en
Feedback
እስልምና እና ክርስትና

እስልምና እና ክርስትና

Open in Telegram

t.me//AkeelComparative የእስልምና እና የክርስትና ሐይማኖት ንፅፅሮችን በጥልቀት ይዳስሳል። ቻናሉን #join ሌሎችንም #add ያድርጉ!!

Show more
315
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የሥላሴ አማንያን፦ "አይ ያህዌህ እኮ በብዜት የተጠቀሰው በስም መደብ "ኤሎሂም" ተብሎ ብቻ ሳይሆን በብዜት በግስም መደብ ጭምር ነው" ብለው ይህንን ጥቅስ ይጠቅሳሉ፦  ዘፍጥረት 20፥13 "ኤሎሂምም ከአባቴ ቤት "ባወጣኝ" הִתְע֣וּ  ጊዜ አልኋት"። እዚህ አንቀጽ ላይ "ባወጣ" ለሚለው የገባው የዕብራይስጥ ቃል "ሂትኡ" הִתְע֣וּ  ሲሆን ቃል በቃል ሲተረጎም "ባወጡ" ነው፥ "አወጣ" ለማለት ነጠላ ቃል "ታህ" תָּעָה  መሆን ነበረበት። እና ምን ለማለት ፈልጋችሁ ነው? ስንላቸው "ሦስት አካላትን ያሳያል" ይሉናል ይህ ውኃ የማይቋጥር ስሑት አካሄድ ነው፥ በባይብል አንድ ነገር ሦስትነት ሳይኖረው ብብዜት ግስ መቀመጥ የተለመደ ነው፦ ዘጸአት 32፥4 "ከእጃቸውም ተቀብሎ በመቅረጫ ቀረጸው፥ ቀልጦ የተሠራ ጥጃም አደረገው፤ እርሱም፦ እስራኤል ሆይ፥ እነዚህ ከግብፅ ምድር "ያወጡህ" הֶעֱל֖וּךָ  አማልክትህ ናቸው" አላቸው"። ጥጃው አንድ ሆኖ ሳለ በነጠላ "አለህ" עָלָה  ማለትም "ያወጣ" በማለት ፋንታ በብዙ የግስ መደብ "ሂልኡ" הֶעֱל֖וּ  ማለትም "ያወጡ" በማለት መጠቀሙ ጥጃው ሦስት አካል አሊያም ሥላሴ መሆኑን ያሳያልን?  ፍልስጤማውያን ያህዌህ ሥላሴ መሆኑን አያምኑም፥ ግን ስለ ያህዌህ ሲናገሩ፦ "እነዚህ አማልክት ግብጻውያንን በምድረ በዳ በልዩ በልዩ መቅሠፍት የመቱ ናቸው" ብለዋል፦ 1ኛ ሳሙኤል 4፥8 "ወዮልን ከእነዚህ ከኃያላን አማልክት እጅ ማን ያድነናል? እነዚህ አማልክት ግብጻውያንን በምድረ በዳ በልዩ በልዩ መቅሠፍት "የመቱ" ናቸው"። ፍልስጤማውያን ያህዌህን በብዙ ቁጥር "የመቱ" ስላሉ ያህዌህ ሦስት አካል መሆኑ ገብቷት ነውን?  ሳሙኤል አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ "ሲወጡ" በሚል በብዙ የግስ መደብ ተቀምጧል፦ 1 ሳሙኤል 28፥13 ሴቲቱም ሳኦልን፦ "አማልክት ከምድር "ሲወጡ" አየሁ" አለችው። 1 ሳሙኤል 28፥14 "እርስዋም፦ ሽማግሌ ሰው "ወጣ" መጐናጸፊያም ተጐናጽፎአል" አለች። ሳኦልም ሳሙኤል እንደ ሆነ አወቀ፥ በፊቱም ተጐነበሰ፥ በምድርም ላይ እጅ ነሣ"። ሴትየዋ ሳሙኤልን በብዙ ቁጥር "ሲወጡ" ስላለች ሳሙኤል ሦስት አካል መሆኑ ገብቷቸው ነውን?  ከላይ የዘረዘርነው የሙግት ነጥብ እና አካሄድ ኤሎሂም ለሥላሴ አስተምርሆት እንዳልሆኑ በቂ ማሳያ ነው፥ እንደውም እኮ ገድለ ተክለ ሃይማኖት ላይ፦ "የሥላሴ ሦስትነታቸው እና አንድነታቸው ወልድ ሰው እስከሆነ ድረስ አይታወቅም ነበር" ይለናል፦ ገድለ ተክለ ሃይማኖት ገጽ 8 ቁ. 24 "የሥላሴ ሦስትነታቸው እና አንድነታቸው ወልድ ሰው እስከሆነ ድረስ አይታወቅም ነበር"፡፡ ታዲያ "የብሉይ ኪዳን ሰዎች ብዜትን የሚጠቀሙት ለሥላሴ ነው" መደምደም እንዴት ይቻላል?  የብዜት የስም መደብ በተመለከተ የሚያጅበው እኮ “አዶን” אָד֖וֹן   በነጠላ “ጌታ” ማለት ሲሆን “አዶን” በሚለው ቃል ላይ “ኢም” ים  የምትለዋ ስትጨመር “አዶኒም” אֲדֹנִ֣ים  ትሆናለች፥ የአዶን አገናዛቢ ዘርፍ “አዶኒ” אדֹנִ֗י  ማለትም “ጌታዬ” ማለት ነው፥ የአዶኒም አገናዛቢ ዘርፍ ደግሞ በብዜት “አዶናይ” אֲדֹנָ֥י  ነው።

