ኢትዮ🇪🇹🦋ፍልስጢን🇵🇸✌️
Open in Telegram
Ethio🦋 Palestine በዚህ ቻናል ለፍልስጤም ለኢስላም ትልቅ መሰዋትነት የከፈሉ የታላላቅ ጀግኖች ታሪኮች ስለፍልስጤም አስገራሚ ክስተቶች ፍልስጤም የተላኩ ነብያቶች ታሪክ የሚለቀቅበት ቻናል ነው። ሼር አድርጉልን ለአስተያየት 👇 @Palestinians_bot 🇵🇸ፍልስጢን አቅሳ🇪🇹 #አቅሷ_ትጣራለች #FREE_PALESTINE✌
Show more2 810
Subscribers
-324 hours
+137 days
+2230 days
Posts Archive
2 810
-የዮርዳኖስ ንጉሥ አብዱላህ ሁለተኛና የቻይናው ፕሬዝዳንት Xi Jinping የጋዛ የተኩስ ማቆም እንዲጠናከርና የሰብዓዊ እርዳታ ያለገደብ እንዲገባ ጥሪ አቅርበዋል።
2 810
ፋታህ እና ሐማስ በካይሮ ለመወያየት ተዘጋጅተዋል
🇵🇸 በፍልስጤም የፖለቲካ አንድነትን ማጠናከር
የጋዛን አስተዳደር ከጦርነቱ በኋላ እንዴት መመስረት እንደሚቻል መወያየትን
የፍልስጤም የጋራ የፖለቲካ አቋም ለመፍጠር መሞከር
በዌስት ባንክና ጋዛ የሚኖረውን የፍልስጤም አስተዳደር ጉዳይ ማየት የሚሉት ናቸዉ “።
-ነሐሴ 18 በካይሮ ስብሰባ ሊይ
የፋታህ ከፍተኛ ልዑክ ከሐማስ ጋር የሚወያየው በተለይ የፍልስጤም ሕግ አውጪ ምርጫ ዝግጅት እና በጋዛ ምርጫው እንዴት እንደሚካሄድ ነው።
-የፍልስጤም ሕግ አውጪ ምርጫ በኖቬምበር 28፣ 2026 እንዲካሄድ ተወስኗል፤ ይህም ከ2006 በኋላ የመጀመሪያው ሕግ አውጪ ምርጫ ሊሆን ይችላል።
-ሐማስም በሰፊ ብሔራዊ ጥምረት ውስጥ ሆኖ በምርጫው ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳለው ተገልጿል።
2 810
50 ፍልስጤማውያን አስከሬን ከፍርስራሽ ከተወጣ በኋላ በጋዛ ሲቲ የጅምላ ቀብር ተደርጓል።
የአል-ሺፋ ሆስፒታል የinterventional radiology ክፍል እንደገና ተጠግኖ መከፈቱ ተዘግቧል።
2 810
እዚህ ያላችሁ ወዳጆቼ ከታች ባለዉ ሊንክ እየገባችሁ ዋሲሁን ተስፋዬን አበረታቱልኝ እህቶቻችን ለራሳችሁ ለወዳጅ ለዘመድ ስጦታ አበርክቱ ወንዶች እህት እናት ያላችሁ በስጦታ አጎናፅፋ የፍልስጤም አይከን የሆነ ቦርሳ ነዉ
2 810
ሐዘም ቃሲም የሐማስ ቃል አቀባይ፣ በጋዛ የተፈጸመውን ጥቃት እንደ የተኩስ አቁም ጥሪዎችን መጣስ በመግለጽ፣ አስታራቂዎች፣ ዋስትና ሰጪ ሀገራት እና የአሜሪካ አስተዳደር የተኩስ አቁሙ እንዲከበር ጫና እንዲያደርጉ ጠይቋል።
በተያያዘም የጋዛ ጤና ሚኒስቴር በሰጠው ባለፉት 24 ሰዓታት 1 ሰው በጉዳቱ ምክንያት ሞቷል፣ 2 ሰዎችም ቆስለው ወደ ሆስፒታል ገብተዋል ይላል።
አሁንም አንዳንድ ተጎጂዎች ከፍርስራሽ ስር ወይም በመንገድ ላይ እንዳሉ፣ አምቡላንስና የሲቪል መከላከያ ቡድኖች እነሱን ለመድረስ እንዳልቻሉ ይገልጻል።
በሪፖርቱ መሠረት፣ ከጥቅምት 11 ከተኩስ አቁም ጀምሮ 1,266 ሰዎች ሞተዋል፣ 4,200 ቆስለዋል፣ 813 አስከሬኖችም ከፍርስራሽ ተወጥተዋል ተብሏል።
