en
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

Open in Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

Show more
1 157
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-130 days
Posts Archive
Jumu‘ah Practice Check Which of the following Sunnah actions did you perform today? This poll is only for self-reflection, not judgment. (Choose all that apply — honesty is for your own growth)
Anonymous voting

🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا
🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉 ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ ﷺ 🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟 ۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦ ➊ መታጠብ ➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች) ➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም ➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ ➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት "ሱረቱል ካህፍን በጁምዓ ቀን መቅራት፤ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል የሚበራ ብርሃን (ኑር) ይሆንልሃል/ ይሆንልሻል።" ይህ ማለት አላህ እስከሚቀጥለው አርብ ድረስ ልብአችንን በብርሃን ይሞላዋል፣ ትክክለኛውንና ስህተቱን የምንለይበትን ጥበብ ይሰጠናል ማለት ነው። ➏ በጊዜ መስጂድ መግባት ➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ ‣ በመጨረሻው ሰአት ዱዓ ማድረግ (ማለትም ከአስር በኋላ ኡማውን በዱዓ እናስታውስ በውዱ ነብያችን ላይ ሶለዋት ማብዛትንም አንርሳ❤️ اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً ﷺ 🌟 መልካም ጁምአ🌟 @fivekjemaa

ጀመዓችን ተጨማሪ ቪዲዮ ኤዲተር  ያስፈልገዋልና ቪዲዮ ኤዲት በማድረግ ጀመዓውን ማገዝ ምትችሉ በ @Aaumuslimstudentsunion1 አናግሩን። ትልቁ ምንዳ ከአሏህ ነውና ባላችሁ እውቀት ኡማውን ከማገዝ አትቦዝኑ። @aaumsu

ጀመዓችን ተጨማሪ ቪዲዮ ኤዲተር  ያስፈልገዋልና ቪዲዮ ኤዲት በማድረግ ጀመዓውን ማገዝ ምትችሉ በ @Aaumuslimstudentsunion1 አናግሩን። ትልቁ ምንዳ ከአሏህ ነውና ባላችሁ እውቀት ኡማውን ከማገዝ አትቦዝኑ። @aaumsu

⭐️ Announcement: Short Online Course ⭐️ ⭐️ Ahkam al-Siyam ⭐️ 👋 Assalamu alaykum wa rahmatullahi wa barakatuh We are pleased to announce a short online course based on “Memo on the Rulings of Fasting (مذكرة في أحكام الصيام)”, aimed at helping Muslims learn the essential rules of fasting correctly before Ramadan. 🕌 What This Course Covers: - Definition and ruling of fasting - Conditions and pillars of fasting - Recommended acts and Sunnahs - Acts that invalidate the fast - Permissible matters for the fasting person - Excuses for breaking the fast - Qada, Fidya, and Kaffarah - Common mistakes during fasting - Contemporary questions related to fasting 🗓 Registration Period: 📅 February 4 – February 8 📝 Registration Requirements: To complete registration, both steps are required: 👉 Join the Jemmah Qira’at Telegram Channel 👇 https://t.me/qirat_channel_5k 👉 Fill out the Google Registration Form https://forms.gle/rrJ4A8LCqqdvgga99 📌 Note: Learning the rulings of fasting is obligatory for everyone who intends to fast. 📢 Stay tuned for course details and schedule. 🤲 May Allah grant us correct knowledge and accepted worship.

As we prepare our hearts for Ramadan, we must understand the two greatest inner struggles: desire and pride.
The Prophet ﷺ said to his companions: “In the sexual act of one of you there is charity.” They said, “O Messenger of Allah, when one of us fulfills his desire, will he have a reward?” He ﷺ said, “Do you not see that if he were to satisfy it in a haram way, he would bear sin? Likewise, if he satisfies it in a halal way, he will have reward.”
📖 Sahih Muslim Desire itself is not evil — how we channel it is what matters. If a person slips due to desire, the door of repentance is always open. This is why Adam (عليه السلام) disobeyed due to desire, but he immediately returned to Allah, repented sincerely, and Allah accepted him. But pride is different.
The Prophet ﷺ said: “Whoever has an atom’s weight of pride in his heart will not enter Jannah.”
📖 Sahih Muslim Iblis disobeyed Allah not because of desire, but because of pride and he never returned. The companions understood this deeply. When Abu Dharr (رضي الله عنه) once insulted Bilal (رضي الله عنه) by referring to his lineage, the Prophet ﷺ said to him: “You are a man who still has ignorance (jahiliyyah) in you.”  📖 Bukhari & Muslim Abu Dharr was shattered. He did not defend himself. He did not justify his words. Instead, he placed his cheek on the ground and said to Bilal: “Step on my face, until I know humility.” This is how pride is crushed. As Ramadan approaches, let us prepare properly: * Desire → guide it through halal * Pride → destroy it completely, even if it is hidden This is how hearts become ready for Ramadan....

