en
Feedback
ሙሐመድ የንፅፅር ማህደር

ሙሐመድ የንፅፅር ማህደር

Open in Telegram

የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! በእኛና በእናንተ መካከል ትክክል ወደኾነች ቃል ኑ፡፡(እርሷም) አሏህን እንጅ ሌላን ላንገዛ፣ በእርሱም ምንንም ላናጋራ፣ ከፊላችንም ከፊሉን ከአሏህ ሌላ አማልክት አድርጎ ላይይዝ ነው፣በላቸው። እምቢ ቢሉም፦እኛ ሙስሊሞች መኾናችንን መስክሩ በሏቸው።3:64 መልካም የማንበብና የማነፃፀር ጊዜ ይሁንሎ!

Show more
957
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-2130 days
Posts Archive
“ዘመነ ማቱዮስ”  ብለው አስረከቡት አላህ በፈጠረው  ቀንና ሌሊቱ ያለ ማንም አጋዥ  በብቸኝነቱ፤ ጌትነቱን ክደው  ነጠቁት መብቶቹ አካፍለው ጨረሱት  ለፍጥረታቶቹ። ቀናቶች ለመልኣክ  ለታቦት ቸርችረው ለተቀሩት ሰጡ  ዘመናት ከፋፈለው። 21ለማርያም  ሌላኛው ለገብርኤል አንዱ ለልደታ  ሌላው ለሚካኤል። “ዘመነ ማቲዮስ”  ብለው አስረከቡት ለሉቃስ ቀጣዩ  ወስደው ሊያወርሱት። የሁሉም ፈጣሪ  ለነበረው ☝️ጌታ ታድያ ምን ቀረለት  በእነርሱ ሙገታ❓ ሁሉም ከለከሉት  ሁሉንም ነፈጉት አምላክነት ሳይቀር  ለ3 አካፈሉት። ለዚህ ክህደታቸው  ይከፍላሉ ዋጋ🔥 ጌታህ ይታገሳል  ምንም አይዘነጋ!! ✍️ከሐምዱ ቋንጤ -------------------------------------- ሙሐመድ የንፅፅር ማህደር ወሠላሙ ዐለይኩም

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته 📜መውሊድን በተመለከተ በኡስታዝ ኢብኑ ሙነውር የተዘጋጁ ከፊል ፅሁፎችን በቀላሉ እንዚህን ሊንኮችን በመጫን ማንበብ እንችላለን። ለወዳጅ ዘመድ በማጋራት የመመራት ምክንያት እንሁን። 1, ነብዩ ﷺ መቼ ተወለዱ? 2, መውሊድን ማን ጀመረው? በመረጃ ለሚያምኑ ብቻ 3, መውሊድ ለምን አላማ እንደተጀመረ ያውቃሉ? 4, መውሊድና ነባሩ እስልምና አይተዋወቁም! {ምስክር እራሳቸው!} 5, “በአላህ እዝነት ይደሰቱ...” - ትልቁ የመውሊድ አጋፋሪዎች ምርኩዝ 6, የሰኞ ፆም እና መውሊድ 7, ዐቂቃ ሌላ መውሊድ ሌላ! 8, ዓሹራን ለመውሊድ? 9, መውሊድ ውስጥ እነዚህ አደጋዎች አሉ! 10, በመውሊድ ላይ ስለሚፈፀመው ጭፈራ ዑለማዎች ምን እንዳሉ ታውቃለህ? 11, መውሊድን የሚፈቅዱትም አይፈቅዱትም! 12, መውሊድ የማያከብር ሰው የሙሐመድ ﷺ ጠላት ከሆነ፣ ገና የማያከብር ሰው የዒሳ ጠላት ነው! 13, እውን የሡወይባ ታሪክ ለመውሊድ ማስረጃ ይሆናል? 14, ሸውካኒ እና መውሊድ (ወሳኝ ነጥቦች የተዳሰሱበት) 15, ሲዩጢ፣ የመውሊድ ደጋፊዎች ሌላኛው ምርኩዝ 16, እውን ኢብኑ ተይሚያ መውሊድን ፈቅደዋል? 17, በሸይኹል አልባኒ እና “መውሊድ ይፈቀዳል” በሚል ሰው መካከል የተደረገ ድንቅ ቃለ-ምልልስ 18, ከ“ወሃብዮች” በፊት የነበሩ የመውሊድ ተቃዋሚዎች 19, መውሊድ ተከሽኖ 20, ለምንድን ነው የመውሊድ ተቃውሞ ኢኽዋኖችን ምቾት የሚነሳቸው? 21, መሷሊሐል ሙርሰላ፣ የመውሊድ አክባሪዎች የመጨረሻው ምሽግ -----------------Ω-------------------------- https://t.me/muhammed6964 ወሠላሙ ዐለይኩም

ክፍል 13 በሌሎች አካባቢዎች… በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ፥ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡       በሌሎች አካባቢዎች እንዲሁ ጥንት አረማውያን አምላክ በሶስት ማንነቶች ይገለፃል የሚል እምነት እንደነበራቸው የታሪክ ድርሳናት ይገልፃሉ። ሶርያና ሊባኖስ ድንበር ላይ ይገኙ በነበሩ የ‹‹ፈኒሻ›› ጥንታዊ ከተሞች ‹‹ኡሎሙስ››፣ ‹‹ኡሎሱሮስ›› እና ‹‹ኢሉን›› የተባሉ ሶስት አምላኮች እንደ አንድ ይመለኩ ነበር። ሮማውያን ክርስትናን ከመቀበላቸው በፊት ደግሞ ‹‹ጁፒተር››፣ ‹‹ኔፕቱን›› እና ‹‹ፕልቶ›› አምላኮቻቸው ነበሩ። በጀርመናውያን እንዲሁ ከክርስትና በፊት ‹‹ዎደን››፣ ‹‹ሶር›› እና ‹‹ፍሪኮ›› የተባሉ ሶስት አምላኮችን በአንድነት ያመልኩ ነበር።(1)       መጽሐፍ ቅዱስንም ብንመለከት ጥንታዊ አረማውያን ከግዑዛን ጣዖታት ባለፈ አስታሮት፣ ሚልኮም፣ ካሞሽና ሞሎክ የሚባሉትን ጨምሮ ሌሎች አማልክትንም ይገዙ እንደነበረ ይጠቅሳል።(2) ጥንት የነበሩ እስራኤላውያንም በተለያየ ወቅት በኣል (ጣዖት) እውነተኛ አምላክ ነው ብለው ያምኑ እንደነበረ ተፅፎ እናገኛለን። በዚህም ምክንያት አምላክ በተለያዩ ጊዜያት ነቢያትን በማስነሳት ጣዖታትን ርቀው እሱን ብቻ እንዲያመልኩ ጠርቷቸዋል። ከነቢያቱም መካከል አንዱ የሆነው ኤልያስ ‹‹እስከ መቼ ድረስ በሁለት አሳብ ታነክሳላችሁ? እግዚአብሔር አምላክ ቢሆን እርሱን ተከተሉ፤ በኣል ግን አምላክ ቢሆን እርሱን ተከተሉ።››(3) በማለት ሕዝቡ እውነቱን አውቆ ምርጫ እንዲያደርግ ጠይቆ እንደነበረም ተጠቅሷል።       እስራኤላውያን በኣልን ማምለክ የጀመሩት ሰማያዊ አምላክ የለም ከማለት እሳቤ ሳይሆን አምላካዊ ባህሪን ለፍጡራን በመስጠን ወይንም ሁለቱን ባህርያት በመቀየጥ በተፈፀመ ስህተት እንደሆነ ታሪካቸው ይነግረናል። ለአብነት በሙሴ ዘመን የተከሰተውን ብናይ ሙሴን በሲና ተራራ ላይ በመዘግየቱ በምድር የሚመራቸው ሌላ መሪ ስለፈለጉ አሮንን ‹‹ይህ ከግብፅ ምድር ያወጣን ሰው ሙሴ ምን እንደሆነ አናውቅምና ተነሥተህ በፊታችን የሚሄዱ አማልክት ሥራልን አሉት››(4) እንጅ ሰማያዊ አምላክ የለም ብለው አልካዱም ነበር።       የዚህ አይነት ታሪክ በነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) ዘመንም የተከሰተ ሲሆን ሰሐባዎች (ባልደረቦቻቸው) በጊዜው አዲስ ወደ ኢስልምና የገቡ በመሆናቸው እንደ ጣዖታውያኑ በጉዞ ላይ የሚያርፉበትንና መጠጊያ የሚሆናቸው (የሚለማመኑት) ዛፍ እንዲያደርጉላቸው ጠይቀው እንደነበር በሐዲስ ተፅፏል። ነቢዩም (ሰዐወ) በጥያቄያቸው እጅግ በመደመም ‹‹አላህ ታላቅ አምላክ ነው። ነፍሴ በእጁ በሆነው ጌታዬ እምላለሁ! ይህች ያለፉት ትውልዶች መንገድ ናት። ልክ እናንተ እንደጠየቃችሁት የእስራኤል ልጆችም ሙሳን (ዐሰ) ‹ለእኛም እንደ ጣዖታውያኑ አማልክት አድርግልን› ብለው ጠይቀውት ነበር። እሱም ‹እናንተ ሊመለክ የሚገባውን የማታውቁ ሕዝቦች ናችሁ› ብሏቸዋል። እናንተም ታዲያ በስህተት ያለፉትን ሰዎች መንገድ ልትከተሉ ትፈልጋላችሁ?››(5) የሚል መልስ ሰጥተዋቸዋል።       በአጠቃላይ ይህ የታሪክ ፍሰት ከ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በኋላ የመጡት የሥላሴ ክርስትና መስራቾች በነቢያት አፍ ሲነገር የኖረውን አንዱንና ብቸኛውን መለኮታዊ አምላክ ልክ እንደ አይሁዶችና ቀደምት ሙስሊሞች (ምንም እንኳ ሙሴና ነቢዩ ሙሐመድ እርምት ቢያደርጉም) በተሳሳተ መንገድ በአካባቢያቸው ከተንሰራፋው የአረማውያን በኣል (ጣዖት) ጋር በመቀየጥ የሶስትነት አምላክን እንደፈጠሩና በዚህም ምክንያት ከትክክለኛው የነቢያት መንገድ እንደራቁ ያሳየናል።       እናም ወደ መጽሐፍ ቅዱስ ከተመለስን በበርካታ ምዕራፎች ውስጥ ስለ ፈጣሪ አንድነት ቀላል መረዳት እንዳለ እንገነዘባለን። የኢየሱስ ዋነኛ ትምህርትም ይሄው እንደነበረ ማስረጃዎችን ጠቅሰናል። እስካሁን እንዳየነውም ‹‹ሶስትነት›› የሚባለው ሮማውያን ከጥንት አረማዊ እምነታቸው የተዋሱት እንጅ ትክክለኛው የጥንት ነቢያት እምነት እንዳልሆነ መጽሐፍ ቅዱስም የታሪክ መዛግብትም ምስክሮቻችን ናቸው።       አሳዛኙ ነገር ግን ይህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሰረት የሌለው አስተምህሮት በብዙዎች ዘንድ እንደ እውነት ተቆጥሮ ችላ መባሉ ነው። በግሌ ለእምነታቸው ያደሩ ብዙ ክርስቲያኖችን አውቃለሁ። አንዳቸውም ግን ስለ ሥላሴ እርግጡን አያውቁም።ምናልባትም ‹‹ሶስት›› ነው በሚለው ጥርጣሬ ‹‹አንድ›› ነው በሚለው እውነት መሃል እየዋለሉም ይሆናል። አንዳንዶች ደግሞ በዚሁ ጥርጣሬ ውስጥ ሆነው ከአንዱ እምነት ወደ ሌላው እምነት ሲዘዋወሩ እናያለን። ምን ፍለጋ እንደሆነ አይገባኝም። ሁሉም ማረጋገጫ የሌለውን የሥላሴን አምላክነት የሚቀበሉ ከሆነ  ካቶሊክም ሆነ ኦርቶዶክስ ወይንም ፕሮቴስታንት የቅርፅ እንጅ የይዘት ልዩነት የላቸውምና።       ቤተክርስቲያንም ‹‹ሥላሴ ምስጢር ነው›› በሚል ትምህርት የአማንያኑን ዕይታ በመሸፈን የአምላካቸውን ብዝኃነት እንዳይረዱት እያደረገች ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሥላሴ ምስጢር ስለመሆኑ ምንም የተነገረ ነገር ባይኖርም አብያተክርስቲያናቱ የአስተምህሮቱን ባዕድነት ለመደበቅ ‹‹ምስጢር›› የሚል ‹‹ጭንብል›› እያለበሱት እንደሆነ እንረዳለን። በሥላሴ ላይ ጥናት የሚያደርግ ማንኛውም ሰው በስተመጨረሻ የሚረዳው ነገር ቢኖር ግን በሥላሴ ውስጥ ምንም ምስጢር እንደሌለ ብቻ ነው። በቁጥር 3 የሆኑ አካላት ‹‹አንድ›› መባላቸው ምስጢር ሳይሆን ‹‹ስህተት›› ነውና። ሶስት አካላት በየትኛውም አይነት ስሌት ‹‹አንድ›› ሊሆኑ አይችሉም። ይህ እውነታ ነው። ‹‹ምስጢር›› የሚለው ቃልም የመጣው 3ቱን ‹‹1›› ለማድረግ ብቻ ነው። እናም ክርስቲያን አማኞችም ‹‹ምስጢር›› የሚለውን ጭንብል ገልጠው የአምላካቸውን ስንትነት በትክክል ሊያውቁና የተዛባውን አመለካከት ሊያስወግዱት ይገባል እላለሁ።       በመጨረሻም ቁርኣን ከመጽሐፍ ቅዱሱ በተመሳሳይ የዚህ ፍጥረተ ዓለም አስገኝ አምላክ በብዛቱ አንድ መሆኑን ያፀደቀ ሲሆን ሶስት አካላት ናቸው ለሚሉት ሰዎች እንዲህ የሚል ምላሽ ሰጥቷል፡-       ‹‹ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም። ያን ጊዜ (ሌላ አምላክ በነበረ) አምላክ ሁሉ በፈጠረው ነገር በተለየ ነበር። ከፊላቸውም በከፊሉ ለይ በላቀ ነበር። አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ።››       (ሙዕሚኑን 92)       በሌላ የቁርኣን ምዕራፍ ደግሞ በጥንት ቅዱሳን መጽሐፍት ሲታመንበት የኖረውንና ትክክለኛውን የነቢያት አስተምህሮት በመጥቀስ ለክርስቲያን አማኞች እንዲህ የሚል ጥሪ ያቀርባል፡-       ‹‹የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! በእኛና በእናንተ መካከል ትክክል ወደ ኾነች ቃል ኑ። (እርሷም) አላህን እንጅ ሌላን ላንገዛ፣ በርሱም ምንንም ላናጋራ፣ ከፊላችንም ከፊሉን ከአላህ ሌላ አማልክት አድርጎ ላይይዝ ነው፤ በላቸው። እምቢ ቢሉም፡- እኛ ሙስሊሞች መኾናችንን መስክሩ በሏቸው።››       (ኢምራን 64) __ (1) THOMAS MAURICE (1798). “THE HISTORY OF HINDOSTAN”, VOL. 2, P. 171 (2) 1ኛ ነገሥት 11፡1,2,5,7 (3) 1ኛ ነገሥት 18፡21 (4) ዘጸአት 32፡1 (5) JAMI AT-TIRMIDHI, VOL. 4, BOOK 7, HADITH 2180 -------------------Ω-------------------------- https://t.me/muhammed6964 ወሠላሙ ዐለይኩም

