en
Feedback
The son of God

The son of God

Open in Telegram

ሻሎም ሻሎም የአባቴ ልጆች 🤚🤚 በመጀመርያ የእዚህ ቻናል ቤተሰብ ስለ ሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን 🔥🔥 በዚህ ቻናል የሚለቀቁ spiritual priach, music, video እንድትባረኩ ይሁን 🔥🤚 አስተያየት, ጥያቄ 👉 @ATSGOD #YouTube 👇 https://youtube.com/@THESONOFGOD-S.G?si=R-VmI9EFhmf8 JOIN US t.me/ThesonofGod1

Show more
2 145
Subscribers
-324 hours
-117 days
-4930 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
September '26
September '26
+2
in 0 channels
August '26
+4
in 0 channels
Get PRO
July '26
+4
in 0 channels
Get PRO
June '26
+7
in 0 channels
Get PRO
May '26
+6
in 0 channels
Get PRO
April '26
+7
in 0 channels
Get PRO
March '26
+9
in 0 channels
Get PRO
February '26
+3
in 0 channels
Get PRO
January '26
+4
in 0 channels
Get PRO
December '25
+3
in 0 channels
Get PRO
November '250
in 0 channels
Get PRO
October '25
+2
in 0 channels
Get PRO
September '25
+5
in 0 channels
Get PRO
August '25
+5
in 0 channels
Get PRO
July '25
+5
in 0 channels
Get PRO
June '25
+7
in 0 channels
Get PRO
May '25
+14
in 0 channels
Get PRO
April '25
+120
in 0 channels
Get PRO
March '25
+286
in 0 channels
Get PRO
February '25
+342
in 2 channels
Get PRO
January '25
+340
in 0 channels
Get PRO
December '24
+160
in 0 channels
Get PRO
November '24
+120
in 0 channels
Get PRO
October '24
+85
in 0 channels
Get PRO
September '24
+200
in 0 channels
Get PRO
August '24
+501
in 0 channels
Get PRO
July '24
+548
in 0 channels
Get PRO
June '24
+351
in 0 channels
Get PRO
May '24
+103
in 0 channels
Get PRO
April '24
+146
in 1 channels
Get PRO
March '24
+245
in 0 channels
Get PRO
February '24
+259
in 1 channels
Get PRO
January '24
+490
in 1 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
10 September0
09 September0
08 September0
07 September0
06 September+1
05 September0
04 September0
03 September0
02 September0
01 September+1
Channel Posts