photo content

ከሸዕባን አጋማሽ በኋላ መፆም ~ ከሸዕባን አጋማሽ በኋላ መፆምን በተመለከተ በዑለማዎች ሁለት አይነት ሀሳቦች ተሰንዝረዋል፡፡ * አንደኛው ወገን፡- መፆሙን የሚከለክሉ ናቸው፡፡ በርካታ ሻፍዒያዎች ይህንን አቋም መርጠዋል፡፡ ማስረጃቸውም፡- “ሸዕባን ሲጋመስ እንዳትፆሙ” የሚለው ሐዲሥ ነው፡፡ [አቡ ዳውድ፡ 2337] [ቲርሚዚይ፡ 738] * ሌላኛው ወገን፡- ከሸዕባን አጋማሽ በኋላ መፆም ይቻላል የሚሉ ናቸው፡፡ ይሄኛው ምርጫ የብዙሃን ዑለማዎች ምርጫ ነው፡፡ ማስረጃዎቻቸው፡- 1. አቡ ሁረይራ ባስተላለፉት ሐዲሥ የአላህ መልእክተኛ ﷺ “ረመዳንን በአንድ ቀን ፆም ወይም በሁለት ቀን ፆም አትቀደሙት፡፡ የተለመደን ፆም የሚፆም ሰው ቢሆን እንጂ፡፡ እሱ ግን ይፁም” ብለዋል፡፡ [ቡኻሪ፡ 1969] [ሙስሊም፡ 1156] ይሄ ሐዲሥ ረመዳን ሊገባ አንድና ሁለት ቀን እስከሚቀረው ድረስ መፆም እንደሚቻል ይጠቁማል፡፡ ስለዚህ ከሸዕባን አጋማሽ ጀምሮ ረመዳን ሊገባ አንድና ሁለት ቀን እስከሚቀረው ድረስ መፆም ይቻላል ማለት ነው፡፡ ቀድሞ ካስለመደው ፆም ጋር የገጠመለት ሰው ግን ከረመዳን በፊት ያለውን አንድና ሁለት ቀንም ጭምር መፆም ይችላል፡፡ 2. እናታችን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዲህ ብላለች፡- “ነብዩ ﷺ ከረመዳን በስተቀር ሙሉ የፆሙት ወር የለም፡፡ እንደ ሸዕባን ፆም ያበዙበት አላየሁም፡፡” [ቡኻሪ፡ 1914] [ሙስሊም፡ 1082] በሌላ ዘገባ ደግሞ እንዲህ ብላለች፡- “ሸዕባንን ጥቂት ሲቀር እንዳለ ይፆሙት ነበር፡፡” [ሙስሊም] 3. እናታችን ኡሙ ሰለማ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዲህ ብላለች፡- “ነብዩን ﷺ ሁለት ወሮችን አከታትለው ሲፆሙ አላየሁም፣ ሸዕባንና ረመዳንን ቢሆን እንጂ፡፡” [ቲርሚዚይ: 736] አልባኒይ ሶሒሕ ብለውታል፡፡ [ሶሒሑ ተርጊብ ወተርሂብ፡ 1025] እዚህ ላይ የሸዕባንን አብዛኛውን ለማለት እንጂ ሙሉ ለማለት አይደለም፡፡ በዐረብኛ በዚህ መልኩ መግለፅ የተለመደ ነውና ይላሉ ዑለማዎች፡፡ እነዚህ ከሸዕባን አጋማሽ በኋላ መፆም ይቻላል የሚሉ ዓሊሞች የሚጠቅሷቸው ማስረጃዎች ናቸው፡፡ ሌሎችም ማስረጃዎች አሉ፡፡ ግን ከሸዕባን አጋማሽ በኋላ መፆም አይቻልም የሚሉ አካላት ያቀረቡትን “ሸዕባን ሲጋመስ እንዳትፆሙ” የሚለውን ሐዲሥ በተመለከተ “መፆም ይቻላል” የሚሉት ዓሊሞች ምን አሉ? 1. ከፊሎቹ ሐዲሡ ደካማ ነው ሲሉ ዘግተዋል፡፡ ኢማሙ አሕመድ፣ ኢብኑ መዒን፣ አቡ ዙርዐህ፣ ዐብዱረሕማን ብኑ መህዲ፣ በይሀቂ እና ሌሎችም ሐዲሡ “ሙንከር ነው” በማለት ደካማ እንደሆነ ከገለፁት ውስጥ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ 2. ከፊሎቹ መልእክቱ የተገደበ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ ሐዲሡን ቲርሚዚይ፣ ኢብኑ ሒባንና ኢብኑ ማጃህ ሶሒሕ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን ኢብኑ ሐዝም፣ ኢብኑል ቀይምና አልባኒይ ሐዲሡን ደካማ ነው ያሉትን ጠንከር አድርገው ሞግተዋል፡፡ ሆኖም ግን የሐዲሡ መልእክት ከነጭራሹ ከሸዕባን አጋማሸ በኋላ መፆምን ለመከልከል ሳይሆን ቀድሞ ልምድ ሳይኖረው ወይም በወሩ የመጀመሪያ አጋማሽ ምንም ሳይፆም ከሁለተኛው አጋማሽ በኋላ የሚፆምን ነው የተከለከለው ይላሉ፡፡ ኢብኑ ባዝ፣ ዐብዱል ሙሕሲን አልዐባድና ሌሎችም ይህንን ሀሳብ ከደገፉት ውስጥ ናቸው፡፡ 3. ከፊሎች ደግሞ በሐዲሡ ውስጥ የተገለፀው ክልከላ ሐራምነት የሚደርስ ሳይሆን እንደማይበረታታ ለመጠቆም ነው ይላሉ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ለረመዳን ፆም መዳከም እንዳይከተል ለማሳሰብ ነው ይላሉ፡፡ ሸይኽ ኢብኑል ዑሠይሚን ሐዲሡ ሶሒሕ እንኳን ቢሆን ክልከላው ሐራምነት አይደርስም ይላሉ፡፡ አልቃሪም ይህንን ሀሳብ መርጠዋል፡፡ ሲጠቃለል፡- 1. ከሸዕባን አጋማሽ በኋላ መፆም የሚከለክለውን ሐዲሥ አብዛኞቹ ዑለማዎች ደካማ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን ከላይ የቀረቡትን ማስረጃዎች መነሻ በማድረግ በሁለተኛው የሸዕባን አጋማሽ ውስጥ መፆም እንደሚቻል ገልፀዋል፡፡ 2. ነገር ግን * የመጀመሪያው አጋማሽ ውስጥ ያልፆመ፣ * ሰኞና ሐሙስ ወይም መሰል ልማድ የሌለው ሰው እንዲሁ ከሸዕባን አጋማሽ በኋላ ለመፆም ባይነሳ የተሻለ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ ከልካዩን ሐዲሥ “ሶሒሕ ነው” የሚሉ ዓሊሞች ትንታኔ ጠንከር ያለ ስለሆነ ከሸዕባን 15 በኋላ #ያለምንም_መነሻ ፆም በመጀመር እራሳችንን ኺላፍ ውስጥ ከማስገባት ልንቆጠብ ይገባል፡፡ 3. ሰኞና ሐሙስ ወይም ሌላ ያስለመደው ፆም ያለው ሰው፣ እንዲሁም በመጀመሪያው የሸዕባን አጋማሽ ውስጥ ሲፆም የነበረ እና መሰል ሰበቦች ያሉት ሰው ፍላጎቱ ከሆነ በሁለተኛውም አጋማሽ መፆም ይችላል፡፡ ወልላሁ አዕለም። © ኢብኑ ሙነወር

