5killo Jem'a official Channel
Open in Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
Show more1 162
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+730 days
Posts Archive
Repost from AAU - Muslim Students Union
+1
ከወሎ ደሴ ነው ---
ስለ ሒጃብ፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ስለደረሰው የመብት ጥሰት፤ ስለሙስሊም ተማሪዎች መብት፤ ስለሕዝበ ሙስሊሙ አጀንዳዎች ጥያቄ አለን ብለዋል። ለሁሉም ጥያቄዎችም ፍትሐዊ መልስ ሊሰጥ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ፍትሕ፤ እኩልነት እና ነፃነት እስኪሰፍን ጥያቄ አለን!
ሒጃብ ለብሶ መማር መብት ነው!!
በሀገር ውስጥ በእኩልነት መተዳደር፤ የሚገባንን በፍትሕ ማግኘት መብት ነው!!!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በስኮላርሺፕ ለመግባት አስባችሁ ለUAT ፈተና ክፍያ፤ የትራንስፖርት ወጪ አቅማችሁ የማይችል ሙስሊም ተማሪዎች፦
ጀመዓችን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በዚህ ችግር ምክንያት ተማሪዎች አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ከመቀላቀል ወደሗላ እንዳይሉና የሙስሊም ተማሪዎችን ተሳትፎ ለማበረታት በማሰብ የጥቂት ተማሪዎችን የUAT ክፍያ፤ የመመዝገቢያ ወጪ እና የትራንስፖርት ክፍያ ለመሸፈን አስቧል። ስለሆነም አቅሙ የሌላችሁና ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተማሪዎች https://forms.gle/Bap5GQQZMigtBKES6 አመልክቱ።
ማስታዎሻ፦ ወጪው የሚሸፈነው አቅሙ ለሌላቸው ተማሪዎች ብቻ ነው። የሚሸፈነውም ለጥቂት ተማሪዎች ብቻ ነው። አላህ ኡማውን የምትጠቅሙ ያድርጋችሁ።
@aaumsu
ልክ በዛሬዋ እለት ከ1438 አመት በፊት በረቢዐል አወል 12 የአሏህ መልዕክተኛ ﷺ ወደ አኼራ ሄደዋል ። እሳቸው በሞቱ ሰአት የነበረውን ክስተት አነስ ኢብኑ ማሊክ ሲናገር እንዲህ ይላል፦ “ረሱል ﷺ የሞቱ እለት እኛ ልክ በዝናባማ ሌሊት እንደጠፉ በጎች ሆንን”
ሀቢባችን አርአያችን የሆኑት ሙስጦፋል አሚን እንዲህ ነበሩ ፦
