه الله አደራችሁን እንደኔ እንዳትሆኑ አላቸው ይባላል። 🏵 ምነው ብለው ጠየቁት አንድ ተግባር ብዙ ነገር አሳጣኝ አላቸው ☢️ ምን አሳጣህ አሉት ብዙ ነገር አላቸው።ግን ሲጠቀለሉ 3 ናቸው ። 1. አላህ የሰጠኝ መልካም ነገሮች አሳጣኝ 2. ያሳጣኝ ለመመለስ ፈለግኩኝ ለካስ የቱ ጋር እንደጣልኩትም አስረስቶኛል። 3. ምናልባት እዚህ ጋር ይሆናል ብዬ መፈለግ ስጀምር ራሴንም አጣው። ☢️ ያ ተግባር ምንይሆን ብለው ጠየቁት!! ወንጀል አላቸው። وصدق ابو إسحاق عندما قال ولا ترض المعايب فهي عار عظيم يورث محبوب مقتا

🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا
🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ ﷺ 🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟 ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ከህፍ መቅራት ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ اللَّهُــمَّ صَلِ وَسَـــلِّمْ وَبَارِكْ على نَبِيِّنَـــا مُحمَّد ﷺ @fivekjemaa

Sorry again, class is at E-122 electrical floor

Room is changed to electrical floor 138 @10:45LT

📚 Tutorial Program for 2nd year Students! 🌟 As-salamu Alaikum wa Rahmatullahi wa Barakatuh 🌟 We are back with our Applied Mathematics Tutorial! ✨ Dear brothers and sisters taking 2nd year 1st semester courses 😊 The 5 Kilo Muslim Students’ Jem’a Academic Sector is pleased to announce that the 2nd year Tutorial Program will continue tomorrow with a dedicated Mathematics session: 📘 Subject: Applied Mathematics 🕙 Time: 10:20 LT 📅 Date: Thursday, January 15 📍 Venue: E-Block, Room E-131 ✨ Let’s strengthen our understanding and excel in our studies — together, In shaa Allah! 📌 Don’t miss out! 📌 Invite your classmates too! 🔗 Join our Telegram channel for updates: 👉 t.me/fivekjemaa

Some Duas for exams: Dua for Ease and Relief:
اللّهُمّ لا سَهْلَ إِلّا مَا جَعَلْتَهُ سَهْلًا، وَأَنتَ تَجْعَلُ الْحَزِينَ سَهْلًا.
O Allah, nothing is easy except what You make easy, and You can make the difficult easy. Dua for Confidence:   
اللّهُمّ انّي أسألكَ الثّباتَ في الأمرِ، والعزمَ على الرّشدِ، والنجاحَ في الامتحان
General Dua for Help:
اللّهُمَّ أَنتَ الْمُعِينَ، أَعِنِّي عَلَى قَضَاءِ حَوَائِجِي. حسبي الله ونعم الوكيل.
Allah is sufficient for me, and He is the best disposer of affairs ⚡️Try to memorize these Duas and don't forget to recite them when you start your exams. 👉Put your trust in Allah, for Allah is sufficient as a guardian. ©AAU6kilojemea

📚 Tutorial Program for 2nd year Students! 🌟 As-salamu Alaikum wa Rahmatullahi wa Barakatuh 🌟 We are back with our Applied Mathematics Tutorial! ✨ Dear brothers and sisters taking 2nd year 1st semester courses 😊 The 5 Kilo Muslim Students’ Jem’a Academic Sector is pleased to announce that the 2nd year Tutorial Program will continue tomorrow with a dedicated Mathematics session: 📘 Subject: Applied Mathematics 🕙 Time: 10:20 LT 📅 Date: Thursday, January 15 📍 Venue: E-Block, Room E-131 ✨ Let’s strengthen our understanding and excel in our studies — together, In shaa Allah! 📌 Don’t miss out! 📌 Invite your classmates too! 🔗 Join our Telegram channel for updates: 👉 t.me/fivekjemaa

🗣🗣اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎👋👋 ✅ኢንሻአላህ ዛሬ (ማክሰኞ ) የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ደርስ ይኖረናል ።  6ኪሎ እና 5ኪሎ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች በጊዜ እንገኝ ሌሎችንም በማስከተል  ቡዙ እናተርፍለን። قَالَ رَسُولُ اللَّهِ : فَضْلُ الْعَالِمِ عَلَى الْعَابِدِ كَفَضْلِ الْقَمَرِ عَلَى سَائِرِ النُّجُومِ 📚 سنن أبي داود (٣ٌ٤٥) — حديث صحيح "የእውቀት ባለቤት የሆነ ሰው አሏህን ተገዢ በሆነ ሰው ላይ ያለው ብልጫ ፤ ጨረቃ በተቀሩት ከዋክብት ላይ ያላትን ብልጫ መሣይ ነው" ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ ቦታ፡ 6ኪሎ አቅሳ መስጅድ 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/durus_at_aqsa ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934 @fivekjemaa