የሰዎች ነቀፋ ከፈጣሪህ ፍቅር እንዳያርቅህ! 💡 ንጉሥ ዳዊት በደስታና በቅንነት እግዚአብሔርን ሲያመሰግን፣ የሳኦል ልጅ ሜልኮል “የእስራኤል ንጉሥ ዛሬ ራሱን አዋረደ” ስትል በአፌዘችበት ወቅት፤ ዳዊት የሰውን ይልቅ የአምላኩን ክብር በመምረጥ “እኔስ ከሳኦል ቤት መርጦ ለሾመኝ ጌታ ነው የዘመርኩት፤ ከዚህም በላይ እዋረዳለሁ!” ሲል ድንቅ ምላሽ ሰጥቷታል። ይህ ታሪክ ሰዎች “ተዋረድክ” የሚሉህ ቦታ በእግዚአብሔር ፊት የምትከብርበት ሊሆን እንደሚችልና እግዚአብሔርን በቅንነት ስናመሰግን የሰዎችን ትችትና መመዘኛ ወደ ጎን ትተን የሰጠንን አምላክ ማስቀደም እንዳለብን ያስተምረናል። 🙏 (📖 *2ኛ ሳሙኤል 6:20-22*) @ዶ/ር ሬቨረንድ ተዘራ ፍርድ @ThesonofGod1

2
ቸርች እንዴት ነበር? (How was Church?) "...ከመርከብ ወደ ዉሃ..." “በጽዮን ላሉ ዓለመኞች፥ በሰማርያም ተራራ ላይ ተዘልለው ለተቀመጡ፥ የእስራኤልም ቤት ወደ እነርሱ ለመጡባቸው ለአሕዛብ አለቆች ወዮላቸው!” — አሞጽ 6፥1 “Woe to them that are at ease in Zion, and trust in the mountain of Samaria, which are named chief of the nations, to whom the house of Israel came!” — Amos 6፥1 (KJV) ✍️ ብዙ ጊዜ ባለንበት ቦታ እና በደረስንበት ደረጃ ተመቻችተን መቀመጥን እንመርጣለን። በሕይወታችን በየደረጃው ትልልቅ ስኬቶች የሚመጡት ተዘልለን ከተቀመጥንበት ወንተን ዋጋ ለመክፈል ዝግጁ ስንሆን እና በእምነት ስንመላለስ ነው። እምነት አንዱ ከእኛ የሚፈልገው ትግበራን ሲሆን፤ ያም የሚሆነው በአንደበታችን ስንናገር እና ስንንቀሳቀስ ነው። እንዲሁም እምነት Risk መውሰድን የሚያካትት ሲሆን፤ አሁን ባለንበት ቦታ እና ልንደርስበት ባለው ቦታ መሃል ያለው ነገር Risk ነው። በዚህ እርግጠኝነት በሌለበት ዓለም እርግጠኛ ሆነን እንድንኖር የሚያደርገን እምነት ሲሆን፤ ይህ እምነት በእግዚአብሔር ላይ መደገፍ ማለት እንጂ መገመት ወይንም በእግዚአብሔር ላይ መደፈር አይደለም። በመጨረሻም በእምነት እንጂ በማየት እና በስሜት ስንመላለስ ያኔ በጣም ተመችቶን አለን ማለት ነው። በዚህም ምክንያት ነው እግዚአብሔር የሆነን ነገር ሲለን ከሞቾቶቻችን ወጥተን ማድረግ የሚከብደን። ከምቾት መውጣት እና በእምነት መንቀሳቀስ ውርሳችንን እንድናገኝ ያደርገናል። ማቴዎስ 14 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁷ ወዲያውም ኢየሱስ ተናገራቸውና፦ አይዞአችሁ፥ እኔ ነኝ፤ አትፍሩ አላቸው። ²⁸ ጴጥሮስም መልሶ፦ ጌታ ሆይ፥ አንተስ ከሆንህ በውኃው ላይ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዘኝ አለው። ²⁹ እርሱም፦ ና አለው። ጴጥሮስም ከታንኳይቱ ወርዶ ወደ ኢየሱስ ሊደርስ በውኃው ላይ ሄደ። ቀን እሁድ 07/10/2018 ⛪️ የክብር ሕይወት ቤተክርስቲያን አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ መልካም የመነሳትና የማብራት ምሽት @ThesonofGod1
185
3