🗯 ‎እኔም_ባለአደራ_ነኝ!!! 🗯 ‎ 🔥 ‎[ ••• አዲስ ነገር ••• ] 🔥 ‎ ✨ ‎የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ኅብረት በቀረው የዕረፍት ጊዜያችን በያለንበት ሆነን የሙተነቂብ እህቶቻችንን አደራ የምንወጣበት « እኔም ባለአደራ ነኝ» የተሰኘ የ 1 ሳምንት ንቅናቄ ይዞልን መጥቷል። ‎ ‎አደራው ገንዘብ አይደለም... ‎አደራው ዕቃ አይደለም... ‎ ‎••• አደራው ቃል ነው! አደራው እውቀት ነው! አደራው ግንዛቤ ነው! አደራው ማድረስ ነው! አደራው ማስተላለፍ ነው! ‎ እስኪ እራሳችንን ከመፈተሽ እንጀምር፡ ፈተና ጨርሰን ወደቤት ከገባን ጀምሮ (ባለፈው 1 ሳምንት ጊዜ ውስጥ) ምን ያህል ጊዜ ከቤተሰቦቻችን፣ ከዘመዶቻችን፣ ከጓደኞቻችን፣ ከጎረቤቶቻችን... ጋር በኒቃብና በመብትነቱ ዙሪያ አውርተናል?! ‎ ‎~ ከዛሬ ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 7 ቀናት ግን ሙተነቂብ እህቶቻችን፦ ‎ ‎• ስለ እኛ፤ ‎• ዩኒቨርሲቲው አግባብነት በሌለው መመሪያው አማካኝነት እየተጋፋቸው ስላሉ መብቶቻችን፤ ‎• ስለሒጃባችን፣ ስለክብራችንና ስለነጻነታችን ዋጋ፤ ‎ ‎ከቤታችሁ በመጀመር ላላችሁበት አካባቢ ማኅበረሰብ ሁሉ አድርሱልን ሲሉ አማናችንን "እንካችሁ" ብለውናል። ‎ ‎ከዚህ በኋላ ባሉት 7 ቀናት የቤታችን፣ የአካባቢያችን፣ የሰፈራችን፣ የዘመድ ስብስቦቻችን፣ የጓደኝነት ቡድኖቻችን ዋነኛው የመወያያ አጀንዳ በአላህ ፈቃድ «ኒቃቧ» ይሆናል። ይህንን ለመወያየት መታደል በራሱ መመረጥ ነውና ••• በአደራችን ላይ አደራ!!! ••• ። ‎ እኔም ባለአደራ ነኝ!!! ©aaumsu @fivekjemaa

