en
Feedback
እስልምና እና ክርስትና

እስልምና እና ክርስትና

Open in Telegram

t.me//AkeelComparative የእስልምና እና የክርስትና ሐይማኖት ንፅፅሮችን በጥልቀት ይዳስሳል። ቻናሉን #join ሌሎችንም #add ያድርጉ!!

Show more
315
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
. እየሱስን ማምለክ #ከመጽሐፍ #ቅዱስ እና #ከቁርዓን ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። እየሱስ አምላክ ነው ብሎ እየሱስን የማምለክ ምሳሌውም #የሸረሪት ቤት እንደሠራ ሰው ምሳሌ ነው። ይላል #bible & #Quran 29፡ 41 مثل الذين اتخذوا من دون الله أولياء كمثل العنكبوت اتخذت بيتا ۖ وإن أوهن البيوت لبيت العنكبوت ۖ لو كانوا يعلمون <<የእነዚያ ከአላህ ሌላ ረዳቶችን (ጣዖታትን) የያዙ ሰዎች ምሳሌ ቤትን እንደ ሠራች #ሸረሪት ብጤ ነው፡፡ ከቤቶችም ሁሉ በጣም ደካማው #የሸረሪት #ቤት #ነው፡፡ ቢያውቁ ኖሮ (አማልክት አድርገው አይግገዟቸውም ነበር)፡፡ >> ፡ 42 إن الله يعلم ما يدعون من دونه من شيء ۚ وهو العزيز الحكيم <<አላህ ያንን ከእርሱ ሌላ የሚግገዙትን ማንኛውንም ያውቃል፡፡ እርሱም አሸናፊው ጥበበኛው ነው፡፡>> - መጽሐፈ ኢዮብ ምዕ. 8 13፤ እግዚአብሔርን የሚረሱ ሁሉ ፍጻሜአቸው እንዲሁ ነው፤ የዝንጉም ሰው ተስፋ ይጠፋል። 14፤ ተስፋው ይቈረጣል፥ እምነቱም እንደ #ሸረሪት #ቤት ይሆናል። 15፤ ቤቱን ይደግፈዋል፥ አይቆምለትም፤ ይይዘውማል፥ አይጸናለትም። - መጽሐፈ ኢዮብ ምዕ. 27 18፤ የሚሠራው ቤት እንደ #ሸረሪት #ድር ይሠራል፥ ጠባቂም እንደሚሠራው ጎጆ ነው። 19፤ ባለጠጋ ሆኖ ይተኛል፥ ዳግመኛም አይተኛም፤ ዓይኑን ይከፍታል፥ እርሱም የለም። 20፤ ድንጋጤ እንደ ጐርፍ ታገኘዋለች፤ በሌሊትም ዐውሎ ነፋስ ትነጥቀዋለች። @AkeelComparative ✔ እየሱስ ጌታ አትበሉኝ ጌታ አይደለሁም ጌታ የሚለኝ ሰው ምሳሌውም እንደዚሁ ቤት እንደሰራ ሰው ምሳሌ ነው ይላሉ፦ - የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 7 21፤ በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ #ጌታሆይ፥ #ጌታሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት #የሚገባ #አይደለም። 22፤ በዚያ ቀን ብዙዎች። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል። 23፤ የዚያን ጊዜም <ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ>። 24፤ ስለዚህ #ይህን #ቃሌን ሰምቶ #የሚያደርገው ሁሉ #ቤቱን #በዓለት ላይ የሠራ ልባም ሰውን ይመስላል። 25፤ ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት ገፋው፥ በዓለት ላይም ስለ ተመሠረተ #አልወደቀም። 26፤ ይህንም ቃሌን ሰምቶ #የማያደርገው ሰው ሁሉ ቤቱን #በአሸዋ ላይ የሠራ #ሰነፍ ሰውን ይመስላል። 27፤ ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት መታው፥ ወደቀም፥ #አወዳደቁም #ታላቅ #ሆነ። 3፡49 ورسولا إلى بني إسرائيل أني قد جئتكم بآية من ربكم ۖ أني أخلق لكم من الطين كهيئة الطير فأنفخ فيه فيكون طيرا بإذن الله ۖ وأبرئ الأكمه والأبرص وأحيي الموتى بإذن الله ۖ وأنبئكم بما تأكلون وما تدخرون في بيوتكم ۚ إن في ذلك لآية لكم إن كنتم مؤمنين << ወደ እስራኤልም ልጆች መልክተኛ ያደርገዋል፡፡ (ይላልም)፡- «እኔ ከጌታዬ ዘንድ በተዓምር ወደ እናንተ መጣሁ፡፡ እኔ ለናንተ ከጭቃ እንደ ወፍ ቅርፅ እፈጥራለሁ፡፡ በርሱም እተነፍስበታለሁ፡፡ በአላህም ፈቃድ ወፍ ይኾናል፡፡ በአላህም ፈቃድ ዕውር ኾኖ የተወለደን፣ ለምጸኛንም አድናለሁ፡፡ ሙታንንም አስነሳለሁ፡፡ የምትበሉትንና በቤታችሁ የምታደልቡትንም ሁሉ እነግራችኋለሁ፡፡ የምታምኑ እንደኾናችሁ ለእናንተ በዚህ ውስጥ በእርግጥ ተዓምር አለበት፡፡»> 3፡ 51 إن الله ربي وربكم فاعبدوه ۗ هذا صراط مستقيم «አላህ ጌታዬና ጌታችሁ ነው፤ ስለዚህ ተገዙት፤ ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» (አላቸው)፡፡ ለበለጠ መረጃ ግሩፓችንን ይቀላቀሉ ሌሎችንም add ያድርጉ!! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 t.me//AkeelComparative

. #ኢየሱስ ከተሰቀለ እርሱ #የሞተው #ለሕዝብ #ሐጢአት ነውን!? ▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷ መቼም እየሱስ እንዳልተሰቀሉና እንዳልሞቱ ግልፅ ቢሆንም እንደ የክርስትና እምነት ተከታዮች አስተሳሰብ ከሆነ ግን እየሱስ የሞተው እኛ ከአዳም በወረስነው የውርስ ሐጢአት ምክንያትም እኛን ለማዳን ስጋ ለብሶ በመገለጥ የእኛን ሐጢአት ለማስተሰረይ ሲል ተሰቅሏል በማለት ይናገራሉ። ለመሆኑ ግን እየሱስ ለሰው ልጅ ሐጢአት ስል እሰቀላለሁ ብሏልን!? እግዚአብሔርስ የሰው ልጆች የሚድኑት በእየሱስ ስቅለት ነው ብሏልን!? ማናቸውም ይህንን አልተናገሩም። ሆኖም ግን እየሱስ እነንዲሰቀል የወሠነው አንድ #ቀያፋ የተባለ ንጉስ ነው። ለዚህም፦ - የዮሐንስ ወንጌል ምዕ. 11 49፤ በዚያችም ዓመት ሊቀ ካህናት የነበረ #ቀያፋ የሚሉት ከእነርሱ አንዱ። እናንተ ምንም አታውቁም፤ 50፤ #ሕዝቡም #ሁሉ #ከሚጠፋ #አንድ #ሰው #ስለ #ሕዝቡ #ይሞት #ዘንድ #እንዲሻለን #አታስቡም አላቸው። - የዮሐንስ ወንጌል ምዕ. 18 13፤ አስቀድመውም ወደ ሐና ወሰዱት፤ በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት ለነበረው ለቀያፋ አማቱ ነበርና። 14፤ #ቀያፋም። #አንድ #ሰው #ስለ #ሕዝብ #ይሞት #ዘንድ #ይሻላል #ብሎ #ለአይሁድ #የመከራቸው #ነበረ ። ይህን ይመስላል እንግዲህ እውነቱ!! የሐጢአት ውርስ ብሎ ነገር የለም። ምክንያቱም፦ - ትንቢተ ሕዝቅኤል ምዕ. 18 19፤ እናንተ ግን። #ልጅ #የአባቱን #ኃጢአት ስለ ምን አይሸከምም? ትላላችሁ። ልጅ ፍርድንና ቅን ነገርን ባደረገ ትእዛዜንም ሁሉ በጠበቀና ባደረገ ጊዜ ፈጽሞ በሕይወት ይኖራል። 20፤ ኃጢአትን የምትሠራ ነፍስ እርስዋ ትሞታለች፤ #ልጅ #የአባቱን #ኃጢአት #አይሸከምም፥ #አባትም #የልጁን #ኃጢአት #አይሸከምም፤ የጻድቁ ጽድቅ በራሱ ላይ ይሆናል፥ የኃጢአተኛውም ኃጢአት በራሱ ላይ ይሆናል። 21፤ ኃጢአተኛውም ካደረጋት ኃጢአት ሁሉ ቢመለስ ትእዛዜንም ሁሉ ቢጠብቅ ፍርድንና ቅን ነገርንም ቢያደርግ ፈጽሞ በሕይወት ይኖራል እንጂ አይሞትም። 22፤ የበደለው በደል ሁሉ አይታሰብበትም፤ በሠራው ጽድቅ በሕይወት ይኖራል። 23፤ በውኑ ኃጢአተኛ ይሞት ዘንድ እፈቅዳለሁን? ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ከመንገዱስ ይመለስና በሕይወት ይኖር ዘንድ አይደለምን? . አይሁዶች እየሱስን ሰቀልነው ይበሉ እንጂ አልተሰቀሉም አልተገደሉም፦ 4፡ 157 وقولهم إنا قتلنا المسيح عيسى ابن مريم رسول الله وما قتلوه وما صلبوه ولكن شبه لهم ۚ وإن الذين اختلفوا فيه لفي شك منه ۚ ما لهم به من علم إلا اتباع الظن ۚ وما قتلوه يقينا «እኛ የአላህን መልክተኛ የመርየምን ልጅ አልመሲሕ ዒሳን ገደልን» በማለታቸውም (ረገምናቸው)፡፡ አልገደሉትም አልሰቀሉትምም፡፡ ግን ለእነሱ (የተገደለው ሰው በዒሳ) ተመሰለ፡፡ እነዚያም በእርሱ ነገር የተለያዩት ከእርሱ (መገደል) በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡ ጥርጣሬን ከመከተል በስተቀር በእርሱ ነገር ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ በእርግጥም አልገደሉትም፡፡>> እንደ መፅሐፍ ቅዱስ ገለፃ ከሆነ በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው። (ኦሪት ዘዳግም ምዕ. 21) ---------- 22፤ ማንም ሰው ለሞት የሚያበቃውን ኃጢአት ቢሠራ፥ እንዲሞትም ቢፈረድበት፥ በእንጨትም ላይ ብትሰቅለው፥ 23፤ በእንጨት ላይ የተሰቀለ በእግዚአብሔር ዘንድ የተረገመ ነውና ሬሳው በእንጨት ላይ አይደር፤ ነገር ግን አምላክህ እግዚአብሔር ርስት አድርጎ የሰጠህን ምድር እንዳታረክስ በእርግጥ በዚያው ቀን ቅበረው። ታድያ እየሱስ የተረገመ ነውን!??? t.me//AkeelComparative