አላህ ከሰጣቸው ነገር አንድንም ነገር አያጣጥሉም፡፡ አይንቁም፡፡ ትንሿን የአላህ ፀጋ እንደ ትልቅ ያያሉ፡፡ በልተውም ሆነ ጠጥተው ያመሰግናሉ፡፡ ሁሉንም ነገር እንደሁኔታው ይቀበላሉ፡፡ አላህ የሻላቸውን ይወዳሉ፡፡ ያገኙትን ሰው በሰላምታ ይቀድማሉ ። ታጋሽና ቁጥብ ፤ ትሁትና ጨዋ ናቸው ፡፡ ከኩራት፣ ከመመፃደቅና ከጉራ የራቁ ናቸው፡፡ እንዲያልቋቸው አይፈቅዱም፡፡ ኮስታራ አይደሉም ፣ በሻሻ ናቸው፡፡ አንዳች የሚስብ ነገር አላቸው፡፡ ሳቃቸው አብዛኛውን ጊዜ ፈገግታ ነው፡፡ ስለ ሶሃቦቻቸው ሁኔታ ይጠይቃሉ ፡፡ የቸገረውንና የጠፋውን ያጠያይቃሉ፡፡ በነገራቸው ሁሉ መካከለኛና ሚዛናዊ ናቸው ፡፡ ለየት ያለ ዙፋንም ሆነ መቀመጫ የላቸውም፡፡ አላህን ያወሱ ቢሆን እንጂ አይቆሙም፤ አይቀመጡም ፣ አይተኙም አይነሱም፡፡ እያንዳንዱ ሰው እኔን ነው የሚወዱት ብሎ እስኪያስብ ድረስ አንዱን ከሌላኛው ሳይለዩ ያቀርባሉ፡፡ እጃቸውን የያዛቸው ሰው እስካልለቀቃቸው ድረስ ቀድመው አይለቁም፡፡ አንድ ሰው ከርሳቸው አንዳች ነገር የፈለገ እንደሆነ ሳይሰጡት አይመልሱትም ።
ባህሪያቸው ለሁሉም የሚመች ገር ነው፡፡ አቀራረባቸው ለረጅም ጊዜ እንደሚተዋወቅ ሰው ነው። ማህበራዊ ኑሮአቸው ልስላሴ የተሞላበት ነው፡፡ አይራገሙም፣ አይቆጡም፣ አይጮሁም። ይቀልዳሉ ነገርግን ሐቅን እንጂ አይናገሩም፡፡አንድንም ሰው አይዘልፉም፣ አይበድሉም፡፡ የጎዳሁት ሰው ካለ ዛሬውኑ ካሳውን ይቀበለኝ ይሉ ነበር፡፡ የሰዎችን ገመና አይከታተሉም፡፡ ሰዎች ከሰዎች ይልቅ ወደራሳቸው ችግር እንዲመለከቱ ይመክሩ ነበር፡፡ ሰሓቦቻቸው በሚስቁት ይስቃሉ ፡፡ እነርሱ በሚደነቁት ነገር ይደነቃሉ፡፡ ከአንድም ሰው ሙገሳን አይፈልጉም፡፡
የሚኖሩትም ሆነ የሚሰሩት ለአላህ ነው፡፡ሲናገሩም ሆነ ቁርአን ሲያነቡ ድምፃቸው ውብ ነው፡፡ ከልጆች ጋር ይቀልዳሉ፡፡ ህፃናትን ያጫውታሉ፡፡ ልጆችን ተሸክመው ይሰግዳሉ፡፡
በግመላቸው ላይ ሆነውም ጭምር ቁርአን ያነቡ ነበር ፡፡ መዓዛቸው እጅግ ያውዳል፡፡ ላባቸው እንደሚስክ ሽታ ነው፡፡
እጅግ መልካም ሰው፣ እጅግ ብልሃተኛ፣ ለጋሽና እጅግ ጀግና ናቸው፡፡ ሲመፀውቱ ድህነትን የማይፈራ ዓይነት ሰው መመጽወትን ይመፀውቱም ነበር .. ሶለዋቱሏሂ ወሰላሙሁ አለይህ
እኛም በቻልነው ሁሉ ለሰው ጠቃሚና አዛኝ እንሁን። ያየን ሰው የሱ ዓይነት ሰው በሆንኩ ብሎ የሚመኘው ዓይነት መልካም ሰው እንሁን። ስለ እኛ የሰማ ሊያየን የሚጓጓ፣ ስለኛ ያወቀ ዱዓ የሚያደርግልን ዓይነት ሰው እንሁን።
በሁሉም ነገራችን የነቢያችንን ባህሪ ለመያዝ እንሞክር። የርሳቸዉን ባህሪ የወረሰ ተቀብሮ መሬት ሥር ሆኖም ሽታው ያዉዳልና...!