ሐዲሰል ቁድሲ! ከአቡ ሁረይራ (ተይዞ፡ ረሱል ከጌታቸው በሚያወሩት የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦ ﴿أَذْنَبَ عَبْدٌ ذَنْبًا، فَقالَ: اللَّهُمَّ اغْفِرْ لي ذَنْبِي، فَقالَ تَبارَكَ وَتَعالى: أَذْنَبَ عَبْدِي ذَنْبًا، فَعَلِمَ أنَّ له رَبًّا يَغْفِرُ الذَّنْبَ، وَيَأْخُذُ بالذَّنْبِ، ثُمَّ عادَ فأذْنَبَ، فَقالَ: أَيْ رَبِّ اغْفِرْ لي ذَنْبِي، فَقالَ تَبارَكَ وَتَعالى: عَبْدِي أَذْنَبَ ذَنْبًا، فَعَلِمَ أنَّ له رَبًّا يَغْفِرُ الذَّنْبَ، وَيَأْخُذُ بالذَّنْبِ، ثُمَّ عادَ فأذْنَبَ فَقالَ: أَيْ رَبِّ اغْفِرْ لي ذَنْبِي، فَقالَ تَبارَكَ وَتَعالى: أَذْنَبَ عَبْدِي ذَنْبًا، فَعَلِمَ أنَّ له رَبًّا يَغْفِرُ الذَّنْبَ، وَيَأْخُذُ بالذَّنْبِ، اعْمَلْ ما شِئْتَ فقَدْ غَفَرْتُ لَكَ﴾ “አንድ (የአላህ) ባሪያ ኃጢአት ፈፀመና ‘አላህ ሆይ! ኃጢአቴን ይቅር በለኝ’ አለ። አላህም፦ ‘ባሪያዬ አንድ ኃጢአት ሠርቶ ኃጢአቶቹን ይቅር የሚልና በእሱም የሚቀጣ አንድ ጌታ እንዳለው አውቋል’ አለ። ከዚያም በድጋሚ ኃጢአት ሠራና ‘ጌታዬ ሆይ! ኃጢአቴን ይቅር በለኝ’ አለ። አላህም፦ ‘ባሪያዬ አንድ ኃጢአት ሰርቶ ኃጢአቶችን ይቅር የሚልና በእሱም የሚቀጣ አንድ ጌታ እንዳለ አውቋል’ ይላል። ከዚያም በድጋሚ ኃጢአት ሰርቶ ‘ጌታዬ ሆይ! ኃጢአቴን ይቅር በለኝ’ አለ። አላህም፦ ‘ባሪያዬ አንድ ኃጢአት ሰርቶ ኃጢአቶችን ይቅር የሚልና በእሱም የሚቀጣ አንድ ጌታ እንዳለ አውቋል የፈለግኸውን ብትሠራም ይቅር ብዬሃለሁ’ ይለዋል።” ቡኻሪ (7507) ሙስሊም (2758)

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته በነገው ዕለት final exam ለምትጀምሩ ፍሬሽ ወንድምና እህቶች ሁሉ መልካም እድል እንመኛለን። ወደ ፈተና ከመግባታችሁ በፊት አላህ ፈተናውን እንዲያገራላችሁ ዱዓ ማድረጋችሁን አትዘንጉ!!!!!! እነዚህን እና መሰል ዱኣዎችን ብታደርጉ መልካም ነው ። { رب اشرح لي صدري ويسر لي أمري واحلل عقدة من لساني يفقهوا قولي } اللهم لا سهل إلا ما جعلته سهلا وأنت تجعل الحزن إذا شئت سهلا. يا حي يا قيوم برحمتك أستغيث أصلح لي شأني كله ولا تكلني إلى نفسي طرفة عين. አላህ ፈተናውን እንዲያገራላችሁ፣ ጥሩ ወጤት እንዲሰጣችሁ :የምትፈልጉትን ዲፓርትመንት እንዲወፍፍቃችሁ ምኞታችን ነው።            