ቸርች እንዴት ነበር? (How was Church ?) "...መሞት፣ መቀበርና መነሳት..." 1ኛ ቆሮንቶስ 15 ³ እኔ ደግሞ የተቀበልሁትን ከሁሉ በፊት አሳልፌ ሰጠኋችሁ እንዲህ ብዬ፦ መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥ ⁴ መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፥ ✍️ የጌታ የኢየሱስ ትንሳኤ የፋሲካ ልብ ነው፤ መስቀሉ ኢየሱስ ስለ ኀጢአታችን መሞቱን ያሳያል፤ ትንሳኤው ደግሞ መስዋዕትነት ተቀባይነት ማግኘቱን ማንነቱ እዉነት መሆኑን እና ድሉ ሙሉ መሆኑን ያረጋግጣል። ትንሳኤ ማለት ጌታ ኢየሱስ ስለ እኛ ኀጢአትና በደል ከሞተ በኋላ በአካል ከሙታን መነሳቱን ነው። ይህም ዝም ብሎ ሀሣብ ብቻ ሳይሆን እዉነተኛ ታሪካዊ ክስተት ነዉ፤ ማለትም በትክክል ሞቶ ነበር፣ ተቀብሮ ነበር እንዲሁም በሦስተኛ ቀን በእውነት ተነስቷል። ትንሳኤው ኢየሱስ ሰው ብቻ እንዳልሆነ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን፣ የመስቀሉን መስዋዕትነት ተቀባይነት ማግኘቱን፣ ሞትን ድል ማድረጉን፣ አዲስ ሕይወት መስጠቱን፣ የኀጢአትን ኀይል መስበሩን፣ የመንፈስ ቅዱስ ኀይል መለቀቁን አረጋግጧል። በመጨረሻም ትልቅነት የሚለካው በተቋቋምነው እና ባለፍነው መከራ ልክ ነውና፤ ኢየሱስ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ከሆነለት በኋላ ወደ መንፈስ ቅዱስ የኀይል ሙላት የገባው በፈተና እና በመከራ በማለፍ ነዉ። ሁልጊዜ ልንዘነጋው የማይገባን እዉነት ከእነዚህ ሁሉ መከራ በኋላ ግን ትንሳኤ አለ! ስለዚህ ኢየሱስን ከሙታን ባስነሳው በውስጣችን ባለዉ በመንፈስ ቅዱስ እንታመን! “ነገር ግን ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው የእርሱ መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ ክርስቶስ ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው እርሱ በእናንተ በሚኖረው በመንፈሱ፥ ለሚሞተው ሰውነታችሁ ደግሞ ሕይወትን ይሰጠዋል።” — ሮሜ 8፥11 ሬቨ. ዶ/ር ተዘራ ያሬድ ቀን እሁድ 18 /08/2018 መልካም የመነሳትና የማብራት ምሽት @ThesonofGod1
135
4
ቸርች እንዴት ነበር? (How was Church?) "...ለመስራት ተፈጥሬአለሁ ! ..." “እግዚአብሔርም አለ፦ እነሆ መብል ይሆናችሁ ዘንድ በምድር ፊት ሁሉ ላይ ዘሩ በእርሱ ያለውን ሐመልማል ሁሉ፥ የዛፍን ፍሬ የሚያፈራውንና ዘር ያለውንም ዛፍ ሁሉ ሰጠኋችሁ፤” — ዘፍጥረት 1፥29 ✍️ እግዚአብሔር ሰውን ከመፍጠር በፊት ያዘጋጀለት ስፍራ እና ከፈጠረውም በኋላ ያዘዘው መሠረታዊ ነገር ስራ ነው፤ ማለትም እንዲንከባከብ እና እንዲያበጅ። ለዛም ነው ምድር ያላበቀለችው የሚሠራባት ሰው ስላልነበር ነው የሚለው። ዘፍጥረት 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁵ የሜዳ ቁጥቋጦ ሁሉ በምድር ላይ ገና አልነበረም፤ የሜዳውም ቡቃያ ሁሉ ገና አልበቀለም ነበር፣ እግዚአብሔር አምላክ ምድር ላይ አላዘነበም ነበርና፥ ምድርንም የሚሠራባት ሰው አልነበረም፤ በመጀመሪያ የተፈጠርነው ለመስራት ሲሆን ስራ ለሰው ልጅ የተሰጠው ከኀጢአት መግባት በፊት ነው። በዚህ ምክንያት ነው የትኛውም ያለንበት ስራ ላይ በትጋት እና በደስታ ልንሰራ የሚያስፈልገን። ⁸ እግዚአብሔር አምላክም በምሥራቅ በዔድን ገነትን ተከለ የፈጠረውንም ሰው ከዚያው አኖረው። ⁹ እግዚአብሔር አምላክም ለማየት ደስ የሚያሰኘውን፥ ለመብላትም መልካም የሆነውን ዛፍ ሁሉ ከምድር አበቀለ፤ በገነትም መካከል የሕይወትን ዛፍ፥ መልካምንና ክፉን የሚያስታውቀውንም ዛፍ አበቀለ። እግዚአብሔር በመጀመሪያ ሰውን ፈጥሮ በዔደን ገነት ተክሎ በዚያ ማስቀመጡ የሚያሳየን እግዚአብሔር በሰው ሕይወት ውስጥ የሚያስቀምጠው