5killo Jem'a official Channel
Open in Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Show more1 161
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+730 days
Posts Archive
🎓✨ GRADUATION FAREWELL CEREMONY 2026 ✨🎓
Five years ago, we entered university with dreams and hopes for the future. Today, by the grace of Allah, we stand at the beginning of a new chapter after years of sacrifice, growth, service, and unforgettable memories.
Among us are brothers and sisters who dedicated themselves to serving the Jemmah, leaving behind a legacy that will continue to inspire others, in sha' Allah.
🌟 Join us as we honor the graduating Class of 2026 and celebrate a journey that shaped us all.
✨ A farewell to remember
✨ A celebration of achievement
✨ A tribute to service and sacrifice
🎤 In sha' Allah, the program will be graced by alumni, campus Amirs and Amiras, union representatives, and other distinguished guests. Their experiences and advice will benefit not only our graduates but also current students—especially those striving to serve the Jemmah.
🎁 And that's not all! Exciting surprises await you: delicious refreshments, games, prizes, inspiring experiences, special recognitions, and much more!
📅 Friday, June 19, 2026
⏰ 11:00 LT (Please be on time)
📍 Ambassador
💐 Graduates, students, alumni ,friends, and well-wishers are warmly invited.
🤍 Class of 2026 — Thank you for your service, sacrifice, and legacy.
💡የአላህን ጥበቃ የሚያገኙት ሰዎች!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿ثلاثةٌ كلُّهم ضامنٌ على الله إن عاش رُزِقَ وكُفِيَ، وإن مات أدخله اللهُ الجنَّةَ: من دخل بيتَه فسلّم، فهو ضامنٌ على اللهِ، ومن خرج إلى المسجدِ فهو ضامنٌ على اللهِ، ومن خرج في سبيلِ اللهِ فهو ضامنٌ على اللهِ﴾
“ሶስት ሰዎች ሁሉም አላህ ዘንድ ዋስትና (ጥበቃና እንክብካቤ) ይደረግላቸዋል። በህይወት ቢቆዩ ሲሳይና (ሪዝቅና) ፍላጎታቸው ይሟላላቸዋል፤ ቢሞቱ ደግሞ ጀነትን ያስገባቸዋል። እነሱም አላህ ዋስትና የሚሰጣቸው፦ ወደ ቤቱ ሲገባ ሰላምታ (ሰላም) ብሎ የሚገባ፣ ሶላት ለመስገድ ወደ መስጂድ የሚጓዝና በአላህ መንገድ ላይ ጂሃድ የወጣን ሰው ናቸው።”
📚 ሶሂህ አተርጊብ፡ 321
ለተመራቂ ተማሪዎች ከዚህን በፊት እንዳሳወቅነው በህብረታችን በኩል የተዘጋጀ ሪቫንና ባይንደር እንዳለ ያሳወቅናቹ እንደነበር ይታወሳል። ይህንንም ተከትሎ ብዙዎች በመመዝገብ ላይ ይገኛሉ።
እስከአሁን ድረስ ያልተመዘገባቹ እህትና ወንድሞች ያለው ጊዜ የተወሰነ በመሆኑ ከወዲሁ ምዝገባው ሳይጠናቀቅ ሙሉ ስማችሁን ግቢያችሁን እና ስልክ ቁጥራችሁን በዚህኛው @Niqab_issueBot ቦት ላይ በማስቀመጥ እንድትመዘገቡ ለማስታወስ እንወዳለን።
@aaumsu