🌙 Reminder– A Special Day Tomorrow اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎ Dear brothers and sisters, Let us not forget :Tomorrow is a very special day: * It is Monday * It falls in the blessed month of Shaban * And it is from Ayyam al-Bid (the white days: 13th, 14th, 15th) 📌 Why is Shaban special? Shaban is a month that many people neglect, yet it is a month of great honor. Usāmah ibn Zayd (رضي الله عنه) asked the Prophet ﷺ: “O Messenger of Allah, I do not see you fasting in any month as much as you fast in Shaban.” The Prophet ﷺ replied: “That is a month people are heedless of, between Rajab and Ramadan. It is a month in which deeds are raised to the Lord of the worlds, and I love that my deeds be raised while I am fasting.” (Reported by an-Nassiand others – authentic) Key lessons for us: * Shaban is a month when our deeds ascend to Allah * It is a time when many people are distracted—so worship now is more beloved * Fasting on Monday follows the Sunnah * Fasting the Ayyam al-Bid carries great reward 🤲 Let us not be among the heedless. Let us prepare our hearts for Ramadan by fasting, making dua, and renewing our intentions. May Allah accept our deeds as they ascend to Him.

🌙 Reminder– A Special Day Tomorrow اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎ Dear brothers and sisters, Let us not forget :Tomorrow is a very special day: * It is Monday * It falls in the blessed month of Shaban * And it is from Ayyam al-Bid (the white days: 13th, 14th, 15th) 📌 Why is Shaban special? Shaban is a month that many people neglect, yet it is a month of great honor. Usāmah ibn Zayd (رضي الله عنه) asked the Prophet ﷺ: “O Messenger of Allah, I do not see you fasting in any month as much as you fast in Shaban.” The Prophet ﷺ replied: “That is a month people are heedless of, between Rajab and Ramadan. It is a month in which deeds are raised to the Lord of the worlds, and I love that my deeds be raised while I am fasting.” (Reported by an-Nassiand others – authentic) Key lessons for us: * Shaban is a month when our deeds ascend to Allah * It is a time when many people are distracted—so worship now is more beloved * Fasting on Monday follows the Sunnah * Fasting the Ayyam al-Bid carries great reward 🤲 Let us not be among the heedless. Let us prepare our hearts for Ramadan by fasting, making dua, and renewing our intentions. May Allah accept our deeds as they ascend to Him.

✨💫እነሆ አጅር የማፈሻ ተከታታይ ቀናቶች መጡልን!!!✨ 💥የሻዕባን አያመል ቢድ💥 ሻዕባን 13-እሁድ ሻዕባን 14-ሰኞ ሻዕባን 15-ማክሰኞ አሁን ያለነው የሻዕባን ወር ላይ ነው::ረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በብዛት የፆሙት ወር ነው::ለረመዷን እንዲያግዘን ከወዲሁ መልካም ስራዎች ላይ እንበራታ። እነዚህን ቀናቶች እንፁም:: መፆም ካልቻልን እንኳ እህት ወንድሞቻችንን ወደዚህ ኸይር ስራ እንጋብዛቸው:: ኢንሻአላህ ወደ ኸይር ያመላከተ ልክ እንደ ሰሪው ይሆናልና:: ©