ክፍል 12 ሥላሴ በተለያዩ እምነቶች በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ፥ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡       የታሪክ መዛግብት እንደሚያስረዱን ኢየሱስ ከመወለዱ በፊት በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች በሚኖሩ ጥንታዊ ማህበረሰቦች ዘንድ በሶስት በሶስት የተደራጁ ወይም በሶስትነት የተጣመሩ አማልክትን ማምለክ የተለመደ እንደነበረ ይገልፃሉ። ይህ የአረማውያን የሶስትነት አምላክ አስተምህሮትም ከኢየሱስ እርገት ከ300 ዓመታት በኋላ እያደገ በመጣው የክርስትና ‹‹ሥላሴ›› ላይ ከፍተኛ ጫና እንዳሳደረ በርካታ ምሁራን ፅፈዋል። ከእነዚህ ጥንታዊ የጣዖት እምነቶች መካከል ጥቂቶቹን እንመልከት።       ግብፅ፡- በታሪክና በእምነት ቀደምት የሆኑት ጥንታዊ ግብፃውያን እንደሚያምኑት አምላካቸው ‹‹አሙን›› ሶስት ማንነት አለው። ‹‹አሙን›› የአምላክ ስውር ማንነቱ ነው። ‹‹ሬ›› ፊቱ ‹‹ፓዝ›› ደግሞ አካሉ ነው። እነዚህ ሶስቱ ‹‹ማንነቶች›› ተጣምረው ‹‹አሙን›› የተሰኘውን አምላክ ይፈጥራሉ። የኃይማኖት አጥኝዎች እንደሚሉት ይህ የጥንታዊ ግብፃውያን እምነት ከክርስትናው ሥላሴ ጋር እጅግ የተቀራረበ ሲሆን ለአስተምህሮቱ መፈጠር ትልቅ መሰረት ጥሏል።       ከእነዚህ የታሪክ ምሁራን መካከል አንዱ የሆኑት ዊል ዱራንት ጥንታዊ የግብፅና የግሪክ ሰዎች በ‹‹ሶስትነት›› ላይ የተመሰረተ አምላክ ያመልኩ እንደነበረ ከገለፁ በኋላ ‹‹የመለኮታዊ ሥላሴ ሐሳብ የመነጨው ከግብፅ ነው›› ብለዋል።(1)       ጄምስ ሐስቲንግ የተባሉ ሌላ የታሪክ ምሁርም የሥላሴ አስተምህሮት ከሐዋርያት ዘመንም ይሁን ከዚያ በኋላ በመጡት ትውልዶች እንደማይታወቅ ገልፀው ‹‹ሥላሴ በእነአትናቴዎስ የዳበረ የጥንት ግብፃውያንና ግሪካውያን አረማዊ እምነት ነው›› በማለት የዊል ዱራንትን ሀሳብ ደግፈዋል።(2)       ይህንን ሀሳብ የሚደግፉ በርካታ የእምነትና ታሪክ አጥኝዎች በዓለማችን ላይ ያሉ ሲሆን በተጨባጭ መረጃ የተደገፈ ዳጎስ ያለ መጽሐፍ ካስነበቡን መካከል እንደነ ቶማስ ሞረስ፣ አተር ዊገል፣ ጀምስ ቦንዊክ፣ መሪን ሲንክለር የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል።       ሱመርያ፡- በጥንታዊ ሱመርያዎች እምነት ፍጥረተ ዓለሙ በሶስት አማልክት ተከፋፍሎ ይተዳደራል። ‹‹አኑስ›› የሰማዩን ክፍል አምላክ ነው። ምድር ደግሞ ለ‹‹ኢንሊል›› ተሰጥታለች። ‹‹ኢ›› የውሃውን ክፍል ይገዛል። ከዚያም አንድ ላይ በመሆን የሶስትነት አምላክን ይመሰርታሉ።(3)       ባቢሎን፡- ባቢሎናውያን በጥንት ዘመን በአምላክ ሶስትነት ያምኑ ነበር። እነዚህ አምላኮች አንድ ሰው ሆነው በሶስት ራሶች ይገለፃሉ። ክርስቲያኖች በዘመናችን ለሥላሴ ተምሳሌትነት የሚጠቀሙበትን ጎነ እኩል ሶስት ማዕዘን ቅርፅ ጥንት ባቢሎናውያን ይጠቀሙበት እንደነበረም ይታወቃል።(4)       ሕንድ፡- ፑራናስ ከ3,000 ዓመታት በላይ እድሜ ያለው የሒንዱዎች መጽሐፍ ነው። በውስጡም እንዲህ የሚል ቃል ተፅፎ እናገኛለን።       ‹‹አንድ ቀናዒ ኃይማኖተኛ ሰው ‹እናንተ ሶስት አምላኮች ሆይ! እኔ በአንድ አምላክ እንደማምን ታውቃላችሁ። ከእናንተ መሀከል ማናችሁ ትክክለኛ አምላክ እንደሆነ እባካችሁ ንገሩኝና አምልኮቴን ለእሱ ብቻ ላድርግ› ሲል ይጠይቃል። ሶስቱ አምላኮች ብርሐማ፣ ቪሽኑና ሲቫ ሲመልሱለትም ‹ይህንን እወቅ አንተ ኃይማኖተኛ ሰው። በእኛ መካከል ምንም ልዩነት የለም። እኛ ሶስት ሆነን የተገለፅንልህ በመልክ ብቻ ነው። አንድ ነገር በፈጣሪነት በጠባቂነትና በጥፋት በሶስት መልኮች ሊገለፅ ይችላል። እርሱ ግን አንድ ነው።››(5)       ግሪክ፡- በጥንታዊ ግሪካውያን ዘንድ ሶስቱ አምላኮች ማለትም ‹‹ዚዩስ›› የአማልክቶች አምላክ፣ ‹‹ፐሳይደን›› የውሃና የመሬት መንቀጥቀጥ አምላክ፣ ‹‹አዶነስ›› ደግሞ የልምላሜ አምላክ ተብለው ይታመኑ ነበር። ይህንን በማስመልከት በ400 ዓመት (ከክ.በ) ግሪካዊው ፈላስፋ አርስቶትል እንዲህ ሲል ፅፎ ነበር፡- ‹‹ሁሉም ነገሮች ሶስት ናቸው። እንዲሁም ሶስትነት ሁሉም ነገር ነው። ፓይታጎረስ እንደተናገረውም ሁሉም ነገሮች በሶስት ክፍሎች ይወሰናሉ። በዚህ መሰረት በአንድ ነገር ውስጥ መጨረሻ መካከልና መጀመሪያ የሚሉ ሶስት ቁጥሮችን እናገኛለን። ይህም የአምላክን ሶስትነት ይገልፃል።››(6) __ (1) Will Durant (1944). Caesar and Christ፡ (The Story of Civilization III)”, 653-664 (2) Hastings, James: Encyclopedia of Religion and Ethics TRINITY, pp. 461 (3) Robert Graves (1994). “The Larousse Encyclopedia of Mythology”, pp.54-55 (4) Thomas Dennis Rock (1867). “The Mystical Woman and the Cities of the Nations” pp. 22-23 (5) SINCLAIR, PP. 382-383 (6) ARTHUR WEIGALL (1928). “PAGANISM IN OUR CHRISTIANITY”, PP.197-198 --------------------Ω---------------------------- https://t.me/muhammed6964 ወሠላሙ ዐለይኩም

አይጣጣምም።       ይህንን ለማብራራት በምሳሌ እንየው፡- እኔ ‹‹አንድ›› ሰው ነኝ። ነገር ግን ዓይን አለኝ፣ እጅ አለኝ፣ እግር አለኝ...ብዬ ብከፋፍል ከአንድ በላይ ሰው ልሆን አልችልም። ዓይኔ በራሱ ‹‹ሰው›› ሊሆን አይችልም። እጄም ብቻውን ‹‹ሰው›› ሊሆን አይችልም። ሌላውም የሰውነት አካሌ ተነጥሎ ብቻውን ‹‹ሰው›› ሊሆን አይችልም። እኔ ‹‹ሰው›› የምባለው የተያዩ የአካል ክፍሎቼ ተጣምረው ነው። ሥላሴዎች ግን ሶስቱም በራሳቸው ‹‹አምላክ›› ናቸው። በአንድ ነገር ውስጥ ያሉ ክፍልፋዮች ሳይሆኑ በራሳቸው ቋሚ አካል ናቸው። ስለዚህ በአንድ አካል ውስጥ ያሉ ክፍልፋዮች አስመስሎ ለማቅረብ መሞከሩ አስተምህሮቱን ይቃረነዋል።       የባልና ሚስቱንም ምሳሌ ካየን ሁለቱ በስጋ አንድ ናቸው ተብሏል። ያስተውሉ አንድ የሆኑት ‹‹በስጋ›› ነው። በስጋ ማለት በኑሮ በህይወት ማለት ነው። ሁለቱ ተጣምረው ህይወት ወይም ኑሮ ይመሰርታሉ ማለት ነው። ነገር ግን ጥምረቱ ካልተፈጠረ ኑሮው አይመረሰትም። ምክንያቱም ሁለቱም በየራሳቸው ህይወትን መመስረት ስለማይችሉ። ሥላሴን ስናይ ግን ሶስቱ በአንድነት አምላክ ቢሆኑም ለየብቻቸውም ደግሞ አምላክ ናቸው። አንዱ የአንዱ ድጋፍ ሳያሰኘው በራሱ አምላክ ነው። እናም የሁለቱ ጉዳይ ለየቅል ነው።       ‹‹አንድ ወር›› የምንለውንም በምሳሌነት ብንጠቀም በውስጡ 30 ቀናት እንዳሉት ይታወቃል። ነገርግን እያንዳንዱ ቀን በራሱ ወር አይባልም። እያንዳንዱ ቀን ወር ቢሆን ኖሮ በእርግጥ ሥላሴን በ‹‹አንድ›› አምላክ ውስጥ ያለ ክፍልፋይ ነው ልንለው ይቻለን ነበር።       ሌላም በተደጋጋሚ የሚጠቀስ ምሳሌ እናንሳ። አንድ ዛፍ አለ። ስር፣ ግንድና ቅርንጫፍ አለው። ነገር ግን ሶስት አካላት ስላሉት ሶስት ዛፍ አይባልም፤ አንድ ዛፍ እንጅ ይባላል። ይሄም ምሳሌ ከላይ ካየነው ጋር ተመሳሳይ ነው። አንድ ዛፍ ሶስት ወይም ከዛ በላይ ክፍሎች ቢኖሩትም አንድ ዛፍ ነው የሚባለው። ነገር ግን ሶስቱም ክፍሎች በየራሳቸው ዛፍ አይሆኑም። ስሩ በራሱ ዛፍ አይሆንም። ግንዱም በራሱ ዛፍ አይሆንም። ቅርንጫፉም እንዲሁ በራሱ ዛፍ አይሆንም። ዛፍ የሚሆነው ሶስቱ ሲጣመሩ ብቻ ነው። ከላይ እንደጠቀስኩት ግን ሥላሴዎች በራሳቸው አምላክ ናቸው። ወይም በምሳሌው ዛፍ ናቸው። አብ በራሱ ዛፍ ነው። ወልድ በራሱ ዛፍ ነው። መንፈስ ቅዱስም በራሱ ዛፍ ነው። ስለዚህ ሶስት ዛፎች እንጅ አንድ ዛፍ አይደሉም።       ሌላ የመጨረሻ ምሳሌ እንጨምር። አንድ ፀሐይ አለች። ክበቧ፣ ሙቀቷና ብርሃኗ ሶስት ክፍሎች ናቸው። ነገር ግን አንድ ፀሐይ እንጅ ሶስት ፀሐይ አይደለችም ይባላል። አሁንም ያንኑ ምክንያት ነው የምናነሳው። ፀሀይ ሶስት ክፍሎች ቢኖሯትም እያንዳንዱ ክፍል ግን በራሱ ፀሐይ አይደለም። ክበቧ በራሱ ፀሐይ አይደለም፤ ሙቀቷ በራሱ ፀሐይ አይደለም፤ ብርሃኗም በራሱ ፀሐይ አይደለም። ፀሐይ የሚፈጠረው የግድ ሶስቱ ሲጣመሩ ነው። ነገር ግን ከሥላሴ ትምህርት አንፃር ካየነው አብ በራሱ ፀሐይ ነው። ወልድ በራሱ ፀሐይ ነው። መንፈስ ቅዱስም በራሱ ፀሐይ ነው። ስለዚህ ሶስት ፀሐይ እንጅ አንድ ፀሐይ አይደሉም ማለት ነው።       በአጠቃላይ ምክንያታዊ አስተሳሰብ ይዘን ቃሉን የተለየ ፍልስፍና ሳንጨምርበት እንደተነገረን ተቀብለን ከተረጎምነው ‹‹አንድ›› እግዚአብሔር የሚለው ቃል አምላክ በአካል ሶስት የሆነ ክፍልፋይ ሳይሆን በቁጥር ‹‹አንድ›› የሆነ አካል መሆኑን ያረጋግጥልናል። ------------------------------Ω-------------------------------------- https://t.me/muhammed6964 ወሠላሙ ዐለይኩም