ከጥቅምት 7፣ 2023 ጀምሮ የሞቱት 73,400 እና የቆሰሉት 174,312 መድረሳቸውን የጤና ሚኒስቴሩ ገልፆል
2 810
የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ጃሬድ ኩሽነር ከቤንያሚን ኔታንያሁ ጋር ለጋዛ የሰላም/ተኩስ አቁም ዕቅድ ተወያይቷል። ነገር ግን በዋና ጉዳዮች—በተለይ የሀማስ ትጥቅ መፍታት እና የእስራኤል ሠራዊት መውጣት—ላይ እስካሁን ግልጽ ስምምነት አልተገኘም ብሏል።
-በጋዛ ጥቃቶች መቀጠላቸው: ዛሬ የወጡ ሪፖርቶች በጋዛ ውስጥ ጥቃቶች እንደቀጠሉ እና ሰዎች መገደላቸውና መቁሰላቸው እንደቀጠለ ይገልጻሉ።
IMEMC
ዌስት ባንክ ቁስራ: በቁስራ መንደር የፍልስጤም ቤተሰቦች በሰፋሪዎች እንደተከበቡ እና ከቤታቸው መውጣት እንደተገደበ ሪፖርቶች ያሳያሉ።
2 810
ናታንያሁ ትራምፕ ለጋዛዊያን ያቀረበውን የ 15 ነጥብ የስምምነት ሃሳብ ተገደን እንጂ የምንተገብረው እኔ አልተቀበልኩትም ካለ ከደቂቃዎች በኋላ ሐማስ የትራምፕን የስምምነት ሃሳብ በተሟላ ሁኔታ ለመተግበር ቁርጠኛ ነን ብሏል።
2 810
ወራሪዋ እስራኤል በዘንድሮው ዓመት ብቻ በሰፋሪዎች ጥቃት እና ቤት ፈረሳ ምክንያት ከ3,200 በላይ ፍልስጤማውያን ከቀያቸው መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (OCHA) አስታውቋል።
2 810
በናብሉስ አቅራቢያ በሚገኘው የቁስራ መንደር የአይሁድ ሰፋሪዎች የአል-ራህማ መስጊድን ጨምሮ የፍልስጤማውያንን መኖሪያ ቤቶች እና ተሽከርካሪዎች በእሳት አቃጥለዋል። በጥቃቱ ወቅት "የአይሁድ በቀል" የሚሉ የዕብራይስጥ ፅሁፎች በመስጊዱ ግድግዳ ላይ ተፅፈው ተገኝተዋል።
- ኔታንያሁ በዌስት ባንክ ላይ ጠንካራ ወታደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ትዕዛዝ ካስተላለፉ በኋላ፣ የእስራኤል ጦር ናብሉስን ጨምሮ በተለያዩ ከተሞች ሰፊ አሰሳ በማድረግ ከ70 በላይ ፍልስጤማውያንን በቁጥጥር ስር አውሏል።
2 810
ዶክተር ኸሊል አል-ሐያ የሀማስoverall political bureau chief) መሾሙን ድርጅቱ አስታውቋል። እሱ በ2024 በእስራኤል ጦር ከተገደለው ያህያ ሲንዋር በኋላ በይፋ ይህን ሹመት አግኝቷል ።
2 810
መከራ እና ግፍ መቋቋም ቢያቅተዉ መሳሪያዎች ቀምቶ 3 የወራሪውን ወታደር ገሎ ተሰዋ ጀግና ይዉጣልሽ ተብላ የተመረቀች ሀገር ፍልስጤም
2 810
ሐማስ ዛሬ በቤይሩት የሞተውን ጃፓናዊ አብዮታዊ ተዋጊ ኮዞ ኦካሞቶ በሐዘን አስታውሷል። ሐማስ ኦካሞቶ ህይወቱን ለፍልስጤም ጉዳይ በመደገፍ እንዳሳለፈ፣ በእስራኤል እስር ቤቶች ያሳለፈው ዓመታት ደግሞ የዓለም አቀፍ አንድነትና የነፃነት ትግል ምልክት እንደሆነ ገልጿል።