. አምሳያ የሌለው ጌታ [[ Bible @ Quran ]] 📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚 እስቲ ይህንን የቁርዓን ምዕራፍ (ሱረቱል ኢህላስን) በተመለከተ #ከbible ጋር እያስተነተንን እንመልከተው፦ 112፡ 1 { قل هو الله أحد በል << እርሱ አላህ አንድ ነው። #bible ✔ ትንቢተ ሚልኪያስ 2፥10 " ፈጣሪ አምላካችን አንድ ነው።" ✔ 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ 8፥6 " እግዚአብሔር (አብ) አንድ አምላክ ነው።" ✔ ትንቢተ ኢሳያስ 45፥ 5-6 " እኔ እግዚአብሄር ነኝ ከእኔም ሌላ ማንም የለም፤ ከእኔም በቀር አምላክ የለም። ✔ ትንቢተ ኢሳያስ 45፥21 " እኔ እግዚአብሔር ነኝ ከእኔም በቀር ሌላ አምላክ የለም እኔ ፃድቅ አምላክ ነኝ፥ ከእኔም በቀር ማንም የለም። t.me//AkeelComparative 112፡ 2 ٱلله ٱلصمد << አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው። #bible ✔ መዝሙረ ዳዊት 18፥2 " እግዚአብሔር አምላኬ መድሀኒቴ የምተማመንበት ረዳቴ #መጠጊያዬም ነው።" ✔ መዝሙረ ዳዊት 33፥ 20 " እግዚአብሔር ረዳታችንና #መጠጊያችን ነው።" t.me//AkeelComparative 112፡3 لم يلد ولم يولد << አልወለደም ፤ አልተወለደምም። #bible እየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ አይደለሁም ይላሉ፦ ✔ የማቴዎስ ወንጌል 22፥ 41-45 " ፈሪሳውያንም ተሰብስበው ሳሉ፥ እየሱስ። ስለክርስቶስ ምን ይመስላችኋል? የማንስ ልጅ ነው? ብሎ ጠየቃቸው። የዳዊት ልጅ ነው አሉት። እርሱም እንኪያስ ዳዊት ጌታ ጌታዬ ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው ሲል እንዴት በመንፈስ ጌታ ብሎ ይጠራዋል!? ዳዊትስ ጌታ ብሎ ከጠራው እንዴት ልጁ ይሆናል? አላቸው።" t.me//AkeelComparative 112፡ 4 ولم يكن له كفوا آحد . } << ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም።>> ✔ መፅሐፈ ነገስት ቀዳማዊ 8፥23 " በሰማይ በታችም በላይ አንተን የሚመስል አምላክ የለም።" ✔ ኦሪት ዘፀአት 8፥10 " አምላካችን እግዚአብሔርን የሚመስል የለም።" ✔ መፅሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 6፥14 " በሰማይ ወይም በምድር አንተን የሚመስል አምላክ የለም።" @@@@@@@///@@@@@@@@ ለተጨማሪ የንፅፅር መረጃዎች ግሩፓችንን #join #add & #share ያድርጉ t.me//AkeelComparative

. ጳውሎስ ለአምላክ የማይታዘዝና ለፍጡራን የሚገዛ እርሱም ጣኦት አምላኪ ሰው መሆኑን ።።።።።።።።።።።። ///።።።።።።።።።።።።። ጳውሎስ ለሰይጣንና ለመላዕክት የሚታዘዝ ለእነርሱም የሚገዛ፤ እንዲሁም ለመላዕክት የሚሰግድና ለሠይጣን የሚሰዋ በአጠቃላይ እውነተኛውን የአምላክ ሀይማኖት በመተው መጤ እምነትን የሚከተል እንዲሁም የአምልኮ ተግባራትን ለፍጡራን የሚያደርግ ጣኦት አምላኪ ሠው ነበር። ለዚህም ጳውሎስ ስለራሱ የአምልኮ ሁኔታ ሲናገር እንዲህ ይላል፦ - የሐዋርያት ስራ 24፥ 14 " ነገር ግን ይህን እመሠክራለሁ። በህጉ ያለውንና በነብያትም የተነገረውን ሁሉ አምኜ የአባቶቼን አምላክ እነርሱ ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ።" ጳውሎስ የሚያመልከው የአምልኮ አይነት ይህን ይመስላል። ታድያ ጳውሎስ " የአባቶቼን አምላክ እነርሱ ኑፋቄ ብለው በሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ" ይላልና ለመሆኑ ኑፋቄ ማለት ምን ማለት ነው? በዚህ መንገድ ማምለክ ሲባልስ እንዴትና በምን አይነት መንገድ ማምለክ ማለት ነው? 🧌 ኑፋቄ ምንድ ነው? ኑፋቄ ማለት ጥሬ ቃሉ ወይም ፍቺው መንፈቅ ፣ መክፈል፣ መግመስ፣ መቅደድ... ማለት ነው። ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ ማምለክ የማለት ትርጉሙም፦ የአንድን ነገር እውነት ላይ ቀዳዳ በማበጀትና የሀሰት ፈጠራዎችን በመፍጠር እንዲሁም እውነተኛውን ሀሳብ ላይ የራስ ፈጠራዎችን በማካተት እውነተኛውን ሀሳብ ከእውነታው እንዲርቅ የሚያደርግ የአምልዕኮ ተግባር ነው። በሌላ አባባል በዚህ በኑፋቄ መንገድ ማምለክ ማለት እውነተኛውን አምላክ በመካድ የሚያጠፋ የሆነን ጣኦት ማምለክ ማለት ሲሆን ይህም ደግሞ እውነተኛውን ሀይማኖት በመተው አዲስና መጤ እምነትን መከተል ማለት ነው። ለዚህም ደግሞ፦ - 2ኛው የጴጥሮስ መልዕክት 2፥ 1 - 15 "... ነገር ግን ሀሰተኞች ነቢያት ደግሞ በህዝቡ መካከል ነበሩ እኝዲሁም በመካከላቸው ደግሞ ሀሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ። እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳን ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው እየሳቡ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ። ብዙዎች በመዳራታቸው ይከተሏቸዋል፥ በእነርሱም ጠንቅ የእውነት መንገድ ይሰደባል።... ቅንን መንገድ ትተው ተሳሳቱ።" ይላል!! ስለዚህ የኑፋቄ ትርጉምና ኑፋቄ በሚሉት መንገድ ማምለክ ማለት ትርጉማቸው ይህ ከሆነ ለመሆኑ በኑፋቄአውያን የሚሰደበው የእውነት መንገድ የትኛው ነው? የሚዋጅ ጌታስ ማነው? 170 መሊከል ሙሉክና ብቸኛ ተመላኪ የሆነው ሀያሉ ጌታችን በቅዱስ ቃሉ ሲናገር እንዲህ ይላል፦ 3 ፥ 83- 85 << በሰማያትና በምድር ያሉ በውድም በግድም ለርሱ <የታዘዙ> ወደ እርሱም የሚመለሱ ሲሆኑ ከሀዲዎች ከአላህ ሀይማኖት ሌላን ይፈልጋሉ።... ከኢስላም ሌላ ሀይማኖትን የሚፈልግ ሰው ከርሱ ፈፅሞ ተቀባይ የለውም። እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው።>> -> የታዘዙ ፦ ማለት < اسلم > / < አስለም> ሲሆን < مسلم > / < ሙስሊም> ከሚለው ስርወ ግንድ የተገኘ ቃል ነው። ስለዚህ ኢስላም ማለት በኑፋቄአውያን የሚሰደበው የእውነተኛው መንገድ ወይም ሀይማኖት ሲሆን ሙስሊም ማለት ደግሞ ለአምላኩ የሚታዘዝ ፣ የታዘዘውን የሚፈፅም (የአምልዕኮ ክንውኖችን ለአምላኩ የሚያደርግ ( የሚሰግድ፣ የሚፆም፣...) ነው። ታድያ ጳውሎስ ለማን ነው የሚታዘዘው? ለማነው የሚሰግደው? በመጀመሪያ ደረጃ ስግደት ማለት ምን ማለት ነው? ስግደት ፦ ማለት ለአንድ አካል መስገድ ማጎብደድ፣ ማምለክ፣ መታዘዝ.. ማለት ሲሆን ስግደት በሁለት ይከፈላል፦ እነርሱም የአምልኮ ስግደት እና የአክብሮት ስግደት ናቸው። 1) የአምልኮ ስግደት፦ ይህ ስግደት ለፈጣሪ አምላክ በብቸኝነት መስገድ ፤ የአምልኮ ክንውኖችን ለአንድ ፈጣሪ ማድረግ ማለት ነው። - ኦሪት ዘዳግም 10 ፥ 12-13 " እግዚአብሔር አምላክህን በፍፁም እውነት በፍፁም ልብህ አምልክ።" 41 ፥ 37 << አላህን በብቸኝነት ተገዙት ፥ ለእርሱም ብቻ ስገዱ። >> 2) የአክብሮት ስግደት፦ ይህ ስግደት ከአምላክ ውጪ ላሉት ለባዕድ ነገሮች (ለጣኦታት) መስገድ ፣ ማምለክ... ማለት ነው። ጣኦት ማለት ምን ማለት ነው? ከአንድ ፈጣሪ አምላክ ውጪ ሌላ የሚመለክና የሚሰገድለት ማንኛውንም አካል ካለ እርሱ ጣኦት ይባላል። ለዚህም 29 ፥ 17 << ከአላህ ሌላ የምትግገዙት ጣኦት ብቻ ነው። ውሸትንም ትቀጣጥፋላችሁ...። >> ጣኦት በሁለት ይከፈላል፦ አስናም እና አውሳን በመባል። - አስናም ማለት ከእንጨት ፣ ከወርቅ፣ ከብር ፣ ከነሀስ የተቀረፁትን የሚያመልክ ማለት ነው። - ትንቢተ ዳንኤል 5፥ 4 & 5፥23 " የወይን ጠጅም እየጠጡ ከወርቅ፣ ከብር፣ ከነሀስና ከእንጨት የተቀረፁትን ጣኦታት አመሠገኑ።" #ከቁርዓን ደግሞ 6፥74 መመልከት - አውሳን ማለት ደግሞ ፦ ከድንጋይ የተቀረፁትን የሚያመልክ ማለት ነው። - ኦሪት ዘሌዋውያን 26፥ 1 " እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝ፥ ለእናንተ ጣኦት አታድርጉ፥ የተቀረፀ ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ፥ ትሰግዱለትም ዘንድ ምድራችሁ ላይ ከድንጋይ የተቀረፀ አታኑሩ።" #ከቁርዓን ደግሞ 29፥17ን ማየት ታድያ ጳውሎስ እንዴትና በምን መልኩ ነው ጣኦት አምላኪ ሰው ነው ሊባል የቻለው?? 〰〰〰〰〰〰〰///〰〰〰〰〰〰 ይቀጥላል፦ t.me//AkeelComparative

