en
Feedback
መፅሀፍት እና ትረካ

መፅሀፍት እና ትረካ

Open in Telegram

በዚህ ቻናል ውስጥ የተለያዩ አዲስ ና ቆየት ያሉ መፅሐፍቶችን አስገራሚ እውነታዎች እንዲሁም አጫጭር እና ረዣዥም # ግጥሞች # ወጎች # ልብወለድ # አስተማሪ እና አነቃቂ ፅሁፎች ሚያገኙ ይሆናል!

Show more
1 734
Subscribers
No data24 hours
-17 days
+730 days
Posts Archive
"ተነሥቷል እንጂ በዚህ የለም፡፡" ሉቃ. ፳፬፥፭ እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን🙏
"ተነሥቷል እንጂ በዚህ የለም፡፡" ሉቃ. ፳፬፥፭ እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን🙏

📚ርዕስ:-  አዲስ ሕይወት 📝ደራሲ:- ዳግማዊ አሰፋ 📜ይዘት:- እውነተኛ ታሪክ 📅ዓ.ም:-  2009 📖የገፅ ብዛት:- 142 @bookandnarriation

"የእኛ ቢሆን ብላቹ በምትመኙት፣ በምትወዱት፣ ከልባቹ በምትናፍቋቸው ሰዎች ግዴለሽነት፣ ችልተኝነት፣ አለመፈለግ ሲገጥማቹ ቀድሞ ወደ አዕምሯቹ የሚመጣው ምን ይሆን? ለነዛ ሰዎች እንደማትገቧቸው እንደማትመጥኗቸው ወይስ እነዛ ሰዎች እንደማይገቧቹ እንደማይመጥኗቹ? "እራሳችሁን እንደ ሰዎች ፍላጎት ማሟያነት የምታስቡ ከሆነ ወደዳችሁም ጠላችሁም ሚዛናቹ በእነርሱ ተቀባይነት ማግኘት አለማግኘታቹ ነው። እራሳችሁን ለእነርሱ ብቁ ማድረግ ላይ ካተኮራቹ መለኪያቹ የእነርሱ ምላሽና ተቀባይነት ይሆናል። እነርሱ የሚያሰምሩላችሁን መስመር መቀበልና ማለፍ ሲሳናቹ የጀመራችሁትን የእራሳችሁን ትክክለኛ መንገድም ትስታላቹ። የእነርሱን ምላሽ እንደ ማንነታቹ ልኬት መቀበል ትጀምራላቹ። በናተ ደረጃ በናተ ልኬት ያልሆነ አናተን የማይመጥን የትኛውም ነገር አናተ ጋር የሚሆንበት ምክንያት አይኖረውም። ብዙ ጊዜ እናተ በቂ ሳላልሆናቹ ሳይሆን እናተ ከበቂ በላይ ስለሆናቹ መተው ያለባቹ ሁኔታዎች ወይም ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ። ከናተ አንሶ መገኘት፣ ከናተ አለመቻል፣ ከናተ ብቁና ዝግጁ አለመሆን ሳይሆን ከተቀባያቹ ከደረጃ ማነስና ብቁ አለመሆን ያሰባችሁት ነገር ላይሳካ ይችላል። ለራሳቹ ትክክለኛ ታማኝ ወዳጅ፣ ተንከባካቢና አሳቢ እንደሆናቹ ከተሰማቹ ወደ ህይወታቹ የሚገቡትም ሰዎች እንደዛው ይሆናሉ ብላቹ አትጠብቁ። አናተ ታታሪ፣ ጠንካራ፣ ለአላማቹ የምትታገሉ ከሆናቹ በጥቃቅን ጊዜያዊ ተግባር ላይ ጉልበትና ግዜያችሁን የምታጠፉ ከሆነ በእርግጥም የማይመጥናቹ ስፍራ ላይ ተገኝታችኋል ማለት ነው። በህይወታቹ ጥበቃን ተለማመዱ። ትክክለኛውን ጊዜ ጠብቁ። የሚመጥናችሁን ሰውም ሆነ ሁኔታ በትዕግስት ተጠባበቁ። የናተ ለነገሮች ዝግጁ መሆን ብቻ ግንኙነታችሁን ወይም ስራችሁን ውጤታማና ስኬታማ አያደርግም። በምትወዱት ሰው አለመወደድ የናተ ችግር አይደለም። በምትወዱት ስራ ለውጤት አለመብቃት የናተ ክፍተት አይደለም። የምትፈልጉት ቦታ ያልደረሳችሁት ስለማትችሉ አይደለም። አንድም ፍላጎታቹ ከናተ ልኬት በታች ነው ሌላም ጊዜው አሁን ስላልሆነ ነው። የማይወዳችሁን ሰው እንዲወዳቹ የመታገል ግዴታ የለባችሁም። የማይመለከታቹ ስፍራ መገኘት አይኖርባችሁም። በተመጣጣኝ ሁኔታ ለናተ ስሜት ከሌለው ሰው ጋር ጊዜያችሁን የምታባክኑበት ምንም ምክንያት የለም። Benefits of Thinking Positively, and How to Do It Positive thinking isn’t magic አዎንታዊ አስተሳሰብ አስማት አይደለም፤ ችግራችሁን አያጠፋላችሁም። ሆኖም ያለባችሁን ችግር አምናችሁ ተቀብላችሁ ለበጎ ነው ብላችሁ በአዎንታዊ መንገድ እንድትፈቱ ይረዳችኋል እንጂ። How to think positive thoughts አዎንታዊ ሃሳቦችን እንዴት ማሰብ ይቻላል በጥሩ ነገሮች ላይ አተኩሩ አስቸጋሪ ፈታኝ ጊዜያቶች ሲያጋጥማችሁ በተቃራኒው ባላችሁ ጥሩ ነገሮች ላይ አተኩሩ። Focus on the good things በጥሩ ነገሮች ላይ አተኩሩ አስቸጋሪ ፈታኝ ጊዜያቶች ሲያጋጥማችሁ በተቃራኒው ባላችሁ ጥሩ ነገሮች ላይ አተኩሩ። Practice gratitude ምስጋናን ተለማመዱ አመስጋኝ ሁኑ። ከፈጣሪያችሁ ጀምሮ በህይወታችሁ ላሉ ነገሮች ሁሉ አመስጋኝ ሁኑ። በህይወታችሁ ያሉ ሰዎች ለሚሰጧችሁ ፍቅር፣ ድጋፍ፣ ወዳጅነት፣ አክብሮት አመስጋኝ ሁኑ። በለት ተለት ተግባራችሁ ላይ የስራ ሙያዊ ግዴታቸው እንኳን ቢሆን አገልግሎት ለሚሰጧችሁ ሰዎች አመስጋኝ ሁኑ። Open yourself up to humor  ቀልድና ጨዋታን ተቀበሉ ቀልደኛ ተጫዋች ሁኑ። ይሄ ቁምነገር አልባ አያደርጋችሁም። ለሁሉም ጊዜ አለው። ጥናቶች እንደሚያመለክቱት ቀልድ ጨዋታ ጭንቀት ድብርትን ይቀንሳል። Spend time with positive people ከአዎንታዊ ሰዎች ጋር ጊዜ አሳልፉ እራሳችሁን አሉታዊ መጥፎ አመለካከት ካላቸው ሰዎች አርቁ። በህይወታችሁ ያሉ ሰዎች አዎንታዊነት በጨመረ ቁጥር ነገሮችን በቀናነት መመልከት በችግር ውስጥ ብትሆኑም እንኳን የተሻለ ነገር እንዳለ እንድታስቡ አዎንታዊ ኢነርጂ እንዲኖራችሁ ይረዳል:: ሁሌ የሚወቅሱ፣ የሚያማርሩ፣ ስልቹ የሆኑ ሰዎች ይሄን አሉታዊ ኢነርጂያቸውን ያጋቡባችኋል። Start every day on a positive note እያንዳንዱን ቀን በአዎንታዊ መንፈስ ጀምሩ ቀናችሁን አዎንታዊ በሆነ ነገር ጀምሩ። ጥሩ ቀን እንደምታሳልፉ ከማመን ጀምሮ የምትወዱትን የሚያስደስታችሁን ነገሮች በማድረግ። Share and join @bookandnarriation