ክፍል 11 የእግዚአብሔር አንድ አካልነት በመጽሐፍ ቅዱስ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ፥ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡      የብሉይና የአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ከአንድ አምላክ የተሰጡ መመሪያዎች ናቸው እየተባለ በአንፃሩ በርካታ የአስተምህሮት ልዩነት እንዳላቸው ቢስተዋልም የአምላክን አንድ አካልነት በተመለከተ ግን ተመሳሳይ አቋም አላቸው። እግዚአብሔር በሁለቱም ኪዳናት አንድነቱን የገለፀበት በርካታ አንቀፆችን እናገኛለን። እነዚህ አናቅፅ የአምላክን ሶስትነት የሚሰብከውን የሥላሴን ትምህርት ባዕድነት የሚነግሩን ህያው ምስክሮች ናቸው።     ከብሉይ ኪዳኑ ‹‹ፊተኛው ትዕዛዝ›› ከሚባለው የመጀመሪያው ምስክር ስንጀምር እንዲህ ይላል፡-      ‹‹እስራኤል ሆይ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው።››       (ዘዳ 6፡4)       ይህ ቃል ለአይሁዶችዋናው የእምነታቸው መሰረት ሲሆን እግዚአብሔር በነቢያቱ በኩል ያወረደው የመጀመሪያው ትዕዛዝ እንደሆነ ያትመናል። ማንኛውም ነቢይ ሲነሳም የዚህን ቃል ትክክለኛነት ካላረጋገጠላቸው ሃሳዊ ነው ብለው ያወግዙታል። በዚህም ምክንያት ኢየሱስ ወንጌልን በሚሰብክበት ወቅት ከፃፎች አንዱ ‹‹ከሁሉ ፊተኛይቱ ትዕዛዝ ማንቻይቱ ናት?›› ጠይቆታልም። ኢየሱስም፡-       ‹‹ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ። እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው።››       (ማር 12፡29)       የማለት ምላሽ ሰጥቶታል። ኢየሱስ በዚህ ንግግሩም ሆነ በአጠቃላይ ትምህርቱ አምላክ አንድ መሆኑን እንጅ በአንድነቱ ውስጥ ሶስት አካላት ስለመኖራቸው አስተምሮ አያውቅም።       የአሞጽ ልጅ ነቢዩ ኢሳያስ ደግሞ የአምላክን አንድነት በተዋበ ቋንቋ በገለፀበት መጽሐፉ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል መናገሩን ፅፏል፡-       ‹‹ሁሉን የፈጠርሁ፥ ሰማያትን ለብቻዬ የዘረጋሁ ምድርንም ያጸናሁ እግዚአብሔር እኔ ነኝ፤ ከእኔ ጋር ማን ነበረ?›› (ኢሳ 44፡24)       እግዚአብሔር በዚህ ግልፅና በተብራራ ቃሉ ‹‹አንድ›› እና ‹‹ብቸኛ›› መሆኑን ተናግሯል። በምንም ምክንያት ‹‹3›› አካላት ‹‹ብቸኛ›› ሊሆኑ አይችሉም። ከቋንቋ ሰዋሰው ጋር ሊታረቅ የሚችል አስተሳሰብም አይደለም። እንዲሁም በሌላ አንቀፅላይ እግዚአብሔር ፍፁም አንድ መሆኑን ከመሰከረ በኋላ ከእሱ ሌላ አምላክ ካለ ይነሳ ሲል ይጋብዛል።       ‹‹እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። እኔ ፊተኛ ነኝ እኔም ኋለኛ ነኝ፤ ከእኔ ሌላም አምላክ የለም። እንደ እኔ ያለ ማን ነው? ይነሣና ይጥራ።››       (ኢሳ 44፡6-7)       ነቢዩ ኤርምያስም በተመሳሳይ እንዲህ ሲል የእግዚአብሔር ቃል ወደኔ መጣ በማለት ተናግሯል፡- ‹‹እነሆ፤ እኔ የሥጋ ለባሽ ሁሉ አምላክ እግዚአብሔር ነኝ።››       (ኤር 32፡27)       እግዚአብሔር የስጋ ለባሽ ሁሉ አምላክ ነኝ ብሏልና ስጋ ለባሽ የሆነው ኢየሱስም በዚህ ውስጥ እንደሚካተት ግልፅ ነው። አንዳንዶች ታዳ የኢየሱስ ስጋ የተገኘ እንጅ የተፈጠረ አይደለም ሲሉ ይከራከራሉ። ይሁን እንጅ ካለመኖር ወደ መኖር የመጣ ነውና ፍጡር ከመሆን አያግደውም። (ይህንን ጉዳይ ‹‹አምላክ ስጋ ለብሷልን?›› በሚለው ምዕራፍ ሰፋ አድርገን እናየዋለን።)       የአዲስ ኪዳን መጽሐፍትንም ስናይ አብን ብቻ ‹‹እግዚአብሔር›› በማለት ሲጠሩት እናያለን። እነጳውሎስ ኢየሱስን አምላካዊ ባህርይ ቢሰጡትም ‹‹አንድ እግዚአብሔር›› በማለት አብን፣ ወልድንና መንፈስ ቅዱስን በአንድ ላይ ጠርተው አያውቁም። ኢየሱስ በራሱ አንደበት እግዚአብሔር አንድ ስለመሆኑ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ከተናገራቸው ብንጀምር፡-       ‹‹እስራኤል ሆይ! ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው።››       (ማር 12፡29)       ‹‹ኢየሱስም፤ ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም አለው።››       (ማር 10፡18)       የሚሉት አንቀፆች ተጠቃሽ ናቸው። በሌሎች የአዲስ ኪዳን መጽሐፍት ውስጥ ከተጠቀሱት ለአብነት ካየን ደግሞ ቀጣዮቹን አንቀፆች እናገኛለን፡-       ‹‹መቼም ብዙ አማልክትና ብዙ ጌቶች አሉ፤ ነገር ግን በሰማይ ሆነ በምድርም ሆነ አማልክት የተባሉ ምንም ቢኖሩ፥ ለእኛስ ነገር ሁሉ ከእርሱ የሆነ እኛም ለእርሱ የሆንን አንድ አምላክ አብ አለን።››       (1ኛ ቆሮ 8፡5-6)       ‹‹ከሁሉ በላይ የሚሆን በሁሉም የሚሠራ በሁሉም የሚኖር አንድ አምላክ የሁሉም አባት አለ።››       (ኤፌ 4፡4-6)       ‹‹ብቻውን አምላክ ለሚሆን ለማይጠፋው ለማይታየውም ለዘመናት ንጉሥ ምስጋናና ክብር እስከ ዘላለም ድረስ ይሁን አሜን።››       (1ኛ ጢሞ 1፡17)       እናም እነዚህና ሌሎች ምዕራፎች ‹‹አንዱ እግዚአብሔር›› ማለት ሶስቱን ማለትም አብን፣ ወልድንና መንፈስ ቅዱስን በአንድነት አጠቃልሎ ሳይሆን ‹‹አብ›› ብቻውን መሆኑን ይገልፁልናል።       በጊዜው እነጳውሎስ ኢየሱስን መለኮታዊ ባሕርይ የሰጡት ቢሆንም ከብሉይ ኪዳን ዘመን ጀምሮ ‹‹አንዱ እግዚአብሔር›› እየተባለ ሲጠራ የነበረው አብ ውስጥ ኢየሱስንና መንፈስ ቅዱስን ደምረው በአንድነት ‹‹አንዱ እግዚአብሔር›› ወደሚል መደምደሚያ ላይ አልደረሱም ነበር። ጳውሎሳውያኑ የወጠኑትን የኢየሱስን አምላክነት አስተምህሮ አሳድገው ከጫፍ ያደረሱት እነአትናቴዎስ ናቸው። ይህም በመግቢያው ላይ እና ‹‹ኢየሱስ አምላክ ነውን?›› በሚለው ምዕራፍ የተብራራ በመሆኑ እዚህ መድገም አያስፈልገንም።       ከላይ ለጠቀስናቸው የእግዚአብሄርን አንድነት የሚገልፁትን አንቀፆች በተመለከተና በተለይም ባብዛኛው ከብሉይ ኪዳን ለሚነሱት ጥያቄዎች አሳማኝ ምላሽ ከማጣት ጋር በተያያዘ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አንዳንድ ሚሽነሪዎች እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ‹‹አንድ›› ነኝ ሲል መለኮታዊ አንድነቱን ለመግለፅ እንጅ በአካል ከአንድ በላይ (COMPOUND UNITY) መሆናቸውን አይሽረውም የሚል መከራከሪያ ይዘው ብቅ ብለዋል።       ለዚህም እንደ ማስረጃነት ‹‹ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፤ በሚስቱም ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።››       (ዘፍ 2፡24) የሚለውን ቃል በመጥቀስ ባልና ሚስት አንድ ስጋ ስለተባሉ በአካልም አንድ ናቸው ማለት አይደለም ይላሉ።       ‹‹አንድ›› ከሚለው የብሉይ ኪዳን ቃል ስንነሳ እግዚአብሔር በሁሉም ምዕራፎች ‹‹አንድ›› ነኝ ሲል የሚጠቀመው ቃል ‹‹ኢሐድ›› የሚለውን የእብራይስጠኛ ቃል ሲሆን ትርጉሙም በቁጥር ‹‹አንድ›› (NUMERAL ONE) ማለት ነው። በግዕዘኛው ደግሞ ‹‹አሐድ››። ኢሐድ፣ ሻናዪም፣ ሻሎሽ…1, 2, 3...ማለት ነው።       እዚህ ላይ እንደምናየው ‹‹ኢሐድ›› የቁጥሮች መጀመሪያ ነው። ይህም በቁጥር አንድ የሆነን አካል ለመግለፅ ተመራጭ ቃል ያደርገዋል። በእርግጥ ሚሽነሪዎቹ እንደሚሉት ‹‹አንድ›› በምንለው አካል ውስጥ ብዙ ክፍልፋዮች ሊኖሩ ይችላሉ።ነገር ግን ይህ ገለፃ ከሥላሴ ጋር አይስማማም። ምክንያቱም ሥላሴ ‹‹3›› ራሳቸውን የቻሉ አካላት እንጅ ክፍልፋይ አይደለምና። እንደ አትናቴዎስ ድንጋጌ አብ በራሱ እግዚአብሔር ነው፤ ወልድም በራሱ እግዚአብሔር ነው፤ መንፈስ ቅዱስም በራሱ እግዚአብሔር ነው። ሶስቱም ራሳቸውን የቻሉ ሕልው እግዚአብሔሮች ናቸው። የጥምረት አንድነት (COMPOUND UNITY) ስንል ግን እያንዳንዱ ክፍልፋይ በራሱ የቆመ አካል ስላልሆነ ከሥላሴ አስተምህሮት ጋር

      ነገሩን ስናሳርገው የፈጣሪ በአካል ሶስት የመሆን ጉዳይ ተፈጥሯዊነት የለውም። ህሊናችንም ከውስጣችን ጋር ሊያስታርቀው አይቻለውም። በቁጥር ሶስት የሆነ አምላክ አለ ብሎ ለመቀበል ማስረጃዎችን ብንፈትሽ፤ በነፃው ህሊናችን ምክንያታዊ ሁነቶችን ብንመረምር ከምናብ የዘለለ እውነታን አናገኝም። ይህም ቁርኣን እንዳለው የሰው ልጅ በአንድ አምላክ በማመን እምነት ላይ የተፈጠረ በመሆኑ ነው።       (1) St. Thomas Aquinas, “The Summa theological” pp.213 (2) St. Augustine, “On the Trinity” (Book VIII), disc 5 --------------------Ω---------------------------- https://t.me/muhammed6964 ወሠላሙ ዐለይኩም     