ራዕይ ሆነ አላማ የሚገለጠው በስራ መሆኑን ነው። ስራ የማያደክመን በስራ ደስተኛ ከሆንን ብቻ ሲሆን ደስተኛ አለመሆን እና ከስራ ውጪ ሆኖ በስንፍና መሆን ትልቅ ዋጋ መክፈል እና ከተፈጠርንበት አላማ መራቅ ያመጣል። ነገር ግን በትጋት ለሚሰራ ሰው... “በሥራው የቀጠፈ ሰውን አይተሃልን? በነገሥታት ፊት ይቆማል፤ በተዋረዱም ሰዎች ፊት አይቆምም።” — ምሳሌ 22፥29 በመጨረሻም ስራ የተፈጠርንበት አላማ ሲሆን ስራን በትጋትና በደስታ መስራት የሚጠበቅብን የክርስቲያን የሕይወት ዘይቤ እና አኗኗር ነው። በገዛ እጃችን በመስራትና በትጋት እንታወቅ! “የሰረቀ ከእንግዲህ ወዲህ አይስረቅ፥ ነገር ግን በዚያ ፈንታ ለጎደለው የሚያካፍለው እንዲኖርለት በገዛ እጆቹ መልካምን እየሠራ ይድከም።” — ኤፌሶን 4፥28 ሬቨ. ዶ/ር ተዘራ ያሬድ ቀን እሁድ 27/07/2018 @ThesonofGod1
165
5
…..መልካም ነገርም አያጡም!!! “የአንበሳ ደቦሎች ያጣሉ፤ ይራባሉም፤ እግዚአብሔርን የሚፈልጉት ግን ምንም አይጐድልባቸውም፤ መልካም ነገርም አያጡም።” መጽሐፈ መዝሙር 34 : 10 አማ05 ጥቅሱን በአጭሩ በሦስት ዋና ዋና ነጥቦች እንዲህ መረዳት ይቻላል፡- 1. የአንበሳ ደቦሎች ምሳሌነት በተፈጥሮ ሕግ አንበሳ ጠንካራ፣ አዳኝና በራሱ የሚተማመን እንስሳ ነው። ነገር ግን ያ የላቀ ጥንካሬውና ኃይሉ እንኳ ሳይቀር ለረሃብና ለችግር ሊዳርገው እንደሚችል ቃሉ ይነግረናል። ይህ የሚያሳየው በሰውኛ ጉልበትና ጥበብ ብቻ መታመን መጨረሻው እጦት ሊሆን እንደሚችል ነው። 2. እግዚአብሔርን መፈለግ "እግዚአብሔርን የሚፈልጉ" ሲል በሙሉ ልባቸው በእርሱ የሚታመኑትን፣ መመሪያውን የሚከተሉትንና እርዳታውን የሚጠባበቁትን ያመለክታል። እነዚህ ሰዎች ትኩረታቸው በራሳቸው ችሎታ ላይ ሳይሆን በፈጣሪ ቸርነት ላይ ነው። 3. የመጥገብና የመትረፍረፍ ተስፋ ጥቅሱ የሚደመድመው በታላቅ ተስፋ ነው፦ * "ምንም አይጎድልባቸውም"፦ መሰረታዊ ፍላጎታቸው ይሟላል። * "መልካም ነገርን አያጡም"፦ እግዚአብሔር ለሕይወታቸው የሚጠቅመውንና የሚያስፈልገውን በወቅቱ ይሰጣቸዋል። ባጭሩ፦ ይህ ቃል የሚያስተምረን የሰው ልጅ ኃይልና ሀብት ለሁሉ ነገር ዋስትና እንደማይሆኑና እውነተኛው እርካታና ሙሉነት የሚገኘው ደግሞ በፈጣሪ ላይ በመታመን ብቻ እንደሆነ ነው። በአለም ላይ ብርቱዎች ሲዝሉ፣ በእግዚአብሔር የሚታመኑ ግን በበረከቱ ይጠግባሉ። ኮሜንት ያ ሰው እኔ ነኝ!!!! መልካም ምሽት!!! ሬቨ ዶ/ር ተዘራ ያሬድ @ThesonofGod1
188
6
ቸርች እንዴት ነበር? (How was Church?) "...በእምነት..." “ነገር ግን፦ አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ያው አንዱ የእምነት መንፈስ ስላለን፥ እኛ ደግሞ እናምናለን ስለዚህም እንናገራለን፤” — 2ኛ ቆሮ 4፥13 ✍️ ሰዎች እንዲያምኑ እንዲሁም እንዳያምኑ የሚያደርጋቸው ትምህርት ሲሆን ሰዎችን እንዳያምኑ ማስተማር ኃጢአት ነው ሰዎች እንዲያምኑ ማስተማር ደግሞ በእምነት ሕይወት እንዲመላለሱ መርዳት ነው። የእምነት መንፈስ የውስጥ ሰው አመለካከት ወይንም ዝንባሌ ነው። ማለትም የእምነት መንፈስ የሚለው ሀረግ የሚከተለው የውስጥ አቋምን ነው። "መንፈስ" ስንል የሚያመላክተው የውስጥ ሰውን (ልብን)፣ የእምነት እና የማመን ማዕከልን ነው። ስለዚህ የእምነት መንፈስ የላይ ላይ ንግግር እና የውጭ ባህርይ ብቻ አይደለም ነገር ግን ስለ እግዚአብሔር ያለ የጸና የውስጥ መረዳት (persuasion) ነው። እንዲሁም