. የክርስትና ሀይማኖት የእምነቱ መመሪያ የክርስትና ሀይማኖት መመሪያ መፅሐፍት በጣም በርካታ ቢሆኑም ከእነዚህም መፅሐፍት መካከልም በዋነኛነት ቅዱስና አምላካዊ ቃል ነው ተብሎ የሚታመንበት የእምነቱ መመሪያ መፅሐፍም ደግሞ በብዙዎች ዘንድ መፅሐፍ ቅዱስ እንደሆነም ይታመናል። ነገር ግን የትኛው መፅሐፍ ቅዱስ? መፅሐፍ ቅዱስ ✅ መፅሐፍ ቅዱስ በይዘት ረገድ ሠፊ ልዩነት ያላቸው ብዙ መፅሐፍ ቅዱሶች ይገኛሉ። ✅ መፅሀፍ ቅዱስ ከእትም እትም ይለያያል። ለምሳሌ፦ - የለንደን እትም - የሮማ እትሞች - የቤይሩት እትሞችና ሌሎችም ይገኛሉ። ✅ በአንድ ተመሣሣይ ቋንቋ የሚታተሙ እትሞች እንኳን ብዙ ልዩነቶች አሏቸው። ለምሳሌ፦ - ፕሮቴስታንቶች በባለ 39 መፅሐፍ ብሉይ ኪዳን ያምናሉ። - ኦርቶዶክሶች በብሉይ ኪዳን 46 + 35 በአዲስ ኪዳን በድምሩ 81 ምዕራፎች ያሉት መፅሐፍ ቅዱስ ያምናሉ። - ካቶሊኮች በፕሮቴስታንቶቹ ላይ ተጨማሪ 7 ምዕራፎች አሉት - የሠማርያውያን ብሉይ ኪዳን ደግሞ በ39/46 ፈንታ 5 ምዕራፎችን ብቻ ያካትታል። ✅ ከላይ እንደተገለፀው መፅሐፍ ቅዱስ በውስጡ አንድም ቦታ ላይ የመፅሐፉ መጠሪያ የሆነው ስሙ መፅሐፍ ቅዱስ ተብሎ አልተገለፀም። በአንፃሩ ግን የኢየሱስ አስተምህሮት የነበረው የእምነታቸው መመሪያ መፅሐፍ ወንጌል የሚባል የመፅሐፉ ስም ነበረው። - የሉቃስ ወንጌል 4 ፥ 17-20 " ኢየሱስም የጌታ መንፈስ በእኔ ላይ ነው ለድሆችም ወንጌል እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና... አለ። " የክርስትና ሀይማኖት መመሪያ መፅሐፍ የሆነው መፅሐፍ ቅዱስ በውስጡ የስሙን ስያሜ ካለመጠቀሱ አንፃር የእስልምና ሀይማኖት መመሪያ የሆነው ቅዱስ ቁርዓንን የተመለከትን እንደሆነ ቅዱስ ቁርዓን ✅ በቁርዓን ውስጥ የቅዱስ ቁርዓን ስም ከ130 ጊዜ በላይ ተጠቅሷል። ✅ አረብኛ ቋንቋ ሆኖ መውረዱን ተገልጿል። 12፥2 " እኛ ፍቹን ታውቁ ዘንድ አረብኛ ቁርዓን ሲሆን በእርግጥ አወረድነው። " ✅ በጠንካራና በተብራራ አንቀፅ መውረዱን 11፥1 " አሊፍ ላም ራ (ይህ) ቁርዓን አንቀፆቹ በጥንካሬ የተሰካኩ ከዚያም የተዘረዘሩ የሆነ መፅሀፍ ነው። ጥበበኛው ውስጠ አዋቂ ከሆነው ዘንድ (የተወረደ) ነው።" ✅ በአንድ ጊዜ ከሠማይ ተጠቅልሎ ዱብ ያለ ሳይሆን በተለያየ ጊዜ ተከፋፍሎ ተከፋፍሎ ለነብዩ(ሰ.ዓ.ወ) በራእይ የወረደ መሆኑንና ለሠው ልጆችም መገሠጫነት የመጣ ነው። 53፥ 2- 4 " ነብያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም አልጠመመምም፤ ከልብ ወለድም አይናገርም። እርሱ(ንግግሩ) የሚወርድ ራእይ እንጂ ሌላ አይደለም።" 3 ፥ 3 "... ቁርዓንን ባንተ ላይ ከፋፍሎ በእውነት አወረደ። ተውራትንና ኢንጅልም አውርዷል።" 76፥23 " እኛ ቁርዓንን ባንተ ላይ ማውረድን እኛው አወረድነው። " 4፥174 " እናንተ ሰዎች ሆይ ከጌታችሁ ዘንድ በእርግጥ አስረጅ መጣላችሁ፤ ወደ እናንተም ገላጭ የሆነን ብርሃን ( ቁርዓን) አወረድን። " ✅ ሌላው የመፅሐፍ ቅዱስ የስሙን ስያሜ የሠጡትም የእምነቱ ምሁራኖቹ ሲሆኑ በመፅሀፉ የተለያዩ ምዕራፎች ውስጥ የተለያዩ ግለሰቦች ተሳትፎ አድርገውበታል። በተለይም አዲስ ኪዳን ተብሎ በሚጠራው የመፅሐፉ ምዕራፎች ውስጥ የጳውሎስ የስራ ድርሻ እጅግ ከፍተኛ ነው። ።።።።።።።።።።።።።።////።።።።።።።።።።።።። t.me//AkeelComparative

"ታላቅ መመሪያ"Great Commission" የሚባለው ኢየሱስ ለሐዋርያቱ ከማረጉ በፊት የሰጠው መመሪያ ነው፥ የኢየሱስ ሐዋርያ ማቴዎስ ከ 45-50 ድኅረ-ልደት በሚገመት ጊዜ ውስጥ ለዕብራውያን በዕብራውያን ቋንቋ ደብዳቤ ጽፎላቸው ነበር። እዚህ ደብዳቤ ላይ ኢየሱስ እንዲህ በማለት ተናግሮ ነበር፦ "እንግዲህ ሂዱ እና አሕዛብን ሁሉ በስሜ ደቀ መዛሙርት አድርጉ" "Go ye therefore, and make disciples of all nations in my name. πορευθέντες μαθητεύσατε πάντα τὰ ἔθνη ἐν τῷ ὀνόματί μου. ይህ ትውፊት የተገኘው ከቂሳሪያው አውሳቢዎስ ነው። ይህ ለዕብራውያን በዕብራውያን ቋንቋ የተጻፈው ደብዳቤ ሲጠፋ ከ 80-90 ድኅረ ልደት በሚገመት ጊዜ ውስጥ በግሪክ ኮይኔ የማርቆስን ምንጭ መሠረት ያደረገ በማቴዎስ ስም ወንጌል ተዘጋጀ፥ እዚህ ላይ፦ "እንግዲህ ሂዱ እና አሕዛብን ሁሉ በአብ፣ በወልድ እና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው" የሚል ቃል ተፈጠረ። ይህ ቃል የቤተ ክርስቲያን አበው ጀስቲን፣ ኢራኒየስ፣ ቱርቱሊያ፣ ኦሪገን ወዘተ ሲጠቀሙበት፣ ከ 120-150 የጻፈው ማንነቱ በማይታወቀው በዲዳኬ 7፥1 ላይ የተጻፈ እና በኃላ ላይ በግሪክ እደ ክታባት"manuscripts" ላይ የሥላሴ አማንያን ያሰፈሩት ነው፥ "በስሜ" የሚለውን "በአብ፣ በወልድ እና በመንፈስ ቅዱስ ስም" በሚል የተለወጠው ሆን ተብሎ እንደሆነ የካቶሊክ መድብለ-ዕውቀት እንዲህ ያትታል፦ 1. ዓለም ዓቀር መደበኛ የባይብል መድብለ ዕውቀት ቅፅ 4, ገፅ 2637 "ማቴዎስ 28፥9 በኃላ በቤተክርስቲያን ሁኔታ በተለየ ብቻ ቀኖናዊ የሆነ ነው፥ ለዛ ነው ዓለም አቀፋዊነቷ ከቀደምት የክርስቲያን ታሪክ እውነታዎች ጋር የሚቃረን የሆነው። የሥላሴአውያን ቀመር ለኢየሱስ ንግግር ባዕድ ነው"። The International Standard Bible Encyclopedia, Vol. 4, page 2637, "Matthew 28:19 "In particular only canonizes a later ecclesiastical situation, that its universalism is contrary to the facts of early Christian history, and its Trinitarian formula is foreign to the mouth of Jesus." 2. የካቶሊክ መድብለ ዕውቀት ቅፅ 2, ገፅ 263 "የጥምቀት ቀመር "በኢየሱስ ስም" ከሚል ወደ "በአብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ስም" ወደሚል በዓለም ዐቀፍ ቤተክርስቲያን በሁለተኛው ክፍለ ዘመን ተለውጧል"። The Catholic Encyclopedia, II, page 263: "The baptismal formula was changed from the name of Jesus Christ to the words Father, Son, and Holy Spirit by the unversal Church in the second century." 3. ቴንደል የአዲስ ኪዳን ማብራሪያ ቅፅ 1, ገፅ 275 "በአብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ስም" የኢየሱስ ቃል ሳይሆን በኃላ የተጨመረ ቃል ነው"። The Tyndale New Testament Commentaries, I, page 275: "The words in the name of the Father, and of the Son, and of the Holy Ghost are not the exact words of Jesus, but a later liturgical addition." 4. 1989 አዲሱ የተሻሻለ የመደበኛ ባይብል እትም፦ "ዘመናዊ ኂስ ይህንን የሥላሴአውያን ቀመር ኢየሱስን ማስዋሸት ነው፥ ያ በኃላ ላይ የቤተክርስቲያን ትውፊት የሚወክል ነው"። 1989 New Revised Standard Version says this about Matthew 28:19: "Modern critics claim this trinitarian formula is falsely ascribed to Jesus and that it represents later church tradition. ባይብል ላይ ያልተባሉ ነገር ጽፎ ማስገባት እኮ አዲስ ነገር አይደለም፥ እሩቅ ሳንሄድ በቀዳማይ የግሪኩ እደ ክታባት"MSS" ሳይኖር ጄሮም በ 382 ድኅረ ልደት በላቱን ቩልጌት ላይ የሥላሴን ቀመር 1 ዮሐንስ 5፥7 ላይ ጨምሯል፦ 1 ዮሐንስ 5፥7 "በሰማይ የሚመሰክሩ ሦስት አብ፣ ቃል እና መንፈስ ቅዱስ ናቸው። እነዚህ ሦስቱ አንድ ናቸው"። There are Three who give testimony in heaven, the Father, the Word, and the Holy Ghost. And these three are one. quia tres sunt qui testimonium dant in caelo, Pater, Verbum, et Spiritus Sanctus. Et hi tres unum sunt.