ክፍል 10 ሥላሴ በተፈጥሮ/ህሊና በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ፥ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡       ከአራተኛው መቶ ክ/ዘመን ጀምሮ የተለያዩ የእምነቱ ልሂቃን የሥላሴን ሶስትነት በአንድነት የሚለውን አመለካከት ሰዎች ይረዱታል በሚሉት መንገድና ምሳሌዎች ሁሉ ለማብራራት ሞክረዋል። ያም ሆኖ ዛሬም ከምዕተ ዓመታት በኋላ ሥላሴን በትክክል ተረድቼዋለሁ የሚል አማኝ ማግኘት ይከብዳል። ተረድተነዋል ብለው የሚያስቡ ሰዎችም ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች አጥጋቢ መልስ ሲሰጡ አይታይም።       ይልቁንም ሥላሴን ለመረዳት የመንፈስ ቅዱስ እገዛ ያስፈልጋል የሚለው ገኖ ይወጣል። በእርግጥም መረዳቱ የሚገኘው በመንፈስ ቅዱስ መገለጥ ከሆነ ደግሞ ለምን እነዚህ የተገለፀላቸው ሰዎች የተረዱትን ማካፈሉ ተሳናቸው? የሚል ጥያቄ እንድናነሳ ያደርገናል። እነሱ የተገለፀላቸውን ለሰዎች ማስረዳት ካልቻሉ ተረዳነው የሚሉትን ነገር ስሜት አልባ ያደርገዋል። ሰው የተረዳውን ነገር ለሌላ ማስረዳት ካልቻለ የተረዳው መሰለው እንጅ ራሱም አልገባውምና። ለነገሩ ስለ ሥላሴ በርካቶች ይፃፉ እንጅ አንዳቸውም በመንፈስ ቅዱስ መገለጥ ተረድቼዋለሁ ብለውም አያውቁም።       በሥላሴ ጉዳይ ላይ ህሊናችን ከማይቀበላቸው ነገሮች ዋነኛው ታዲያ አምላክ በአካሉ ሶስት ነው የመባሉ ጉዳይ ነው። ሁልጊዚም ቢሆን ነፃ ህሊናችን የሚነግረን በአካሉም በመለኮቱም ‹‹አንድ›› አምላክ እንዳለ ብቻ ነው። ሶስትነቱን ደጋግመው ቢነግሩንም እንኳን ከተፈጥሮ ውጭ ነውና አዕምሯችን ከሰሌዳው ሊፅፈው አይቻለውም። በዚህ ጉዳይ ምናልባት ወደፊት ሊገባን ይችላል ከሚል ተስፋ እንጅ እርግጠኛ ሆኖ የሚያምንበት አንድም ክርስቲያን ማግኘት ይቸግራል። በዚህ ተስፋ መጽሐፍ ቅዱስ በማንበብ ዓይናቸው የደከሙ አዛውንቶችን ብንጠይቅም ዛሬም ከህሊናቸው ጋር ሊስማማ እንዳልቻለ ነው የሚነግሩን። ይሄንን በእምነቱ ውስጥ ኖረንበትም ብዙዎቹን ጠይቀንም ያረጋገጥነው እውነታ ነው።       አንድ ቀድሞ የፕሮቴስታንት ፓስተር የነበረ ወንድማችን ሲናገር ‹‹ክርስቲያን በነበርኩበት ሰዓት አዕምሮዬ መልስ የሚያጣለት ጉዳይ አምላክ ሶስት አካል ነው የሚለውን ነው። አንድ ሰው በአንድ ጊዜ ሶስት አምላኮችን ሊጠራ አይችልምና›› ብሏል። እርግጥ ነው በአንድ ጊዜ ሶስት አካላትን መጥራት አንችልም። ብዙ ከሆኑ አሁን እየጠራት ያለሁት ማንኛውን ነው? የሚል ጥያቄ ወደ ህሊናችን መምጣቱ አይቀርም። ይህም አምላክ ሶስት አካል ነው መባሉ ከተፈጥሮ ጋር የማይስማማ በመሆኑ ነው። (በዚህ አጋጣሚ ለሥላሴ አማኞች አስተሳሰቡ ለተፈጥሮ የተገራ አይደለምና በዕድሜ መግፋት ወይም በማንበብ ብዛት አምላክ ሶስት አካል ነው የሚለውን ወደፊት ህሊናችን ሊቀበለው ይችላል በሚል ተስፋ ከዕድሜ ጋር ጨዋታ እንዳይያዝ ማስታወስ እፈልጋለሁ።)       ሌላው ህሊና የማይቀበለው ወልድና መንፈስ ቅዱስ ካስገኛቸው አብ ጋር በጊዜ አይቀዳደሙም መባሉ ነው። በሥላሴ አማኞች ወልድም እና መንፈስ ቅዱስ ቅድመ ዓለም ከእግዚአብሔር አብ እንደተገኙ ይታመናል። መወለድና መገኘት ደግሞ ጅማሮ አለው። ይህ ሆኖ ሳለ አስገኚው ከግኙጋር በጊዜ አይቀዳደምም የሚለው አስተሳሰብ ከእውነታ ጋር የሚይታረቅ አይደለም። የጊዜ መቀዳደም በሌለበት አንዱ አንዱን ሊያስገኘው አይችልም። እግዚአብሔር አብ የሁለቱ እግዚአብሔሮች አስገኚ ከሆነ በመገኘት ከእነሱ መቅደሙ ግልፅ ነው። ምክንያቱም የእሱ መኖር ሁለቱን አስገኝቷልና። ነገር ግን አስገኝና ግኚ ሁለት ፍፁም የተለያየ ማንነት እንዳላቸው እየታመነ በጊዜ አይቀዳደሙም የሚለው አስተሳሰብ ፍፁም ተፈጥሯዊ አይደለም። ከአዕምሯችን በላይ ነው እንዳንል ከአዕምሮ በላይ ማለት አዕምሮ የሚቀበለው ሆኖ የነገሩን ጥግ ያልደረሰበት ማለት ነው። ይህኛው ግን አዕምሮ የማይቀበለውና ሊሆን የማይችል እሳቤ ነው።       የታሪክ መዛግብት እንደሚነግሩን ታዲያ ከህሊና ጋር የተኳረፈውን የሥላሴን ትምህርት ለማስታረቅ በ12ኛው ክ/ዘ ሥላሴ ምክንያታዊ (ሎጅካል) በሆነ መንገድ ሊገለፅ ይገባል የሚል ‹‹ስኮላስትሲዝም›› ተሰኘ እሳቤ ተነስቶ እንደነበረ ይነገራል።የአስተምህሮቱ አቀንቃኝ ቶማስ አክዋናስ ‹‹ሥላሴ በአካል ሶስት ነው ተብሎ የሚገለፅ አይደለም፤ በመለኮት ግን የሶስትነት ባህርይ አለው›› ሲል ተናግሯል። ነገርግን በአካል ሶስት ሆነው ካልተከፋፈሉና በመለኮት ግን የሶስትነት ባህርይ ካላቸው ለምን ሶስት ናቸው ይባላሉ? ለሚለው ጥያቄ መልስ ሊያገኝለት አልቻለም።(1)       ከዚህ ለየት ያለው ደግሞ ኦጋስተን ነው። ይህ ሰው በጥናቱ እንደደረሰበት ሥላሴን ማመን እንጅ መግለፅ አይቻልም ሲል ፅፏል። የሥላሴ መለኮታዊነት በሰው ልጅ አዕምሮ የማይደረስበት ስለሆነ በሞኝነት ማመን ይገባናል ብሏልም። ይህ የኦጋስተን ሃሳብ በአሁኑ ሰዓት በክርስትናው ዓለም በስፋት የሚታመንበት ሲሆን ጳውሎስ በ1ኛ ቆሮንቶስ 1፡1 ላይ፡-       ‹‹ዓለም እግዚአብሔርን በጥበብዋ ስላላወቀች፥ በስብከት ሞኝነት የሚያምኑትን ሊያድን የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ሆኖአል››       በማለት የተናገረው ክርስትና ማለት ሞኝነት ነው ለሚለው እሳቤ በማጣቀሻነት ያነሱታልም።ይሁን እንጅ ራሱ ጳውሎስ 1ኛ ተሰሎንቄ 5፡20 ላይ፡- ‹‹ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ›› ብሎ እንደተናገረው የሰው ልጅ አዕምሮ ያልተመለሰለትን ጥያቄ ከማሰላሰል አይቦዝንምና ዛሬም የሥላሴ ትምህርት በእያንዳንዱ አማኝ ህሊና ውስጥ ይብዛም ይነስም የዘወትር ጥያቄ ሆኖ ተቀምጧል።(2)       ቁርኣን ስለዚሁ ጉዳይ ሲናገር አምላክ በብዛቱ ፍፁም ‹‹አንድ›› መሆኑ ከህሊና ጋር የተስማማና ተፈጥሯዊ ነው ይላል።       ‹‹የአላህን ፍጥረት ያችን አላህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን (ኃይማኖት ያዟት)። የአላህን ፍጥረት መለወጥ የለም። ይህ ቀጥተኛ ኃይማኖት ነው። ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች አያውቁም።››       (ሩም 30)       ነቢዩ ሙሐመድም (ዐሰወ) በአንድ ወቅት ከባልደረባቸው አንዱ ‹‹አንድ ነገር ትክክል ይሁን ስህተት በምን ማወቅ እችላለሁ?›› ብሎ በጠየቃቸው ጊዜ ‹‹ህሊናህን ጠይቀው›› ሲሉ መልሰውለታል። በተመሳሳይ ከህሊናችን ጋር የታረቀ ትክክል መሆኑን ከህሊናችን የተጣላ ደግሞ ስህተት መሆኑን የሚገልፁ በርካታሐዲሶችንም እናገኛለን።       እኛም የምንጠይቀው የሥላሴ አስተምህሮት ከተፈጥሮና ከህሊና ጋር ካልተስማማ በምን መንገድ ትክክል መሆኑን ማረጋገጥ እንችላለን? ነው። አንድን ነገር በትክክል ተረድተነው መግለፅ ካልቻልን እናውቀዋለን ማለት አንችልም። በትክክል ካላወቅነው ደግሞ እንዴት ሳንጠራጠር ልናምንበት ይቻለናል?       አንዳንድ ጊዜ ታዲያ ከክርስቲያን አማኞች ጋር ስለ አምላክ ሶስትነት ስወያይ ‹‹ማነው ፈጣሪ ሶስት ነው ያለህ? ሶስት ነው የሚል ተፅፎ አግኝተሃል?›› ይሉኛል። እርግጥ ነው አምላክ በአካሉ ሶስት ነው የሚል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አልተፃፈም። ይሄ ወደ ህሊናችን ስንቀርብ የምንረዳው እውነታ ነው። እኛም እያልን ያለነውከዚሁ እውነታ አትውጡ ነው። ካልሆነ ያልተመለሰና ሊመለስም የማይችል ጥያቄ አዕምሯቸው ውስጥ ተሰንቅሮ መቅረቱ አይቀርም። ይህ ደግሞ ትርፉ ጥርጣሬና ዝምታ ነው። የሥላሴ አባት የሚባለው አትናቴዎስ እንኳን አስተምህሮቱ ከተፈጥሮው ጋር ሲቃረንበት አንድ እንጅ ሶስት አምላክ የለም ሲል ፅፏል።

Repost from N/a
      ነገሩን ስናሳርገው የፈጣሪ በአካል ሶስት የመሆን ጉዳይ ተፈጥሯዊነት የለውም። ህሊናችንም ከውስጣችን ጋር ሊያስታርቀው አይቻለውም። በቁጥር ሶስት የሆነ አምላክ አለ ብሎ ለመቀበል ማስረጃዎችን ብንፈትሽ፤ በነፃው ህሊናችን ምክንያታዊ ሁነቶችን ብንመረምር ከምናብ የዘለለ እውነታን አናገኝም። ይህም ቁርኣን እንዳለው የሰው ልጅ በአንድ አምላክ በማመን እምነት ላይ የተፈጠረ በመሆኑ ነው።       (1) St. Thomas Aquinas, “The Summa theological” pp.213 (2) St. Augustine, “On the Trinity” (Book VIII), disc 5 ------------------------------Ω-------------------------------------- https://t.me/muhammed6964 ወሠላሙ ዐለይኩም     

Repost from N/a
ክፍል 10 ሥላሴ በተፈጥሮ/ህሊና በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ፥ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡       ከአራተኛው መቶ ክ/ዘመን ጀምሮ የተለያዩ የእምነቱ ልሂቃን የሥላሴን ሶስትነት በአንድነት የሚለውን አመለካከት ሰዎች ይረዱታል በሚሉት መንገድና ምሳሌዎች ሁሉ ለማብራራት ሞክረዋል። ያም ሆኖ ዛሬም ከምዕተ ዓመታት በኋላ ሥላሴን በትክክል ተረድቼዋለሁ የሚል አማኝ ማግኘት ይከብዳል። ተረድተነዋል ብለው የሚያስቡ ሰዎችም ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች አጥጋቢ መልስ ሲሰጡ አይታይም።       ይልቁንም ሥላሴን ለመረዳት የመንፈስ ቅዱስ እገዛ ያስፈልጋል የሚለው ገኖ ይወጣል። በእርግጥም መረዳቱ የሚገኘው በመንፈስ ቅዱስ መገለጥ ከሆነ ደግሞ ለምን እነዚህ የተገለፀላቸው ሰዎች የተረዱትን ማካፈሉ ተሳናቸው? የሚል ጥያቄ እንድናነሳ ያደርገናል። እነሱ የተገለፀላቸውን ለሰዎች ማስረዳት ካልቻሉ ተረዳነው የሚሉትን ነገር ስሜት አልባ ያደርገዋል። ሰው የተረዳውን ነገር ለሌላ ማስረዳት ካልቻለ የተረዳው መሰለው እንጅ ራሱም አልገባውምና። ለነገሩ ስለ ሥላሴ በርካቶች ይፃፉ እንጅ አንዳቸውም በመንፈስ ቅዱስ መገለጥ ተረድቼዋለሁ ብለውም አያውቁም።       በሥላሴ ጉዳይ ላይ ህሊናችን ከማይቀበላቸው ነገሮች ዋነኛው ታዲያ አምላክ በአካሉ ሶስት ነው የመባሉ ጉዳይ ነው። ሁልጊዚም ቢሆን ነፃ ህሊናችን የሚነግረን በአካሉም በመለኮቱም ‹‹አንድ›› አምላክ እንዳለ ብቻ ነው። ሶስትነቱን ደጋግመው ቢነግሩንም እንኳን ከተፈጥሮ ውጭ ነውና አዕምሯችን ከሰሌዳው ሊፅፈው አይቻለውም። በዚህ ጉዳይ ምናልባት ወደፊት ሊገባን ይችላል ከሚል ተስፋ እንጅ እርግጠኛ ሆኖ የሚያምንበት አንድም ክርስቲያን ማግኘት ይቸግራል። በዚህ ተስፋ መጽሐፍ ቅዱስ በማንበብ ዓይናቸው የደከሙ አዛውንቶችን ብንጠይቅም ዛሬም ከህሊናቸው ጋር ሊስማማ እንዳልቻለ ነው የሚነግሩን። ይሄንን በእምነቱ ውስጥ ኖረንበትም ብዙዎቹን ጠይቀንም ያረጋገጥነው እውነታ ነው።       አንድ ቀድሞ የፕሮቴስታንት ፓስተር የነበረ ወንድማችን ሲናገር ‹‹ክርስቲያን በነበርኩበት ሰዓት አዕምሮዬ መልስ የሚያጣለት ጉዳይ አምላክ ሶስት አካል ነው የሚለውን ነው። አንድ ሰው በአንድ ጊዜ ሶስት አምላኮችን ሊጠራ አይችልምና›› ብሏል። እርግጥ ነው በአንድ ጊዜ ሶስት አካላትን መጥራት አንችልም። ብዙ ከሆኑ አሁን እየጠራት ያለሁት ማንኛውን ነው? የሚል ጥያቄ ወደ ህሊናችን መምጣቱ አይቀርም። ይህም አምላክ ሶስት አካል ነው መባሉ ከተፈጥሮ ጋር የማይስማማ በመሆኑ ነው። (በዚህ አጋጣሚ ለሥላሴ አማኞች አስተሳሰቡ ለተፈጥሮ የተገራ አይደለምና በዕድሜ መግፋት ወይም በማንበብ ብዛት አምላክ ሶስት አካል ነው የሚለውን ወደፊት ህሊናችን ሊቀበለው ይችላል በሚል ተስፋ ከዕድሜ ጋር ጨዋታ እንዳይያዝ ማስታወስ እፈልጋለሁ።)       ሌላው ህሊና የማይቀበለው ወልድና መንፈስ ቅዱስ ካስገኛቸው አብ ጋር በጊዜ አይቀዳደሙም መባሉ ነው። በሥላሴ አማኞች ወልድም እና መንፈስ ቅዱስ ቅድመ ዓለም ከእግዚአብሔር አብ እንደተገኙ ይታመናል። መወለድና መገኘት ደግሞ ጅማሮ አለው። ይህ ሆኖ ሳለ አስገኚው ከግኙጋር በጊዜ አይቀዳደምም የሚለው አስተሳሰብ ከእውነታ ጋር የሚይታረቅ አይደለም። የጊዜ መቀዳደም በሌለበት አንዱ አንዱን ሊያስገኘው አይችልም። እግዚአብሔር አብ የሁለቱ እግዚአብሔሮች አስገኚ ከሆነ በመገኘት ከእነሱ መቅደሙ ግልፅ ነው። ምክንያቱም የእሱ መኖር ሁለቱን አስገኝቷልና። ነገር ግን አስገኝና ግኚ ሁለት ፍፁም የተለያየ ማንነት እንዳላቸው እየታመነ በጊዜ አይቀዳደሙም የሚለው አስተሳሰብ ፍፁም ተፈጥሯዊ አይደለም። ከአዕምሯችን በላይ ነው እንዳንል ከአዕምሮ በላይ ማለት አዕምሮ የሚቀበለው ሆኖ የነገሩን ጥግ ያልደረሰበት ማለት ነው። ይህኛው ግን አዕምሮ የማይቀበለውና ሊሆን የማይችል እሳቤ ነው።       የታሪክ መዛግብት እንደሚነግሩን ታዲያ ከህሊና ጋር የተኳረፈውን የሥላሴን ትምህርት ለማስታረቅ በ12ኛው ክ/ዘ ሥላሴ ምክንያታዊ (ሎጅካል) በሆነ መንገድ ሊገለፅ ይገባል የሚል ‹‹ስኮላስትሲዝም›› ተሰኘ እሳቤ ተነስቶ እንደነበረ ይነገራል።የአስተምህሮቱ አቀንቃኝ ቶማስ አክዋናስ ‹‹ሥላሴ በአካል ሶስት ነው ተብሎ የሚገለፅ አይደለም፤ በመለኮት ግን የሶስትነት ባህርይ አለው›› ሲል ተናግሯል። ነገርግን በአካል ሶስት ሆነው ካልተከፋፈሉና በመለኮት ግን የሶስትነት ባህርይ ካላቸው ለምን ሶስት ናቸው ይባላሉ? ለሚለው ጥያቄ መልስ ሊያገኝለት አልቻለም።(1)       ከዚህ ለየት ያለው ደግሞ ኦጋስተን ነው። ይህ ሰው በጥናቱ እንደደረሰበት ሥላሴን ማመን እንጅ መግለፅ አይቻልም ሲል ፅፏል። የሥላሴ መለኮታዊነት በሰው ልጅ አዕምሮ የማይደረስበት ስለሆነ በሞኝነት ማመን ይገባናል ብሏልም። ይህ የኦጋስተን ሃሳብ በአሁኑ ሰዓት በክርስትናው ዓለም በስፋት የሚታመንበት ሲሆን ጳውሎስ በ1ኛ ቆሮንቶስ 1፡1 ላይ፡-       ‹‹ዓለም እግዚአብሔርን በጥበብዋ ስላላወቀች፥ በስብከት ሞኝነት የሚያምኑትን ሊያድን የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ሆኖአል››       በማለት የተናገረው ክርስትና ማለት ሞኝነት ነው ለሚለው እሳቤ በማጣቀሻነት ያነሱታልም።ይሁን እንጅ ራሱ ጳውሎስ 1ኛ ተሰሎንቄ 5፡20 ላይ፡- ‹‹ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ›› ብሎ እንደተናገረው የሰው ልጅ አዕምሮ ያልተመለሰለትን ጥያቄ ከማሰላሰል አይቦዝንምና ዛሬም የሥላሴ ትምህርት በእያንዳንዱ አማኝ ህሊና ውስጥ ይብዛም ይነስም የዘወትር ጥያቄ ሆኖ ተቀምጧል።(2)       ቁርኣን ስለዚሁ ጉዳይ ሲናገር አምላክ በብዛቱ ፍፁም ‹‹አንድ›› መሆኑ ከህሊና ጋር የተስማማና ተፈጥሯዊ ነው ይላል።       ‹‹የአላህን ፍጥረት ያችን አላህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን (ኃይማኖት ያዟት)። የአላህን ፍጥረት መለወጥ የለም። ይህ ቀጥተኛ ኃይማኖት ነው። ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች አያውቁም።››       (ሩም 30)       ነቢዩ ሙሐመድም (ዐሰወ) በአንድ ወቅት ከባልደረባቸው አንዱ ‹‹አንድ ነገር ትክክል ይሁን ስህተት በምን ማወቅ እችላለሁ?›› ብሎ በጠየቃቸው ጊዜ ‹‹ህሊናህን ጠይቀው›› ሲሉ መልሰውለታል። በተመሳሳይ ከህሊናችን ጋር የታረቀ ትክክል መሆኑን ከህሊናችን የተጣላ ደግሞ ስህተት መሆኑን የሚገልፁ በርካታሐዲሶችንም እናገኛለን።       እኛም የምንጠይቀው የሥላሴ አስተምህሮት ከተፈጥሮና ከህሊና ጋር ካልተስማማ በምን መንገድ ትክክል መሆኑን ማረጋገጥ እንችላለን? ነው። አንድን ነገር በትክክል ተረድተነው መግለፅ ካልቻልን እናውቀዋለን ማለት አንችልም። በትክክል ካላወቅነው ደግሞ እንዴት ሳንጠራጠር ልናምንበት ይቻለናል?       አንዳንድ ጊዜ ታዲያ ከክርስቲያን አማኞች ጋር ስለ አምላክ ሶስትነት ስወያይ ‹‹ማነው ፈጣሪ ሶስት ነው ያለህ? ሶስት ነው የሚል ተፅፎ አግኝተሃል?›› ይሉኛል። እርግጥ ነው አምላክ በአካሉ ሶስት ነው የሚል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አልተፃፈም። ይሄ ወደ ህሊናችን ስንቀርብ የምንረዳው እውነታ ነው። እኛም እያልን ያለነውከዚሁ እውነታ አትውጡ ነው። ካልሆነ ያልተመለሰና ሊመለስም የማይችል ጥያቄ አዕምሯቸው ውስጥ ተሰንቅሮ መቅረቱ አይቀርም። ይህ ደግሞ ትርፉ ጥርጣሬና ዝምታ ነው። የሥላሴ አባት የሚባለው አትናቴዎስ እንኳን አስተምህሮቱ ከተፈጥሮው ጋር ሲቃረንበት አንድ እንጅ ሶስት አምላክ የለም ሲል ፅፏል።