ይህ መንፈስ የሚኖረን ልባችን ሲያምንና በዛ እምነት ላይ ጸንቶ ሲቆም ነው። እምነት በውጤቶች፣ በስሜቶች፣ በሁኔታዎች እና በሰው ልጅ ጥረት ላይ አይመሠረትም ይልቅስ እምነት መጀመሪያ የእግዚአብሔርን ቃል ይፈልጋል። ምክንያቱም ያለ ቃል እምነት የለም! መጽሐፍ ቅዱሳዊ እምነት ሁልጊዜ እግዚአብሔር በዚህ ጉዳይ ላይ ምን ብሏል ለሚለው ጥያቄ መልስ ይሰጣል። በመጨረሻም አማኝ እንዲያምን ማድረግ ያለበት እምነት በራሱ ወዲያው የሚሆን አለመሆኑን ማወቅ እና የእምነት መንፈስ ቃሉን መቀበልን እንዲሁም እንደ እውነት መቁጠርና በውስጣችን ፅኑ እምነትን እንዲፈጥር መፍቀድን እንደሚያካትት መረዳት ነው። እምነት ሁልጊዜ እግዚአብሔር የተናገረውን ሊያደርግ እንደሚችል በልቡ ሙሉ እምነት እንዲኖረን ያደርጋል! “ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም።” — ሮሜ 4፥20-21 ሬቨ. ዶ/ር ተዘራ ያሬድ ቀን እሁድ 27/07/2018 ⛪️ የክብር ሕይወት ቤተክርስቲያን አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ መልካም የመነሳትና የማብራት ምሽት
193
7
ቸርች እንዴት ነበር? (How was Church?) “ነገር ግን፦ አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ያው አንዱ የእምነት መንፈስ ስላለን፥ እኛ ደግሞ እናምናለን ስለዚህም እንናገራለን፤” — 2ኛ ቆሮ 4፥13 "...የእምነት መንፈስ..." ✍️ የእምነት መንፈስ ተናጋሪ መንፈስ ሲሆን በዚህ መንፈስ ሆነን የምንናገረው አድራሻችንን መድረሻችንንም ጭምር ይወስናል። የእምነት መንፈስ ዝም ብሎ አዎንታዊ አስተሳሰብ (Positive thinking)፣ ብሩህ አመለካከት (Optimism) ወይም ስሜታዊ መነቃቃት (Emotional excitement) አይደለም። ይልቅስ የእምነት መንፈስ በእግዚአብሔር ቃል መገለጥና በእግዚአብሔር ማንነት ላይ ባለን መተማመን የሚመነጭ መንፈሳዊ ዝንባሌ ሲሆን፤ አማኝ በጽኑ እንዲያምን፣ በድፍረት እንድንናገር እና ከእግዚአብሔር ቃል ጋር በመስማማት በድፍረት እንዲንቀሳቀስ የሚያደርግ ነው። የእምነት መንፈስ ሁኔታዎች ሌላ ነገር ቢናገሩም እንኳን አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር እንዲቆም የሚያደርግ የውስጥ ኃይል ነው። ይህ አይነት እምነት ደግሞ እንዲህ ይናገራል እግዚአብሔር ተናግሯል ስለዚህ አምናለሁ! ስላመንሁ እናገራለሁ! እንደ እግዚአብሔር ቃል ስለተናገርኩ በመተማመን እሰራለሁ! እግዚአብሔር ታማኝ ስለሆነ ለፍርሃት፣ ለሽንፈትና ላለመታመን እጅ አልሰጥም! በመጨረሻም የእምነት መንፈስ እንደ መንፈሳዊ ሕግ በብሉይ ኪዳን የነበረውን ከአዲስ ኪዳን ሕይወት ጋር በማገናኘት ይታያል ይህ የሚያሳየው የእምነት መንፈስ በሁሉም ዘመናት የማይለወጥ መሆኑን ነው። የእምነት መንፈስ ሕግ ራእይ (መገለጥ)፣ እምነት (ማመን)፣ ማወጅ(መናገር)፣ ተግባር እና መገለጥ በሚለው ሂደት ውስጥ በማለፍ በእምነት በሕይወት ላይ በድል እንድንኖር ያደርጋል። “አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ....” — መዝሙር 116፥10 ሬቨ. ዶ/ር ተዘራ ያሬድ ቀን እሁድ 13/07/2018 ⛪️ የክብር ሕይወት ቤተክርስቲያን አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ መልካም የመነሳትና የማብራት ቀን @ThesonofGod1 @ThesonofGod1