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት የሚተላለፉ መልዕክቶች እና አቅጣጫዎች ይደርሳችሁ ዘንድ በቴሌግራም @aaumsu ፤ በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@aaumsu?_r=1&_t=ZS-97D9UHuTcGO እንዲሁም በዩቲዩብ https://youtube.com/@aaumsu ተከታተሉ። ለሌሎች ይደርስም ዘንድ አሰራጩት።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
በዛሬው እለት በረያን መስጂድ ልናዘጋጀው የነበረው የፓናል ውይይት እንዲሰረዝ መደረጉን ባለመስማት ከቦታው ደርሳችሁ የተመለሳችሁ እህት ወንድሞች፣ እናት አባቶች እና የክብር እንግዶቻችን ሁሉ አላህ ንያችሁን ተቀብሎ እና ልፋታችሁን ቆጥሮ ለሙስሊሙ መብት መከበር ሰበብ የምትሆኑ ያድርግላችሁ። ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም ከከምባታ፣ ሀረማያ፣ ሰላሌ፣ ወራቤ እና ከተለያየ ዩኒቨርስቲ ጀመዓዎች አዲስ አበባ ድረስ መጥታችሁ አድራችሁ የተመለሳችሁ ወንድሞቻችን አላህ የተሻሉ ለውጦችን ማምጣት የምትችሉበትን ብርታት ይስጣችሁ፤ ልፋታችሁንም ይቁጠር።
በአላህ ፈቃድ ለተሻለው ይሆናል። እንድንጠነክር አድርጓል። ለመልካም ለውጥ ሰበብ ይሆናል። ለተሻለ ነገ መሠረት ይሆናል።
የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄዎች ከዚህ ትውልድ አይሻገሩም። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ጥያቄ አለን።
@aaumsu
+1
አንድ ወር ሞላው
ግንቦት ሰባት ላይ ነበር። ሙስሊም ተማሪዎች የደረሰባቸው የመብት ጥሰት ይቋጭ ዘንድ ጥያቄ አለን በማለት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ተሰባሰቡ። የቀኑ ፀሐይ እና የምሽቱ ብርድ ሳይበግራቸው እስከ ምሽት 4:30 ተቀመጡ። ለአመራሮች ችላ ባይነት እና ለፌደራሎች ማስፈራሪያ ሳይበገሩም በዝምታ ውስጥ ትልቅ መልዕክትን አስተላለፉ። በሰላም እና ፀጥታ፤ በስነ-ምግባር እና ቁርጠኝነት መልዕክታቸውን አስተላለፉ።
ዛሬ ሰኔ ሰባት ሆኗል። ያ ታሪካዊው ውሎ እና ምሽት አንድ ወር ደፍኗል። ሆኖም በዚያ ምሽት ከሰላም ሚኒስቴር፤ ከዩኒቨርስቲው፤ ከሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ፤ ከፀጥታ ክፍል፤ ከመጅሊስ ወዘተ... በመምጣት በተማሪው ፊት ዘላቂ መፍትሔን ለማምጣት ቃል ገብተዎ ቢመለሱም ለመፍትሔ የሚሆንን ነገር ሳያደርጉ ጥያቄ አለን የሚለው ቃል ደምቆ እንዲቀጥል ሆኗል።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
ጥያቄ አለን _ መብቶቻችን ተከብረው መማር እስክንችል!!
ጥያቄ አለን _ መብታችን ሳይነፈግ በመስጂዶቻችን መሳበሳብ እስክንችል!!!
@aaumsu
አልሐምዱሊላህ __ ታድለናል !
ገና ባልጠና ጉልበታችን፥ የብዙዎች ያልተሰራ የቤት ሥራ በጫንቃችን ላይ ተጣለብን።
ታድለን ...
የትውልድን ክብር በመጠበቅ ላይ ኃላፊነት ወሰድን።
ታድለን...
የእህታቸው ክብር እየተነካ፥ በሰላም ተኝተው የማያድሩ ዓይኖች ተሰጡን።
ታድለን...
ፍትሕ ስትቀበር «በእኔን ከተመቸኝ ይሁንታ» የማይቀበል አዕምሮ ተሰጠን።
ታድለን...
ቀን እስኪያልፍ የሚጎድልን ክብር የማይታገስ ልብ ተቸርን።
ታድለን...
ሌሎች የፈሩበትን ነገር በድፍረት የመጋፈጥ ወኔ ተሰጠን።
ታድለን...
«አዳኝ» እስኪመጣ ሳንጠብቅ፥ ኃላፊነታችንን የምንወጣበት ተቆርቋሪነት ተሰጠን።
እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?!
ታድለን...
ፍትሕ መጓደል አመመን።
የመብታችን መጣስ ቆረቆረን።
ጭቆና አንገሸገሸን።
ደግሞ እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?!
ታድለንማ'ኮ...
ታሪክ "ካላጎነበሱት" መካከል መዘገበን።
መስዋዕትነት ከገባቸው፤
ትውልዳቸውን ለመታደግ ቁርጠኛ ከሆኑት መሃል መዘገበን።
ደግሞ እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?!
ታድለንማ'ኮ...
በአላህ ላይ ከሚመኩት፣
ለመንገዱ ከሚታመኑት፤
ድልንም ከርሱ ብቻ ከሚጠብቁት ሰራዊቶቹ መሃል አደረገን።
ደግሞ እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?!