፨ ተፍሢሩል ወሢጥ 7፥171 "ሦስት ነው አትበሉ" በተባለው ከተባለው ይልቅ ለምሳሌ፦ "በሦስት አትመኑ" ማለት ነው፥ ምክንያቱም የሦስቱ ጉዳይ የሚሉት አባባል ነው። ትርጉሙም ብትጠይቃቸው "አንዳንድ ጊዜ፦ "አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ" ይላሉ"።  بقوله : ( وَلاَ تَقُولُواْ ثَلاَثَةٌ ) بدل قوله - مثلا - : ولا تؤمنن بثلاثة؛ لأن أمر الثلاثة قول يقولونه ، فإن سألتهم عن معناه قالوا تارة معناه : الآب والإِبن والروح والقدس 

የሰኞ ሰይፈ ሥላሴ ቁጥር 42 "በጽርሐ አርያም ለሚኖር ልዩ ሦስት ለሚሆን አምላክ ሰላምታ ይገባል" የሐሙስ ሰይፈ ሥላሴ ቁጥር 26 "ሦስት ነገሥታት አንድ አገዛዝ ናቸው" የሥላሴአውያን ነገረ መለኮት ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ “እንዚራ ስብሐት” በተባለ መድብሉ ላይ፦ “እንቲ ውእቱ ዕፀት ዘነበርኪ ጥቃ ኀይመት ዘብኪ አጽለሉ ሠለስቱ አጋዕዝት” ትርጉም፦ “በአንቺ ሦስቱ ጌቶች የተጠለሉብሽ በድንኳን አጠገብ የቆምሽ ዕንጨት አንቺ ነሽ” “ሠለስቱ አጋዕዝት” ማለት “ሦስቱ ጌቶች” ማለት ሲሆን አብርሃም ቤት የገቡት ሰዎች ሥላሴ ከማድረግ ባሻገር ሦስት ጌቶች ማድረግ መድብለ-አማልክታዊነት”Polytheism” ነው፥ “አጋዕዝተ ዓለም” ማለት “የዓለም ጌቶች” ማለት ሲሆን “ዓለምን የሚያስተናብሩ ሦስት ጌቶች አሉ” ብሎ ማመን ሥሉሣዊ አምላክ አስተምህሮት”Tritheism” ነው፦ የሐሙስ ሰይፈ ሥላሴ 22-23፦ “ሦስት ልዑላን ገዢዎች፥ ሦስት ጌቶች ናቸው” የአንጾኪያው ኤጲስ ቆጶስ ዲዮናስዮስ ወደ እስክንድርያው ኤጲስ ቆጶስ ወደ ሚናስ በላከው መልእክቱ፦ “አምላክ ሦስት ነው” ብሎ እንቅጩን ፍርጥ አርጎ ተናግሯል፦ ሃይማኖተ አበው ዘዲዮናስዮስ ምዕራፍ 99 “አምላክነስ ሥሉስ እንበለ ተሌልዮ”። ትርጉም፦ “አምላካችን ያለ መለየት ሦስት ነው”። መልክአ ሥላሴ ቁጥር 39 "ሥሉስ ቅዱስ ሆይ! የአደምና የሔዋን "ፈጣሪዎቻቸው" እንደመሆናችሁ" “ዐደድ” عَدَد  ማለት “ቁጥር” ማለት ሲሆን ዐደድ እራሱ በሁለት ይከፈላል። እርሱም "ዐደዱል አስሊያህ" عَدَد اَلْأَصْلِيَّة  ማለትም "መደበኛ ቁጥር"Cardinal number" እና "ዐደዱ አት-ተርቲቢያህ" عَدَد التَرْتِيبِيَّة  ማለትም "ተረኛ ቁጥር"Ordinal number" ናቸው። "አስሊያህ" أَصْلِيَّة  የሚለው ቃል "አስሊይ" أَصْلِيّ  ማለትም "መሠረታዊ" ለሚለው ተባታይ አንስታይ ሆኖ የመጣ ሲሆን "መሠረት" ወይም "መደበኛ" ማለት ነው፥ "ሰላሳህ" ثَلَاثَة  ማለትም "ሦስት" ማለት ሲሆን ዐደዱል አስሊያህ ነው። "ተርቲቢያህ" تَرْتِيبِيَّة‎  የሚለው ቃል "ተርቲቢይ" تَرْتِيبِيّ  ማለትም "ተራዊ" ለሚለው ተባታይ አንስታይ ሆኖ የመጣ ሲሆን "ተራ" ማለት ነው፥ "ሳሊስ" ثَالِث  ማለትም "ሦስተኛ" ማለት ሲሆን ዐደዱ አት-ተርቲቢያህ ነው። ዐደዱ አት-ተርቲቢያህ እና ዐደዱል አስሊያህ አንድ ላይ ሲመጡ "ከሦስቱ አንዱ" ማለት ነው፥ የመጽሐፉ ሰዎች የሆኑትን ዐበይት ክርስቲያኖች ኢየሱስን የላከ አንድ አምላክ አሏህ ሆኖ ሳለ ያንን አንድ አምላክ ከሦስቱ ማንነቶች አንዱ ማንነት ነው" አሉ፦ 5፥73 እነዚያ «አላህ ከሦስቱ አንዱ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡  لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ ثَالِثُ ثَلَاثَةٍ "Certainly they are unbelievers who say: "Allah is one of three". (Farook Malik Translation) "ቃሉ" قَالُوا  ማለት "አሉ" ማለት ነው፥ ቀደም ብለን በባይብል አንድ አምላክ የተባለውን አብን "ከሦስቱ ግጻዌ መለኮት አንዱ ነው" ብለዋል። ከአምላክም አንድ አምላክ እንጅ ሌላ የለም፡፡ ከሚሉትም ነገር ባይከለከሉ ከእነርሱ እነዚያን የካዱትን አሳማሚ ቅጣት በእርግጥ ይነካቸዋል፦ 5፥73 ከአምላክም አንድ አምላክ እንጅ ሌላ የለም፡፡ ከሚሉትም ነገር ባይከለከሉ ከእነርሱ እነዚያን የካዱትን አሳማሚ ቅጣት በእርግጥ ይነካቸዋል፡፡ وَمَا مِنْ إِلَـٰهٍ إِلَّا إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ ۚ وَإِن لَّمْ يَنتَهُوا عَمَّا يَقُولُونَ لَيَمَسَّنَّ الَّذِينَ كَفَرُوا مِنْهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ ተፍሢሩል ቁርጡቢይ 5፥73 የላቀው አሏህ ንግግር፦ "እነዚያ «አላህ ከሦስቱ አንዱ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ" ማለት "ከሦስቱ አንዱ ነው" ማለታቸው ነው። قوله تعالى: { لَّقَدْ كَفَرَ ٱلَّذِينَ قَالُوۤاْ إِنَّ ٱللَّهَ ثَالِثُ ثَلاَثَةٍ }. أي أحد ثلاثة. "መርቁሢያ" مَرقُسِيّة  የሚባሉት በወቅቱ የምሥራቅ "ኡሱዱክሢይ" أُرْثُوذُكْسِيّ  እና የምዕራብ "ካሱሊኪይ" كَاثُولِيكِيّ  ናቸው። እነዚህ መርቁሢያ በአቅኑም ያምናሉ፥ "አቅኑም" أقْنُومْ  ማለትም “ሦስት ማንነነት አንድ ምንነት"hypostasis" ማለት ነው። የመጽሐፉ ሰዎች የሆኑትን ዐበይት ክርስቲያኖች ሦስት የሚሉት አካላት አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ኢብኑ ዐባሥ በተፍሢሩ አስቀምጦታል፦ ተፍሢሩል ኢብኑ ዐባሥ 5፥73 "እነዚያ «አሏህ ከሦስቱ አንዱ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፥ መርቁሢያህ፦ "አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ" አሉ"።   { لَّقَدْ كَفَرَ ٱلَّذِينَ قَالُوۤاْ إِنَّ ٱللَّهَ ثَالِثُ ثَلاَثَةٍ } وهي مقالة المرقوسية يقول أب وابن وروح قدس 4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉም! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ "ኢነማ" إِنَّمَا  ማለት "ብቻ" ማለት ሲሆን በኮይኔ ግሪክ "ሞኖስ" μόνος ነው፥ "አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው" ማለት ሦስትነት የለውም ማለት ነው፥ በተሥሊስ ለምታምኑት ለእናንተ የተሻለ ይህ ነው። "ሦስትም ነው አትበሉ! ተከልከሉ" ብሎ መከልከሉ እራሱ "ሦስት ነው" ማለታቸውን አመላካች ነው፥ እነዚህ ሦስት የተባሉት አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ ናቸው፦ ፨ ተፍሢሩል በገዊይ 7፥171 "ሦስት ነው አትበሉ" ያ "ሦስት ናቸው አትበሉ" ነው፥ ክርስቲያኖች፦ "አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ" ይላሉ"።     (ولا تقولوا ثلاثة ) أي : ولا تقولوا هم ثلاثة ، وكانت النصارى تقول : أب وابن وروح قدس ፨ ተፍሢሩ አት-ተንዊር 7፥171 "ሦስቱ አካላትን የሆኑ ክፍሎችን "አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ" በሚል ሐረግ ይገልጻሉ"። وعبّروا عن مجموع الأقانيم الثلاثة بعبارة ( آبَا ابنَا رُوحا قُدُسا )  ፨ ተፍሢሩል ቁርጡቢይ 4፥171 ክርስቲያኖቹ ከቡድኖቻቸው ጋር በሥላሴ አንድ ሆነው እንዲህ ይላሉ፦ "አሏህ አንድ ኑባሬ ነው፥ ሦስት አካላት አሉት። እያንዳንዱ አካል አምላክ ነው፥ እነርሱ በሕይወት ይኖራሉ። አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ" በሚል ይገለጻሉ"። والنصارى مع فرقهم مجمعون على التثليث ويقولون : إن الله جوهر واحد وله ثلاثة أقانيم ؛ فيجعلون كل أقنوم إلها ويعنون بالأقانيم الوجود والحياة والعلم ، وربما يعبرون عن الأقانيم بالأب والابن وروح القدس