ጠብታ ማር በዴል ካርኔጌ.pdf7.76 MB

👹👹ጥንቃቄ ❌ቀጥታ አካወንታችሁን ነው የሚጠልፉት ይህን ሊንክ ተጭናቹ እንዳትገቡ ከምታምኑት ሰውም ጭምር ቢላክላችሁ እንዳትነኩት የነዛም ሰዎች አካወንት ተጠልፎባቸው ነው። ⚠️ጥንቃቄ ጥንቃቄ ለሁሉ
+1
👹👹ጥንቃቄ ❌ቀጥታ አካወንታችሁን ነው የሚጠልፉት ይህን ሊንክ ተጭናቹ እንዳትገቡ  ከምታምኑት  ሰውም ጭምር ቢላክላችሁ እንዳትነኩት የነዛም ሰዎች አካወንት ተጠልፎባቸው ነው። ⚠️ጥንቃቄ ጥንቃቄ ለሁሉም ሼር አድርጉት ይህ የነካችሁ ካላችሁ በቀጥታ አካወንታቹ ሀክ ተደርጓል ማለት ነው scam ነው ⚙️ይህን ሁለተኛ ፎቶ ላይ ያለውን setting በማስተካከል የተጠለፈባችሁን አካወንት አስመልሱ። 🗣️Settings -> devices -> በቀይ የተፃፈውን Terminat All Other session  የሚለውን ተጭናቹ  ok በማለት 24  ሰአት ሳይቆይ አስወግዱት 24  ሰአት ከቆይ እናንተን ሙሉ ለሙሉ የማስወገድ ሀይል አለው 🌐ለሁሉም ሼር አድርጉት

የጉለሌው ሰካራም የመጀመሪያው የኢትዮጵያ አጭር ልብወለድ @bookandnarriation Share

📖 የተደበቀው ማስታወሻ 🖋 ዶክተር ገበየሁ ተፈሪ 🖋 ደስአለኝ አለሙ @bookandnarriation

📚ርዕስ : ሌላ ሰው 📝ደራሲ : ዶ/ር ምህረት ደበበ ማዕረግ : ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያገኘ 📖የገፅ ብዛት : 450 የተሟላ ገጽና በጥራት የቀረበ! SHARE and JOIN🙏 @bookandnarriation @bookandnarriation

“ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።” — ሉቃስ 2፥11 🎄🌲ለመላው የቻናላችን የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሀነ ልደቱ በሰላም በጤና አደረ
“ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።” — ሉቃስ 2፥11  🎄🌲ለመላው የቻናላችን  የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሀነ ልደቱ በሰላም በጤና አደረሳቹ አደረሰን🎄 🎄🎄መልካም በዓል 🎄🌲

📔 ከዕለታት ግማሽ ቀን ✍ደራሲ፡- አሌክስ አብርሀም መሉ መፅሐፉን እነሆ ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ @bookandnarriation

Think and grow rich ቀደምት ሥስት የአሜሪካን ፕሬዝዳንቶች የገመገሙት ብቸኛው የአለማችን መጽሐፍ! ደራሲ ፦ ናፖሊዮን ሂል ማጋራት አይዘንጋ 🙏 @bookandnarriation

📚ርዕስ:- ቅበላ 📝ደራሲ:- አለማየሁ ገላጋይ 📜ይዘት:-.. 📖የገፅ ብዛት:- 206 📆ዓ.ም:- 2001   @bookandnarriation

📚ርዕስ - መጽሐፈ አክሲማሮስ 📌ማጋራት አይዘንጋ! @bookandnarriation

Maturity is realising that other people are not mind readers, even those who love you. It’s on you to reach out, talk about how you feel, and to explain yourself. ​Everybody is busy living their own lives and is caught up in their own issues & problems, amidst all that you can’t expect them to magically be in tune with your every need and emotion. Communicate. 📌ማጋራት አይዘንጋ! @bookandnarriation