ለምንድን ነው ስደውል ያላነሳሽው? አስተማሪ ታሪክ ~ ለሆነ ጉዳይ ለሶስት ቀናት መንገድ ወጣሁ። ሌላኛው ሃገር እንደደረስኩ ሚስቴንና አንድ ልጄን ደህንነታቸውን ለማስረገጥ ደወልኩ። ከዚህ በፊት ከነሱ ተለይቼ አላውቅም። እነሱም መራቄን አያውቁትም። ካገባሁ ሶስት አመቴ ነው። የሆነ ሆኖ ስልኬ አልተነሳም። ስልኬ ከእጄ ሳይነጠል ሶስት ቀናት አለፉ። ያለ ግነት በየ እሩብ ሰዓቱ ቢበዛ በየ ግማሽ ሰዓት እደውላለሁ። ምላሽ የለም። በሃይለኛ ተበሳጨሁ። ወንድሜ እና እህቴ ላይ ደወልኩ። የትንሿን ቤተሰቤን ደህንነት እንዲያረጋግጡልኝ ጠየቅኳቸው። ሰላም እንደሆኑ ነገሩኝ። አላመንኳቸውም። የሚስቴ እናት (አክስቴ) ላይ ደወልኩ። ሰላም እንደሆኑ ነገረችኝ። ስልካቸውን እንደምጠብቅ ነገርኳት። ብጠብቅ ብጠብቅ አንድም የሚደውል የለም። ሶስቱ ቀናት ረጃጅም ሶስት ወራት ያክል ሆነው አለፉ። አንዳንዴ ቁጣዬ ከውስጥ ሲገነፍል ይሰማኛል። ሌላ ጊዜ በሁኔታው በጣም እየተገረምኩ ምክንያቱን ለማወቅ እሞክራለሁ። ሸይጧን አስፈሪ ጉትጎታዎችን ደግሞ ደጋግሞ ያመጣብኛል። ቀናቱ አለፉ። ወደ ሃገሬ ተመለስኩ። እግሬ እንደረገጠ ወደ ቤቴ ነበር የበረርኩት። እንደደረስኩ በሩን አንኳኳለሁ። እሱም ሳይበቃኝ ደወሉን ላይ በላይ እደውላለሁ። ባለቤቴ በሩን ከፈተች። ከነ ሙሉ ውበቷ፣ ከነ ሙሉ ድምቀቷ። ባማረ በደመቀ ሁኔታ ተቀበለችኝ። ከባድ አጋጣሚ ነበር። ልጄ ከኋላዋ አለ። አይኖቹ በደስታ ይጨፍራሉ። ሊያቅፈኝ እየሮጠ መጣ። እኔ እንደደነዘዘ ሰው ሆኛለሁ። ሰበቡም ጠፋኝ። በፍጥነት በቁጣዬ ቦታ ግርምት ተተካ። ባለቤቴን የዚህ ሁሉ ቸልትኝነት ምክንያቱ ምን እንደሆነ ጠየቅኳት። ጉዞዬን አቋርጬ በፍጥነት ልመለስ ተቃርቤ ነበር። አጉል ጥርጣሬ ከያቅጣጫው ወሮኝ ነበር። ባለቤቴ ተረጋግታ መለሰችልኝ። "ለእናትህ ደውለሃል?" አለችኝ። ለምን እንደጠየቀችኝ ምክንያቷ ባይገባኝም እንዳልደወልኩ ነገርኳት። ንግግሯ ገዳይ ነበር ። እንዲህ አለችኝ፡ "በነዚህ ቀናት ውስጥ ስሜትህ ምን እንደሆነ አየህ አይደል? የእናትህም ስሜት ይሄው ራሱ ነው፣ ለቀናት ሳትደውልላት ስትቆይ። ናፍቆት ለብልቧት፣ ስጋት ገብቷት እሷ ካልደወለች በቀር አንተ ደውለህ ድምጿን አትሰማም። ይሄን ጉዳይ በተደጋጋሚ ላስረዳህ ሞክሬያለሁ። የምትረዳ ግን አልሆንክም። ክቡር ባለቤቴ! ከዚህ የተሻለ መልእክቴን የማደርስበት መንገድ አላገኘሁም። እድሜዋ ትንሽ ዐቅሏ ግን ትልቅ የሆነችዋን ሚስቴን አፈርኳት። አንገቴን ደፋሁ። ትምህርቱ በሚገባ ነው የደረሰኝ። የመኪናዬን ቁልፍ እያቀበለችኝ ወደ ጀሮዬ ጠጋ ብላ "ጀነትህ እየጠበቀችህ ነው" አለችኝ። እድሜ ልኬን የማልረሳውን ትምህርት ከጠቢቧ ሚስቴ ተምሬ ወደ መጀመሪያዋ ውዴ ወደ እናቴ ሄድኩኝ። ፀፀት በማይጠቅምበት ቀን ከመፀፀት ነፍሴን ስላተረፈችኝ ውለታዋን መቼም አልረሳም። ለዚች ጠቢብና አስተዋይ ሚስት ምስጋና ይገባታል። አሳምራ ኮትኩታ ላሳደገቻት እናቷ ምስጋና ይገባታል። እሷን ለመረጠችልኝ እናቴ ምስጋና ይገባታል። እሷን ሰበብ አድርጎ በእዝነቱ ከእንቅልፌ ያነቃኝ ጌታ ምስጋና ይገባዋል። እናቴ! እናታቶቻችሁ ! በዱንያ ያሉ ጀነቶቻችን ናቸው። ሌላው ቢቀር በየቀኑ በመደወል እንኳ ቢሆን አትርሷቸው። ይሄ ትንሹ ነገር ነው። ልቦቻቸው እኛን ይጠብቃሉ። ለኛ ዱዓእ ያደርጋሉ። በየ ሰዓቱ ስለኛ ይጨነቃሉ። እያሰቡ እየተጨነቁም ደጋግመው በመደወል እንዳይረብሹን በመስጋት ከመደወል ይታቀባሉ። ባሎቻችሁን፣ ሚስቶቻችሁን ወላጆቻቸውን እንዲያስቡ በማስታወስ አግዙ። © አሏህ(ሱ.ወ) ሁሌ ቤተሰቦቻቸውን ከሚያስታውሱ እና ከሚንከባከቡ መልካም ባሮቹ ያድርገን።🤲 በምንዘነጋበት ጊዜም እንደዚች ከጎናችን ሁና የምታስታውሰን መልካም የሆነችን እንስት አላህ ይወፍቀን።🤲 እህቶችም ለባሎቻችሁ እውነተኛ አጋር በመሆን ከራሳችሁ አልፋችሁ ለባሎቻችሁም የመልካም ስራ ሰበብ የምትሆኑ አላህ ያድርጋችሁ።🤲 ©aau6kilojemea