የጠዋቱ ሚስጥር (The Unfair Advantage) ​አሰላሙ አለይኩም Ikhwani, ​ፈተና እንዴት ነው?    ​በዚህ ሰዓት ብዙዎቻችን የምንሰራው አንድ  Mistake  አለ። ለሊት ሙሉ እንቅልፍ አጥተን፣ አይናችን ቀልቶ ስናነብ... Productive የሆንን ይመስለናል። ​እውነቱ ግን ይሄ Inefficiency (ብክነት) ነው። ​ለምን መሰላችሁ? Neuroscience እና የፈጅርን ሚስጥር እንይ። ​1. The Neuroscience (የአእምሮህ ባዮሎጂ) ​ሳይንስ እንደሚያረጋግጠው፣ የአንተን ውጤት የሚወስነው የአእምሮህ ክፍል Prefrontal Cortex ይባላል። ይሄ ክፍል ቀኑን ሙሉ በውሳኔ፣ በሶሻል ሚዲያ እና በድካም ሲጨናነቅ ይውላል (Decision Fatigue)። ​ማታ ላይ ገብተህ ለማጥናት ስትሞክር፣ እየነዳህ ያለኸው ጎማው የተነፈሰ አእምሮ ነው። ለዚህ ነው አንድ ቻፕተር ለመጨረስ ብዙ ሰዓት የሚፈጅብህ። በ​ጠዋት ከእንቅልፍ ስትነሳ ግን? አእምሮህ በከፍተኛ የ Alpha Brain Wave ውስጥ ነው የሚገኘው። ይህ ማለት Prefrontal Cortex-ህ አርፏል፣  መረጃን የመቀበል አቅሙ (Absorption Rate) ጣራ ላይ ነው። ማታ 3 ሰዓት የፈጀብህን፣ ጠዋት በ45 ደቂቃ crush ልታደርገው ትችላለህ። ​2. የፈጅር Superpower (The Cheat Code) ​ሳይንሱ "Alpha State" ያለውን፣ ነቢዩ () በዱዓቸው  አረጋግጠውልናል፡- ​"አላህ ሆይ! ለህዝቦቼ በጠዋት ክፍለ-ጊዜያቸው ላይ በረካን አድርግላቸው።" (አቡ ዳውድ) ​ወንድሜ፣ በረካ ማለት የአንተ የተፈጥሮ ብቃት እና የአላህ እርዳታ በአንድ ላይ ሲገናኙ የሚፈጠር ውጤት ነው። ​በዚህ ሰዓት፣ አለም ፀጥ ብላለች ። አእምሮህ ጥርት ብሏል። መላእክት አሉበት። ፈጅርን ሰግዶ የከበደህን ትምህርት ስትጀምር፣ አንተ እያነበብክ ያለኸው በረሱል() ዱዓ ታግዘህ ነው! ​ምን ይሻላል? ​Stop the Zombie Mode: "ለሊት ካላነበብኩ ውጤት አይመጣም" የሚለውን የውሸት ስሜት ተወው። እንቅልፍ ከመጣህ ተኛ። በግማሽ ልብ ከምታነበው ብዙ ምዕራፍ፣ በጠራ አእምሮ የምታነበው 1 ምዕራፍ ዋጋ አለው። ​Attack the Monster: ፈጅርን እንደሰገድክ ስልክህን እንዳትነካ። ያቺ "ወርቃማ ሰዓት" ናት። በጣም የከበደህን ኮርስ በዚህ ሰዓት crush  አድረገው። ትገረማለህ፣ በቀላሉ ይገባሃል። ​Activate it: ማንበብ ስትጀምር "ያ ረብ! ይህን ጊዜ ባርክልኝ" በል። ​ፈተና ማለት የብቃት ብቻ ሳይሆን፣ የ Timing ጨዋታ ነው። አላህ የለፋችሁበትን ሳይሆን፣ በረካ ያደረገበትን ውጤት ይስጣችሁ! ​🔜 በቀጣይ ዋና ጠላታችን ስለሆነው "Social Media & Dopamine" እናወራለን። ​መልካም ፈተና! @AAU6kilojemea

የፈተና ጭንቀትን በዲን መመከትና የሙስሊም ተማሪ መረጋጊያ ጥበቦች 1. ኒያህን አስተካክል ●  ዒባዳ አድርገው: ትምህርትህ በአላህ ዘንድ ዒባዳ እንዲሆን ኒያህን አስተካክል። የምትማረው ለሙስሊም ማኅበረሰብህ ለማገልገል፣ ሃላል ገቢ ለማግኘት እና የምድርን ምትክነት ለመወጣት እንደሆነ አስብ። ይህ አስተሳሰብ ውጥረትን ይቀንሳል፤ ምክንያቱም ትግልህ ለአላህ ይሆናልና። ● ለራስህ ደግ ሁን: ጥሩ ውጤት ለማምጣት ጥረት አድርግ፣ ነገር ግን ውጤቱ ብቻ ማንነትህን እንደማይገልጽ አስታውስ። በውጤቱ ምክንያት ራስህን አትውቀስ። 2. በእውቀት እና በትጋት ● ያለ ጥረት ቱወኩል የለም: በአላህ መመካት  ማለት ድንጋይ ላይ ተቀምጦ ተዓምር መጠበቅ አይደለም። በመጀመሪያ ከባድ ጥረት አድርግ ፣ ከዚያም ውጤቱን ለአላህ ተው። የምትችለውን ሁሉ ካደረግክ በኋላ፣ ውስጣዊ ሰላም ይኖርሃል። ● የጊዜ በረካ : አላህ ጊዜያቸውን ለሰላት ለሚመድቡ በረካን እንደሚጨምር አስብ። ሰላትህ የንባብ ጊዜህን ያበላሻል ብለህ አትፍራ፤ በተቃራኒው ለጥናትህ ብርታትና ብርሃን ይጨምርለታል። 3. ከስሜታዊ ጫና መውጣት ● ሰላትህ ማረፊያህ ነው: የፈተና ጭንቀት በጣም ሲጨምር፣ ወደ ሰላት ሩጥ። ሰላትህ ከዓለማዊ ውጥረት የምታርፍበት እና ወደ አላህ የምትመለስበት መንፈሳዊ መጠጊያህ ነው። ● ዱዓ እና ዚክር: ውጥረትን ለመቀነስ ከሁሉ የተሻለው መንገድ የዱዓ እና ዚክር ብዛት ነው። "ያ ሐዩ ያ ቀዩም ቢራህመቲከ አስተጊስ" (አንተ ህያው የሆንክ፣ ራስህን የቻልክ፣ በእዝነትህ እጠይቅሃለሁ) የሚለውን ዱዓ በብዛት ተጠቀም። ጭንቀትህን ሁሉ ለአላህ ስጥ። ● ንፅፅር አቁም: ጓደኞችህ "ለሊት ሙሉ አነባለሁ" ሲሉ ሰምተህ የጥፋተኝነት ስሜት እንዳይሰማህ። የመኝታ ሰዓትህ መብትህ ነው። እያንዳንዱ ሰው የሚማርበት መንገድ የተለየ ነው። ለጤናህ እና ለአእምሮህ እረፍት ቅድሚያ ስጥ። 4. በራስ መተማመን እና እራስን መቀበል ●በራስ መተማመን: ፈተናውን በተወኩል (በአላህ መመካት) እና በኢጅቲሃድ (ትጋት) መነጽር ተመልከተው። ያለፈው ጥረትህ ሁሉ ዝግጁ እንድትሆን አድርጎሃልና ራስህን አትጠራጠር። የምታውቀውን ነገር በግልጽ አስቀምጥ። ● የውጤት ውሳኔ: ውጤቱ ምንም ቢሆን፣ ይህ የአላህ ውሳኔ  መሆኑን ሙሉ በሙሉ ተቀበል። የምትችለውን ሁሉ ካደረግክ በኋላ፣ ስሜታዊ ሰላምህን ማግኘት አለብህ። የአላህን ውሳኔ መቀበል ድክመት ሳይሆን የእውነተኛ ኢማን ምልክት ነው። ይህ ምክር በፈተና ወቅት ጥረትህን ከአላህ ጋር ያለህን ግንኙነት በማጠናከር እንድትመራው ይረዳሃል። إِنۡ شَآءَ ٱللَّهُ •••••••••••••••••••••••••• ከነገ ጀምራችሁ Final exam የምትወስዱ እህት ወንድሞቻችን አላህ ፈተናውንም ገር ውጤቱንም ጣፋጭ ያደርግላቹ ዘንድ ዱዓችን ነው :: ተረጋግታችሁ እንድትሰሩ : ፈተናው ካሰባችሁት በላይ ቀላል ሆኖ በconfidence እንድትወጡት አላህ ያግራላቹ ::   ለሁላችሁም መልካም ፈተና !! ©