229
8
ይህን መጽሐፍ አንብቡት ትወዱታላችሁ ! አላማ መር ህይወት መልካም ንባብ🙌 ለሌሎች አጋሩዋቸው 🤗 @ThesonofGod1 @ThesonofGod1
743
9
አይመጥኑህም ሳሙኤል ገመስቀል
239
10
Wedaj___ወዳጅ__Hanna_Tekle__Jan_2025(360p).mp4
249
11
ትንቢተ ኤርምያስ 6:16 (NASV) •••••••••• ¹⁶ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “መንታ መንገድ ላይ ቁሙ፣ ተመልከቱም፤ መልካሟን፣ የጥንቷን መንገድ ጠይቁ፤ በእርሷም ላይ ሂዱ። ለነፍሳችሁ ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ እናንተ ግን፣ ‘በእርሷ አንሄድም’ አላችሁ። @ThesonofGod1 @ThesonofGod1
246
12
“በእግዚአብሔር የምታምኑ ሁላችሁ፥ በርቱ ልባችሁም ይጥና።” — መዝሙር 31:24 @ThesonofGod1 @ThesonofGod1
“በእግዚአብሔር የምታምኑ ሁላችሁ፥ በርቱ ልባችሁም ይጥና።” — መዝሙር 31:24 @ThesonofGod1 @ThesonofGod1
252
13
Amazing protestant music piano 🎹🎶 For meditation ☺️ @ThesonofGod1 @ThesonofGod1
202
14
https://t.me/YidnekachewTekaofficial
212
15
በዚህ መዝሙር ተባረኩ መልካም ቀን! @ThesonofGod1 @ThesonofGod1
6
16
🧎ስንወድቅ፤ ሊያነሳን... 🧑‍🦯ስንደክም ፤ ሊያበረታን... 🚶ተስፋ ባጣን ጊዜ ፤ ተስፋን የሚሰጠን... 😔በኃጥያት ልምምድ ውስጥ በሆንን ጊዜ፤ ከዚያ ልምምድ ወተን በጽድቅ እንድንመላለስ የሚያደርገን.... 💆መጸለይ በከበደን ጊዜ፤ እንደገና እንድንጸልይ የሚያደርገን... 🤦የእግዚአብሔርን ቃል ማንበብ ባቃተን ጊዜ፤ በትጋት እንድናነብ እና እንድናጠና የሚደርገን ....            አንድ እውነት አለ! የክርስቶስ ፍቅር !💙 The love of Christ!💙 “የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ #የእግዚአብሔርም_ፍቅር #የመንፈስ_ቅዱስም_ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።”   — 2ኛ ቆሮ 13፥14 መልካም ምሽት!❤️ @ThesonofGod1 @ThesonofGod1
703
17
https://t.me/minister_beki_timothy?livestream
215
18
  ▮Spiritual Discipline▮                  ትርጉም መንፈሳዊ እድገትን ለማምጣት በፈቃደኝነት እና በየቀኑ እራስን ከመግዛት ጋር የሚደረግ መንፈሳዊ ልምምድ።    ክፍል-ሁለት                      PART ➋ 🖱@minister_beki_timothy🖱 🖱@minister_beki_timothy🖱      ── ❖ ──  ✦ ── ❖ ──           🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉ  ✓
210
19
      ▮Spiritual Discipline▮                 ትርጉም መንፈሳዊ እድገትን ለማምጣት በፈቃደኝነት እና በየቀኑ እራስን ከመግዛት ጋር የሚደረግ መንፈሳዊ ልምምድ።    ክፍል-አንድ          PART ➊ 🖱@minister_beki_timothy🖱 🖱@minister_beki_timothy🖱      ── ❖ ──  ✦ ── ❖ ──           🔺ይ🀄️ላ🀄️ሉ  ✓
214
20
No text...
234