ክፍል 9 ‹‹አንድነት›› ወይስ ‹‹አንድ››? በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ፥ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡       በቅድሚያ በሁለቱ ቃላት መካከል ያለውን ልዩነት እንይ። ‹‹አንድነት›› ማለት ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ አካላት የሚፈጥሩት የጋራ የሆነ ማንነት ወይም ህልውና ልንለው እንችላለን። ‹‹አንድ›› ማለት ደግሞ በቁጥር አንድ የሆነን ማንኛውም ነገር ይገለፃል።       የሥላሴ አስተምህሮት ምሁራን እንደሚሉት ሥላሴዎች በአካልና በግብር (ስራ) ሶስት ሲሆኑ አንድ የሚያደርጋቸው መለኮት ወይም ስልጣን ነው። ይህ ማለት መለኮት ‹‹አንድነት›› ፈጠረ እንጅ በቁጥር ‹‹አንድ›› የሆነ አምላክ አይደለም ማለት ነው። ይሄንን ስል ነጣጥዬ እያዬኋቸው አይደለም። ምክንያቱም የማይነጣጠሉት በመለኮት እና በስልጣን እንጅ ሶስቱም የየራሳቸው አካል እስካላቸው ድረስ በቁጥር ሶስት ከመሆን አይወገዱምና።       በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ምንም ማስረጃ አለመኖሩን ወደጎን ትተነው ሥላሴዎች በመለኮት አንድ መሆናቸውን ብንቀበልም እንኳን አንድነታቸውን የስልጣን እንጅ የቁጥር እስካልሆነ ድረስ ሶስት እንጅ አንድ ሊሆኑ አይችሉም። በአካል ሶስት መሆናቸው በራሱ ‹‹አንድ›› ሊያስብላቸው አይቻለም። በየትኛውም የሂሳብ ቀመር ብናሰላው ሶስት ሶስት እንጅ አንድ ሊሆን አይቻለውም። በዚህም የተነሳ ማንኛውንም በሥላሴ የሚያምን ሰው ‹‹አንድ አምላክ አለኝ›› ሊል አይችልም፤ ነገር ግን ‹‹የአንድነት አምላክ አለኝ›› ሊል ይችላል። በሰማይ ስንት ዙፋን አለ?       ማንኛውንም የወንጌል ሰባኪ በሰማይ ስንት ዙፋን አለ? ብላችሁ ብትጠየቁት አንድ ሲል ያለ ጥርጥር ይመልስላችኋል። መጽሐፍ ቅዱስም በሰማይ ባለው ዙፋን ላይ አንድ የተቀመጠበት አካል እንዳለ እንዲህ ይገልፃል፡-       ‹‹እነሆም፥ ዙፋን በሰማይ ቆሞአል በዙፋኑም ላይ ተቀማጭ ነበረ።››       (ራዕ 4፡2)       ታዲያ ይህ በዙፋኑ ላይ የተቀመጠው አካል ማነው? ሥላሴዎች ናቸውን? ሥላሴ ከሆነ እንዴት አንድ አካል ተባለ? ለእነዚህ መጠይቆች የእምነቱ መምህራን የሚሰጡን ምላሽ በዙፋኑ ላይ ተቀምጦ የሚታየው ኢየሱስ ሲሆን የማይታየውን አምላክ ወክሎ ነው የሚል ነው። ለዚህም እንደ ማጣቀሻ የሚያቀርቡት ቀጣዩን የጳውሎስ መልዕክት ነው።        ‹‹እርሱም የማይታይ አምላክ ምሳሌ ነው።››       (ቆላ 1፡15-16)       ከዚህ አንቀፅ ገለፃ በመነሳትም እግዚአብሔር ቃሉን ስጋ አድርጎ በልጁ መልኩን ገለጠ ይላሉ። ይሁን እንጅ ይህ ምላሽ ቀጥለን በምናነሳቸው መጠይቆች ትክክል አለመሆኑን ማረጋገጥ እንችላለን።       አንደኛ ወልድ ለሰዎች የተገለጠው የእግዚአብሔር ዙፋን ወክሎ ነው ቢባልም አብና መንፈስ ቅዱስ ግን ለሰዎች ያልታየ የራሳቸው የሆነ ዙፋን ሊኖራቸው የግድ ነው። ምክንያቱም የየራሳቸው የሆነ አካል እንዳላቸው ተነግሯልና። ምሳሌ አንድ ሰው ሶስት ሰዎችን ወክሎ አንድ ዙፋን ላይ ቢቀመጥ ለሶስቱ ሰዎች አንድ ዙፋን ነው ያለው ሊባል አይቻልም። ከዚህ አንፃር ወልድ የውክልና ስራ በመስራቱ ብቻ አንድ ዙፋን እንዳለ አድርጎ ማቅረቡ የተሳሳተ ግንዘቤ ነው። ምናልባት ሶስቱም አካላት በሶስት ዙፋን ወይም በአንድ ዙፋን ሶስቱም አካላት ይኖራሉ ካልተባለ በቀር።       ሁለተኛ ኢየሱስ ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ ‹‹በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአል።››       የሚለው የዕብራውያን 12፡1-2 መልዕክት የኢየሱስንና የእግዚአብሔርን ዙፋን የተለያዩ መሆናቸውን ይገለፃል። ከጅምሩም ኢየሱስ እግዚአብሔር ቢሆን ኖሮ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ ባልተባለ ነበር። ይህ ደግሞ በእግዚአብሔርና በኢየሱስ መካከል የማንነትና የዙፋን ልዩነት እንዳለ አስረጅ ነው።       በመጨረሻም ጥንት በብሉይ ዘመን ኢሳያስ እንዲህ ሲል ፅፏል፡-       ‹‹እግዚአብሔርን በረጅምና ከፍ ባለ ዙፋን ላይ ተቀምጦ አየሁት፤ የልብሱም ዘርፍ መቅደሱን ሞልቶት ነበር።››       (ኢሳ 6፡1)       በዚህና በሌሎችም የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ውስጥ እግዚአብሔር በዙፋኑ ሆኖ ለሰዎች መገለፁ ተነግሯል። ይህም ለኢየሱስ ብቻ የሚሰጠውን የማይታይ አምላክ ውክልና ጥያቄ ላይ ይጥለዋል።       አንዳንዶች ታዲያ እግዚአብሔር ጥንት ቅድመ ዓለም ኢየሱስን በቃሉ ወልዶታልና በብሉይ ዘመን ለሰዎች ሲገለፅ የነበረው ራሱ ኢየሱስ ነው ይላሉ። ይሁን እንጅ በብሉይ ኪዳን ራሱን ለሰዎች የገለፀው አይሁዳውያኑ አባታችን የሚሉት ‹‹እግዚአብሔር›› እንጅ‹‹ወልድ›› ስለመሆኑ የገለፀበት አንድም አንቀፅ የለም። ኢየሱስም በምድር ላይ በኖረበት ዘመን ጥንት ለሰዎች ይገለፅላቸው የነበረው አምላክ ስለመሆኑ መስክሮ አያውቅም። ይህም እሳቤው መረጃን ያገናዘበ እንዳልሆነ ይገልፅልናል።       በተጨማሪም በብሉይ የተገለፀው ‹‹እግዚአብሔር›› ኢየሱስ ነው ከተባለ በስጋ ከመወለዱ በፊት መለኮታዊ አካል ያልነበረው ሰው ነውን? ወይስ በተለዋዋጭ ለራሱ በመለኮቱ ለሰዎች በሰውነቱ ይገለፅ ነበርን? የሚሉ መሰል ጥያቄዎችን እንድናነሳ ያደርገናል። በዚህ አመለካከት ከሄድንና ኢየሱስ በስጋ ከመወለዱ በፊት ቅድመ ዓለም በአካሉም ሰው ከነበረ ደግሞ መለኮታዊቱ ትርጉም የማይሰጥ ይሆናል።       እናም እነዚህና ሌሎችም ጉዳዩን ተከትለው የሚመጡ ውስብስብ ጥያቄዎች ትክክለኛውን መልስ እስካላገኙ ድረስ በሰማይ ያለውን አንድ ዙፋን ለሶስት አካላት ለመስጠት አንችልም። ------------Ω------------ https://t.me/muhammed6964 ወሠላሙ ዐለይኩም

   "የዐረፋ ገበያ ነው" በሚል በሙስሊሞች ሱቆች ላይ የጉራጊኛ እና የስልጥኛ ዘፈን መክፈት ሳይሆን: "የሙስሊሞች ዐረፋ ነው" በሚል ሙስሊሞች ለመሳብ: ሙስሊም ባልሆኑ ሰዎች ሱቆች ላይ ተክቢራ እንዲከፈት ነው ተፅእኖ መፍጠር ያለብን። ወላሂ ነው ምላቹ………   ለዲናችን ቦታ ቢኖረን ይህንን ማድረግ እንችል ነበር !! ከሌላ ሰው የተወሰደ

ወንጀል ፈጽሟልና ወደ አላህ በተውበት ሊመለስ ይገባዋል፤ ኡድሂያው ግን አይበላሽም። የመልካም ስራ በሮች ብዙ ናቸውና የቻልነዉን ሁሉ በመፈጸም ወደ አላህ መቃረብ ይገባል፤ የታሰረን ወይም የታመመን ሰው መጠየቅ፣ ዝምድናን መቀጠል፣ ሰደቃ ማብዛት፣ ሱና ሰላቶችን ማብዛት፣ ቁርዓን መቅራት፣ ዚክር ማብዛት፣ ዱዓን ማብዛት…ወዘተ ያስፈልጋል። አላህ በነዚህ ወርቃማ ጊዜያት ከሚጠቀሙና አላህ ዘንድ መልካም ምንዳን ከሚያገኙ ጠንካራና ብልህ የአላህ ባሮች ያድርገን።            ዝግጅ- አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ -------------------------------- https://t.me/muhammed6964 ወሠላሙ ዐለይኩም

ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት ምስጋና ለአላህ የተገባ ነው፡፡ የአላህ ሰላምና እዝነት በታላቁ ነብይ በሙሀመድ በባልደረቦቻቸው እና በቤተሰቦቻቻው ሁሉ ላይ ይሁን፡፡ ከተከበሩት ወራት መካከል አንዱ የሀጅ ወር ዙልሂጃ ነው። ከቀናት ሁሉ አላህ ዘንድ የተወደዱት ደግሞ አስሩ የዙልሂጃ ቀናት ናቸው። እንደዉም ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያለቸው እነኝህ ቀናት ናቸው። የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ عن جَابِرِ بْنِ عَبْدِ االلهِ رَضِيَ االله عَنْهُ قَالَ: قَالَ رَسُولَ االلهِ صَلَّى االله عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: "أَفْضَلُ أَيَّامِ الْدُّنْيَا أَيَّامُ الْعَشْرِ، يَعْنِي عَشْرُ ذِي الحْجَّةِ". أخرجه البزار كما فى كشف الأستار (٢/٢٨ ، رقم ١١٢٨ (قال الهيثمي (٤/١٧ : (رجاله ثقات ، وصححه الألباني (صحيح الجامع ، رقم ١١٣٣.( ጃቢር ኢብኑ ዓብዲላህ ባስተላለፉት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል «ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው፤ አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት ናቸው » አልበዛር እና አልሐይሰሚይ ዘግበዉታል አልባኒም ሰሂህ ብለዉታል (ሰሂሁል ጃሚዕ 1133) عن ابن عباس رضي االله عنهما، عن النبي صلى االله عليه وسلم قال: "ما من أيام العمل الصالح فيهن أحب إلى االله منه في هذه الأيام العشر. قالوا ولا الجهاد في سبيل االله !! قال : ولا الجهاد في سبيل االله، إلا رجل خرج بنفسه وماله ولم يرجع من ذلك بشيء" أخرجه البخاري ከኢብኑ ዓባስ በተዘገበ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «በነዚህ አስር ቀናቶች ውስጥ ከሚፈጸም መልካም ስራዎች በበለጠ መልካም ስራዎች አላህ ዘንድ የተወደዱ የሚሆኑባቸው ቀናት የሉም፤ “በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሀድም ጭምር?” ተባሉ። እርሳቸውም፤ “ራሱንና ንብረቱን ይዞ ወጥቶ ምንም ያልተመለሰለት ሰው ሲቀር ጂሀድም ከዚህ አይበልጥም” አሉ።» ቡኻሪ ዘግበውታል በነዚህ ቀናቶች ትኩረት ልንሰጣቸው ከሚገቡ የዒባዳ አይነቶች መካከል፧ 1. ጾም፤ ጾም ከስራዎች ሁሉ በላጭ ነውና በእነዚህ ቀናት መጾም እጅግ የተወደደ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ዘጠኙን የዙልሂጃ ቀናት ይጾሙ እንደነበር ተዘግቧል። (አስረኛው ቀን ግን ዒድ ስለሆነ አይጾምም) 2. ዚክሮችን ማብዛት፤ አላህን ማመስገን (አልሀምዱሊላህ) ፣ ተክቢር፣ ተስቢህ(ሱብሀነላህ) እና ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢለላህ)፤ ኢባዳዉን ለማስታወስና የአላህን ስም ከፍ ለማድረግ በተለያዩ አጋጣሚዎች ድምጽን ከፍ አድርጎ እነዚህን ዚክሮች ማድረግ ይወደዳል። عن عبد االله بن عمر رضي االله عنهما عن النبي صلى االله عليه وسلم قال : "ما من أيام أعظم عند االله ولا أحب إليه العمل فيهن من هذه الأيام العشر فأكثروا فيهن من التهليل والتكبير والتحميد" أخرجه احمد 224/7وصحّح إسناده أحمد شاكر ዓብዱላህ ኢብኑ ዑመር ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩه እንዲህ ብለዋል፤ «ከእነዚህ አስር ቀናት በበለጠ አላህ ዘንድ ታላቅ የሆኑና መልካም ስራ እጅግ የተወደደባቸው ቀናት የሉም፤ ስለዚህ ተህሊል ተክቢር እና ተህሚድ አብዙ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል አህመድ ሻኪርም ሰሂህነቱን አረጋግጠዋል። ከተክቢር አደራረግ መካከል፤ االله أكبر ، االله أكبر لا إله إلا االله ، واالله أكبر والله الحمد “አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ ላ ኢላሀ ኢለላህ ወላሁ አክበር ወሊላሂልሀምድ” የሚለው ዋነኛው ሲሆን ሌሎችም ይዘቶች አሉት። በእነዚህ ቀናት ውስጥ ሊደረግ የሚገባው ይህ ተክቢር ብዙ ሰዎች ስለማይፈጽሙት እየተረሱ ካሉ ሱናዎች ማካከል ነው። ሰዎችን ለማስታወስ እና ሱናን ህያው ለማድረግ ድምጽን ከፍ አድርጎ ተክቢር ማድረግ ያስፈሊጋል። ዓብዱላህ ኢብኑ ኡመር እና አቡሁረይራህ በነዚህ አስር ቀናት ገበያ ወጥተው ተክቢራ ሲያደርጉ ሰዎችም እያስታወሱ ተክቢራ ያደርጉ እንደነበር ተዘግቧል። ይህም፤ ሁሉም ሰው የራሱን ዚክር ያደርጋል ማለት ነው እንጂ ሰዎች እየተሰባሰቡ በአንድ ድምጽ ተክቢራ ያድርጉ ማለት አይደለም። ይህ መረጃ ያልተገኘለት ውድቅ ስራ ነው። 3. ሐጅና ዑምራ፤ በነዚህ ቀናት ውስጥ ከሚፈጸሙ መልካም ስራዎች መካከል ሐጅ ማድረግ ይገኝበታል፤ በነዚህ አስር ቀናት የሐጅ ዒባዳ ላይ ተገኝቶ በተገቢው መልኩ ከፈጸመው በአላህ ፍቃድ ከተከታዩ የአላህ መልዕክተኛه ብስራት ድርሻ ይኖረዋል፤ عن أبي هريرة رضي االله عنه قال: سمعت ه يقول: "الحج المبرور ليس له جزاء إلا الجنة" متفق عليه. ከአቡ ሁረይራ በተላለፈ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛه እንዲህ ብለዋል፤ «ከወንጀል የራቀና ተቀባይነት ያለው ሐጅ (አል-ሐጅ አል-መብሩር) ምንዳው ጀነት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡» ቡኻሪና ሙስሊም ተስማምተውበታል 4. ኡድሂያ- በነዚህ አስር ቀናት ከተወደዱ ተግባሮች መካከል ኡድሂያን በማረድ ወደአላህ መቃረብ ነው። የሚከተሉት ነጥቦች አጠር ያለ ግንዘቤን የሰጣሉ፤ - ኡድሂያ በጣም ከጠነከሩ የነብዩه ሱናዎች መካከል ነው።የነብዩ ኢብራሂምን ሱና ህያው ከማድረጉ በተጨማሪ ለድሆች እና ችግረኞች መድረስ ነው። - ኡድሂያን በተመለከተ አላህ ከኛ የሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍራቻ (ተቅዋ) ነው። - ኡድሂያ የሚታረደው ከዒድ ሰላት በኋላ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ከኢድ ሰላት በፊት ያረደ ሰው እንዲደግም አዘዋል። - ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት የዒድ ሰላት ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ የሶስተኛው ቀን ጸሀይ እስክትጠልቅ ድረስ ኡድሂያን ማረድ ይቻላል። - ወንድም ይሁን ሴት ግመል፣ የቀንድ ከብቶች፣ በግና ፍየል ለኡድሂያ ይታረዱሉ። - የአላህ መልዕክተኛه እንከን ያለባቸውን እንስሳት እንዳናርድ ከልክለዋል። አንድ አይኑ የታወረ፣ ስብራት ያለበት፣ የከሳና የደከመ፣ የታመመ እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም። - ኡድሂያን ለብቻ ማረድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን ወይፈን ወይም በሬ መጋርትም ይቻላል። - አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለራሱ እና በህይወት ላሉም ይሁን በህይወት ለሌሉ ለቤተሰቦቹ አስቦ ሊያርድ ይችላል። - ኡድሂያውን ለራሱ፣ ለስጦታ እና ለሰደቃ አድርጎ መከፋፈሉ ሱና ነው። ይህ ማለት ግን እንደ አስፈላጊነቱ ለሶስቱም ያውለዋል ማለት እንጂ ሶስት እኩል ቦታዎች ይከፋፍለዋል ማለት አይደለም። - በዒድ ቀን ኡድሂያን ለማረድ አስቦ የዙልሂጃ ወር ከገባ ጥፍሩንና ጸጉሩን አይቆርጥም። ቆዳውንም አይቀርፍም። ይህ በሀጅ ላይ ያሉ ሰዎችን የሚመሳሰልበት ነብያዊ ትዕዛዝ ነው። ይህ የሚመለከተው የሚያርደዉን ሰው ብቻ ነው። እያወቀ ጥፍሩን ወይም ጸጉሩን የቆረጠ

      ቀለል ባለ አረዳድ ይሄ የቃላት ጨዋታ ነው። እግዚአብሔር ሶስት ጊዜ ‹‹አምላክ›› ሶስት ጊዜ ‹‹ቅዱስ›› ተብሎ ስለተጠራ በአካል ሶስት ነው ለማለት በአንቀፁ ውስጥ የምናገኘው ምንም ትንታኔ የለም። ቃላቱን በቃላት ጨዋታ እንሞግታቸው ካልን ደግሞ በመጀመሪያው አንቀፅ ላይ እግዚአብሔር ሙሴን፡-       ‹‹እኔ የአባትህ አምላክ፥ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ አለው።››       (ዘጸ 3፡6)       በማለት በአንቀፁ ውስጥ ‹‹አምላክ›› የሚለው ቃል ‹‹አራት›› ጊዜ ነው የተጠቀሰ ሲሆን ነገርግን ብዙውን ጊዜ የክርስትና መምህራን ‹‹የአባትህ አምላክ›› የሚለውን ቃል ያስቀሩና ሶስቱን ብቻ ለምሳሌነት እንዲመቻቸው ሲጠቅሱ ይስተዋላል።       በተጨማሪም በአንድ አንቀፅ ውስጥ ‹‹አምላክ›› የሚለው ቃል ሁለትም፣ ሶስትም፣ አራትም ጊዜ ተጠቅሶ እንደሚገኝም መዘንጋት የለብንም። ለማሳያ ያህል ምሳሌ ጠቅሰን እንለፍ።       ‹‹የአባትህ የአብርሃም አምላክ፤ የይስሐቅም አምላክ እኔ እግዚአባሔር ነኝ።››       (ሁለት ጊዜ) (ዘፍ 28፡13)       ‹‹የአባቶቻችሁ አምላክ፤ የአብርሃም አምላክ፤ የይስሐቅም አምላክ፤ የያዕቆብም አምላክ ወደ እናንተ ላከኝ።››       (አራት ጊዜ) (ዘጸ 3፡15)       ‹‹ቅዱስ›› ተብሎ ሶስት ጊዜ የተጠቀሰውን ተመሳሳይ የቃል ጨዋታ ሲሆን እግዚአብሔር በመጽሐፍ ቅዱስ አንድ ጊዜ፣ ሁለት ጊዜ ወይም ከዚያ በላይ ‹‹ቅዱስ›› ተብሏልና የቃላቱ ቁጥር እንደማይወስነው ማረጋገጥ እንችላለል።       ምናልባት ሶስቱ ቃላት ተከታትለው መጠቀሳቸው አምላክ ሶስት አካል እንደሆነ ይገልፃል ብለን ከሞገትን ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ አንድ አካል ሆነው ስማቸው በተከታታይ ሶስት ጊዜ የተጠቀሱ አሉና እነሱስ ስንት አካል ልንላቸው ነው? የሚል ጥያቄ ያስነሳብናል። አብነት ብንጠቅስ በትንቢተ ኤርምያስ ላይ፡-       ‹‹ምድር ሆይ፥ ምድር ሆይ፥ ምድር ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ስሚ።››       (ኤር 22፡29)       ተብላለችና ምድር ሶስት ጊዜ ስሟ መጠቀሱ ሶስት ናት አልያም በውስጧ ሶስትነት አላት ብለን ልንተረጉመው አይቻለንም። በተመሳሳይም በዚሁ በትንቢት ‹‹የእግዚአብሔር መቅደስ›› ሶስት ጊዜ ተጠቅሶ እናገኛለን፡-       ‹‹የእግዚአብሔር መቅደስ፥ የእግዚአብሔር መቅደስ፥ የእግዚአብሔር መቅደስ ይህ ነው እያላችሁ በሐሰት ቃል አትታመኑ።››       (ኤር 7፡4)       ነገርግን የእግዚአብሔር መቅደስ አንድ እንጅ ሶስት አልነበረም። በመጨረሻም አንድ ምሳሌ እንጥቀስና ርዕሱን እንቋጨው። ኢየሱስ በማቴዎስ ወንጌል ላይ እንዲህ የሚል ቃል ተናግሯል፡-       ‹‹በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።››       (ማቴ 7፡21)       ኢየሱስ በዚህ ንግግሩ ራሱን ሁለትጊዜ ‹‹ጌታ ሆይ! ጌታ ሆይ!›› ብሎ በመጥራቱ ሁለት አካል ነው ማለት አይደለም። ታዲያ ለምን አንድ አካል ሶስት ጊዜ ተደጋግሞ ይጠራል ካልን ደግሞ ግልፅና ቀላሉ መልስ ጉዳዩን አፅንዖት ለመስጠት ነው የሚል ነው።       ➢ በዋናነት በብሉይ ኪዳን ውስጥ ስለ ሥላሴ የተነገሩ ናቸው የሚባሉት አንቀፆች ከላይ የጠቀስናቸው ሲሆኑ መንፈስ ቅዱስን በተመለከተ የተነገሩትን ‹‹መንፈስ ቅዱስ ምንድነው?›› በሚለው ርዕስ ስር እንዳስሳቸዋለን። ------------------------------Ω-------------------------------------- https://t.me/muhammed6964 ወሠላሙ ዐለይኩም