👉 ጊቢ ተማሪ ሆነን እኝን የመሰሉ ድንቅ እና አስገራሚ ሸህ አላህ ወፍቆን ካልተጠቀምንባቸው ወላሂ በጣም ያሳዝናል!!!! 👉ዘውትር ቅዳሜ እና እሁድ የሸህ ሰኢድ ተፍሲር ይቀራል ስለዚህ እንገኝ ፣ ሐሙስ ደግሞ ( الرحيق المختوم)ረሂቀል መህቱም የ ረሱል ሲል ስላለ ተገኝተን ብንሰማ በጣም ብዙ እንጠቀማለን :: ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ ቦታ፡ 6ኪሎ አቅሳ መስጅድ 📎ደርሶቹ በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቁ መከታተል ትችላላችሁ።👇 https://t.me/durus_at_aqsa

የዒልሙ መሐንዲስ - ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ ! ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ በ1945 አ.ል በዋድላ ደላንታ ተወለዱ ። የተወለዱባት መንደር ስያሜ አቃዱር ይሰኝ ነበር ። ከአባታቸው አህመድ ሸይኽ ሙስጠፋ እና ከእናታቸው ተዋበች አጋሽ ነበር የተገኙት ። ገና በለጋ እድሜያቸው በአካባቢያቸው በነበረ የመኖሪያ እና የእርሻ ቦታ እጥረት ምክንያትና የኑሮው ነገር ስላልገራላቸው ከመንደሩ ለቀው እንዲወጡ ግድ ሆነባቸው ። ከመንደራቸው የመኮብለል ጉዳይ ለእናታቸው ወ/ሮ ተዋበች አጋሽ እንዲህ በቀላል የሚታይ አልነበረም ። ከባለቤታቸው ጋር እስከመለያየት አደረሳቸው ። የኑሮ መላ ያስኮበለላቸው የሸይኽ ሰዒድ አባት ፣ ታላቅ ወንድምና አጎታቸው አካባቢውን ለቀው ወደመተከል ያቀናሉ ። ሸይኽ ሰዒድ ግን ከእናታቸው ጋር በመንደራቸው ጸኑ ። አባታቸው ለደረስነት እንዲሁም ልጃቸው በኢልሙ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ልዩ ፍላጎት ነበራቸው ። በርሳቸው ግፊትና ተፅዕኖ ሸይኽ ሰዒድ የደረስነት ህይወት ጀመሩ ። መሰረታዊውን የፊቅህን ስርዓተ እውቀት ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ቦረና ተጉዘው ለ3 ዓመታት ያክል የነህዉንና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነውም ቢሆን የተፍሲር ቂርዓታቸውን ቀጠሉ ። በሀገራችን ኢትዮጵያ የሚሰጡ ኪታቦችን ካጠናቀቁ ቡሀላ ወደ አዲስ አበባ መጡ ። እዚህም የመጡበት ምክንያት ከዚህ ሀገር ወተው ወደ አረብ ሀገራት ተጉዘው የሀዲስ እንዲሁም ሌሎች ቂርአቶችን ለመቅራት አስበው ነበር ። በወቅቱም ሀጂ ሙሐመድ ራፊዕ ከሳውድ አረቢያ ተመልሰው አንዋር መስጂድ ላይ ደረሶችን ሲያቀሩ የሚያቀሩበት ነበርና ያገኟቸዋል ። ሃሳባቸው ከሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ ዘንድ ለመቅራት ነበር ። ቆይተው ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ ወደትውልድ መንደራቸው ይሄዱ ነበርና አልተሳካም ። ሸይኽ ሰዒድ ግን ቂርዓታቸውን ከሐጂ ሙሐመድ ወሌ ዘንድ ይቀጥላሉ ። ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ እስኪመለሱ ድረስ . . .! ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕም የጥቅምት ማገባደጃ ላይ ወደአዲስ አበባ ይመለሳሉ ። ሸይኽ ሰዒድ ወትሮም ጊዜያቸውን በአግባቡ የሚጠቀሙ ነበሩ ። ኩቱቡ ሲታን እሳቸው ጋር ቀርተው ማጠናቀቅ ቻሉ ። በማለዳው ክፍለ ጊዜ ደግሞ ከሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ዘንድ ተፍሲርን ሙራጀዓ ሲያደርጉ ይቆያሉ ። አዲስ አበባ የነበራቸውን ቆይታ እንደጨረሱ ወደ ትውልድ ስፍራቸው ሄደው የማስቀራት ፍላጎት የነበራቸው ቢሆንም እዚሁ አንዋር መስጂድ የነበሩት 3 ታላላቅ ዑለሞች ፍቃደኛ ሳይሆኑ ይቀራሉ ።  