ለኛ የተሰጠው ለማን ተሰጥቷል?! - ዙሪያችሁን አትመለከቱምን?!
በህይወታችን ካየናቸው ብዙ ብዙ ብቸኝነቶች ውስጥ፥ በዚህ የትግል መንገድ ላይ ያለ ብቸኝነትን ያህል ዋጋ ያለው ብቸኝነት የት እናገኛለን?!
አላህ የሚያየው፣ የሚመሰክርለት ብቸኝነት!
ወደ ድል እንጂ የማይደርስ፣ ውድቀት የሌለበት ብቸኝነት!!
ትርጉሙ ጥልቅ፣ ክፍያው ብዙ ብቸኝነት!!!
ይህ እንደዋዛ 'ሚገኝ ነው እንዴ 'ሚመስለን?! በፍጹም።
ለዚህ ብቸኝነት መመረጥ ያሻዋል።
ይህ'ኮ ታላቅ ጸጋ እንጂ ሌላ አይደለም።
አልሐምዱሊላህ!!!
ሐስቡነላህ ወኒዕመል ወኪል!!!
@aaumsu
ሀሳብን መፍራት የውድቀት መጀመሪያ ነው!
ምክንያታዊነት ሲጎድል እና አሳማኝ መከራከሪያ ሲጠፋ፣ ብቸኛው መሸሸጊያ መንገድ ሀሳብን በጉልበት ማፈን ይሆናል። ይሁን እንጂ የሀሳብን ልእልና የሚፈሩ እና እውነትን የሚሸሹ አካላት ውድቀታቸው እጅግ የፈጠነ ነው። ብርሃንን በመጋረድ ጨለማን ማንገስ አይቻልም።
@aaumsu
عن خباب بن الأرت رضي الله عنه :
شَكَوْنَا إِلَى رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى الله عليه وسلم، وهو مُتَوَسَّدُ بُرْدَةً له في ظِلَّ الكَعْبَةِ ، قُلْنَا لَهُ : أَلَا تَسْتَنْصِرُ لَنَا . أَلَا تَدْعُو اللَّهَ لَنَا ؟ قَالَ : كَانَ الرَّجُلُ فِيمَن قَبْلَكُمْ يُحْفَرُ له. في الأرْضِ ، فَيُجْعَلُ فِيهِ ، فَيُجَاءُ بِالمِنْشَارِ فَيُوضَعُ عَلَى رَأْسِهِ فَيُشَقُ بِاثْنَتَيْنِ ، وما يَصُدُّهُ ذلكَ عَن دِينِهِ ، وَيُمْشَطُ. بِأَمْشَاطِ الحَدِيدِ مَا دُونَ لَحْمِهِ مِن عَظْمٍ أَوْ عَصَبٍ ، وما يَصُدُّهُ ذلك عن دِينِهِ ، واللَّهِ لَيُتِمَّنَّ هذا الْأَمْرَ، حَتَّى يَسِيرَ الرَّاكِبُ مِن صَنْعَاءَ إِلى حَضْرَمَوْتَ ، لَا يَخَافُ إِلَّا اللَّهَ ، أَوِ الذَّنْبَ عَلَى غَنَمِهِ ، وَلَكِنَّكُمْ تَسْتَعْجِلُونَ.
رواه البخاري
ከኸባብ ኢቢኑል-አረት (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ፦
"ወደ አላህ መላክተኛ ﷺ ስሞታን አቀረብን፤ እሳቸውም በካዕባ ጥላ ስር መደረቢያቸውን ተንተርሰው ሳለ። “ለእኛ እርዳታን አትለምንልንምን? ለአላህ አትለምንልንምን?” አልናቸው።
እሳቸውም አሉ፡-
'ከእናንተ በፊት በነበሩት ህዝቦች ዘንድ አንድ ሰው በምድር ላይ ጉድጓድ ይቆፈርለትና በውስጡ ይደረግ ነበር፤ ከዚያም መጋዝ ይመጣና በራሱ ላይ ይደረግና ለሁለት ይሰነጠቃል፤ ይህም ከዲኑ አያግደውም ነበር። ከስጋው በታች ከአጥንት ወይም ከጅማት ያለውን በብረት ማበጠሪያዎች ይበጠር ነበር፤ ይህም ከዲኑ አያግደውም ነበር። በአላህ እምላለሁ! ይህ ነገር (እስልምና) ሙሉ ይሆናል፤ አንድ ጋላቢ ከሰንዓእ እስከ ሐድረመውት ድረስ ከአላህ ወይም በበጎቹ ላይ ከተኩላ በስተቀር ሌላን ሳይፈራ የሚጓዝበት ደረጃ ላይ እስኪደርስ ድረስ፤ ነገር ግን እናንተ ትቸኩላላችሁ።'"
በቡኻሪ ዘግበውታል
እስከተጠነከረ ድረስ ተስፋ እስካልተቆረጠ ድረስ ኢንሻአላህ መውጫው ብዙም አይርቅም።
ወርቅ በእሳት እንደሚፈተነው ሁሉ የሰዎች ትክክለኛ ማንነት በፈተናዎች ይለያል።
©
እጅግ አስቸኳይ መረጃ!