ትክክሉ የቱ ነው? "ይሄድላቸዋል" የሚለው የግሪክ ሰፕቱጀንት ወይስ "ይሄድልናል" የማሶሬቲክ እደ-ክታብ? ሁለቱን ለመዳኘት ከግሪክ ሰፕቱጀንት በፊት የነበረውን የነቢያት ፓሌዎ ዕብራይስጥ ጽሑሮች ጠፍተዋል፥ ግን ከደኃራይ ማሶሬቲክ ይልቅ ቀዳማይ ሰፕቱጀንት ሚዛን ይደፋል። ሙግቱን እናጥብብ እና “ይሄድልናል” ቢባልስ ሥላሴን ያሳያልን? በፍጹም። ምክንያቱን አንድ ማንነት ብዜት ተሳቢ ተውላጠ-ስም ተጠቀመ ማለት ያ ማንነት ሥላሴ ነበር ማለት አይደለም፥ “ኒ” נִי የነበረው ነጠላ ተሳቢ ተውላጠ-ስም በብዜት “ኑ” נוּ በሚል መጥቷል፦ ዕዝራ 4፥7 ”በአርጤክስስ ዘመን ቢሽላም፥ ሚትሪዳጡ፥ ጣብኤል ተባባሪዎቹም ለፋርስ ንጉሥ ለአርጤክስስ ጻፉ”። ዕዝራ 4፥18 ሰላም! *”አሁንም “ወደ እኛ” עֲלֶ֑ינָא የላካችሁት ደብዳቤ በፊቴ ተተርጕሞ ተነበበ”*። ልብ አድርግ “አርጤክስስ” የሚለው ቃላ ላይ መነሻ ቅጥያ ያለው “ለ” የሚለው መስተዋድድ ለንጉሡ ብቻ የተላከ ደብዳቤ ነው። ንጉሡ ግን በዐረማይክ “ና” נָא ብሎ በብዜት ተጠቅሟል፥ ግን ንጉሡ አንድም ሦስትም ሆኖ አይደለም፦ ዳንኤል 2፥25 *የዚያን ጊዜም አርዮክ ዳንኤልን ፈጥኖ ወደ ንጉሡ አስገባውና፦ “ከይሁዳ ምርኮኞች ያለውን ለንጉሡ ፍቺውን የሚያስታውቀውን ሰው አግኝቼአለሁ” አለው*። ዳንኤል 2፥36 ሕልሙ ይህ ነው፥ "”አሁንም ፍቺውን በንጉሡ ፊት እንናገራለን” נֵאמַ֥ר "። “አማር” אֲמַר በሚል ግስ ላይ “ኔ” נֵ የሚል “ባለቤት ተውላጠ-ስም አለ። አርዮክ ወደ ንጉሡ ያስገባው ዳንኤልን ብቻ ሆኖ ሳለ ዳንኤን በብዜት “እንናገራለን” ብሏል፥ ግን ዳንኤል አንድም ሦስትም ሆኖ አይደለም። ሙግቱን አሁንም እናጥብበውና “ይሄድልናል” የሚለው ከአንድ በላይ ላሉ ማንነቶች ነው ነው ብንል እንኳን አሁንም ሥላሴን በፍጹም አያሳይም። ዐውዱ ላይ መላእክት አሉ፥ ኢሳይያስ ሲናገር ከሱራፌልም አንዱ እየበረረ ወደ እርሱ መጥቶ፦ “እነሆ፥ ይህ ከንፈሮችህን ነክቶአል፤ በደልህም ከአንተ ተወገደ፥ ኃጢአትህም ተሰረየልህ” አለው፦ ኢሳይያስ 6፥2 "ሱራፌልም ከእርሱ በላይ ቆመው ነበር”"። ኢሳይያስ 6፥5-7 *”እኔም፦ ከንፈሮቼ የረከሱብኝ ሰው በመሆኔ፥ ከንፈሮቻቸውም በረከሱባቸው ሕዝብ መካከል በመቀመጤ ዓይኖቼ የሠራዊትን ጌታ ንጉሡን እግዚአብሔርን ስለ አዩ ጠፍቻለሁና ወዮልኝ! አልሁ*። ከሱራፌልም አንዱ እየበረረ ወደ እኔ መጣ፥ በእጁም ከመሠዊያው በጕጠት የወሰደው ፍም ነበረ። አፌንም ዳሰሰበትና፦ እነሆ፥ ይህ ከንፈሮችህን ነክቶአል፤ በደልህም ከአንተ ተወገደ፥ ኃጢአትህም ተሰረየልህ፡ አለኝ*። እንደ ባይብሉ እግዚአብሔር የሰማይም ሠራዊት ሁሉ በቀኙና በግራው አሉ፥ ያዕቆብ ከእግዚአብሔር እና ከመልአኩ ጋር ስለተነጋገረ ” ከእኛ ጋር ተነጋገረ” ብሏል፦ 1ኛ ነገሥት 22፥19 ”እግዚአብሔር በዙፋኑ ተቀምጦ፥ የሰማይም ሠራዊት ሁሉ በቀኙና በግራው ቆመው አየሁ"። ሆሴዕ 12፥4 ከመልአኩም ጋር ታግሎ አሸነፈ፤ አልቅሶም ለመነው። በቤቴልም አገኘው፥ "”በዚያም “ከ-እኛ” ጋር עִמָּֽנוּ ተነጋገረ"። አየክ “ኑ” נוּ የሚለው ተሳቢ ተውላጠ-ስም ከመላእክት ጋር እንዳገለገለ? በምንም ሒሳብ ሥላሴን አያመለከትም። በተረፈ አንዱ አምላክ አንድ ማንነት ኖሮት ለግነት እኛነት ሲጠቀም በውስጡ ሦስት አባላት አሉት ብሎ ሌሎችን ማንነቶችን በማንነቱ ላይ ማጋራት ሺርክ ነው። እርሱ አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ እኔም ከምታጋሩት ነገር ንጹሕ ነኝ፦ 6፥19 *«እርሱ አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ እኔም ከምታጋሩት ነገር ንጹሕ ነኝ»* በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَا هُوَ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ وَإِنَّنِى بَرِىٓءٌۭ مِّمَّا تُشْرِكُونَ

“ቅዱስ” ነጠላ ተባዕታይ መደብ ሲሆን የቅዱስ ብዙ ቁጥር “ቅዱሳን” ነው። ከዚህ በተቃራኒ ያሬድ ይወድስዋ ላይ መልአኩ ማርያምን ሦስት ቅዱስ እንዳለና ወልድ “ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ ነው” ይለናል፦ “መልአኩም እንዲህ አላት፦ “መንፈስ ቅዱስ ይጠብቅሻል የልዑል ኃይልም ያድርብሻል፥ *ይህ የሚወለደው ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ ነው*። “ይህ የሚወለደው ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ ነው” የሚለው ኃይለ-ቃል ሉቃስ ላይ አለመኖሩ በራሱ የተጭበረበረ ሐረግ ነው፥ በሦስትነት የሚሠለስ ቅዱስ አምላክ የለም። ዐውዱ በመቀጠል የግሪኩ ሰፕቱጀንት እንዲህ ይላል፦ ኢሳይያስ 6፥8 "የጌታንም ድምፅ፦ ማንን እልካለሁ? ለዚህ ሕዝብ ማንስ ይሄድላቸዋል? ሲል ሰማሁ። እኔም፦ እነሆኝ፥ እኔን ላከኝ” አልሁ”። καὶ ἤκουσα τῆς φωνῆς Κυρίου λέγοντος· τίνα ἀποστείλω, καὶ τίς πορεύσεται πρὸς τὸν λαὸν τοῦτον; καὶ εἶπα· ἰδοὺ ἐγώ εἰμι· ἀπόστειλόν με. “ሰፕቱጀንት” ወይም “ሰፕቱአጀንት”Ἑβδομήκοντα” ማለት “ሰባ” ማለት ሲሆን በ 280 ቅድመ-ልደት በአሌክሳንድያ ይኖሩ የነበሩ ሰባ የግሪክ አይሁዳውያን ምሁራን ስም ነው፥ በሮማውያን ቁጥር ምልክት”LXX” ይባላል። እነዚህ ምሁራን 72 ነበሩ፥ ሁለቱ ሲሞቱ ሰባው ሊቃናት የዕብራይስጡን ቅዱሳን ጽሑፎች ወደ ሄለናዊ ግሪክ ኮይኔ ተርጉመውታል።  እዚህ ትርጉም ላይ ለዚህ ሕዝብ ማንስ ይሄድላቸዋል? የሚል ኃይለ-ቃል አለ። ልብ አድርግ የሚለው “ይሄድላቸዋል” ነው፥ ለማን ሲባል “ለዚህ ሕዝብ” ኢሳይያስም በብዜት “እኔን ላኩኝ” ሳይሆን በነጠላ “እኔን ላከኝ” ብሏል፥ ጌታም፦ “ሂድ፥ ይህን ሕዝብ፦ መስማትን ትሰማላችሁ አታስተውሉምም፤ ማየትንም ታያላችሁ አትመለከቱምም” በላቸው” አለ፦ ኢሳይያስ 6፥9 *”እርሱም፦ ሂድ፥ ይህን ሕዝብ፦ መስማትን ትሰማላችሁ አታስተውሉምም፤ ማየትንም ታያላችሁ አትመለከቱምም” በላቸው”*። ነገር ግን ከግሪክ ሰፕቱጀት 1000 ዓመት በኃላ 875 ድኅረ-ልደት የተዘጋጀው ማሶሬቲክ እደ-ክታብ ላይ በተቃራኒው ማንስ ይሄድልናል? የሚል ኃይለ-ቃል አለ፦ ኢሳይያስ 6፥8 "የጌታንም ድምፅ፦ ማንን እልካለሁ? ይሄድልናል? ሲል ሰማሁ። እኔም፦ እነሆኝ፥ እኔን ላከኝ” አልሁ”። וָאֶשְׁמַ֞ע אֶת־קֹ֤ול אֲדֹנָי֙ אֹמֵ֔ר אֶת־מִ֥י אֶשְׁלַ֖ח וּמִ֣י יֵֽלֶךְ־לָ֑נוּ וָאֹמַ֖ר הִנְנִ֥י שְׁלָחֵֽנִ

አብርሃም ሦስት ጊዜ መጠራቱ አብርሃም ሦስት አካላት ነው ያሰኛልን? መልክአ ኢየሱስ የሚባለው የኦርቶዶክስ መጽሐፍ ላይ ኢየሱስን ሦስት ጊዜ “ኢየሱስ፥ ኢየሱስ፥ ኢየሱስ” ይለዋል፦ *“ኢየሱስ ኢየሱስ፥ ኢየሱስ”* ክርስቶስ ዘሰረጽከ እመቤተ ሌዊ ኮሬባዊ መለኮታዊ ቃል ሰማያዊ እም ድንግል ተወለደ። ኢየሱስ የሚለው ቃል ሦስት ጊዜ መደገሙ ከድንግል የተወለደው ኢየሱስ ሦስት አካላት ነውን? ዘፍጥረት ላይ ደግሞ አብርሃም ሁለቴ ስሙ ተደግሟል፦ ዘፍጥረት 22፥11የእግዚአብሔር መልአክም ከሰማይ ጠራና። *“አብርሃም፥ አብርሃም”* አለው። አብርሃም ሁለት አካል ነውን? ኢየሱስን ሁለት ጊዜ “ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ” ይሉታል፦ ማቴዎስ 7፥21 *“ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ”* የሚለኝ ሁሉ መንግስተ ሰማያት የሚገባ አይደለም። ኢየሱስ ሁለት አካል ነውን? ሙሴ ሁለት ጊዜ “ሙሴ ፥  ሙሴ” ተብሏል፦ ዘጽአት 3፥4 “እግዚአብሔር ከቁጥቋጦው ውስጥ እርሱን ጠርቶ፦ *ሙሴ፥ ሙሴ ሆይ አለ*። ሙሴ ሁለት አካል ነውን? እንዳትሰክሩ ብለን እንጂ ማስረጃ በቁና ሰፍረን መስጠት እንችላለን። አይሁዶች በሥላሴ አያምኑም፥ ታዲያ ለምን አንድ ጉዳይ ሶስት ጊዜ ተደጋገመ? ለሚለው መልሳቸው “አንድ ስም ከአንድ በላይ ጊዜ መጠራት ጉዳዩን አጽንዖትና አንክሮት ለመስጠት እንጂ ያንን ስም ብዙ አካል አያደርገውም” ይላሉ። አንዱ አምላክ “ቅዱስ” ተብሏል፥ እንደ እርሱ ያለ ቅዱስ የለም፦ 1ኛ ሳሙኤል 2፥2 “እንደ ያህዌህ ቅዱስ የለምና”።  1ኛ ሳሙኤል 2፥2 "ከአንተ በቀር ቅዱስ የለም"።  ራእይ 15፥4 “አንተ ብቻ ቅዱስ” ነህና"። “አንተ” የሚለው ነጠላ ተውላጠ-ስም አንድ ነጠላ ማንነት ብቻ ቅዱስ እንደተባለ ፍትውና ቁልጭ አድርጎ ያስረዳል፥ ሦስት ማንነትቶች ቢሆኑ ኖሮ “እናንተ” ተብሎ ይቀመጥ ነበር። “ከእናንተ” በቀር ቅዱስ የለም” ቢል ኖሮ ለሦስት አካላት ያዋጣ ነበር፥ ቅሉ ግን “አንተ ብቻ ቅዱስ ነህ” ተብሏል። እርሱ ቅዱስ የተባለው ፍጡራን በተባሉበት ስሌትና ቀመር አይደለም፥ ለምሳሌ ሰው እና መላእክት ቅዱሳን ተብለዋል፦ ዘሌዋውያን 11፥45 *እንግዲህ “እኔ ቅዱስ ነኝ እና እናንተ ቅዱሳን”* ሁኑ። ኢዮብ 15፥15 እነሆ፥ *በቅዱሳኑ ስንኳ አይታመንም*፤ ሰማያትም በፊቱ ንጹሐን አይደሉም።