በሳቸው ላይ ሶለዋት ማውረድም ላይ እንበርታ
ሶለዋት ማብዛት በርካታ ጥቅሞች አሉት ። ለምሳሌ ፦ ወደ አላህ ያቃርባል፣ በፍጥረታት ያስወድዳል፣ ከመላእክት ያጎራብታል፣ ወንጀልን ያስምራል፣ ኃጢአትን ያሳብሳል፣ ሀሳብ ጭንቀትን ያስወግዳል፣ ለዱዓ ምላሽ ያስገኛል፣ የመቃብር ጨለማን ያበራል፣ ከክፉ ፍፃሜ ያድናል፣ በረከትን ያሰፍናል፣ ለዱዓ ምላሽን ያስገኛል ።
የአላህ እዝነትና ሰላም መልካም ነገርን ሁሉ ባስተማሩን ነቢይ ላይ ይስፈን
©
የሀገራዊ ምክክሩ አንደምታ --- ታላቅ የውይይት መድረክ ... በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ !
የሀገራዊ ምክክሩ በዘርፈ ብዙ ሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ ምክክር አድርጎ ምክረ ሀሳቦችን ካጠናቀረ ቀናቶች አልፈዋል። ሕዝበ ሙስሊሙም አጀንዳዎቹን አቅርቦ የመድረኩ አካል እንዲሆኑ አድርጎ ነበር። ለመሆኑ ሀገራዊ ምክክር ምንድን ነው? በምክክር መድረኩ የሕዝበ ሙስሊሙ አጀንዳዎችስ ምን ምን ነበሩ? ምክክሩ ስኬታማ ይሆን ዘንድ መደረግ ያለባቸው ነገሮች ምንድን ናቸው? ከሀገራዊ ምክክሩስ ልንወስዳቸው የሚገቡ ትምህርቶች ምን ምን ናቸው?
እነዚህ እና ሌሎች ጥያቄዎች መልስ የሚያገኙበት ልዩ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ (@aaumsu) የሚዘጋጅ ይሆናል።
ቀን፦ ነሐሴ 24 / 2018 ዓ.ል
ሰዓት፦ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ
ቀጠሯችንን ቀጠሯችሁ አድርጉ። በሰዓቱ እንገኝ፤ ለሌሎችም እናሰራጭ።
@aaumsu
የሒጅራ ካላንደር ከነባሩ ካላንደር ጎን ለጎን እውቅና ተሰጥቶት ተግባራዊ እንዲደረግ መወሰነ በምክክር ፍትሕ ሊመጣ እንደሚችል ያመላከተ ነው !
ቪድዮው ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZSVxo8NXc/ በቲክቶክ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት አድርጉ።
@aaumsu
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መቀላቀል የምትፈልጉ የዘንድሮ 12ኛ ክፍል ተፈታኞች የማመልከቻ ጊዜ ከነገ ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት ክፍት እንደሚሆን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
ዝርዝር መረጃ ከላይ የተያያዙት ፋይሎች ላይ ማግኘት የምትችሉ ሲሆን ማንኛውም የሚያስፈልጋችሁ መረጃ ወይም እገዛ የሚኖር ከሆነ https://t.me/Aaumuslimstudentsunion1 ላይ ጻፉልን።
@aaumsu
ሒጃቧ እምነቷ !
ለሁሉም ይደርስ ዘንድ በቲክቶክ https://vt.tiktok.com/ZSVHmXxjj/ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት ያድርጉ።
@aaumsu
+3
ጀመዓችን የኢንስታግራም አካውንት በከፈተ አንድ ወር ውስጥ
፨ ከ3000 በላይ ተከታዮች
፨ 259,355 View
፨ 19,769 Like
ማግኘት ተችሏል። በመድረኩ የተለያዩ ይዘቶችን በማጋራት ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ድምፅ ለመሆን፤ ስለተለያዩ ጉዳዮች ግንዛቤ ለመፍጠር ተሞክሯል። ሚዲያ ሀሳቦቻችንን የምንሸጥበት፤ መልዕክታችንን የምናስተላልፍበት ብሎም አጀንዳዎቻችንን የሁሉም አጀንዳ የምናደርግበት መድረክ ነውና https://www.instagram.com/p/DcYr4y-jfXo/?img_index=3&igsi=dmc1d3VnbGg5OHg5 በመግባት አካውንታችንን Follow አድርጉ። ለሁሉም ተደራሽ ይሆን ዘንድም አሰራጩ።
እንኳን ደስ አለን 🎉🎉🎉 !!!