📚ርዕስ - የመኝታ ቤት ምስጢሮች 📝ደራሲ - እንዳለ ጌታ ከበደ 📌ማጋራት አይዘንጋ! @bookandnarriation

#ሮማን 💞 ፡ #ክፍል_አራት (የመጨረሻው ክፍል) ....<<ለዛሬ የቀጠርኩህ በሲጋራ ማጨስና ጉዳቱ ዙሪያ ለጤናችን ፕሮግራም ካንተ ጋር ቃለ መጠይቅ ለመስራት ስለፈለግኩ ነው›› የመጨረሻዎቹን ቃላት በውል አላዳመጥኳቸውም፡፡ የተቀመጥኩበት ወንበር ወደ ውስጥ ይዞኝ የገባ መስሎኝ ከንፈሬን በጥርሴ እንደነከስኩ አይኖቼን በሀይል ጨፈንኳቸውና በዝምታዬ ውስጥ ራሴን ገደልኩ፡፡ ከተቀበርኩበት ድንገተኛ ሰመመን ስነቃ ሮማን በእጇ የያዘችውን የድምጽ መቅጃ እያሻሸች በድንጋጤ እየተመለከተችኝ ነበር፡፡ ‹‹ ደህና ነህ? ›› አለችኝ፡፡ ጭንቅላቴን በአዎንታ ነቀነቅኩላት፡፡ ከዚያም እጄን ወደኪሴ ሰድጄ የተጨማተረ ሲጋራ መዘዝኩና አቀጣጠልኩ፡፡ ወደ ውስጥ የሳብኩት ጭስ ከአፌ እየወጣ አየር ላይ ተበታትኖ ወዲያና ወዲህ ሲቅበዘበዝ ሳይ እምባዬ መጣ፡፡ 🚬🚬🚬🚬 መድረሻውን የማያውቀው ጭስ የኔ ህይወት ተምሳሌት መሰለኝ፡፡🚬🚬 እንዲያውም ይህ የሲጋራ ጭስ መነሻውን ያውቃል፡፡ እኔ ግን መነሻና መድረሻዬን የማላውቅ፣ ከየት መጥቼ ወዴት እየሄድኩ እንደሆነ ያልተረዳሁ ምስኪን ሠው ነኝ፡፡ ሲጋራውን ጠላሁት፡፡ ጭሱን ማየት ቀፈፈኝ፡፡ መሬት ላይ ጣልኩትና በጫማዬ ደፈጠጥኩት፡፡ ኪሴ ውስጥ የነበረውን ሁሉ እያወጣሁ ስብርብር አደረግኩት፡፡ ነፍሴ ስትረጋጋ ታወቀኝ፡፡ በዛፎቹ መካከል እየተሽሎከለከ እኛ ወዳለንበት ጎጆ ቤት የሚገባው ነፋስ አዲሱን የህይወቴን ገጽ መግለጥ ጀመረ፡፡ ከዚህ በፊት የማላውቀው አዲስ ስሜት ውስጤ ገብቶ ቦታ ሲፈልግ አገኘሁት፡፡ ልቤን ሰጠሁት፡፡ በደስታ ተሞላሁ፡፡ መጮህ አማረኝ፡፡ ሮማን በሁኔታየ ግራ ተጋብታለች፡፡ ከአፏ ቃል ሳታወጣ በጭንቀት እየተነፈሰች የማደርገውንና የምሆነውን ትከታተላለች፡፡ የውስጤን ስሜት ሳዳምጥ ቆይቼ ዝቅ ባለ ድምጽ‹‹ አመሰግናለሁ ›› አልኳት፡፡ ከፀጉሯ ጋር በጣቷ እየተጫወተች በዝምታ ተመለከተችኝ፡፡ ‹‹ ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዬ ጋ አለያዬሽኝ ›› ደነገጠች፡፡ ‹‹ ምን; ›› እንደምንም ከአፏ የወጣ ቃል ነው፡፡ ‹‹ ለረዥም ጊዜ እንደ ፍቅረኛዬ ስንከባከበው ከነበረው ሱስ ጋር ዛሬ አለያየሽኝ›› ከተቀመጠችበት ድንገት ተነስታ ተጠመጠመችብኝ፡፡ ሽቶዋ ልቤን አጠፋው፡፡ ከልቤ ጋር ፍርሃቴም አብሮ ጠፋ፡፡ ለካ የፍርሃት ቤቱ ልብ ነው! እንደተቃቀፍን የመጣው ይምጣ ብዬ ከንፈሯን ፍለጋ ስኳትን ያ- ክልፍልፍ አስተናጋጅ ዘው ብሎ ገባ፡፡ ‹‹ ጠራችሁኝ እንዴ? ›› እያለ፡፡ ❤️ተፈፀመ❤️ ምርጥ ምርጥ ድርሰቶች ሳይቆራረጥ ቶሎ ቶሎ እንዲለቀቅ ወደ @metshafit group አዲስ ሰው #add አድርጉ 😊 ሙሉ ክፍሉን  @bookandnarriation ላይ ያገኙታል