የሥላሴ አማንያን፦ "በአንድነቱ እና በሦስትነቱ ሲቀደስ እና ሢሠለስ የሚኖር ሥሉስ ቅዱስ አለ" ብለው ያምናሉ፥ "ሥሉስ" ማለት "ሦስት" ማለት ሲሆን ዐበይት ክርስትና፦ “መላእክት አንዱን አምላክ ሦስት ጊዜ “ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ” ማለታቸው ሦስት አካላት እንዳሉ ማሳያ ነው” የሚል ስሑት ሙግት አላቸው፦ ኢሳይያስ 6፥3 አንዱም ለአንዱ፦ “ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥” የሠራዊት ጌታ ያህዌህ፤ ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያለ ይጮኽ ነበር"። ይህ ሙግት ውኃ የማያነሳ እና የማይቋጥር ሙግት ነው። ምክንያቱም አንድ ነገር ሦስት ጊዜ መጠቀሱ ያንን ነገር ሦስት ካደረገው ኤርሚያስ ምድርን ሦስት ጊዜ “ምድር ሆይ፥ ምድር ሆይ፥ ምድር ሆይ” ብሎ ጠርቷል፦ ኤርምያስ 22፥29 “ምድር ሆይ፥ ምድር ሆይ፥ ምድር ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ስሚ። ምድር ሦስት ጊዜ መጠራቷ ምድር ሦስት አካላት ናት ያሰኛልን? በተጨማሪ ኤርሚያስ የእግዚአብሔርን መቅደስ ሦስት ጊዜ “የእግዚአብሔር መቅደስ፥ የእግዚአብሔር መቅደስ፥ የእግዚአብሔር መቅደስ” ብሎ ጠርቷል፦ ኤርሚያስ 7፥4 የእግዚአብሔር መቅደስ፥ የእግዚአብሔር መቅደስ፥ የእግዚአብሔር መቅደስ ይህ ነው እያላችሁ በሐሰት ቃል አትታመኑ። የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሦስት ጊዜ መጠራቱ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሦስት አካላት ነው ያሰኛልን? ሌላ ናሙና የይሁዳ ምድር ባድማ እንደሚያደርጋት ሦስት ጊዜ ተናግሯል፦ ሕዝቅኤል 21፥27 *ባድማ፥ ባድማ፥ ባድማ አደርጋታለሁ*። ባድማ እንደሚያደርግ ሦስት ጊዜ መናገሩ ሦስት ባድማ አሉ ያሰኛልን? መጽሐፈ ኩፋሌ የሚባለው የኦርቶዶክስ የቀኖና መጽሐፍ ላይ ደግሞ አብርሃምን ሦስት ጊዜ አብርሃም፥ አብርሃም፥ አብርሃም” ይለዋል፦ ኩፋሌ 14፥5 “እግዚአብሔርም *አብርሃምን፥ “አብርሃም፥ አብርሃም፥ አብርሃም” ብሎ ጠራው፥ አብርሃምም “አቤት አለሁ”አለ*። አብርሃም ሦስት ጊዜ መጠራቱ አብርሃም ሦስት አካላት ነው ያሰኛልን? መልክአ ኢየሱስ የሚባለው የኦርቶዶክስ መጽሐፍ ላይ ኢየሱስን ሦስት ጊዜ “ኢየሱስ፥ ኢየሱስ፥ ኢየሱስ” ይለዋል፦ *“ኢየሱስ ኢየሱስ፥ ኢየሱስ”* ክርስቶስ ዘሰረጽከ እመቤተ ሌዊ ኮሬባዊ መለኮታዊ ቃል ሰማያዊ እም ድንግል ተወለደ። ኢየሱስ የሚለው ቃል ሦስት ጊዜ መደገሙ ከድንግል የተወለደው ኢየሱስ ሦስት አካላት ነውን? ዘፍጥረት ላይ ደግሞ አብርሃም ሁለቴ ስሙ ተደግሟል፦ ዘፍጥረት 22፥11የእግዚአብሔር መልአክም ከሰማይ ጠራና። *“አብርሃም፥ አብርሃም”* አለው።

እነዚህ ሦስት አናቅጽ ላይ "ኤሎሂም" የተባሉት መላክእት ስለሆኑ ግሪክ ሰፕቱጀንት እና የዕብራውያን ጸሐፊም ጭምር "መላእክት" ብለው በግልጽ አስቀምጠዋል። ስለዚህ አዳም ዛፉን ሲበላ መልካም እና ክፉውን በማወቅ እንደ መላእክት ከሆነ ያህዌህ ደግሞ መልካምና ክፉ ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ የሚለው እነዚህን አማልክት ታሳቢና ዋቢ ያደረገ ነው፦ ሆሴዕ 12፥4 በጕልማስነቱም ጊዜ “ከአምላክ” ጋር ታገለ፤ “ከመልአኩም” ጋር ታግሎ አሸነፈ፤ አልቅሶም ለመነው። በቤቴልም አገኘው፥ በዚያም “ከእኛ” ጋር ተነጋገረ"። ያዕቆብ የተነጋገረው ከመልአኩ ጋር እና ከያህዌህ ጋር ነው፥ ያህዌህ መልአኩን ጨምሮ “ከእኛ” እንዳለ አንባቢ ልብ ይለዋል። አይ ያህዌህ እኛ የሚለው ሥላሴን ያሳየል ከተባለ ዕውዱ ላይ ስለ ሥላሴ የሚያሳይ ኃይለ-ቃል ፈልቅቆ ማሳየት ይጠበቅባችኃል! ወይም "ይህ አንቀጽ ስለ ሥላሴ ያወራል" ብሎ የተናገረ ነብይ ወይም ሐዋርያ ጠቅሳችሁና አጣቅሳችሁ መሞገትና መሟገት ይጠበቅባችኃል።