ለጥንቃቄ❗️❗️❗️ 📌በእጁ ፌስታል ይዞ የተገኘ ከነገ ጀምሮ ይቀጣል። 📌ለደንብ አስከባሪዎች ስልጠናና ትዕዛዝ ተሰጥቷል። አልሰማንም እንዳትሉ‼ 📌 "በ5 ብር ፌስታል 5,000 ብር እንዳትቀጡ" ተ
ለጥንቃቄ❗️❗️❗️ 📌በእጁ ፌስታል ይዞ የተገኘ ከነገ ጀምሮ ይቀጣል። 📌ለደንብ አስከባሪዎች ስልጠናና ትዕዛዝ ተሰጥቷል። አልሰማንም እንዳትሉ‼ 📌 "በ5 ብር ፌስታል 5,000 ብር እንዳትቀጡ" ተብሏል የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከነገ ጥር 23 ጀምሮ  ለአንድ ጊዜ አገልግሎት ብቻ የሚውሉ የፕላስቲክ ከረጢቶችን የሚጠቀሙ፣ የሚያመርቱና ወደሀገር ውስጥ የሚያስገቡ አካላትን መቅጣት ሊጀመር መሆኑን አሳውቋል። ህጉን ተላልፎ በሚገኝ ማንኛውም አካል ላይ በእጅ ይዞ ለተገኘ ግለሰብ፡ 📌ከ2,000 እስከ 5,000 ብር ቅጣት። 📌ለአምራቾች፣ አከማችዎች እና አከፋፋዮች ከ50,000 እስከ 200,000 ብር ቅጣት እና እስከ አምስት አመት የሚደርስ ጽኑ እስራት ያስቀጣል። ለአንድ ጊዜ አገልግሎት ብቻ የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶችን ማምረት፣ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባትና ይዞ መገኘት የሚከለክለው አዋጅ ከሐምሌ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የጸደቀ ቢሆንም፣ ባለስልጣኑ የስድስት ወራት የሽግግር ጊዜ ሰጥቶ መቆየቱን ገልጿል። የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን እንደገለፀው እገዳው ሁሉንም አይነት ፌስታሎች 📌ጥቁር፣ 📌ነጭ፣ 📌ትናንሽ እና 📌ትልልቅ እንደሚያጠቃልል እና በእጁ ፌስታል ይዞ የተገኘ ከነገ ጀምሮ እንደሚቀጣ አሳውቋል፡፡  በመሆኑም የህግ አስከባሪዎች አስፈላጊውን ስልጠና ወስደው በየአካባቢው ለክትትል ዝግጁ የሆኑ ሲሆን ቅጣቱ ይጀመራል ተብሏል፡፡ ​ ©