@aaumsu
Haqni hawaasa tokkoof dhabame, hawaasa hundaaf balaadha. Gaaffiin barattoota Muslimaa AAU gaaffii mirga namummaa ti malee dhimma amantii qofa miti!
Sagaleen keenya namoota dabalataatiin akka gahuuf viidiyoo kana share godhaa: https://www.tiktok.com/@aaumsu/video/7677097862420811029
@aaumsu
ሕያው ምስክር - 1
በ11 ብርሃናማ ሌሊቶች መፍትሔ የተገኘለት የ11 አመታት የመብት ጥያቄ --- በዲላ ዩኒቨርስቲ !
አቅራቢ፦ ኡስታዝ ኑረዲን አብደላህ (የዲላ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት የቀድሞ አሚር)
አዘጋጅ፦ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት !!
@aaumsu
ለግፍ ያላጐነበሰው ንጉሥ 👑
ክፍል 1
ከዘመናት በኋላ በታሪክ ውስጥ አሻራውን ጥሎ ያለፈ አንድ ታላቅ ሰው ወዳፈራችዉ ምድር እንሻገር…………
በዙሪያው ያለው ኃይል ሁሉ በእጁ በነበረበት ጊዜ ✨በምሕረቱ፣
ማንም ሊገዳደረው በማይችልበትና ሊበድል ቢፈልግ አንዲት ስራው በቂ በነበረችበት ሰዓት ደግሞ ✨በፍትሑና በዕኩልነቱ የታወቀ ንጉሥ።
ዓለም በሩን የከፈተለት፣ ተግባሩ ምንም ኃይልና አቅም የሌላቸውን ምስኪን እንግዶች ዕጣ ፈንታ መቀየር የቻለ ታላቅ ሰው።
ከዚህም ጋር እንግዶቹ በመጡ ጊዜ ስለ ኃይላቸው፣ ስለ ብዛታቸው ወይም ለእርሱ ሊያበረክቱት ስለሚችሉት ነገር አንዳችም ጥቅማ ጥቅምን አልጠየቀም።
ይልቁንም አዳመጣቸው፤
ከዚያም ቀላል የማይባል፣ የታሪክ ሚዛኑን ሙሉ በሙሉ የቀየረና ያስዋበን ፤እስከ ዛሬ ድረስ በዚች ምድር ላይ አሻራውን ያኖረ ቆራጥ ውሳኔን ወሰነ።
የታሪክ መጻሕፍት በፍትሕ የመሰከሩለት፣
በሙስሊሞች ልብ ውስጥም ስሙ ከትልልቅ የፍትሕና የሰላም ምዕራፎች ጋር ተያይዞ የሚነሣ ታላቅ ስብዕና።
ታዲያ ይህ ንጉሥ ማን ነው?
ወደ ምድሩ የተሰደዱትስ እነማን ናቸው?
ከሐበሻ ምድር ታሪክ ውስጥስ የእርሱ አቋም ለምን ትልቁን ቦታ ያዘ?
ይህ ሰውስ እንዴት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ታሪክ ዋና አካል ሊሆን ቻለ?
የዛሬው ትግላችን ሊጀምር ሚገባው ከትላንቱ ታሪካችን ከዚህ ነው።
💫ዉዱ ንጉሣችን…………
💫አርአያችን ……..
💫የፍትህ ምሳሌያችን……..
💫ዉቡ ታሪካችን…….