      ይህ አንቀፅ ስለ ሥላሴ ይገልፃል ያስባለው ለአብርሃም የተገለፁት መላእክት ሶስት መሆናቸውና ከእነሱም ጋር እንደ አንድ አካል ‹‹አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ሆነ ባሪያህን አትለፈኝ›› እያለ መነጋገሩ ነው።       እነሱ ሶስት ሆነው ሳለ ለምን እንደ አንድ አካል ሊያናግራቸው ቻለ? ለሚለው የእብራይስጥ ቋንቋን ሊቃውንት የሆኑ አይሁዶቹ እንደሚሉት አንደኛ አብርሃም መላእክቱን እንደ አንድ አካል ያናገራቸው ከአንድ አምላክ የተላኩና እነሱን ማናገር ፈጣሪን ማናገር በመሆኑ ሲሆን ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ መላእክቱ ከፈጣሪ የተላኩ በመሆናቸው ፀሐፊው የሶስቱን ንግግር እንደ አንድ አካል ንግግር ቆጥሮታል የሚል ነው።       ይሄንን በደንብ የሚገልፅልን ደግሞ መላእክቱ አብርሃምን ሲያናግሩት ሶስቱም ናቸው የሚያወሩት ወይስ አንዱ ነው? የሚለው ነው። ሶስቱም በአንድ አፍ ‹‹ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት?›› ሊሉት አይችሉምና። የሚጠይቀው አንዱ ነው። እናም መጽሐፉ ላይ ‹‹ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት? አሉት›› ማለቱ ሶስቱም ሊጠይቁት የመጡት ስለአንድ ጉዳይ በመሆኑ ከስነ ፅሁፍ አንፃር ምንም ስህተት የለበትም።       በተጨማሪም በብዙ የብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ውስጥ የእግዚአብሔር መላእክት እንደ እግዚአብሔር ሆነው ሲነጋገሩ ተስተውሏል። ምሳሌ አንድ መልአክ ለሙሴን ከተገለፀለት በኋላ የተናገረውን ማንሳት እንችላለን።       ‹‹የእግዚአብሔርም መልአክ በእሳት ነበልባል በእሾህ ቍጥቋጦ መካከል ታየው ... እግዚአብሔር ከቍጥቋጦው ውስጥ እርሱን ጠርቶ። ሙሴ፤ ሙሴ ሆይ ... እኔ የአባትህ አምላክ፤ የአብርሃም አምላክ፤ የይስሐቅም አምላክ፤ የያዕቆብም አምላክ ነኝ አለው።››       (ዘጸ 3፡2-6)       በዚህ አንቀፅ ገለፃ ሙሴን ‹‹የአባትህ አምላክ፤ የአብርሃም አምላክ ነኝ›› ያለው መልአኩ ነው። እንዴት መልአክ ሆኖ እኔ የአብርሃም አምላክ ነኝ ይለዋል? ካልን መልሱ ቀላል ነው። መልአኩ የተናገረው የእግዚአብሔርን ንግግር ወክሎ በመሆኑ ፀሐፊው መልአኩ እንደ እግዚአብሔር ሆኖ እንዳናገረው ፅፎታል። ከዚህ የዘለለ ብዙ የሚያመራምር ነገር የለውም።       የኢስማኤል እናት አጋርንም ታሪክ ብናይ በረሃ ላይ ስትንከራተት ያገኛት መልአክ ወደፊት ዘሯን እንደሚያበዛላት መናገሩ ተፅፏል።       ‹‹የእግዚአብሔር መልአክም። ዘርሽን እጅግ አበዛለሁ፤ ከብዛቱም የተነሣ አይቆጠርም አላት።››       (ዘፍ 16፡10)       ለማንም ግልፅ በሆነው አረዳድ መልአኩ ዘሯን ሊያበዛው አይችልም። ነገር ግን ከእግዚአብሔር ተልኮ የመጣ ነውና አምላክ ዘሯን እንደሚያበዛላት ነው ያበሰራት።       አብርሃም ታሪክ ላይ የምናገኘውም የዚሁ ዓይነት ቀላል ገለፃን ነው። ነገርግን የመላእክቱ ሶስት መሆንወደ ሥላሴ ለማቅረብ ይመቻልና ምክንያት እንደተፈለገለት መረዳት እንችላለን። እንደዚያም ሆኖ ሶስቱ መላእክት እንደ አንድ ማውራታቸው ሥላሴ ካሰኛቸው ሎጥ ሁለት መላእክትን እንደ አንድ አካል ማናገሩም ተፅፏልና ይህስ በምን ይተረጎማል? ብለን መጠየቅ እንፈልጋለን።       ዘፍጥረት 18፡22 ላይ እንደተፃፈው ለአብርሃም የተገለጡለት ሰዎች ከእሱ ጋር ንግግራቸውን ከጨረሱ በኋላ ‹‹ሰዎቹም ከዚያ ፊታቸውን አቀኑ፤ ወደ ሰዶምም ሄዱ፤ አብርሃም ግን በእግዚአብሔር ፊት ገና ቆሞ ነበር›› የሚል ቃል ተፅፏል። ከዚያም ምዕራፍ 19 ላይ የሚከተለውን ታሪክ እናገኛለን፡-       ‹‹ሁለቱም መላእክት በመሸ ጊዜ ወደ ሰዶም ገቡ፤ ሎጥም በሰዶም በር ተቀምጦ ነበር። ሎጥም ባያቸው ጊዜ ሊቀበላቸው ተነሣ፤ ፊቱንም ደፍቶ ወደ ምድር ሰገደ።... ሁለቱም ሰዎች ሎጥን አሉት...እኛ ይህን ስፍራ እናጠፋው ዘንድ እግዚአብሔር ሰድዶናል።... ሎጥም፤ አላቸው። ጌቶቼ ሆይ፤ እንዲህስ አይሁን፤ እነሆ ባሪያህ በፊትህ ሞገስን አግኝቶአል፤ ነፍሴን ለማዳን ያደረግህልኝን ምሕረትህንም አብዝተሃል፤ ክፉ እንዳያገኘኝና እንዳልሞት ወደ ተራራ ሸሽቼ አመልጥ ዘንድ አልችልም።››       (ዘፍ 19፡1-19)       ይህ ታሪክ ለአብርሃም የተገለጡለት ‹‹ሰዎች›› ሎጥ ባገኛቸው ጊዜ ‹‹መላእክት›› መባላቸው በሰው መልክ የተገለፁ መላእክት መሆናቸውን የሚገልፅልን ሲሆን ለአብርሃም የተገለጡለት ሰዎች መላእክት አይደሉም የሚለውን የአንዳንድ ሰዎች ማለባበሻ ውድቅ ያደርገዋል። በብሉይ ዘመን መላእክት በሰው ተመስለው መገለጣቸው የተለመደ ሲሆን ዕብ 13፡1 ‹‹አንዳንዶች ሳያውቁ መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና።››       በማለት ሁኔታውን ገልፆታልም።       እናም ታሪኩን በምናነብበት ጊዜ ሎጥ ሰዎቹን ‹‹ጌቶቼ ሆይ!›› ካላቸው በኋላ ‹‹ባሪያህ በፊትህ ሞገስ አግኝቶአል›› በማለት እንደ አንድ አካል ሲያናግራቸው እናያለን። አብርሃም ሶስቱን ሰዎች እንደ አንድ ሲያናግር ሥላሴ ከተባለ ሎጥ ሁለቱን ሰዎች እንደ አንድ ሲያናግር ምን ሊባል ነው? የሚለው ጥያቄ የሚነሳው እዚህ ጋር ነው።       በተጨማሪም ለአብርሃም የተገለጡለት ሶስቱ ሰዎች ሥላሴዎች ናቸው ከተባለና ሎጥን ሲገናኙት ግን ሁለት መሆናቸውና ከመሃላቸው አንዱ ተነጥሎ መቅረቱ ፍፁም አይነጣጠሉም የሚባለውን የሥላሴን አስተምህሮት አያፈርሰውምን? የሚል ጥያቄ እንድናነሳ ያደርገናል።       ባጠቃላይ የፅሁፉን ሙሉ ይዘት ካነበብነው ሶስቱ ሰዎች በሰው ተመስለው የመጡ መላዕክት እንጅ አምላክን ተመስለው የመጡ ሰዎች እንዳልሆኑ እንገነዘባለን። ከመጀመሪያውም ቢሆን መላዕክቱ ከፈጣሪ ብስራት ይዘው መምጣታቸውን እንጅ የአምላክን ሶስትነት ለመግለፅ መላካቸውን አልተናገሩም። ስለዚህ ሌላውን ሁሉ ትቶ ሶስት ነገሮችን ብቻ ወደ ሥላሴ ማስጠጋት ከምክንያታዊነት እንድንወጣ ያደርገናል።       ለግንዛቤ ያህል ቁርኣን ወደ አብርሃም የተላኩት ሰዎች መላዕክት መሆናቸውን የገለፀበትን አንቀፅ ጠቅሰን እናጠቃለው።       ‹‹መልክተኞቻችንም ኢብራሂምን በልጅ ብስራት በእርግጥ መጡት። ሰላም አሉት። ሰላም አላቸው። (ሚስቱን) በኢስሐቅም አበሰርናት። ከኢስሐቅም በኋላ (በልጁ) በያዕቁብ (አበሰርናት)።››       (ሁድ 69-71)       ➢ በመጨረሻም በሶስተኛነት የምናያቸው በአንድ ዓ.ነገር ውስጥ ሶስት ተመሳሳይ ቃላት የተጠቀሱባቸውን አንቀፆች ምሳሌነት ነው። ከአንቀፆቹ ውስጥ ተጠቃሹ ደግሞ እግዚአብሔር ሙሴን እንዲህ ያለው ነው፡-       ‹‹የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ አለው።››       (ዘጸ 3፡6)       ‹‹አምላክ፣ አምላክ፣ አምላክ›› ብሎ ሶስትነቱን፤ ‹‹እኔ እግዚአብሔር ነኝ›› ብሎ አንድነቱን ገልጿል ይባላል። በተመሳሳዩ ቀጣዩ የኢሳያስ ትንቢትም ይጠቀሳል፡-       ‹‹እግዚአብሔርን በልዑል ዙፋኑ ላይ ተቀምጦ አየሁት... ሱራፌልም ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያሉ ይጨሁ ነበር።››       (ኢሳ 6፡1-3)       በዚህም አንቀፅ ውስጥ እግዚአብሔር ‹‹ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ›› ብሎ ሶስትነቱን፤ ‹‹የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር›› ብሎ አንድነቱን መስክሯል የሚል ትርጉም ተሰጥቶታል።

ክፍል 7 ሥላሴ በብሉይ ኪዳን ክፍል-2 በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ፥ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡       የክርስትና መምህራን ታዳ አምላክ ‹‹እኔን ተገዙኝ›› ብሎ በቁጥር አንድ መሆኑን የሚገልፀው ሥላሴዎች በአካል ሶስት ቢሆኑም በመለኮት አንድ በመሆናቸው ነው የሚል ምላሽ ይሰጡናል። እንደዚህ ከሆነ ሥላሴዎች በመፍጠርም ሆነ በመመለክ የማይነጣጠሉ አንድ ከሆኑ ለምን እግዚአብሔር ሰውን ‹‹እንፍጠር›› ሲል በመነጣጠል ብዝኃነቱን ገለፀ? የሚል ጥያቄ እንድናነሳ ያደርገናል።       ሥላሴዎች በመፍጠር የማይነጣጠሉ አንድ ከሆኑ እግዚአብሔር ‹‹እንፍጠር›› ሳይሆን ‹‹ልፍጠር›› ነበር ሊል የሚገባው። ‹‹እንፍጠር›› ካለ ግን በመፍጠር እንደሚነጣጠሉ ያስረዳል። እናም ሥላሴዎች በመመለክም ይሁን በመፍጠር አንድ ናቸው እየተባለ በሌላ አቅጣጫ ደግሞ ‹‹እንፍጠር›› የሚለው ቃል ብዝኃነቱን ይገልፃል ማለት የሥላሴን የማይነጣጠሉ ሶስትነት በአንድነት የሚለውን ድንጋጌ ያፈርሰዋል።       ከዚሁ ነጥብ ሳንወጣ እግዚአብሔር ሰውን ‹‹በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር›› ሲል እግዚአብሔር በወልድ (በኢየሱስ) መልክ ሰውን እንደፈጠረና ኢየሱስም ቅድመ ዓለም ከእግዚአብሔር አንዱ አካል መሆኑን ያስረዳል ሲሉ የሥላሴ ምሁራን ሲናገሩ እንሰማለን።       ጠቅለል አድርገን ስናየው ከጥንት ጀምሮ በአይሁዶች ዘንድ አምላክ አምሳያ እንደሌለው ይታመናል። ለዚህም እንደ ማስረጃነት፡-       ‹‹አምላካችንን እግዚአብሔርን የሚመስል እንደሌለ ታውቅ ዘንድ።››       (ዘጸ 8፡10)       ‹‹እንግዲህ እተካከለው ዘንድ በማን መሰላችሁኝ? ይላል ቅዱሱ።››       (ኢሳ 40፡25)       የሚሉትን አንቀፆች ይጠቀሳሉ። እናም አምላክ ፍፁማዊ ማንነት ስላለው በሁሉም ነገሩ ውስን የሆነው ፍጥረት ሊመስለው አይችልም የሚለው የማይቀየር እምነታቸው ነው። ይሁን እንጅ እግዚአብሔር የሰውን ልጅ በራሱ አምሳል እንደፈጠረው እንዲህ ሲል ተናግሯል፡-       ‹‹እግዚአብሔርም አለ። ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ።››       (ዘፍ 1፡26)       በዚህ ቃል ውስጥ ‹‹በመልካችን›› (tselem) የሚለው የእብራይስጠኛ ቃል ‹‹ምስል›› ወይም ‹‹ጥላ›› የሚሉ ፍችዎችን የያዘ ሲሆን እንደ አይሁድ ሊቃውንት ትርጓሜ አንቀፁ አምላክ የሰውን ልጅ በአካላዊ አምሳያው (physical appearance) ሳይሆን የፍጥረተ ዓለም ገዥ የሆነው አምላክ የሰው ልጅ በምድር ላይ ያሉ ፍጥረታት እንዲገዛ በመፍጠሩ የእሱ ብቻ የሆነውን የገዥነትን ባህርይ እንዳወረሰው ለመግለፅ የተጠቀመበት ቃል ነው ሲሉ ያብራራሉ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በዘፍጥረት 3፡22 ላይ እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ተናግሯል፡-       ‹‹እግዚአብሔር አምላክም አለ። እነሆ አዳም መልካምንና ክፉን ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ።››             በዚህም አንቀፅ ውስጥም አዳም ከአምላክ እንደ አንዱ የሆነው በአካላዊ ገፅታው ሳይሆን መልካምንና ክፉን በማወቅ ደረጃ እንደሆነ ሊቃውንቱ ይገልፃሉ። እናም የብሉይ ኪዳን ባለቤት የሆኑት አይሁዶች የሰው ልጅ በምድር ላይ የአምላኩ ተጠሪ እንደመሆኑና ፈጣሪ የሚወደውን ሊፈፅምና የሚጠላውን ሊርቅ እንደመወከሉ ‹‹ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር›› የሚለውን ቃል ተግባርን እንጅ የአካላዊ ገፅታን መመሳሰል እንደማይገልፅ በፅኑ ያምናሉ። በተመሳሳዩ በዘካርያስ ትንቢትም ውስጥ እንዲህ የሚል ቃል እናገኛለን፡-       ‹‹በዚያም ቀን ከእነርሱ መካከል ደካማው እንደ ዳዊት ይሆናል፤ የዳዊትም ቤት በፊታቸው እንደ እግዚአብሔር መልአክ እንደ አምላክ ይሆናል።››       (ዘካ 12፡8)       በዚህ አንቀፅ ውስጥ ‹‹እንደ አምላክ ይሆናል›› የተባለው የዳዊት ቤት ነው። እግዚአብሔር በኢየሩሳሌም ላይ የሚመጡትን አሕዛብ ሁሉ ከተጋደለ በኋላ የዳዊትን ቤት በፊታቸው እንደ አምላክ እንደሚያደርገው ይናገራል። ይህ አንቀፅ እንደ አምላክ መሆን ማለት በቀጥታ የአካላዊ ገፅታን መመሳሰል እንደማይገልፅ ማሳያ ነው። የሰው ልጅንም ብንመለከት እግዚአብሔር በአምሳሉ የፈጠረው ወንድን (አዳምን) እንጅ ሴትን (ሔዋንን) እንዳልሆነ ይነግረናል።       ‹‹እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው።››       (ዘፍ 1፡27)       የአዳምንና የሔዋንን አካላዊ ገፅታ ካየን ደግሞ ተመሳሳይ ነው። ነገር ግን እግዚአብሔር አምሳያው አዳም እንጅ ሔዋን እንዳልሆነች ነግሮናል። ከፆታው ነው እንዳንል አምላክ ፆታ የለውም። ታዲያ ከምኑ ነው? ካልን መልሱ ምድራዊ ኃላፊነትን ለአዳም ከመስጠቱ ጋር እንደሆነ እንረዳለን። አዳም የዓለም ገዥ ተደርጎ ኃላፊነት ተሰጥቶታልና። በሚስቱም ላይ ራስ ተደርጓልና። እነዚህ በልቅና የተሰጡት ኃላፊነቶች አዳምን የአምላክ አምሳያ አሰኝተውታል።       ነገር ግን የሥላሴ ሰባኪያን ይህንን የብሉይ አስተምህሮት በተሳሳተ መንገድ በመተርጎም ኢየሱስ የፍፁማዊው አምላክ አካላዊ አምሳያው መሆኑን ያስተምራሉ። ለማስረጃነት የሚጠቅሷቸው አንቀፆች ደግሞ ቀጣዮቹ ናቸው፡- ‹‹እርሱም የማይታይ አምላክ ምሳሌ ነው።››       (ቆላ 1፡15)       ‹‹ለእነርሱም የእግዚአብሔር ምሳሌ የሆነ የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን እንዳያበራላቸው፤ የዚህ ዓለም አምላክ የማያምኑትን አሳብ አሳወረ።››       (2ኛ ቆሮ 4፡4)       ከእነዚህ አንቀፆች በመነሳት ኢየሱስ ትክክለኛው የእግዚአብሔር አምሳያ መሆኑን ነገርግን አዳም በእግዚአብሔር አምሳል ቢፈጠርም ኃጢአት ስለሰራ ትክክለኛ አምሳሉ ሊሆን እንዳልቻለ ይናገራሉ። ይሁን እንጅ አዳም ኃጢአት የሰራው ከተፈጠረ በኋላ በመሆኑ ይህ ክርክራቸው ውሃ የሚያነሳ ሆኖ አናገኘውም።       ሰባኪያኑ መጀመሪያ ላይ በዘፍጥረት የተጠቀሰውን ቃል ኢየሱስ ከመወለዱ በፊትበሰማይ ይኖር ስለነበር ‹‹እግዚአብሔር ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር›› ሲል በወልድ (ኢየሱስ) አምሳል እንደሆነና ኢየሱስ ቀድሞም የነበረ የሥላሴ አካል መሆኑን ይገልፃል ሲሉ ይሞግታሉ።       ኢየሱስ ከማርያም ከመወለዱ በፊት ቅድመ ዓለም በሰማይ ይኖር ነበረ የሚለው አስተምህሮት ምንም መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ የሌለው ሲሆን ‹‹ኢየሱስ አምላክ ነውን?›› በሚለው ምዕራፍ ስር በዝርዝር እናየዋለን።       በተጨማሪም ጥንታዊ ባቢሎናውያን አማልክቶቻቸውን የፈጣሪ አምሳል ናቸው ብለው ያምኑ የነበረውን ክርስቲያኖች በቀጥታ ለኢየሱስ እንደተዋሱት የመጽሐፍ ቅዱስ አጥኚ ምሁራንም ይገልፃሉ።       ➢ ሁለተኛው ለሥላሴ አስረጅነት የሚጠቀሰው አንቀፅ እግዚአብሔር ለአብርሃም በሶስት ሰዎች አምሳል ተገልፆለታል የሚባለው ነው።       ‹‹በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት። ዓይኑንም አነሣና እነሆ፥ ሦስት ሰዎች በፊቱ ቆመው አየ፤ ባያቸውም ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ሮጠ ወደ ምድርም ሰገደ። እንዲህም አለ። አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምናለሁ።››       (ዘፍ 18፡1-3)