ኤሎሂም “ኤሎሃ” אלוהּ  ለሚለው ቃል ብዜት “ኤሎሂም” אלהים  ሲሆን ቃል በቃል ትርጉሙ "አማልክት" ማለት ነው፥ “ኤሎሂም” אלהים  የሚለው ቃል ለአንድ ቅዋሜ ማንነት ግርማ፣ ሞገስ፣ ሉዓላዊነት፣ ልዕልና፣ ገናናነት ሆኖ ይመጣል፦ ዘፍጥረት 1፥1 "በመጀመሪያ “ኤሎሂም אלהים  ሰማይንና ምድርን ፈጠረ"። በዐማርኛ ላይ "እግዚአብሔር" ወይም በእግሊዝኛ ላይ "God" አሊያም በግሪኩ ሰፕቱጀንት "ቴኦስ" Θεὸς ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ኤሎሂም” אלהים ሲሆን ምሁራን ወደ ሌላ ቋንቋ ሲተረጉሙት ብዙ ቁጥር ለማመልከት "እግዚአብሔሮች" ወይም "Gods" አሊያም "ቴኦኢ" θεοί በማለት ፋንታ በነጠላ የመተርጎማቸው ምክንያት ቃሉ ብዜት ሳይሆን ግርማን፣ ሞገስን፣ ሉዓላዊነትን፣ ልዕልናን፣ ገናናነትን ስለሚያመለክት ነው፥ ለምሳሌ ግሪግ ሰፕቱጀንት ላይ ተመልከት፦  ዘፍጥረት1፥1 ἐν ἀρχῇ ἐποίησεν ὁ θεὸς τὸν οὐρανὸν καὶ τὴν γῆν. እውን ዘፍጥረት 1፥1 ላይ “ኤሎሂም”אלהים  መባል ሥላሴ "አማልክት" ለመሆናቸው እንደ ማስረጃ መቅረቡ በራሱ ዐበይት ክርስትና የመድብለ-አማልክት ትምህርት"Polytheism" አራማጅ መሆኑን አያሳብቅምን?  ሲቀጥል ዘፍጥረት 1፥1 ላይ ቃል በቃል ብንወስድ እንኳን "አማልክት" አለ እንጂ ሦስት አካላት ወይም አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስን የሚያሳይ ምንም ፍንጭ እና ሽታው የለውም።  ሢሠልስ  “ኤሎሂም” אלהים የተባለ አንድ ማንነት በውስጥ ሦስት ማንነቶችን ያሳያል ከተባለ የመረባት አምላክ ተብሎ የሚታመነው ዳጎን "ኤሎሂም” אלהים  ተብሏል፦ መሳፍንት 16፥23 “ለአምላካቸው” אֱלֹהֵיהֶ֖ם  ለዳጎን ታላቅ መሥዋዕት ይሠዉ ዘንድ ደስም ይላቸው ዘንድ ተሰበሰቡ"። የፍልስጥኤምም መኳንንት ዳጎንን "አንድም ሦስትም ነው" ብለው አያምኑም፥ የመሳፍንት ጸሐፊም ዳጎን "በአንድ ምንነቱ ላይ ሦስት ማንነት አለው" ብሎ አያምንም።  የሴም አምላክ ተብሎ የሚታመነው በኣል "ኤሎሂም” אלהים  ተብሏል፦ 1ኛ ነገሥት 18፥27 "በቀትርም ጊዜ ኤልያስ “ኤሎሂም” אלהים  ነውና በታላቅ ቃል ጩኹ! ምናልባት አሳብ ይዞታል ወይም ፈቀቅ ብሎአል ወይም ወደ መንገድ ሄዶአል፥ ወይም ተኝቶ እንደ ሆነ መቀስቀስ ያስፈልገዋል" እያለ አላገጠባቸው"። ኤልያስ በኣልን በሽሙጥ እና በለበጣ “ኤሎሂም” ሲለው "በአንድ ምንነቱ ላይ ሦስት ማንነት አለው" ማለቱ አልነበረም። ቀጣይ ሌሎች ሙግቶችን እንመልከት፦ መዝሙር 45፥6 “ኤሎሂም” אלהים  ሆይ፥ ዙፋንህ ለዘላለም ነው፤ የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ነው። እንደ አይሁዳውያን ማብራሪያ ይህ አንቀጽ የሚናገረው ስለ ንጉሥ ሰልሞን ነው፥ የዕብራውያንን ጸሐፊ መሠረት በማድረግ ሥላሴአዋያን ይህንን ጥቅስ ለወልድ ነው" ይላሉ።  