ስንታገል ርቀታች እኛው ለእኛው ከመሆን አልፎ ለሌላው እስከመድረስ ጭምር እንዲሆን ተምሰሌት የሆነን መሪ
ይህ ታላቅ ስብዕና👇
ንጉሥ አል-አስሐማ ቢን አብጀር (ነጃሺ) ነው።
የኢስለም አሀዳዊ ጥሪን ፈጽሞ መስማት ያልፈለጉት የመካ ቁራይሾች በሙስሊሞች ላይ የቅጣት በትራቸውን አሳረፉ።
አማኞች ግፍና መከራን አስተናገዱ። ችግርና እንግልት ተከተላቸው። ከእምነታቸው በመመለስ እንደነርሱ የጣኦት አምልኮን ይከተሉ ዘንድ ማዕቀብ ስቃይና ጥቃት ተፈጸመባቸው።
ነብዩ ሙሀመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ) በባልደረቦቻቸው ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት ሊከላከሉ እንደማይችሉ ሲገነዘቡ ወደ ሀበሻ ምድር እንዲሰደዱ መከሯቸው። እንዲህም አሏቸው :-
“ወደ ሀበሻ ተሰደዱ። በእርሷ ዘንድ አንድንጉስ አለ። ከእርሱ ፊት ማንም ተበዳይ አይሆንም፣ስለዚህ ተሰደዱ። አላህ ካላችሁበት ሁኔታ አውጥቶ ድልን እስክንጎናጸፍ ድረስ። “
በዚህም መሰረት የነብያቸውን ትእዛዝ ተቀብለው በ5ኛው የነብይነት አመት የመጀመሪያውን ስደት 12 ሆነው በጀልባ ለ1 ሰው ግማሽ ዲናር ከፍለው ወደ ሀበሻ ተጓዙ።
በገዛ ሀገራቸው ያጡትን የአምልኮ ነጻነት በሀበሻው መሪ አስሃማ ወይም ነጃሺ አገዛዝ ስርም ተጎናጸፉ።
የነብዩ ሙሀመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ባልደረቦች በሀበሻ የገጠማቸውን እንዲህ ሲሉ መስክረዋል:-
……..ክፍል 2 ይቀጥላል
©aaumsu
@fivekjemaa
ሀሳን ኢብኑ ሳቢት ልዩ የስነ-ፅሁፍ ውድድር !
በተደረገው ጥሪ መሠረት ብዙዎች ብዕራቸውን አንስተው ስንኞችን በመቋጠር፤ ሐሳቦችንም በመደርደር በውድድሩ ላይ ተሳትፈዋል። ውድድሩ ስለሕዝበ ሙስሊም የመብት ጥያቄ፤ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጉዳይ፤ ስለክብራችን፤ ስለነፃነታችን የመክተብ ነው። በግጥምም ሆነ በዝርው፤ ገጠመኝም ሆነ ማንኛውንም ሐሳብ ማቅረብ ይቻላል።
ከ1-3 የሚወጡ ተሸላሚ የሚሆኑ ይሆናል።
1ኛ፦ 1500 ብር፤ የምስክር ወረቀት እና ተጨማሪ ልዩ ስጦታዎች
2ኛ፦ 1000 ብር፤ የምስክር ወረቀት እና ተጨማሪ ልዩ ስጦታዎች
3ኛ፦ 500 ብር፤ የምስክር ወረቀት እና ተጨማሪ ልዩ ስጦታዎች
የጥበብ ውጤቶቻችሁን @Niqab_issueBot ላኩልን።
@aaumsu
✴️ «መዉሊድ »
📚 ትርጉም እና አዘጋጅ፦ ኢብን አቢ ዱንያ
t.me/ibnabidunyaa
📝 ቅንብር፦ አቡ ኡሳማ ዘይድ
https://t.me/akhuabdusemed
✨ እውነታውን መመልከት ለፈለግ
✨ ግልፅ ነገር ብቻ የተቀመጠበት
الحمد لله الذي بنعمته تتم الصالحات
ፕሮግራማችን ባማረ ሁኔታ ተጠናቋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲን ታሪካዊ የመብት ትግል ላጋሩን፤ እንደ ታላቅ ወንድም፤ እንደ አሚር እና እንደ ኡስታዝ ሆነው ምክራቸውን ላካፈሉን የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የቀድሞ አሚር ኡስታዝ ኑረዲን አብደላህ ከልብ እናመሰግናለን።
እንዲሁምፕሮግራሙ እንዲሳካ ለተነቀሳቀሱ እህት እና ወንድሞች ሁሉ ጀዛኩሙሏሁ ኸይራ ማለት እንወዳለን!