ምክንያታቸው ደግሞ በወቅቱ የነበረው የደረሳ መጠን መብዛት ሸይኽ ሰዒድ እዚህ መቆየታቸውን ግድ ይል ነበር ። ትዕዛዙን ተቀብለው ሸይኽ ሰዒድ ዒልምን ማቅራት ጀመሩ ። በቆይታቸው የማረፍያ ስፍራና የእለት ጉርስ ማግኘት በጣም አስቸጋሪ ሆኖባቸው እንደነበር ይናገራሉ ። በዚያ ወቅትም ቀኑን ወሎ ሰፈር ድረስ በእግራቸው በመጓዝ ልጆችን ያቀራሉ ። እዚያው ቤትም ምሽቱን በጥበቃነት ማገልገል ይጀምራሉ ። በቀጣዩ የህይወት ምዕራፋቸው ለ15 አመታት አንዋር መስጂድ ዒልምን ሲያቀሩ ቆይተዋል ። ሸይኽ ሰዒድ በእድሜ ዘመናቸው በደማቁ ከሚወሱበት አበርክቷቸው መሐል በኢትዮጵያ ታሪክ  የመጀመሪያውን የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ማህበር ወይም በተለምዶ ሙነዘማን ማቋቋም ነበር ። እጅግ ብዙ ጥረትና ልፋት የታየበት ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች መብታቸው የሚጠይቁበትና ማንነታቸውን የሚያስከብሩበት ተቋም መሆን የቻለ 165 ያህል ቅርንጫፍ ማዕከላትን ማቋቋም የቻለ ነበር ። በጊዜው መንግስት ለተቋሙ ሕጋዊ እውቅናና ፈቃድ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም የኋላ ኋላ ስጋት ይሆናል በሚል አደረጃጀቱ እንዲፈርስ የተለያዩ ስራዎች ተሰርተዋል ። ሸይኽ ሰኢድ አህመድ ሙስጠፋ በዚህ ሁኔታ ላይም ሆነው በ 5 መስጂዶች ላይ ተፍሲርን በማቅራት ሙሉ በሙሉ አጠናቀው የነበረ ሲሆን በኒ መስጂድ ፣ አንዋር መስጂድ ፣ ሀሺም መስጂድ ይገኙበታል ። በዚህ አጋጣሚ ኡምራ የማድረግ እድል ያገኙት ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ ዑምራቸውን ፈጽመው ከ15 ቀናት በኋላ የመመለስ እቅድ ነበራቸው ። ያ ግን በተለያየ ምክንያት ሊሰምር አልቻለም ። እርሳቸው ሄደው ቀናት ባስቀጠሩበት አጋጣሚ አገር ውስጥ ነገሮች ተቀያይረዋል ። ታዲያ በጊዜው አንድ ሁነት ይከሰትና ነገሮች መልካቸውን ይቀይራሉ ። የወቅቱ መንግስት በአንዋር መስጂድ እጅግ ብዙ ወጣቶችን ህይወት በመቅጠፍ እንዲሁም ሙስሊሞች ተለይተው ድብደባ እንደተፈጸማባቸው  ፣ የተለያዩ መሻዒኾች እየታሰሩ የግድያ ፍርድም እየተፈረደባቸው እንደሆነና እሳቸውም በጥብቅ እየተፈለጉ እንደሆኑ ይሰማሉ ። ሸይኽ ሰዒድም በነዚህና መሰል ምክንያቶች ሳዑዲ አረቢያ ይሰነብታሉ ። በዚህ ሁኔታ ቀናት ቀናትን እየተካ ወራትም ወራትን እየተኩ አመታት ተቆጠሩ ። ሸይኽ ሰዒድ የመኖሪያ ፍቃድ ስላልነበራቸው ከአደባባይ ተሸሽገው ከማንም ጋር ሳይገናኙ ለ 2 አመት ያክል ከቆዩ ቡሀላ ሳዑዲ አረቢያ ይኖሩ የነበሩት ሸይኽ አህመድ ሀዲ ሸይኽ ሰኢድን አፈላልገው ያገኟቸዋል ። ሸይኽ አህመድ ያላቸውን አቅም ያውቁ ስለነበር  ወደ አራት የሚጠጉ የዓቂዳ ኪታቦችን እንዲያቀሩና የድምፃቸውም ቅጂ ወደ ኢትዮጵያ በካሴት መልክ ተዘጋጅቶ እንዲሰራጭ ያማክሯቸዋል ። ሸይኽ ሰዒድም በጣም ደስተኛ እንደሆኑ በመናገር ስራቸውን ይጀምራሉ ። ቆይቶ ሙሉ ለሙሉ ስራቸውን በማጠናቀቅ ሸይኽ አህመድ ሙአሰተል ሀረመይን ከሚባል ድርጅት ጋር የነበራቸውን ትውውቅ ተጠቅመው የሸይኽ ሰዒድ አህመድ ድምፅ ተቀድቶ በካሴት መልክ ወደ ኢትዮጵያ እንዲሰራጭ ሆነ ። ስራቸው ተወዳጅነት ማትረፍ የቻለና በብዙዎች ዘንድ የሚወሳ መሆን ችሏል ። ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖች ጭምር ወደው ያደምጡት እንደነበር ይወሳል ። ሸይኽ ሰዒድ ሌላኛው ግዙፍ እድል ብለው የሚያነሱት አንጋፋው አፍሪካ ቲቪ ምስረታውን ያደርጋል ። እሳቸውም በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪው በሆነው ኢስላማዊ የሳተላይት የቴሌቭዥን ጣቢያ የቁርዓን ተፍሲርን ማስማር ጀመሩ ። የብዙዎች ዘንድ ተወዳጅ እና ተናፋቂ ሆኖ የብዙዎችን ልብ ከቁርዓን ጋር አዛምዷል ። በዚህ ሁሉ ውስጥ የ9 ልጆች አባት የሆኑት ሸይኽ ሰዒድ ቤተሰባቸውን አልዘነጉም ነበር ። ከቅርብ ዓመታት በፊት ለ23 ዓመታት ርቀዋት ወደቆዩት አገራቸው በመመለስ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ማገልገላቸውን ቀጥለዋል ። በአፍሪካ ቲቪ አል ፈታዋን ጨምሮ የተለያዩ ሸሪዓዊ መሰናዶዎች እያቀረቡ ያሉ ሲሆን አፍንጮ በር የሚገኘው የአቅሷ መስጂድ ዒማምና ኸጢብ በመሆን ከዚያን ባሻገር በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት የዑለሞች ምክር ቤት አባል በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ ። አላህ ( ሱ.ወ ) ከመልካም አበርክቷቸው ጋር አጽንቶ በረዥም እድሜ በበረታ አፍያ ያቆያቸው ። #አፍሪካ_ቲቪ #የህይወት_ጎዳና

"አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ" ቢስሚላህ በዱንያ ላይ ደስተኛ መሆን የምንችለው 🔴ነገሮቻችንን ጉዳዮቻችንን በሙሉ ወደ አላህ ስናስጠጋነው 🔴ሁሌም በየትኛውም ሁኔታ ላይ ብንሆን ማመስገን(الحمد لله على كل حالٍ) ማለትን እንልመድ ምክንያቱም ነገራቶች በአጠቃላይ ከአላህ ዘንድ መልካም ናቸው ጥሩ ና መጥፎ የሚሆኑት በእኛ እይታ ነው ይህ ደግሞ የአላህን ሂክማ(ጥበብ) አለማወቃችን ነው 🔴 በቀደር ማመን ይህ ግልፅ ነው በተቻለ አቅም ላሰብነው ነገር (ለጉዳያችን) ሰበቡን ማድረስ ከዛም ለ አላህ መተው 🔴 አላህን አብዝቶ ማውሳት (ቁርአንን መቅራት፣ፈርድ እና ሱና ሰላቶች ላይ መበርተት...) ሌሎችም ወደ አላህ የሚያቃርቡንን ኢባዳዎችን መፈፀም " الَّذِينَ آمَنُوا وَتَطْمَئِنُّ قُلُوبُهُم بِذِكْرِ اللَّهِ ۗ أَلَا بِذِكْرِ اللَّهِ تَطْمَئِنُّ الْقُلُوبُ" "(እነሱም) እነዚያ ያመኑ ልቦቻቸውም አላህን በማውሳት የሚረኩ ናቸው፡፡ ንቁ! አላህን በማውሳት ልቦች ይረካሉ፡፡" (ሱረቱል ረዕድ አንቀፅ28) 🔴 በጉዳዮችን ሁሉ አላህ ና መልዕክተኛው የደነጉትን ማስቀደም አንድን ነገር ከመፈፀማችን በፊት በሸሪአ መነፅር ማየት ሸሪአው ምን ይላል የሚለውን መመልከት 🔴 የዱንያ ጉዳዮች እዳሉ ሁነው ሁሌም ግን ለዲን ቅድሚያ መስጠት 🔴 አላህ መፍራት፣በሱ ላይም መመካት(ለምሳሌ ተማሪ ብትሆኑ የፈለጋችሁትን ያህል አጥንታችሁ ሁሉንም አንብባችሁ እንኳን ብትገቡ የፈተናው ቦታ ላይ ስትሆኑ ምንም እደማታውቁ ማመን ድል የሚመጣው ከአላህ እንጂ ከ እናንተ አለመሆኑን ማመን) " وَمَن يَتَّقِ اللَّهَ يَجْعَل لَّهُ مَخْرَجًا" "አላህንም የሚፈራ ሰው ለእርሱ መውጫን ያደርግለታል፡፡" "وَمَن يَتَوَكَّلْ عَلَى اللَّهِ فَهُوَ حَسْبُهُ ۚ " "በአላህም ላይ የሚጠጋ ሰው እርሱ በቂው ነው፡፡ " በመጨረሻም ومن جرب وجد ومن وجد الله فماذا فقد؟! ومن فقد الله ماذا وجد؟! سبحانك الهم وبحمدك أشهد الا إله إلا أنت أسغفرك وأتبو إليك" ©islamicpsychologycommunity @fivekjemaa