አብሽሪ!! የኔዋ ጀግና እህት! የጌታሽን ትእዛዝ አክብረሽ ያ ውቡን አካልሽን በጣም ውብ በሆነ ጨርቅ የሸንፈሽዋ! አዎ አንቺን ነው አላህ ይጠብቅሽና! ነቢይሽ  እነደነገሩሽ "ዱንያ ለሙእሚን እስርቤት ናት"...ታዲያ ውዴዋ ምንም አይነት ፈተና: እንግልት: ስቃይን ብታስተናግጂ እስር ቤት ውስጥ ያለሽ መሆኑን አትዘንጊ... አትርሺ ይህች ዱንያ ጊዜያዊ መቆያሽ ብቻ ናት!... ዘላለማዊ መኖሪያሽ ግን አኺራ ናት!:: ዱንያ ከባድ ብትሆንብሽ በቆይታሽ ልክ ነው...አላህ ይጠብቅሽና ኣኺራም ከባድ ብትሆንብሽ በቆይታሽ ልክ ነው! ታዲያ እቴዋ የትኛው ለመሸከም ይከብዳል እ?....አኺራቸውን የዘነጉ ሰዎች ይህች ትንሿን ፈተና አግዝፈው ቢያሳዩሽ የጌታሽን የማይሻር ቃልኪዳንን አስቢ...እሱ በእርሱ መንገድ ላይ የታገሉ እንዲሁም የታገሱትን አያሳፍርምና!! እነዚያም በእኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን፡፡ አላህም በእርግጥ ከበጎ ሠሪዎች ጋር ነው፡፡ [ 29:69] እቴዋ አደራ የቂንሽን ነፍሲያሽ እንዳትሸረሽረው!!...ፈተናዎች የበዙብሽ ጊዜ የመንገዱ ማብቂያ እንደሆኑ አታስቢ!! እቴ አደራ ልብሽ እንዳትወላውል!! ጌታሽ ለነገሮች በሙሉ በቂ እንደሆነ አሁንም ለልብሽ ንገሪው!...እሱን ለፈራ መውጫን እንደሚያደርግለትም ደጋግመሽ አስታውሺው!! ልክ ከፍ ያለው ጌታሽ  እንዳለው:- ...وَمَن يَتَّقِ اللَّهَ يَجْعَل لَّهُ مَخْرَجًا ...አላህንም የሚፈራ ሰው ለእርሱ መውጫን ያደርግለታል፡፡ [65:2] በትግልሽ ላይ በርቺ!...ስንቱ ሰው መሰለሽ ነፍሲያውን ማሸነፍ አቅቶት በተዘፈቀበት ሐራም ነገር እየተፈተነ ያንን መዕሲያ ላይ ለመዘውተር እየታገለ ያለው?! ጌታሽ ግን አንቺን በሱ መንገድ ላይ ከሚታገሉት ጋር መድቦሽ ለዚህ ፈተና እጩ ሲያደርግሽ አትደሰቺም ኦይ!?...አመስግኚ!!...ደግሞ አንቺ ብቻ በትዕግስት እና በሶላትሽ ላይ ታገሺ እንጂ አላህ ከአንቺ ጋር ነው!! ياَأَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اسْتَعِينُوا بِالصَّبْرِ وَالصَّلَاةِ ۚ إِنَّ اللَّهَ مَعَ الصَّابِرِينَ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በመታገስና በሶላት ተረዱ፡፡ አላህ (በእርዳታው) ከታጋሾች ጋር ነውና፡፡ [2:153] አደራ!! ያንን የምወድልሽ የክብር ካባሽ ላይ አትደራደሪ!! እንደዚያ የምድር ክዋክብት መሾለሽ ላይሽ እሻለውና!! Šaaumsu @fivekjemaa

የጁሙዓ ማለዳ ስንቅ 🌅 የሳምንቱ ምርጥ ቀን ጁሙዓ መጣ! ይህ ቀን የሙስሊሞች የሳምንቱ በዓል እና ጌታችን አላህ ታላላቅ ክስተቶችን የፈጸመበት የተባረከ ቀን ነው። ዛሬን በማረ ሁኔታ ለማሳለፍ እነዚ
የጁሙዓ ማለዳ ስንቅ 🌅 የሳምንቱ ምርጥ ቀን ጁሙዓ መጣ! ይህ ቀን የሙስሊሞች የሳምንቱ በዓል እና ጌታችን አላህ ታላላቅ ክስተቶችን የፈጸመበት የተባረከ ቀን ነው። ዛሬን በማረ ሁኔታ ለማሳለፍ እነዚህን የጁሙዓ ሱናዎች እናስታውስ፦ 1.መታጠብ እና ሽቶ መቀባት፦ áˆˆáŒáˆ™á‹“ ሶላት ገላን መታጠብ፣ ጥርስን መፋቅ እና መልካም መዓዛን መቀባት የነቢዩ () ትልቅ ሱና ነው። 2. ንጹህ ልብስ መልበስ፦ áŠŤáˆ‰áŠ• ልብሶች መካከል ምርጡንና ንጹሁን መርጦ መልበስ የዕለቱ ክብር መገለጫ ነው። 3. ሱረቱል ካህፍን መቅራት፦ á‰ áŒáˆ™á‹“ ቀን "ካህፍን" የሚቀራ ሰው አላህ እስከሚቀጥለው ጁሙዓ ድረስ ብርሃን ያበራለታል። 4. በነቢዩ  () ላይ ሶለዋት ማብዛት፦ "በጁሙዓ ቀን በእኔ ላይ ሶለዋትን አብዙ" ብለዋልና። (اللهم صل وسلم على نبينا محمد) 5. ወደ መስጂድ ቀድሞ መሄድ፦ á‹¨áŠšáŒĽá‰Łá‹áŠ• ሰዓት መጠበቅና በዝምታ ማዳመጥ የአጅር ክምር ያስገኛል። 6. ዱዓ ማድረግ፦ á‰ áŒáˆ™á‹“ ቀን ዱዓ ተቀባይነት የሚያገኝባት አንዲት አጭር ሰዓት አለች፤ በተለይ ከዓስር ሶላት በኋላ ባለው ጊዜ አጥብቀን እንለምን። መልካም ጁሙዓ!