​#ሮማን 💞 ፡ ፡ #ክፍል_ሦስት ፡ ፡ ፈገግ አለች፡፡ ፈገግታዋን ከመብረቁ ብልጭታ ጋር ማወዳደር ጀመርኩ፡፡ በምድር ስትመጣ እንዳላየኋት ሁሉ ከሰማይ የወረደች መሰለኝ፡፡ እኔም ፈገግ አልኩላት፡፡ ጥርሶቼን ግን አልገለጥኳቸውም፡፡ ሁሌም እንዲህ ነኝ፡፡ በዓይኖቼ እንጅ በጥርሶቼ አልስቅም፡፡ በልጅነቴ ህጻናት ማሳደጊያ ውስጥ እያለሁ ጓደኞቼ አይኖቼ እንደሚያምሩ ይነግሩኝ ስለነበር ከጥርሶቼ ይልቅ በአይኖቼ እኮራለሁ፡፡ በርግጥ ያኔ ጥርሶቼ ያምሩ ነበር፡፡ ዛሬ ግን በሲጋራ ጭስ በልዘው አፌን የሲኦል መንገድ አስመስለውታል፡፡ ሮማን እጆቿን ለሰላምታ ዘረጋችልኝ፡፡ ስለኔ ጥርስና ስለእሷ ውበት እያሰብኩ ለሰላምታ የትኛውን እጄን መዘርጋት እንዳለብኝ ጠፋኝ፡፡ ሁለት እጆቼን አነባብሬ ሰጠኃት፡፡ በሚያማምሩ ጣቶቿ የቀኝ እጄን ለቀም አደረገችውና ለአፍታ በአይኖቿ ገላይን ከላይ እስከታች ዳበሰችው፡፡ ዛሬ ያለወትሮዬ ሽክ ብያለሁ፡፡ አለባበሴን እንደወደደችው ከአስተያየቷ ተረዳሁ፡፡ ከጓደኛዬ የተዋስኩትን ጥቁር ሱፍ ጀርባዋ ከተቀደደ ባለነጠብጣብ ሸሚዝ ጋር ለብሻለሁ፡፡ የጨበጠችውን እጄን ሳትለቅ ‹‹ ወደመናፈሻው እንግባ?›› ስትል ጠየቀችኝ፡፡ ስትናገር የምትዘፍን ትመስላለች፡፡ ‹‹ደስ ይለኛል›› አልኳት ሊስም ፈልጎ ያሞጠሞጠ ከንፈሬን ወደ ቦታው እየመለስኩ፡፡ ሰላሳኛ አመቴን እየደፈንኩ ቢሆንም ካሁን በፊት የሴት ጓደኛ ኖሮኝ አያውቅም፡፡ ፍቅሬን ለሲጋራ እንጂ ለሴት የሰጠሁበት ጊዜ አልነበረም፡፡ የወንድ ጓደኞቼ በየጊዜው ፍቅረኛዬ ናት እያሉ የተለያዩ ሴቶቻቸውን ያስተዋውቁኝና ‹‹ያንተን ፍቅረኛ ግን ለምን አታስተዋውቀንም?›› ይሉኛል፡፡ ‹‹የለኝም›› ስላቸው አያምኑኝም፡፡ ‹‹እንዴት ላይኖርህ ይችላል አንተኮ ለሴት እንጂ ለወንድ የማይገባውን ውበት ይዘሃል፡፡ መልከ መልካም ነህ፡፡ በዚያ ላይ ገንዘብ ባይኖርህ እንኳ አሪፍ ጭንቅላት አለህ፡፡ ታዲያ እንዴት ፍቅረኛ የለኝም ትላለህ?›› ይሉኛል፡፡ ዝም እላቸዋለሁ፡፡ እነሱን ለማስረዳት ከምሞክር ከአዲስ አበባ ባህርዳር በእግሬ ብጓዝ እመርጣለሁ፡፡ ፈፅሞ ሊያምኑኝ አይችሉም፡፡ እኔና እግዚአብሔር በምናውቀው ሃቅ ግን እኔ እንኳን ሴት ፍቅረኛ ሴት እህት የለኝም፡፡ ብዙ ጊዜ ቆንጆ ሴቶችን ሳይ ቀድሞ ጉልበቴ ይዝላል፡፡ ላብ በጀርባዬና በግንባሬ ይፈሳል፡፡ ያደኩት ህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ከወንዶች ጋር