በባይብል አንድ ማንነት "ኑ" ብሎ ሲያዝ ከእርሱ ውጪ ከሆኑ ማንነቶች ጋር እየተነጋገረ እንደሆነ ስሙር እና ዕሙር ነው፦ ዘፍጥረት 11፥3 እርስ በርሳቸውም፦ "ኑ" ጡብ "እንሥራ"። ዘፍጥረት 37፥20 አሁንም "ኑ"  እንግደለውና በአንድ ጕድጓድ ውስጥ እንጣለው"። ዘኍልቍ 14፥4 እርስ በርሳቸውም፦ "ኑ" አለቃ ሾመን ወደ ግብፅ "እንመለስ" ተባባሉ። 1ኛ ሳሙኤል ቀዳማዊ 11፥14 ሳሙኤልም ሕዝቡን፦ "ኑ" ወደ ጌልገላ "እንሂድ"፥ በዚያም መንግሥቱን "እናድስ" አላቸው። ሰዎች ለሰዎች "ኑ" ብለው በትእዛዛዊ ግስ ማዘዛቸው የደረጃ መግዛትን"functical subordination" ሲያመለክት "እንሥራ" "እንግደለው" "እንጣለው" "እንመለስ" "እንሂድ" "እናድስ" የሚለው የንግግር መመላለስ እንዳለ አመላካች ነው። በአንድ ወቅት ያህዌህ ለእስራኤል ሕዝብ፦ "ኑ እንዋቀስ" ብሏቸው ነበር፦ ኢሳይያስ 1፥18 "ኑ" እና "እንዋቀስ" ይላል ያህዌህ"። ያህዌህ አንድ ከሆነ ይህ አንድ ያህዌህ በሁለተኛ መደብ "ኑ" በማለት የሚያዘው እና "እንዋቀስ" በሚል በብዜት ግስ የሚያናግረው ከእርሱ ውጪ ያሉትን ፍጡራን እንደሆነ ቅቡል ነው፥ "ኑ" የሚለው ትእዛዛዊ ግስ በራሱ የኑባሬ መግዛትን"ontological subordination" ያሳያል። በተመሳሳይ ሰዋስው አንዱ አምላክ ያህዌህ ከእርሱ ውጪ ለሆኑ ፍጡራን "ኑ" ዘፍጥረት 11፥ ያህዌህም አለ፦ ዘፍጥረት 11፥7  "ኑ" "እንውረድ" አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ "እንደባልቀው"። የሚያጅበው አንዱ ያህዌህ "ሃባህ" הָ֚בָה የሚለው ከሁለት ማንነት የሆኑ ማንነቶችን ነው፥ እነዚህ ማንነቶች መላእክት መሆናቸውን በ 1952 ድኅረ-ልደት AD በቁምራን ዋሻ የሙት ባህር ጥቅል የተገኘው ጁብልይ በአገራችን መጽሐፍ ኩፋሌ ይናገራል፦ ግዕዙ፦ ኩፋሌ 10፥13 "ወይቤለነ እግዚአብሔር አምላክነ ለነ፤ ናሁ ሕዝብ አሐዱ፤ መወጠነ ይግበር፤ ወይእዜኒ ኢናኀርቅ እምኔሆሙ ንዑ ንረድ ወንከዐው ልሳናቲሆሙ። ዐማርኛ፦ ኩፋሌ 10፥13 "ፈጣሪአችን እግዚአብሔር እኛን እንዲህ አለን፦ አንድ ቋንቋ የሆነ ወገን ግንብ ይሰሩ ጀመር "ኑ" ወርደን በቋንቋ እንለያቸው"። "ፈጣሪአች" የሚሉት መላእክት ስለመሆናቸው ከዚህ በፊት አይተናል፥ "ኑ" ያለውም ለመላእክት እንደሆነ ይህ ትውፊት አስረጂ ነው። የአይሁድ ኮመንታርይ ባጠቃላይ ያህዌህ "ኑ" "እንውረድ" ለመላእክት እንደሆነ አንዳች ልዩነት የላቸው። በተጨማሪም አንድ ያህዌህ አለ፥ ይህ አንድ ያህዌህ መላእክትን ጨምሮ "እኛ" ይላል፦ ዘዳግም 6፥4 "እስራኤል ሆይ ስማ! "አምላካችን ያህዌህ አንድ ያህዌህ ነው"። שְׁמַע, יִשְׂרָאֵל: יְהוָה אֱלֹהֵינוּ, יְהוָה אֶחָד. ዘፍጥረት 3፥22 "ያህዌህ አምላክም አለ፦ "እነሆ አዳም መልካምንና ክፉን ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ"። וַיֹּאמֶר יְהוָה אֱלֹהִים, הֵן הָאָדָם הָיָה כְּאַחַד מִמֶּנּוּ, לָדַעַת, טוֹב וָרָע; וְעַתָּה פֶּן- “እንደ አንዱ” እና “እኛ” ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን ነጥብ በነጥብ ጥርስና ምላሱን እየነቀስን እናየዋለን፦ “እንደ አንዱ” እና “እኛ” ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን ነጥብ በነጥብ ጥርስና ምላሱን እየነቀስን እናየዋለን፦ ነጥብ አንድ “እንደ አንዱ” “ከ-አሐድ” כְּאַחַ֣ד ማለት “እንደ አንዱ”as one of” ማለት ነው፤ ያ ማለት በከፊል መመሳሰልን ያሳያል፦ 1ኛ ሳሙኤል 17፥36 *እኔ ባሪያህ “አንበሳ እና ድብ” መታሁ፤ ይህም ያልተገረዘው ፍልስጥኤማዊ የሕያውን አምላክ ጭፍሮች ተገዳድሮአልና “ከእነርሱ እንደ አንዱ” ይሆናል*። גַּם אֶת-הָאֲרִי גַּם-הַדֹּב, הִכָּה עַבְדֶּךָ; וְהָיָה הַפְּלִשְׁתִּי הֶעָרֵל הַזֶּה, כְּאַחַד מֵהֶם, כִּי חֵרֵף, מַעַרְכֹת אֱלֹהִים חַיִּים. “ከ-አሐድ ሜሄም” כְּאַחַד מֵהֶם ማለት “ከእነርሱ እንደ አንዱ”as one of them” ማለት ሲሆን ፍልስጥኤማዊ ጎልያድ በዳዊት በመገደል ደረጃ “እንደ አንበሳ እና ድብ” ይሆናል ማለት ነው እንጂ ጎልያድ አውሬ ይሆናል ማለት አይደለም፥ “እንደ” የሚለው ተውሳከ-ግስ የተወሰነን መመሳሰል ለማመልከት የሚገባ ነው። ልክ እንደዚሁ አደም መልካምና ክፉ በማወቅ እንደ እንደ እነርሱ ሆኗል፥ ለዛ ነው “ከ-አሐድ ሜንሁ” כְּאַחַ֣ד מִמֶּ֔נּוּ ማለትም “ከእኛ እንደ አንዱ”as one of us” የሚለው። ያህዌህ ታዲያ ማንን ጨምሮ ነው “እኛ” የሚለው? ነጥብ ሁለት “እኛ” ያህዌህ “እኛ” የሚለው ማንን ጨምሮ ነው? የሚለው ለመረዳት እዚሁ ዐውድ ላይ አዳም ከእኛዎቹ እንደ አንዱ የሚሆነው “መልካምንና ክፉን ለማወቅ” እንደሆነ ይሰመርበት! እዛው ዐውድ ላይ አዳም ቢበላ “እንደ አማልክትም መልካምንና ክፉን የሚያውቁ” እንደሆነ ተነግሯል፦ ዘፍጥረት 3፥5 "ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ “እንደ አማልክትም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ” ያህዌህ ስለሚያውቅ ነው እንጂ"። כִּי, יֹדֵעַ אֱלֹהִים, כִּי בְּיוֹם אֲכָלְכֶם מִמֶּנּוּ, וְנִפְקְחוּ עֵינֵיכֶם; וִהְיִיתֶם, כֵּאלֹהִים, יֹדְעֵי, טוֹב וָרָע. የግዕዙ ዕትም፦ ዘፍጥረት 3፥5 “ዘይቤ ከመ ኢትኩኑ አማልክተ ወኢታምሩ ሠናየ ወእኩየ”። የኢንግሊሹ ዕትም፦ For God doth know that in the day ye eat thereof, then your eyes shall be opened, and "ye shall be as gods, knowing good and evil".(KJV) የግሪክ ሰፕቱአጀንት”LXX”፦ ዘፍጥረት 3፥5 ᾔδει γὰρ ὁ Θεός, ὅτι ᾗ ἂν ἡμέρᾳ φάγητε ἀπ᾿ αὐτοῦ, διανοιχθήσονται ὑμῶν οἱ ὀφθαλμοὶ καὶ ἔσεσθε ὡς "θεοί", γινώσκοντες καλὸν καὶ πονηρόν. የግዕዙ ዕትም ላይ “አማልክት” ብሎ እንዳስቀመጠው አስተውል! “ኤሎሂም” כֵּֽאלֹהִ֔ים ማለት “አማልክት” ማለት ነው፥ ይህ ቃል ለነጠላ ማንነት ወይንም ለብዙ ማንነት ይውላል። ግን እዚህ አንቀጽ ላይ ግን ለብዙ መባሉን በግሪክ ሰፕቱጀንት ላይ “ቶኢ” θεοί ማለትም “አማልክት” ብሎ በብዙ ቁጥር አስቀምጦታል፥ ልብ አድርግ የቴኦ ነጠላ “ቴኦስ” Θεὸς ነው። “ቴኦስ” ብሎ በነጠላ አለማስቀመጡ ለብዙ ማንነቶች መሆኑን ያሳያል፥ በኢንግሊሹም ደግሞ በብዙ ቁጥር “gods” መባሉን አስተውል። በብሉይ ደግሞ ብዙ ቦታ አማልክት የተባሉት መላእክት ናቸው፦ መዝሙር 97፥7 ”አማልክትም” כֵּֽאלֹהִ֔ים ሁሉ ስገዱለት። መዝሙር 8፥5 *“ከአማልክትን” כֵּֽאלֹהִ֔ים እጅግ ጥቂት አሳነስኸው"። መዝሙር 138፥1 ”በአማልክት כֵּֽאלֹהִ֔ים ፊት እዘምርልሃለሁ"።

የሥላሴ አማንያን፦ "አይ ያህዌህ እኮ በብዜት የተጠቀሰው በስም መደብ "ኤሎሂም" ተብሎ ብቻ ሳይሆን በብዜት በግስም መደብ ጭምር ነው" ብለው ይህንን ጥቅስ ይጠቅሳሉ፦  ዘፍጥረት 20፥13 "ኤሎሂምም ከአባቴ ቤት "ባወጣኝ" הִתְע֣וּ  ጊዜ አልኋት"። እዚህ አንቀጽ ላይ "ባወጣ" ለሚለው የገባው የዕብራይስጥ ቃል "ሂትኡ" הִתְע֣וּ  ሲሆን ቃል በቃል ሲተረጎም "ባወጡ" ነው፥ "አወጣ" ለማለት ነጠላ ቃል "ታህ" תָּעָה  መሆን ነበረበት። እና ምን ለማለት ፈልጋችሁ ነው? ስንላቸው "ሦስት አካላትን ያሳያል" ይሉናል ይህ ውኃ የማይቋጥር ስሑት አካሄድ ነው፥ በባይብል አንድ ነገር ሦስትነት ሳይኖረው ብብዜት ግስ መቀመጥ የተለመደ ነው፦ ዘጸአት 32፥4 "ከእጃቸውም ተቀብሎ በመቅረጫ ቀረጸው፥ ቀልጦ የተሠራ ጥጃም አደረገው፤ እርሱም፦ እስራኤል ሆይ፥ እነዚህ ከግብፅ ምድር "ያወጡህ" הֶעֱל֖וּךָ  አማልክትህ ናቸው" አላቸው"። ጥጃው አንድ ሆኖ ሳለ በነጠላ "አለህ" עָלָה  ማለትም "ያወጣ" በማለት ፋንታ በብዙ የግስ መደብ "ሂልኡ" הֶעֱל֖וּ  ማለትም "ያወጡ" በማለት መጠቀሙ ጥጃው ሦስት አካል አሊያም ሥላሴ መሆኑን ያሳያልን?  ፍልስጤማውያን ያህዌህ ሥላሴ መሆኑን አያምኑም፥ ግን ስለ ያህዌህ ሲናገሩ፦ "እነዚህ አማልክት ግብጻውያንን በምድረ በዳ በልዩ በልዩ መቅሠፍት የመቱ ናቸው" ብለዋል፦ 1ኛ ሳሙኤል 4፥8 "ወዮልን ከእነዚህ ከኃያላን አማልክት እጅ ማን ያድነናል? እነዚህ አማልክት ግብጻውያንን በምድረ በዳ በልዩ በልዩ መቅሠፍት "የመቱ" ናቸው"። ፍልስጤማውያን ያህዌህን በብዙ ቁጥር "የመቱ" ስላሉ ያህዌህ ሦስት አካል መሆኑ ገብቷት ነውን?  ሳሙኤል አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ "ሲወጡ" በሚል በብዙ የግስ መደብ ተቀምጧል፦ 1 ሳሙኤል 28፥13 ሴቲቱም ሳኦልን፦ "አማልክት ከምድር "ሲወጡ" አየሁ" አለችው። 1 ሳሙኤል 28፥14 "እርስዋም፦ ሽማግሌ ሰው "ወጣ" መጐናጸፊያም ተጐናጽፎአል" አለች። ሳኦልም ሳሙኤል እንደ ሆነ አወቀ፥ በፊቱም ተጐነበሰ፥ በምድርም ላይ እጅ ነሣ"። ሴትየዋ ሳሙኤልን በብዙ ቁጥር "ሲወጡ" ስላለች ሳሙኤል ሦስት አካል መሆኑ ገብቷቸው ነውን?  ከላይ የዘረዘርነው የሙግት ነጥብ እና አካሄድ ኤሎሂም ለሥላሴ አስተምርሆት እንዳልሆኑ በቂ ማሳያ ነው፥ እንደውም እኮ ገድለ ተክለ ሃይማኖት ላይ፦ "የሥላሴ ሦስትነታቸው እና አንድነታቸው ወልድ ሰው እስከሆነ ድረስ አይታወቅም ነበር" ይለናል፦ ገድለ ተክለ ሃይማኖት ገጽ 8 ቁ. 24 "የሥላሴ ሦስትነታቸው እና አንድነታቸው ወልድ ሰው እስከሆነ ድረስ አይታወቅም ነበር"፡፡ ታዲያ "የብሉይ ኪዳን ሰዎች ብዜትን የሚጠቀሙት ለሥላሴ ነው" መደምደም እንዴት ይቻላል?  የብዜት የስም መደብ በተመለከተ የሚያጅበው እኮ “አዶን” אָד֖וֹן   በነጠላ “ጌታ” ማለት ሲሆን “አዶን” በሚለው ቃል ላይ “ኢም” ים  የምትለዋ ስትጨመር “አዶኒም” אֲדֹנִ֣ים  ትሆናለች፥ የአዶን አገናዛቢ ዘርፍ “አዶኒ” אדֹנִ֗י  ማለትም “ጌታዬ” ማለት ነው፥ የአዶኒም አገናዛቢ ዘርፍ ደግሞ በብዜት “አዶናይ” אֲדֹנָ֥י  ነው።

