en
Feedback
Don Bosco Catholic Primary school (1-4) A.A 2017 E.C

Don Bosco Catholic Primary school (1-4) A.A 2017 E.C

Open in Telegram
1 846
Subscribers
+124 hours
+37 days
+2930 days
Posts Archive
ለ2018ዓ.ም የሚንስትሪ ተፈታኝ  የ 2019 ዓ.ም የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችና ወላጆች ውድ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች የዶን ቦስኮ ካቶሊክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መረጃ የሚለቀቅበት የቴሌግራም ቻናል ከታች የተያያዘው ሊንክ መሆኑን እየገለፅን join በማለት (የቴሌግራም አባል ) በመሆን የሚለቀቁ አዳዲስ መረጃዎችን እንድትከታተሉ ለማሳሰብ እንወዳለን።👇👇👇 https://t.me/donbosco2021

የ2018ዓም የት/ቤት ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ የተማሪ ወላጆች በሙሉ የ2018ዓም የተማሪዎች ሪፖርት ካርድ ለወላጅ የሚሰጠው ቅዳሜ ሃምሌ 05/2018ዓም መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ከፍላችሁ ያላጠናቀቃችሁ ወላጆች ነገ ረቡዕ ሃምሌ 01 እና አርብ ሃምሌ 03/2018ዓም ከፍላችሁ እንድታጠናቅቁ እያሳስብን  ያላጠናቀቁ ተማሪዎችን ሪፖርት ካርድ የመለየት ስራ የምንሰራ  እና እሁድ ሪፖርት ካርዱን የምንይዝ(የማንሰጥ) መሆኑን እያሳወቅን ማንኛውንም ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ በአፋጣኝ(ከላይ በተጠቀሱት ቀናት ብቻ) ከፍላችሁ እንድታጠናቅቁ በጥብቅ እናሳስባለን። ማሳሰቢያ 👉ክፍያ ላላጠናቀቁ ተማሪዎች ካርድ የማንሰጥ መሆኑን እያሳወቅን ሪፖርት ካርድ ባለመውሰዳችሁ  ከምዝገባ ጋር ለሚፈጠር ማንኛውም ችግር ኃላፊነቱን ወላጅ የሚወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።                             ት/ቤቱ

ዒድ ሙባረክ! ለእስልምና እምነት ተከታይ ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው ታላቁ የኢድ አል አድሃ(አረፋ) በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ! በዓሉ የሠላምና የፍቅር እንዲሆንላችሁ እንመኛለኝ :: ዶን ቦስኮ ካቶሊክ ት/ቤት

07/09/2018 ዓ.ም ለተከበራችሁ የዶን ቦስኮ ካቶሊክ አንደኛና መካከለኛ ት/ቤት የ 6ኛና8ኛ ክፍል ተማሪዎች / ወላጆች / አሳዳጊዎች በሙሉ 📖የ6ኛና8ኛክፍል ከተማ አቀፍ የሞዴል ፈተና የቀን ለውጥ ተደርጎበታል፡፡ 👉🏻ከግንቦት 12-14/2018 ባሉት ቀናት የሚሰጥ በመሆኑ ተማሪዎች ዝግጅት እንዲያደርጉ ድጋፍ እንድታ ደረጉ ለማሳወቅ እንወዳለን:: ት/ቤቱ

ለዶን ቦስኮ ካቶሊክ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ወላጆች እንደሚታወቀው የ3ኛው ሩብ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና ረቡዕ እስከ አርብ (ከ07- 09/ 08/ 2018 ዓ.ም ) ድረስ እንደሚሰጥ  ለወላጆች በላክነው ኘሮግራም ላይ መግለፃችን ይታወቃል። ስለዚህ ተማሪዎች ከበዓል ጋር ተያይዞ መዘናጋት እንዳይፈጠርና  ጥናታቸው ላይ እንዲያተኩሩ  እገዛና ክትትል ታደርጉላቸው ዘንድ ከወዲሁ ለማሳሰብ እንወዳለን:: * ነገ ማክሰኞ 06/08/2018 ዓ.ም የሙሉ ቀን ትምህርት ይቀጥላል:: ት/ቤቱ

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው አደረሳችሁ!!! ለክርስትና እምነት ተከታይ ተማሪዎቻችንና ወላጆች  እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!! በዓሉ የሰላም የፍቅር የመተሳሰብ እንዲሆንልን እንመኛለን።   መልካም  በዓል!!

ት/ቤታችን ይህንን አመርቂ ውጤት እንዲያስመዘግብና የዋንጫ ተሸላሚ እንሆን ያደረጋችሁ ውድ ተማሪዎቻችንና  ሥራውን በኃላፊነት ስትመሩ የነበራችሁ መ/ራን ላደረጋችሁት የላቀ አስተዋፅዖ ከልብ እናመሰግናለን እጅግ በጣም ኮርተንባችኋል ! እንኳን ደስ አላችሁ ! ዶን ቦስኮ  ካቶሊክ ት/ቤት