የነገው ፕሮግራም እንዲሰረዝ ተደርጓል!
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በረያን መስጂድ በነገው እለት ሊያዘጋጀው የነበረው የፓናል ውይይት እንዲሰረዝ ተደርጓል። ለዚህም በዋነኝነት የተሰጠው ምክንያት "የመንግስት አካላት ፕሮግራሙ እንዳይካሄድ ክልከላ አድርገዋል" የሚል ነው። ህብረታችንም ሙስሊሙን ማህበረሰብ የሚወክለው መጅሊስ እና ሌሎችም የሚመለከታቸው አካላት የዜጎችን ህገ-መንግስታዊ እና ተፈጥሯዊ መብት ከማስከበር አኳያ ከጎናችን በመቆም መፍትሄ ያመጣሉ ብለን ተስፋ አድርገን የነበረ ቢሆንም፤ በሚያሳዝን ሁኔታ ተገቢውን ከለላ፣ ድጋፍ እና መፍትሄ ማግኘት አልተቻለም።
ፕሮግራሙን ለመታደም ከተለያየ ዩኒቨርስቲ መጥታችሁ አዲስ አበባ ያደራችሁ የጀመዓ አሚሮች፤ አላህ (ሱ.ወ) ጥረታችሁን በጀነት ይመንዳችሁ። ጁምዓ በየመስጂዱ ጥሪ ሲደረግ በእምባ ታጅባችሁ ዱዓ በማድረግ ጭምር እንደምትመጡ የነገራችሁን እናት አባቶች፤ አላህ ዱዓችሁን ይቀበልልን። ከተለያየ ሀይስኩል፣ ኮሌጅ እና መድረሳዎች ለመምጣት የተሰናዳችሁ እህት ወንድሞቻችን፣ የሚዲያ ሽፋን ለመስጠት የተሰናዳችሁ ቲቪዎች፣ ኡስታዞች፣ መሻይኾች እና የክብር እንግዶቻችን፤ ኒያችሁን አላህ ያሳምርላችሁ።
መስጂድ የሁሉም ሙስሊም የጋራ ቤት ነው። በሰላማዊ መንገድ መሰባሰብ እና ስለጋራ ጉዳያችን መወያየት በማንም ሊገፈፍ የማይችል ሕገ-መንግስታዊ መብታችን ነው። የሚዳፈንም ሆነ ወደኋላ የሚጎተት ጥያቄ የለንም። መብታችንን ለማስከበር የምናደርገው ጉዞ በህግ፣ በስርአት እና በኢስላማዊ አዳብ የታነፀ ሆኖ ይቀጥላል።
ይህ መልእክት በጊዜው ያልደረሳቸው እና ለፕሮግራሙ በነገው እለት ወደ መስጂዱ የሚመጡ በርካታ ወንድም እና እህቶች ሊኖሩ ስለሚችሉ፤ ይህንን ፕሮግራም ያገዳችሁ አካላት፣ ቢያንስ እንኳን ይህን አላዋቂ እንግዳ በእንግድነቱ ልክ በክብር በማስተናገድ እና በጥሩ ቃል በመመለስ ከሚጠበቅባችሁ ትንሹን እንድታደርጉ እናሳስባለን።
ቀጣዩን አቅጣጫችንን በቅርቡ እስከምናሳውቅ ድረስ በዱዓ፣ በሰብር እና በፅናት ጠብቁን።
"በእርግጥም የአላህ እርዳታ ሁሌም ቅርብ ነው።" (አል-በቀራህ 214)
@aaumsu
የፓናል ውይይት ስለ መብቶቻችን
- የዚህ ታላቅ ታሪካዊ ዝግጅት አካል እንሁን
ነገ እሁድ ጠዋት 2:30 ወደ ጦር ሀይሎች (ረያን መስጅድ)
- ትራንስፖርት ተዘጋጅቷል !
