Don Bosco Catholic Primary school (1-4) A.A 2017 E.C
Open in Telegram
Show more
1 846
Subscribers
+124 hours
+37 days
+2930 days
Posts Archive
ለ2018ዓ.ም የሚንስትሪ ተፈታኝ የ 2019 ዓ.ም የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችና ወላጆች
ውድ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች የዶን ቦስኮ ካቶሊክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ የሚለቀቅበት የቴሌግራም ቻናል ከታች የተያያዘው ሊንክ መሆኑን እየገለፅን join በማለት (የቴሌግራም አባል ) በመሆን የሚለቀቁ አዳዲስ መረጃዎችን እንድትከታተሉ ለማሳሰብ እንወዳለን።👇👇👇
https://t.me/donbosco2021
የ2018ዓም የት/ቤት ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ የተማሪ ወላጆች በሙሉ
የ2018ዓም የተማሪዎች ሪፖርት ካርድ ለወላጅ የሚሰጠው ቅዳሜ ሃምሌ 05/2018ዓም መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ከፍላችሁ ያላጠናቀቃችሁ ወላጆች ነገ ረቡዕ ሃምሌ 01 እና አርብ ሃምሌ 03/2018ዓም ከፍላችሁ እንድታጠናቅቁ እያሳስብን ያላጠናቀቁ ተማሪዎችን ሪፖርት ካርድ የመለየት ስራ የምንሰራ እና እሁድ ሪፖርት ካርዱን የምንይዝ(የማንሰጥ) መሆኑን እያሳወቅን ማንኛውንም ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ በአፋጣኝ(ከላይ በተጠቀሱት ቀናት ብቻ) ከፍላችሁ እንድታጠናቅቁ በጥብቅ እናሳስባለን።
ማሳሰቢያ
👉ክፍያ ላላጠናቀቁ ተማሪዎች ካርድ የማንሰጥ መሆኑን እያሳወቅን ሪፖርት ካርድ ባለመውሰዳችሁ ከምዝገባ ጋር ለሚፈጠር ማንኛውም ችግር ኃላፊነቱን ወላጅ የሚወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።
ት/ቤቱ
ዒድ ሙባረክ!
ለእስልምና እምነት ተከታይ ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ
እንኳን ለ1447ኛው ታላቁ የኢድ አል አድሃ(አረፋ) በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ!
በዓሉ የሠላምና የፍቅር እንዲሆንላችሁ እንመኛለኝ ::
ዶን ቦስኮ ካቶሊክ ት/ቤት
07/09/2018 ዓ.ም
ለተከበራችሁ የዶን ቦስኮ ካቶሊክ አንደኛና መካከለኛ ት/ቤት የ 6ኛና8ኛ ክፍል ተማሪዎች / ወላጆች / አሳዳጊዎች በሙሉ
📖የ6ኛና8ኛክፍል ከተማ አቀፍ የሞዴል ፈተና የቀን ለውጥ ተደርጎበታል፡፡
👉🏻ከግንቦት 12-14/2018 ባሉት ቀናት የሚሰጥ በመሆኑ ተማሪዎች ዝግጅት እንዲያደርጉ ድጋፍ እንድታ ደረጉ ለማሳወቅ እንወዳለን::
ት/ቤቱ
ለዶን ቦስኮ ካቶሊክ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ወላጆች
እንደሚታወቀው የ3ኛው ሩብ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና ረቡዕ እስከ አርብ (ከ07- 09/ 08/ 2018 ዓ.ም ) ድረስ እንደሚሰጥ ለወላጆች በላክነው ኘሮግራም ላይ መግለፃችን ይታወቃል። ስለዚህ ተማሪዎች ከበዓል ጋር ተያይዞ መዘናጋት እንዳይፈጠርና ጥናታቸው ላይ እንዲያተኩሩ እገዛና ክትትል ታደርጉላቸው ዘንድ ከወዲሁ ለማሳሰብ እንወዳለን::
* ነገ ማክሰኞ 06/08/2018 ዓ.ም የሙሉ ቀን ትምህርት ይቀጥላል::
ት/ቤቱ
እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው አደረሳችሁ!!!
ለክርስትና እምነት ተከታይ ተማሪዎቻችንና ወላጆች እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!
በዓሉ የሰላም የፍቅር የመተሳሰብ እንዲሆንልን እንመኛለን።
መልካም በዓል!!
ት/ቤታችን ይህንን አመርቂ ውጤት እንዲያስመዘግብና የዋንጫ ተሸላሚ እንሆን ያደረጋችሁ ውድ ተማሪዎቻችንና ሥራውን በኃላፊነት ስትመሩ የነበራችሁ መ/ራን ላደረጋችሁት የላቀ አስተዋፅዖ ከልብ እናመሰግናለን
እጅግ በጣም ኮርተንባችኋል !
እንኳን ደስ አላችሁ !
ዶን ቦስኮ ካቶሊክ ት/ቤት