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ሊመሰረት ነው ለዘመናት በፅናት የተካሄደው ትግልና የተከፈለው ውድ መስዋዕትነት ፍሬ አፍርቶ፣ የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ታሪካዊ የምስረታ ጉባኤውን
የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ሊመሰረት ነው ለዘመናት በፅናት የተካሄደው ትግልና የተከፈለው ውድ መስዋዕትነት ፍሬ አፍርቶ፣ የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ታሪካዊ የምስረታ ጉባኤውን በመጪው እሁድ ጥር 03 ቀን 2018 በአድዋ ዜሮ ዜሮ አዳራሽ በደመቀ ሁኔታ ያከናውናል። ይህ ምስረታ ለዓመታት ለዘለቀው የወጣቶች ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ ትልቅ የድል ቀን ሲሆን፣ የአዲስ አበባ ሙስሊሞችን ብቻ ሳይሆን መላው የኢትዮጵያ ሙስሊሞችንም አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያራምድ ታላቅ ሁነት ነው። ካውንስሉ ከመደበኛ መዋቅር ባለፈ የወጣቱን ሁለንተናዊ እድገት የሚያፋጥንና የአንድነት ድልድይ ሆኖ የሚያገለግል ተቋም በመሆኑ ይህ ዕለት በታሪካችን ውስጥ ትልቅ ቦታ ይኖረዋል። ​የካውንስሉ መመሥረት ወጣቱን በስነ ምግባር በእውቀትና በኢኮኖሚ በማብቃት ረገድ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ አለው። አላህ ሱ.ወ በሱረቱል ካህፍ "እነርሱ በጌታቸው ያመኑ ወጣቶች ናቸው፤ መመራትንም ጨመርንላቸው" እንዳለው ሁሉ ይህ ተቋምም ወጣቱ በኢማን የታነፀና በአላህ እርዳታ እየተመራ ኃይሉንና ችሎታውን በተደራጀ መልኩ ለዲኑና ለሀገሩ እንዲያውል የሚያስችል ብቁ መድረክ ይሆናል። የካውንስሉ ዋና ሚና ወጣቱ በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የራሱን አሻራ እንዲያኖር ማስቻል በመልካም ስነ ምግባር የታነፀ ትውልድ መገንባትና የሙስሊሙን ማህበረሰብ ድምፅ በላቀ ተቋማዊ ብቃት ማስተጋባት ነው። ከዚህም ባለፈ ካውንስሉ የእውቀት ሽግግር ማዕከልና የወደፊት አመራሮች መፍለቂያ ሆኖ በማገልገል የነገን ተስፋ በፅኑ መሰረት ላይ ይተክላል። ​በዚህ ታሪካዊ ዕለት የሚበሰረው አዲስ ጅማሮ፣ በኢትዮጵያ ሙስሊም ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍትና የወጣቱን ሚና የሚያጎላ በመሆኑ፣ ሁላችንም በጋራ የምንቆምበትና የምንኮራበት የጋራ ውጤታችን ነው። ©: ካውንስሉ

~ የፈተና ሰሞን!! ዒልም ምግብና መጠጥ ከሚያስፈልገን በላይ ያስፈልገናል። ምናልባት የምንመገበው በቀን ሁለት/ሶስት ጊዜ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን የሸሪዓ ዒልም ስንተኛም ስንነሳ፣ ስንበላም ስንጠጣ፣ ስንለብስ፣ ጌታችንንም ስንቃረብ፣ ዱንያን ስንለፋም የዱንያን ትምህርት ስንማር፣ ቤትም፣ ት/ቤትም፣ መጸዳጃ ቤትም ስንገባ፣ ዝም ስንልም ስናወራ፣ ለህጻኑም ለሽማግሌው፣ ለሴቷም ለወንዱ ፣ለላጤውም ለባለትዳሩ፣ ለዶክተሩም ለመሃይሙ... ለሁሉም ሁሌም ያስፈልጋል። አንድ እርምጃ ያለ እውቀት ሲሆን፡ የሰራነው ወይ ውድቅ ይሆናል ወይ ምንዳው ይቀንሳል፤ በተናገርነውም እንጸጸታለን። ጅህልና ጨለማ ሲሆን ዒልም ደግሞ ብርሃን ነው። ለጠመሙ መመሪያ፣ ለተራቡ ምግብ፣ ለታረዙ ልብስ፣ ለተጨነቁ እረፍት፣ ለደከሙ ጥንካሬ፣ ለፈዘዙት ንቃት፣ ድንበር ላለፉ ተስፋ፣ የልብ በሽታ ላለባቸው መድሃኒት... ነው። እንደው እስቲ እንደምሳሌ አሁን የፈተና ሰሞንም ስለሆነ ሁላችንም ጥናት ላይ ነን አይደል? ከሰላታችን እስክንሰርቅ ድረስ በማጥናት ድንበር የምናልፍም አለን አላህ ይታረቀንና!! ይህ ሁሉ ስናደርግ አላርም ቀጥረን ለሊት ስንነሳ፣ ቀኑን ሙሉ ቸክለን ስንውል፣ የምግብ ሰአታችን ቀንሰን፣ ከሰው ጋር ለማውራት መቆም እረ እንደውን ኦንላይን መግባት ራሱ እያዘናጋን ነው ብለን ሁሉን ነገር ትተን የምናጠናው ለፋይናል ፈተና ይጠቅመናል... ጥሩ ውጤት ለማምጣት ብለን አይደል?? አሁን እዚ ጊዜ ላይ ስለሆንን ስሜቱን እንረዳዋለን መቼም... 📌 ግን ሰማያትና ምድርን ያለ ምሰሶ ያቆመው በሆነው ጌታ እምላለሁ... ትክክለኛ የሸሪዓ ዒልም ለዘላለማዊው ለጊዜያዊው ህይወታችን ከዚህም በላይ ይጠቅመናል ያስፈልገናልም። ታድያ አሁን ለአካዳሚክሱ ከሆንነው በላይ ሆነልነታል ወይ??? ውሃ እንደሚጠማን ዒልም ይጠማናል ወይ? ምግብ እንደሚርበን ይርበናል ወይ? ከማዕዱ ስንርቅ ልባችንስ ባዶነት ይሰማዋል? ﴿بَلْ تُؤْثِرُونَ الْحَيَاةَ الدُّنْيَا۝١٦ وَٱلۡـَٔاخِرَةُ خَیۡرࣱ وَأَبۡقَىٰۤ ۝١٧﴾ [ ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡ መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡]  ሱረቱል አዕላ፡ 17 ©qireat6k @ fivekjemaa

«إذا كنتَ في نعمةٍ فارعَها، فإنّ الذنوبَ تُزيلُ النِّعَمَ، وصُنْها بطاعةِ اللهِ، فإنّ اللهَ سريعُ النِّقَمِ.»

🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا
🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ ﷺ 🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟 ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ከህፍ መቅራት ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ اللَّهُــمَّ صَلِ وَسَـــلِّمْ وَبَارِكْ على نَبِيِّنَـــا مُحمَّد ﷺ @fivekjemaa

የዒልሙ መሐንዲስ - ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ ! ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ በ1945 አ.ል በዋድላ ደላንታ ተወለዱ ። የተወለዱባት መንደር ስያሜ አቃዱር ይሰኝ ነበር ። ከአባታቸው አህመድ ሸይኽ ሙስጠፋ እና ከእናታቸው ተዋበች አጋሽ ነበር የተገኙት ። ገና በለጋ እድሜያቸው በአካባቢያቸው በነበረ የመኖሪያ እና የእርሻ ቦታ እጥረት ምክንያትና የኑሮው ነገር ስላልገራላቸው ከመንደሩ ለቀው እንዲወጡ ግድ ሆነባቸው ። ከመንደራቸው የመኮብለል ጉዳይ ለእናታቸው ወ/ሮ ተዋበች አጋሽ እንዲህ በቀላል የሚታይ አልነበረም ። ከባለቤታቸው ጋር እስከመለያየት አደረሳቸው ። የኑሮ መላ ያስኮበለላቸው የሸይኽ ሰዒድ አባት ፣ ታላቅ ወንድምና አጎታቸው አካባቢውን ለቀው ወደመተከል ያቀናሉ ። ሸይኽ ሰዒድ ግን ከእናታቸው ጋር በመንደራቸው ጸኑ ። አባታቸው ለደረስነት እንዲሁም ልጃቸው በኢልሙ ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ ልዩ ፍላጎት ነበራቸው ። በርሳቸው ግፊትና ተፅዕኖ ሸይኽ ሰዒድ የደረስነት ህይወት ጀመሩ ። መሰረታዊውን የፊቅህን ስርዓተ እውቀት ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ቦረና ተጉዘው ለ3 ዓመታት ያክል የነህዉንና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነውም ቢሆን የተፍሲር ቂርዓታቸውን ቀጠሉ ። በሀገራችን ኢትዮጵያ የሚሰጡ ኪታቦችን ካጠናቀቁ ቡሀላ ወደ አዲስ አበባ መጡ ። እዚህም የመጡበት ምክንያት ከዚህ ሀገር ወተው ወደ አረብ ሀገራት ተጉዘው የሀዲስ እንዲሁም ሌሎች ቂርአቶችን ለመቅራት አስበው ነበር ። በወቅቱም ሀጂ ሙሐመድ ራፊዕ ከሳውድ አረቢያ ተመልሰው አንዋር መስጂድ ላይ ደረሶችን ሲያቀሩ የሚያቀሩበት ነበርና ያገኟቸዋል ። ሃሳባቸው ከሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ ዘንድ ለመቅራት ነበር ። ቆይተው ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ ወደትውልድ መንደራቸው ይሄዱ ነበርና አልተሳካም ። ሸይኽ ሰዒድ ግን ቂርዓታቸውን ከሐጂ ሙሐመድ ወሌ ዘንድ ይቀጥላሉ ። ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕ እስኪመለሱ ድረስ . . .! ሐጂ ሙሐመድ ራፊዕም የጥቅምት ማገባደጃ ላይ ወደአዲስ አበባ ይመለሳሉ ። ሸይኽ ሰዒድ ወትሮም ጊዜያቸውን በአግባቡ የሚጠቀሙ ነበሩ ። ኩቱቡ ሲታን እሳቸው ጋር ቀርተው ማጠናቀቅ ቻሉ ። በማለዳው ክፍለ ጊዜ ደግሞ ከሐጂ ሙሐመድ ሳኒ ዘንድ ተፍሲርን ሙራጀዓ ሲያደርጉ ይቆያሉ ። አዲስ አበባ የነበራቸውን ቆይታ እንደጨረሱ ወደ ትውልድ ስፍራቸው ሄደው የማስቀራት ፍላጎት የነበራቸው ቢሆንም እዚሁ አንዋር መስጂድ የነበሩት 3 ታላላቅ ዑለሞች ፍቃደኛ ሳይሆኑ ይቀራሉ ።  