ኤሎሂም “ኤሎሃ” אלוהּ  ለሚለው ቃል ብዜት “ኤሎሂም” אלהים  ሲሆን ቃል በቃል ትርጉሙ "አማልክት" ማለት ነው፥ “ኤሎሂም” אלהים  የሚለው ቃል ለአንድ ቅዋሜ ማንነት ግርማ፣ ሞገስ፣ ሉዓላዊነት፣ ልዕልና፣ ገናናነት ሆኖ ይመጣል፦ ዘፍጥረት 1፥1 "በመጀመሪያ “ኤሎሂም אלהים  ሰማይንና ምድርን ፈጠረ"። በዐማርኛ ላይ "እግዚአብሔር" ወይም በእግሊዝኛ ላይ "God" አሊያም በግሪኩ ሰፕቱጀንት "ቴኦስ" Θεὸς ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ኤሎሂም” אלהים ሲሆን ምሁራን ወደ ሌላ ቋንቋ ሲተረጉሙት ብዙ ቁጥር ለማመልከት "እግዚአብሔሮች" ወይም "Gods" አሊያም "ቴኦኢ" θεοί በማለት ፋንታ በነጠላ የመተርጎማቸው ምክንያት ቃሉ ብዜት ሳይሆን ግርማን፣ ሞገስን፣ ሉዓላዊነትን፣ ልዕልናን፣ ገናናነትን ስለሚያመለክት ነው፥ ለምሳሌ ግሪግ ሰፕቱጀንት ላይ ተመልከት፦  ዘፍጥረት1፥1 ἐν ἀρχῇ ἐποίησεν ὁ θεὸς τὸν οὐρανὸν καὶ τὴν γῆν. እውን ዘፍጥረት 1፥1 ላይ “ኤሎሂም”אלהים  መባል ሥላሴ "አማልክት" ለመሆናቸው እንደ ማስረጃ መቅረቡ በራሱ ዐበይት ክርስትና የመድብለ-አማልክት ትምህርት"Polytheism" አራማጅ መሆኑን አያሳብቅምን?  ሲቀጥል ዘፍጥረት 1፥1 ላይ ቃል በቃል ብንወስድ እንኳን "አማልክት" አለ እንጂ ሦስት አካላት ወይም አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስን የሚያሳይ ምንም ፍንጭ እና ሽታው የለውም።  ሢሠልስ  “ኤሎሂም” אלהים የተባለ አንድ ማንነት በውስጥ ሦስት ማንነቶችን ያሳያል ከተባለ የመረባት አምላክ ተብሎ የሚታመነው ዳጎን "ኤሎሂም” אלהים  ተብሏል፦ መሳፍንት 16፥23 “ለአምላካቸው” אֱלֹהֵיהֶ֖ם  ለዳጎን ታላቅ መሥዋዕት ይሠዉ ዘንድ ደስም ይላቸው ዘንድ ተሰበሰቡ"። የፍልስጥኤምም መኳንንት ዳጎንን "አንድም ሦስትም ነው" ብለው አያምኑም፥ የመሳፍንት ጸሐፊም ዳጎን "በአንድ ምንነቱ ላይ ሦስት ማንነት አለው" ብሎ አያምንም።  የሴም አምላክ ተብሎ የሚታመነው በኣል "ኤሎሂም” אלהים  ተብሏል፦ 1ኛ ነገሥት 18፥27 "በቀትርም ጊዜ ኤልያስ “ኤሎሂም” אלהים  ነውና በታላቅ ቃል ጩኹ! ምናልባት አሳብ ይዞታል ወይም ፈቀቅ ብሎአል ወይም ወደ መንገድ ሄዶአል፥ ወይም ተኝቶ እንደ ሆነ መቀስቀስ ያስፈልገዋል" እያለ አላገጠባቸው"። ኤልያስ በኣልን በሽሙጥ እና በለበጣ “ኤሎሂም” ሲለው "በአንድ ምንነቱ ላይ ሦስት ማንነት አለው" ማለቱ አልነበረም። ቀጣይ ሌሎች ሙግቶችን እንመልከት፦ መዝሙር 45፥6 “ኤሎሂም” אלהים  ሆይ፥ ዙፋንህ ለዘላለም ነው፤ የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ነው። እንደ አይሁዳውያን ማብራሪያ ይህ አንቀጽ የሚናገረው ስለ ንጉሥ ሰልሞን ነው፥ የዕብራውያንን ጸሐፊ መሠረት በማድረግ ሥላሴአዋያን ይህንን ጥቅስ ለወልድ ነው" ይላሉ።  ወልድ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ "ኤሎሂም" ስለተባለ ወልድ እራሱ ሦስት ማንነት ነውን? ያህዌህ ሙሴን በፈርዖን ላይ “ኤሎሂም” אלהים  አርጎታል፦ ዘጸአት 7፥1 ያህዌህም ሙሴን አለው፦ እይ! እኔ ለፈርዖን “ኤሎሂም” אלהים   አድርጌሃለው"።  ሙሴ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ "ኤሎሂም" ስለተባለ ሦስት ማንነት ነውን? በዕብራይስጥ ቃላት ውስጥ የብዜት ቃላት ለክብር መምጣት የተለመደ ነው፦  መኃልይ ዘሰሎሞን 5፥16 "አፉ" እጅግ “ጣፋጭ” מַמְתַקִּים  ነው፥ እርሱም ፈጽሞ “ያማረ” מַחֲמַדִּים  ነው"።  ሱናማይቱ ልጃገረድ የንጉሥ ሰልሞንን አፍ “ጣፋጭ” ነው ትለናለች፥ “ጣፋጭ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል በነጠላ “ሙተቅ” מֹתֶק  ሳይሆን በብዜት “መምተቂም” מַמְתַקִּים  ማለትም “ጣፋጮች” ነው። ታዲያ የንጉሥ ሰልሞን አፍ ሥስት ማንነት ይዟልን? በመቀጠል እዛው አንቀጽ ላይ “ያማረ” ነው ትለናለች፥ “ያማረ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል በነጠላ “መኽመድ” מַחְמַד  ሳይሆን በብዜት “መኽመዲም” מַחֲמַדִּים  ማለትም “ያማሩ” ነው። ታዲያ የንጉሥ ሰልሞን አፍ ሥስት ማንነት ይዟልን? እስቲ እንቀጥል፦ ኢሳይያስ 19፥4 "ግብጻውያንንም በጨካኝ “ጌታ” אֲדֹנִ֣ים  እጅ አሳልፌ እሰጣለሁ፥ ጨካኝ ንጉሥም ይገዛቸዋል” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌህ"። “አዶን” אָדוֹן  ደግሞ በነጠላ “ጌታ” ማለት ሲሆን “አዶኒም” אֲדֹנִ֣ים በብዜት “ጌቶች” ማለት ነው፥ የአሦር ንጉሥ አስራዶን በ 670 ቅድመ-ልደት የተነሳ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ “አዶኒም” אֲדֹנִ֣ים  ስለተባለ አስራዶን ሦስት ማንነት ነውን? ሙግታችንን እንቀጥል፦ ዘፍጥረት 21፥7 "ደግሞም ሣራ “ልጆችን” בָנִ֖ים  እንድታጠባ ለአብርሃም ማን በነገረው? በእርጅናው ልጅን ወልጄለታለሁና" አለች*። “ባኒም” בָנִ֖ים  በብዜት ሲሆን “ልጆች” ማለት ሲሆን በነጠላ “ቤን” בֵ֖ן  ነው፥ ይስሐቅ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ “ባኒም” בָנִ֖ים  እንደተባለ አስተውል! ሳራ ያጠባችው ልጅ ይስሐቅ “ልጆች” ስለተባለ ይስሐቅ ሥላሴ ነውን? 

ዮሐንስ 17፥3 *”እውነተኛ አምላክ ብቻህን የሆንህ አንተን እና የላክኸውን ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት*። αὕτη δέ ἐστιν ἡ αἰώνιος ζωή, ἵνα γινώσκωσιν σὲ τὸν μόνον ἀληθινὸν θεὸν καὶ ὃν ἀπέστειλας Ἰησοῦν Χριστόν. የተጠቀምኩት 1980 አዲስ ትርጉም ነው።

ማርቆስ 10፥18 “ኢየሱስም፦ ስለ ምን ቸር "እኔን" ትለኛለህ? ከአንዱ አምላክ በቀር ቸር ማንም የለም”። ὁ δὲ Ἰησοῦς εἶπεν αὐτῷ Τί με λέγεις ἀγαθόν; οὐδεὶς ἀγαθὸς εἰ μὴ εἷς ὁ θεός. And Jesus said unto him, Why callest thou me good? there is none good but one, that is, God. (King James version)

“እግዚእ” ማለት “ጌታ” ማለት ነው፥ የእግዚእ ብዙ ቁጥር ደግሞ “አጋዕዝት” ሲሆን “ጌቶች” ማለት ነው። የነቢያት እና የሐዋርያት አስተምህሮት፦ “አምላካችን አንድ ጌታ” የሚል ነው፦ ማርቆስ 12፥29 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ “ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ እስራኤል ሆይ ስማ! ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው”። ከዚህ በተቃራኒው የሥላሴአውያን ነገረ መለኮት ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ “እንዚራ ስብሐት” በተባለ መድብሉ ላይ፦ “እንቲ ውእቱ ዕፀት ዘነበርኪ ጥቃ ኀይመት ዘብኪ አጽለሉ ሠለስቱ አጋዕዝት” ትርጉም፦ “በአንቺ ሦስቱ ጌቶች የተጠለሉብሽ በድንኳን አጠገብ የቆምሽ ዕንጨት አንቺ ነሽ” “ሠለስቱ አጋዕዝት” ማለት “ሦስቱ ጌቶች” ማለት ሲሆን አብርሃም ቤት የገቡት ሰዎች ሥላሴ ከማድረግ ባሻገር ሦስት ጌቶች ማድረግ መድብለ-አማልክታዊነት”Polytheism” ነው፥ “አጋዕዝተ ዓለም” ማለት “የዓለም ጌቶች” ማለት ሲሆን “ዓለምን የሚያስተናብሩ ሦስት ጌቶች አሉ” ብሎ ማመን ሥሉሣዊ አምላክ አስተምህሮት”Tritheism” ነው። የአንጾኪያው ኤጲስ ቆጶስ ዲዮናስዮስ ወደ እስክንድርያው ኤጲስ ቆጶስ ወደ ሚናስ በላከው መልእክቱ፦ “አምላክ ሦስት ነው” ብሎ እንቅጩን ፍርጥ አርጎ ተናግሯል፦ ሃይማኖተ አበው ዘዲዮናስዮስ ምዕራፍ 99 “አምላክነስ ሥሉስ እንበለ ተሌልዮ”። ትርጉም፦ “አምላካችን ያለ መለየት ሦስት ነው”። የሐሙስ ሰይፈ ሥላሴ 366፦ “ሦስት ልዑላን ገዢዎች፥ ሦስት ጌቶች ናቸው” ከነቢያት እና ከሐዋርያት መካከል፦”ሦስት ጌቶች” ወይም “አምላክ ሦስት ነው” ብሎ ያስተማረ ማንም የለም። ስለዚህ «ሦስት ነው» አትበሉም! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፦ 4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