ክፍል 6 ሥላሴ በብሉይ ኪዳን ክፍል-1 በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ፥ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡       ብሉይ ኪዳን የመጽሐፍ ቅዱስን 74% የሚሸፍነው ትልቁ ጥራዝ ነው። ይህ መጽሐፍ በጥብቁ የአይሁዳውያን አንድ አምላክ በአንድ አካል የማመን አስተምህሮት ላይ ተመስርቶ የተፃፈ መጽሐፍ ነው።       በብሉይ ኪዳን መጽሐፍት በአንዳንድ ቦታዎች እግዚአብሔር ‹‹አባት›› ተብሎ የተጠራ ሲሆን በሥላሴ ውስጥ ‹‹አብ›› የሚባለው ቃል የኖረበት ምክንያቱም ይህ ነው። ‹‹ወልድ›› የሚለውን ቃል ግን በብሉይ ኪዳን ተፅፎ አናገኘውም። ምናልባት ‹‹ወልድ›› ተብሎ ያልተጠቀሰው በጊዜው በስጋ ባለመወለዱ ምክንያት ነው ብለው የሚያምኑ ካሉ ወልድ ከአብ ቅድመ ዓለም በባህርይ እንደተወለደ ይታመናልና ገና በስጋ ያለመወለዱ ምክንያት እንዳልሆነ መጠቆም እፈልጋለሁ።       ‹‹መንፈስ ቅዱስን›› በተመለከተ ቃላቱ ተዟዙረው ‹‹ቅዱስ መንፈስ›› በሚል ሁለት ቦታ1 ሲጠቀስ ‹‹መንፈስ›› የሚለው ቃል ግን በተናጠል በበርካታ ቦታዎች ተፅፏል። ‹‹መንፈስ›› ተብሎ የተጠቀሰው በራሱ አምላክ ነው ወይስ አይደለም የሚለውን ‹‹መንፈስ ቅዱስ ምንድነው?›› የሚል የራሱ ርዕስ ስላለው ወደፊት እንመጣበታለን።       ለመንደርደሪያነት ይህንን ካልን ከብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ለሥላሴ አምላክነት ማስረጃ ናቸው ተብለው የሚጠቀሱትን አንቀፆች ቀጥለን ደግሞ እንመለከት።       ➢ የመጀመሪያዎቹ ተጠቃሽ አናቅፅ ቀጣዮቹ በዘፍጥረት ላይ የምናገኛቸው ብዝኃነትን ገላጭ ቃላት ናቸው።       ‹‹እግዚአብሔርም አለ። ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር›› (ዘፍ 1፡26)       ‹‹እግዚአብሔር አምላክም አለ። እነሆ አዳም መልካምንና ክፉን ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ።››       (ዘፍ 3፡22)       ‹‹እግዚአብሔርም አለኑ፥ እንውረድ፤ ቋንቋቸውን እንደባልቀው።››       (ዘፍ 11፡6-7)       በእነዚህ አናቅፅ ‹‹እንፍጠር››፣ ‹‹እኛ›› እና ‹‹ኑ እንውረድ›› የሚሉት ቃላት ብዝኃነትን ገላጭ በመሆናቸው ለሥላሴ የተነገሩ አስረጅዎች ተደርገው ይወሰዳሉ። እኛም እነዚህ ቃላት ከቋንቋ ሰዋሰው አንፃር ብዝኃነትን የሚያሳዩ ቢሆንም ነገርግን የአምላክን ሶስት አካልነት እንደማይገልፁ ቀጥለን ሶስት አብይት ነጥቦችን እናያለን፡-       ➢ የመጀመሪያው ነጥብ ‹‹እንፍጠር፣ እኛ›› የሚሉት ቃላት ከአንድ በላይ ለሆነ ቁጥር የሚያገለግሉ ቢሆንም በሶስት ቁጥር ሊወሰን አለመቻሉ ነው። እግዚአብሔር ‹‹እንፍጠር›› ስላለ በቁጥር ከአንድ በላይ ነው ከተባለ ሁለትም፣ ሶስትም፣ አራትም፣ አስርም ሊሆን ይችላል ማለት ነው። እናም እግዚአብሔር በግልፅ ስለ ሶስትነቱ እስካልተናገረ ድረስ ቁጥሩን በሶስት ወስኖ መደምደም አይቻልም።       ➢ ሁለተኛው ነጥብ በሴሜቲክ የቋንቋ አጠቃቀም አንድን አካል ወይም ሰው ለአክብሮትና ውዴታን ለመግለፅ ሲባል ብዝኃነትን ገላጭ በሆነ ቃል መጥራት የተለመደ መሆኑ ነው። በቋንቋ ሰዋሰዋዊ አጠራር በአንቀፆቹ ውስጥ ‹‹እኛ›› የሚለው ቃል የመጀመሪያ መደብ ብዜት ስያሜ (First person Plural term) የምንለው ነው። ምሳሌ ዘፍ 3፡22 ላይ የተፃፈውን ብናይ መጀመሪያ ላይ ‹‹አምላክም አለ›› በማለት አንድ መሆኑን ከጠቀሰ በኋላ መልሶ ‹‹ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ›› በማለት ራሱን በብዙ ቁጥር ይገልፀዋል። ይህ አይነት አነጋገር በሴሜቲክ ቋንቋ የታወቀና የተለመደ ሲሆንአንድ አካል ወይም አንድ ሰው ክብሩንና ልዕልናውን ለመግለፅ ‹‹እኛ›› ሲል የሚናገረው ነው። እብራይስጥ ደግሞ (አረብኛና አማርኛን ጨምሮ) አንዱ የሴሜቲክ ቋንቋ ዝርያ ነውና እስራኤላውያን አንድን ንጉስ ወይም የተከበረ ሰው ‹‹እነሱ›› በማለት ክብሩን ለመግለፅ በብዝኃነት ቃል እንደሚጠሩት ይታወቃል።       በተመሳሳይ አማርኛም የሴሜቲክ ቋንቋ ዝርያ በመሆኑ ይሄንን አገላለፅ ይጠቀማል። ምሳሌ ‹‹ጠቅላይ ሚንስትሩ እንዲህ አሉ››፣ ‹‹ንጉሱ እንዲህ ተናገሩ››፣ ‹‹ዶክተሩ እንዲህ አዘዙ›› የሚሉት ቃላት ብዝኃነት ገላጭ ቢሆኑም አንድን ሰው በአክብሮት ለመጥራት እንደምንጠቀምባቸው ግልፅ ነው። እንዲሁም ከሰዎች ‹‹ታዲያስ›› የሚል ሰላምታ ሲቀርብላቸው ‹‹አለን›› ብለው ሲመልሱ ይስተዋላል። ‹‹አለን›› ማለታቸው አክብሮትን እንጅ ብዛትን ለማመልከት እንዳልሆነም ይታወቃል። እናም ከሁሉም በላይ የተከበረው አምላክ ‹‹እኛ›› እያለ መናገሩ ታላቅነቱንና ኃያልነቱን ለመግለፅ እንጂ በቁጥር ከአንድ በላይ መሆኑን የሚያሳይ አይደለም። ማንኛውም የእብራይስጥ ቋንቋ ምሁርም በዚህ ይስማማል። እስራኤላውያንም በታሪካቸው ከዚህ የተለየ ፍችም ሰጥተውትም ተወዛግበውበትም አያውቁም።       ‹‹ኦሎህ›› የሚለውን ቃል ስናይም አምላክ ማለት ሲሆን አልቀው ሲጠሩት ደግሞ ‹‹ኤሎሂም›› ይሉታል። ኤሎሂም ቀጥተኛ ትርጉሙ ‹‹ብዙ አምላክ›› ማለት ነው። ነገር ግን በብዝኃት የሚጠሩት ክብሩንና ልቅናውን ለመግለፅ እንጅ አንድ ለመሆኑማ ቀድመው ‹‹ኦሎህ›› ብለው ጠርተውታል።       በአረብኛ ቋንቋ ውስጥም ይህ ክብርን የሚገልፀው የብዝኃት ገላጭ ቃል በስፋት የተለመደ ሲሆን ለአብነት በቁርኣን ውስጥ፡-       ‹‹እኛ ቁርኣንን እኛው አወረድነው። እኛም ለእርሱ ጠባቂዎቹ ነን።››       (ሂጅር 9)       የሚሉና መሰል ቃላትን በብዛት እናገኛለን። በእነዚህ አናቅፅ አላህ አንድ ሲሆን ‹‹እኛ›› እያለ ራሱን የሚጠራው የአክብሮት ስለመሆኑ በእምነቱ ምሁራን መካከል ምንም ውዝግብ አስነስቶ አያውቅም። በተረፈ እንዲህ ያሉ ጉዳዮችን ስናጠና በቅድሚያ የቋንቋው ባለቤቶችን መጠየቅና የአነጋገር ዘያቸውን ማወቅ እንደሚገባ መረዳት ያስፈልጋል።       ➢ ሶስተኛውና የመጨረሻው ነጥብ እግዚአብሔር አንድም ቦታ ‹‹እኛን ተገዙን›› ወይም ‹‹አምልኩን›› ብሎ በብዝኃት ቁጥር ተናግሮ አለማወቁ ነው። ‹‹እንፍጠር›› ማለቱ ብዙኃነቱን ይገለፃል ከተባለ ‹‹እኛን ተገዙን፤ አምልኩን›› ሊል ሲገባው ‹‹እኔን ተገዙኝ፤ አምልኩኝ›› በማለት ራሱን በነጠላ ቁጥር በመጥራቱ ቃላቱ የአክብሮት እንጅ የቁጥር ብዝኃነትን እንደማይገልፁ ይነግረናል። አንቀፆቹንም ካስተዋልናቸው ‹‹እንፍጠር አለ›› እንጅ ‹‹እንፍጠር አሉ›› አይልም። __ (1) መዝሙር 51፡11 እና 143፡10 ---------------------------Ω----------------------------------- https://t.me/muhammed6964 ወሠላሙ ዐለይኩም