እንዲሁም ለቤተሰቡና ለጓዶቹ በPopular Front for the Liberation of Palestine (PFLP) የሐዘን መልዕክት በመላክ፣ ኦካሞቶ በጭቆናና በግፍ ላይ የሚደረግ ተቃውሞ ዘላቂ ምልክት ሆኖ እንደሚታወስ ገልጿል።
Kozo Okamoto ጃፓናዊ ተወላጅ ሲሆን በ1970ዎቹ ከጃፓን የግራ አክራሪ ቡድን Japanese Red Army (JRA) ጋር የተቆራኘ ነበር።
በጣም የሚታወቀው በ1972 በLod Airport (አሁን Ben Gurion Airport) በተፈጸመው ጥቃት ተሳታፊ በመሆኑ ነው። በዚያ ጥቃት 26 ሰዎች ተገድለው ብዙዎች ቆስለዋል። ሁለቱ ከእሱ ጋር የነበሩ ተሳታፊዎች ሲሞቱ፣ ኦካሞቶ በሕይወት ተይዞ ተያዘ።
ከዚያ በኋላ፦
በእስራኤል ፍርድ ቤት የዕድሜ ልክ እስራት ተፈረደበት።
በ1985 በእስረኞች ልውውጥ ተፈትቶ ወደ ሊባኖስ ሄደ።
ከዚያ በኋላ በቤይሩት ኖረ፣ ከፍልስጤም የግራ ቡድኖች ጋር ግንኙነቱን ቀጠለ።
ኦካሞቶ ለፍልስጤም ታጋይ ነዉ በልቡ ዉስጥ ፍልስጤም አለች
በወቅቱ የፍልስጤም ጭቆና ሲበዛ ሶስት ጃፓኖች ከPopular Front for the Liberation of Palestine ጋር በመተባበር ተካሂዷል።
በአውሮፕላን ተጓዥ መስለው ወደ አየር ማረፊያው ገብተው በጠመንጃና በእጅ ቦምብ ጥቃት ፈጽመዋል።
26 የወራሪዋን ዜጎች ገለዉ ከ80 በላይ ቆስለዋል።
ሁለቱ አጥቂዎች በጥቃቱ ወቅት ሲሞቱ፣ ኮዞ ኦካሞቶ በሕይወት እንደተያዘ መረጃዎች ያመላክታሉ።
ኢትዮ ፍልስጤም
2 810
የስፔን የሕፃናትና ወጣቶች ሚኒስትር ሲራ ሬጎ በእስራኤል መንግሥት ላይ እጅግ ጠንካራና የበረታ ወቀሳ ሰንዝረዋል።
ሚኒስትሯ ማድሪድ በእስራኤል ላይ የምታቀርበውን ትችት በተመለከተ በሰጡት አስተያየት "እኛ የስም ማጥፋት አልፈጸምንም፤ ገጽታችሁን ገለጽን እንጂ፤ እናንተ የዘር ማጥፋት ፈጻሚና ወንጀለኛ መንግሥት ናችሁ" ሲሉ የእስራኤልን አካሄድ አጥብቀው ኮንነዋል።
ይህ አስተያየት የተሰጠው ስፔን በጋዛ እየተካሄደ ያለውን ወታደራዊ እርምጃ በተደጋጋሚ ስትቃወም እና እስራኤል ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ሕጎችን ጥሳለች በማለት ተጠያቂ እንድትሆን በጽኑ ስትጠይቅ በቆየችበት ማዕቀፍ ውስጥ ነው።
2 810
ሀማስ፣ በZaher Jabareen የሚመራ ልዑክ ወደ Cairo መድረሱን አረጋግጧል።
ውይይቱ የተኩስ አቁም ስምምነትን በተግባር ለማስፈጸም ያተኮረ ነው።
ዋና ዋና የውይይቱ ጉዳዮች፦
በGaza Strip እየተባባሱ ያሉ የእስራኤል ወታደራዊ እርምጃዎችንና ጥቃቶችን ማስቆም።
ለሆስፒታሎች፣ ለመሠረተ ልማት አስፈላጊ የሆነ የሰብዓዊ እርዳታ እንዲገባ ማረጋገጥ።
Sharm el-Sheikh agreement የተባለው ስምምነት እንዲፈጸም መነጋገር።
አስተዳደራዊ ኮሚቴ ማቋቋም፣
ዓለም አቀፍ ጥበቃ ማግኘት፣
የእስራኤል ኃይሎች ከጋዛ ሙሉ በሙሉ እንዲወጡ ማድረግ፣
በመጨረሻም የፍልስጤማውያንን የፖለቲካ መብቶችና መንግሥት የመመስረት ግብ ለማሳካት መሥራት በሚመለከት ነዉ