@aaumsu
📢 የStory Challenge!
የነገውን ፕሮግራም ለብዙ ተማሪዎች እንዲደርስ ይህን ፖስተር በTelegram, WhatsApp, Instagram እንዲሁም Facebook Story ላይ ያጋሩ።
አንድ Story ማድረግ ብቻ ብዙ ሰዎችን ፕሮግራሙ ላይ እንዲገኙ ሊያነቃቃ ይችላል። ጓደኞቻችሁም story እንዲያደርጉት ጋብዟቸው!
📌 ርዕስ ፦ "የሙስሊም ተማሪዎች መብት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት!"
⏰ እሁድ ከጠዋቱ 2:30
📍 ጦርሀይሎች ረያን መስጅድ 3ኛ ፎቅ
#StoryChallenge #ShareAndInvite
#NiqabIssue #panelDiscussion
@fivekjemaa
📢 የStory Challenge!
የነገውን ፕሮግራም ለብዙ ተማሪዎች እንዲደርስ ይህን ፖስተር በTelegram, WhatsApp, Instagram እንዲሁም Facebook Story ላይ ያጋሩ።
አንድ Story ማድረግ ብቻ ብዙ ሰዎችን ፕሮግራሙ ላይ እንዲገኙ ሊያነቃቃ ይችላል። ጓደኞቻችሁም story እንዲያደርጉት ጋብዟቸው!
📌 ርዕስ ፦ "የሙስሊም ተማሪዎች መብት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት!"
⏰ እሁድ ከጠዋቱ 2:30
📍 ጦርሀይሎች ረያን መስጅድ 3ኛ ፎቅ
#StoryChallenge #ShareAndInvite
#NiqabIssue #panelDiscussion
@fivekjemaa
ነገ አይቀርም!
እኔ አልቀርም ... እርስዎስ?!
ሙሐመድአሚን ካሳው ... የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፕሬዚዳንት ! ! !
@aaumsu
አንድ ቀን ብቻ ቀርቷል __ ለታሪካዊው ቀን ...
ከላይ ያለው ምስል ስቶሪ ይደረግ ... ከፕሮፋይልም ይቀመጥ ! ! !
ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ከ100 በላይ ኪሎሜትሮችን ተጉዘው ሊታደሙ የሚመጡ አሉ። በአዲስ አበባ ዙሪያ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች በፕሮግራሙ ለመታደም ይመጣሉ። የመድረሳ ተማሪዎች፤ የሀይስኩል ተማሪዎች፤ የኮሌጅ ተማሪዎች፤ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፤ እናት አባቶቻችን፤ እህት ወንድሞቻችን፤ ኡስታዞቻችን፣ መሾይኾች፣ ሁሉም ስለአንድ አላማ በአንድ መድረክ ይሰባሰባሉ።
የታሪክ ምሁሩ አብዱልጀሊል በታሪክ ውስጥ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የደረሰውን ያብራራል ... የሕግ ፕሮፌሰሩ ዘላለም እየተጣሱ ስላሉት መብቶች ከሕግ አንፃር ያለውን እውነታ ያስቃኛል ... ኡስታዝ ሺሃቡዲን ሸህ ኑራም በእንዲህ አይነት ሁኔታዎች ውስጥ የእኛ ሚና ምን መሆን እንዳለበት ያስቀምጣሉ። ስለ አሁኑ እና ስለወደፊቱ ከተማሪዎች በኩል ያለውንም እናደምጣለን።
ሰኔ 07 / 2018 ዓ.ል
እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ
ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ
ከላይ ያለውን ምስል ስቶሪ አድርጉ ... ከፕሮፋይላችሁ ላይም አስቀምጡት ! ! !
የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች
@aaumsu
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡‐
“የአላህን ውሳኔ የሚመልሰው ዱዓ ብቻ ነው። እድሜን የሚያስረዝመው መልካም ስራ ብቻ ነው።”
📚ሲልሲለቱ አሶሂሃ: (154)
@fivekjemaa