ምክንያታቸው ደግሞ በወቅቱ የነበረው የደረሳ መጠን መብዛት ሸይኽ ሰዒድ እዚህ መቆየታቸውን ግድ ይል ነበር ። ትዕዛዙን ተቀብለው ሸይኽ ሰዒድ ዒልምን ማቅራት ጀመሩ ። በቆይታቸው የማረፍያ ስፍራና የእለት ጉርስ ማግኘት በጣም አስቸጋሪ ሆኖባቸው እንደነበር ይናገራሉ ። በዚያ ወቅትም ቀኑን ወሎ ሰፈር ድረስ በእግራቸው በመጓዝ ልጆችን ያቀራሉ ። እዚያው ቤትም ምሽቱን በጥበቃነት ማገልገል ይጀምራሉ ። በቀጣዩ የህይወት ምዕራፋቸው ለ15 አመታት አንዋር መስጂድ ዒልምን ሲያቀሩ ቆይተዋል ። ሸይኽ ሰዒድ በእድሜ ዘመናቸው በደማቁ ከሚወሱበት አበርክቷቸው መሐል በኢትዮጵያ ታሪክ  የመጀመሪያውን የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ማህበር ወይም በተለምዶ ሙነዘማን ማቋቋም ነበር ። እጅግ ብዙ ጥረትና ልፋት የታየበት ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች መብታቸው የሚጠይቁበትና ማንነታቸውን የሚያስከብሩበት ተቋም መሆን የቻለ 165 ያህል ቅርንጫፍ ማዕከላትን ማቋቋም የቻለ ነበር ። በጊዜው መንግስት ለተቋሙ ሕጋዊ እውቅናና ፈቃድ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም የኋላ ኋላ ስጋት ይሆናል በሚል አደረጃጀቱ እንዲፈርስ የተለያዩ ስራዎች ተሰርተዋል ። ሸይኽ ሰኢድ አህመድ ሙስጠፋ በዚህ ሁኔታ ላይም ሆነው በ 5 መስጂዶች ላይ ተፍሲርን በማቅራት ሙሉ በሙሉ አጠናቀው የነበረ ሲሆን በኒ መስጂድ ፣ አንዋር መስጂድ ፣ ሀሺም መስጂድ ይገኙበታል ። በዚህ አጋጣሚ ኡምራ የማድረግ እድል ያገኙት ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ ዑምራቸውን ፈጽመው ከ15 ቀናት በኋላ የመመለስ እቅድ ነበራቸው ። ያ ግን በተለያየ ምክንያት ሊሰምር አልቻለም ። እርሳቸው ሄደው ቀናት ባስቀጠሩበት አጋጣሚ አገር ውስጥ ነገሮች ተቀያይረዋል ። ታዲያ በጊዜው አንድ ሁነት ይከሰትና ነገሮች መልካቸውን ይቀይራሉ ። የወቅቱ መንግስት በአንዋር መስጂድ እጅግ ብዙ ወጣቶችን ህይወት በመቅጠፍ እንዲሁም ሙስሊሞች ተለይተው ድብደባ እንደተፈጸማባቸው  ፣ የተለያዩ መሻዒኾች እየታሰሩ የግድያ ፍርድም እየተፈረደባቸው እንደሆነና እሳቸውም በጥብቅ እየተፈለጉ እንደሆኑ ይሰማሉ ። ሸይኽ ሰዒድም በነዚህና መሰል ምክንያቶች ሳዑዲ አረቢያ ይሰነብታሉ ። በዚህ ሁኔታ ቀናት ቀናትን እየተካ ወራትም ወራትን እየተኩ አመታት ተቆጠሩ ። ሸይኽ ሰዒድ የመኖሪያ ፍቃድ ስላልነበራቸው ከአደባባይ ተሸሽገው ከማንም ጋር ሳይገናኙ ለ 2 አመት ያክል ከቆዩ ቡሀላ ሳዑዲ አረቢያ ይኖሩ የነበሩት ሸይኽ አህመድ ሀዲ ሸይኽ ሰኢድን አፈላልገው ያገኟቸዋል ። ሸይኽ አህመድ ያላቸውን አቅም ያውቁ ስለነበር  ወደ አራት የሚጠጉ የዓቂዳ ኪታቦችን እንዲያቀሩና የድምፃቸውም ቅጂ ወደ ኢትዮጵያ በካሴት መልክ ተዘጋጅቶ እንዲሰራጭ ያማክሯቸዋል ። ሸይኽ ሰዒድም በጣም ደስተኛ እንደሆኑ በመናገር ስራቸውን ይጀምራሉ ። ቆይቶ ሙሉ ለሙሉ ስራቸውን በማጠናቀቅ ሸይኽ አህመድ ሙአሰተል ሀረመይን ከሚባል ድርጅት ጋር የነበራቸውን ትውውቅ ተጠቅመው የሸይኽ ሰዒድ አህመድ ድምፅ ተቀድቶ በካሴት መልክ ወደ ኢትዮጵያ እንዲሰራጭ ሆነ ። ስራቸው ተወዳጅነት ማትረፍ የቻለና በብዙዎች ዘንድ የሚወሳ መሆን ችሏል ። ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖች ጭምር ወደው ያደምጡት እንደነበር ይወሳል ። ሸይኽ ሰዒድ ሌላኛው ግዙፍ እድል ብለው የሚያነሱት አንጋፋው አፍሪካ ቲቪ ምስረታውን ያደርጋል ። እሳቸውም በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪው በሆነው ኢስላማዊ የሳተላይት የቴሌቭዥን ጣቢያ የቁርዓን ተፍሲርን ማስማር ጀመሩ ። የብዙዎች ዘንድ ተወዳጅ እና ተናፋቂ ሆኖ የብዙዎችን ልብ ከቁርዓን ጋር አዛምዷል ። በዚህ ሁሉ ውስጥ የ9 ልጆች አባት የሆኑት ሸይኽ ሰዒድ ቤተሰባቸውን አልዘነጉም ነበር ። ከቅርብ ዓመታት በፊት ለ23 ዓመታት ርቀዋት ወደቆዩት አገራቸው በመመለስ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ማገልገላቸውን ቀጥለዋል ። በአፍሪካ ቲቪ አል ፈታዋን ጨምሮ የተለያዩ ሸሪዓዊ መሰናዶዎች እያቀረቡ ያሉ ሲሆን አፍንጮ በር የሚገኘው የአቅሷ መስጂድ ዒማምና ኸጢብ በመሆን ከዚያን ባሻገር በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት የዑለሞች ምክር ቤት አባል በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ ። አላህ ( ሱ.ወ ) ከመልካም አበርክቷቸው ጋር አጽንቶ በረዥም እድሜ በበረታ አፍያ ያቆያቸው ። #አፍሪካ_ቲቪ #የህይወት_ጎዳና