መጀመሪያ አካባቢ ስለነበረው የኔትዎርክ መቆራረጥ ይቅርታ እየጠየቅን፤ በቀጥታ መከታተል ላልቻላችሁ ሪከርድ የሚለቀቅ ይሆናል።
ህያው ምስክር ፕሮግራማችን በቀጣይም ከሌላ እንግዳና ሌላ አስተማሪ የትግል ታሪክ ጋር በቅርቡ የሚመለስ ይሆናል።
©aaumsu
@fivekjemaa
Repost from AAU - Muslim Students Union
https://t.me/aaumsu?livestream=734f01b6cb97f0269e
ፕሮግራማችን ሊጀምር ስለሆነ ተቀላቀሉ።
ሰዓታት ብቻ ይቀሩታል!
ምስሉን ፕሮፋይል እናድርግ
በስቶሪዎቻችን ላይ እናጋራ
ቻናል እና ግሩፕ ያላችሁ መልዕክቱን በዚያ በኩል አድርሱ
ኢንቦክስ በመግባትም ለምናውቃቸው ሁሉ እንላክ!
ዛሬ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እንገናኝ !
@aaumsu
🎉ደርሷሷልል ❕
🔥 ሕያው ምስክር ~ 1 ~ 🔥
ዘመናትን ሲሸጋገር የቆየው የ ጭቆና ብትር በ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ!!
እነሆ ታሪካዊው መድረካችን 1 ብሎ ለ ዛሬ ቀጠሮውን ይዟል! እውነታዎችን በማስተንተን ማንነትን በ አግባቡ መገንባት ላይ ያተኮረው "የሕያው ምስክር" መድረክ በ ታሪክ ገጽ ደምቆ የሰፈረወን የ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል ሊያስቃኛቹ ዝግጅቱን አጠናቋል !!
🗯የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች የነፃነት ጉዞ ምን ይመስል ነበር !?
🗯አምስቱ ዋና ጥያቄዎቻቸው ምን ምን ነበሩ ?!
🗯እጅግ ፈታኝና ተስፋ አስቆራጭ የነበረው ትግል በምን መልኩ መፍትሄ ሊያገኝ ቻለ ?!
በ ሙስሊምነታቸው ሲደርስባቸው የነበረውን መራራ በደል "ከሙተነቂቦች መንደር" በ ጥቂቱ ልናስቃኛችሁ ሞክረናል፣ በ ዛሬው ምሽት በ 2017 ስለ ተደረገው የተቀናጀ እና ብዙዎችን ስላስደመመው፣ ጠይቆ ታግሎ ማንነትን እና መብትን በማስከበር ረገድ ትልቅ ተምሳሌት ሆኖ ስላለፈው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል በ ጥልቅ እንዳስሳለን።
✨ከ ሃይስኮል እስከ ኮሌጅ
✨ከ ዩኒቨርሲቲ እስከ ሥራው ዓለም ድረስ ስለ ችግሮቻችን ያሰሰበው ሁሉ፣ ለተጨነቀ እና ለመፍትሄው ለተብሰለሰል ሁሉ ለመንገዳችን ትልቅ ስንቅ ምንሰንቅበት ልዪ መድረክ ነው!
🗓ዛሬ(ጁምዐ) ማታ 3:00 በቀጠሯችን እንገናኝ!
@aaumsu
ሰዓታት ብቻ ይቀሩታል!
ምስሉን ፕሮፋይል እናድርግ
በስቶሪዎቻችን ላይ እናጋራ
ቻናል እና ግሩፕ ያላችሁ መልዕክቱን በዚያ በኩል አድርሱ
ኢንቦክስ በመግባትም ለምናውቃቸው ሁሉ እንላክ!
ዛሬ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እንገናኝ !
@aaumsu