ስለነበር ሴቶች ባሉበት ቦታ መገኘት ያስፈራኛል፡፡ ሴቶችን እንዴት ማናገር እንዳለብኝ እንኳን ጠንቅቄ አላውቅም፡፡ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ እያለሁ ጓደኞቼ ከሴቶች ጋር ‹በግተራ› ሲያመሹ እኔ ቤተመፅሐፍት ውስጥ ተቀብሬ ምሽቱን አሳልፍ እንደነበር አልዘነጋውም፡፡ አንዳንዴ ፍቅረኛ የሚኖረኝ መቼ ነው ስል እራሴን እጠይቅና አንድ ቀን በሚል መልስ እዘጋዋለሁ፡፡ እንዳልኩትም ያ - አንድ ቀን ከረጅም አመታት በኋላ ዛሬ ከተፍ አለ፡፡ ቀስ በቀስ ፍርሃቴ እየጠፋ መጥቷል፡፡ ‹‹አዎን ከዚያው መምጣቴ ነው›› አለች አረማመዷን ከኔ ፍጥነት ጋር ለማስተካከል እየሞከረች፡፡ ዝናቡ ማንጠባጠብ ጀምሯል፡፡ መናፈሻ ውስጥ ካሉት ትንንሽ ጎጆ ቤቶች መካከል አንዱን መርጠን ገባን፡፡ ወዲያው የሆነ ክልፍልፍ አስተናጋጅ እየተንደረደረ መጥቶ የምንፈልገውን ጠየቀን፡፡ ፈጥኖ መምጣቱ አበሳጭቶኛል፡፡ ‹‹ቡና!›› አልኩት በቁጣ፡፡ የኔን ትዕዛዝ ተቀብሎ በመጣበት አኳኋን እየተክለፈለፈ ተመልሶ ሄደ፡፡ ሳቄ መጣ፡፡ ከጥድፊያው የተነሳ እሷን ሳይታዘዛት ነው የሄደው፡፡ እጄን ላጨበጭብ ስዘጋጅ ሮማን ድንገተኛ ወሬ ጀመረች፡፡ ‹‹ያው ለዛሬ የቀጠርኩህ.....›› ከማለቷ አስተናጋጁ ተመልሶ መጣ፡፡ ‹‹ለእርስዎስ ምን ላምጣልዎት እመቤቴ?›› ሲል ጠየቃት እየተቅለሰለሰ፡፡ ‹እርስዎ› ስላላት ይሁን ወይም ንግግሯን ስላቋረጣት እንጃ ቆጣ ብላ ‹‹ለኔም ቡና!›› አለችው፡፡ እየሮጠ ወጣ፡፡ ሲሮጥ ድንጋይ አደናቅፎት ሊወድቅ ነበረ፡፡ እንደሰካራም ተንገዳግዶ ለጥቂት ተረፈ፡፡ እሱ እንደወጣ ሮማን ንግግሯን ቀጠለች፡፡ ‹‹ምን መሰለህ? ለዛሬ የቀጠርኩህ...እ...›› ጭኗ ላይ ያስቀመጠችውን ቦርሳ መደባበስ ያዘች፡፡ ልቤ በድንጋጤ መምታት ጀምሯል፡፡ አፈቅርሃለው የምትለዋን ቃል ለመስማት መቁነጥነጥ ያዝኩ፡፡ ግን ምንድነው የምመልስላት? እኔም አፈቅርሻለሁ ልበላት? ይሄ እንኳን አይሆንም፡፡ ገና በአንድ ቀን እንደዛ ብላት ትንቀኛለች፡፡ በቃ ላስብበት እላታለሁ፡፡ ወይኔ ጉዴ! ምንድነው የሚያቃዠኝ? እኔ በሃሳብ ስዳክር ሮማን ጉሮሮዋን አፅድታ የጀመረችውን ንግግር ጨረሰችው፡፡ ‹‹ያው ለዛሬ የቀጠርኩህ..... 💞ይቀጥላል💞 ቶሎ ቶሎ እንዲለቀቅ ወደ @metshafit group አዲስ ሰው #add አድርጉ ከዛም ክፍል አራት ይቀጥላል ሙሉ ክፍሉን  @bookandnarriation ላይ ያገኙታል