ወልድ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ "ኤሎሂም" ስለተባለ ወልድ እራሱ ሦስት ማንነት ነውን? ያህዌህ ሙሴን በፈርዖን ላይ “ኤሎሂም” אלהים  አርጎታል፦ ዘጸአት 7፥1 ያህዌህም ሙሴን አለው፦ እይ! እኔ ለፈርዖን “ኤሎሂም” אלהים   አድርጌሃለው"።  ሙሴ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ "ኤሎሂም" ስለተባለ ሦስት ማንነት ነውን? በዕብራይስጥ ቃላት ውስጥ የብዜት ቃላት ለክብር መምጣት የተለመደ ነው፦  መኃልይ ዘሰሎሞን 5፥16 "አፉ" እጅግ “ጣፋጭ” מַמְתַקִּים  ነው፥ እርሱም ፈጽሞ “ያማረ” מַחֲמַדִּים  ነው"።  ሱናማይቱ ልጃገረድ የንጉሥ ሰልሞንን አፍ “ጣፋጭ” ነው ትለናለች፥ “ጣፋጭ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል በነጠላ “ሙተቅ” מֹתֶק  ሳይሆን በብዜት “መምተቂም” מַמְתַקִּים  ማለትም “ጣፋጮች” ነው። ታዲያ የንጉሥ ሰልሞን አፍ ሥስት ማንነት ይዟልን? በመቀጠል እዛው አንቀጽ ላይ “ያማረ” ነው ትለናለች፥ “ያማረ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል በነጠላ “መኽመድ” מַחְמַד  ሳይሆን በብዜት “መኽመዲም” מַחֲמַדִּים  ማለትም “ያማሩ” ነው። ታዲያ የንጉሥ ሰልሞን አፍ ሥስት ማንነት ይዟልን? እስቲ እንቀጥል፦ ኢሳይያስ 19፥4 "ግብጻውያንንም በጨካኝ “ጌታ” אֲדֹנִ֣ים  እጅ አሳልፌ እሰጣለሁ፥ ጨካኝ ንጉሥም ይገዛቸዋል” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌህ"። “አዶን” אָדוֹן  ደግሞ በነጠላ “ጌታ” ማለት ሲሆን “አዶኒም” אֲדֹנִ֣ים በብዜት “ጌቶች” ማለት ነው፥ የአሦር ንጉሥ አስራዶን በ 670 ቅድመ-ልደት የተነሳ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ “አዶኒም” אֲדֹנִ֣ים  ስለተባለ አስራዶን ሦስት ማንነት ነውን? ሙግታችንን እንቀጥል፦ ዘፍጥረት 21፥7 "ደግሞም ሣራ “ልጆችን” בָנִ֖ים  እንድታጠባ ለአብርሃም ማን በነገረው? በእርጅናው ልጅን ወልጄለታለሁና" አለች*። “ባኒም” בָנִ֖ים  በብዜት ሲሆን “ልጆች” ማለት ሲሆን በነጠላ “ቤን” בֵ֖ן  ነው፥ ይስሐቅ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ “ባኒም” בָנִ֖ים  እንደተባለ አስተውል! ሳራ ያጠባችው ልጅ ይስሐቅ “ልጆች” ስለተባለ ይስሐቅ ሥላሴ ነውን? 

ዮሐንስ 17፥3 *”እውነተኛ አምላክ ብቻህን የሆንህ አንተን እና የላክኸውን ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት*። αὕτη δέ ἐστιν ἡ αἰώνιος ζωή, ἵνα γινώσκωσιν σὲ τὸν μόνον ἀληθινὸν θεὸν καὶ ὃν ἀπέστειλας Ἰησοῦν Χριστόν. የተጠቀምኩት 1980 አዲስ ትርጉም ነው።

ማርቆስ 10፥18 “ኢየሱስም፦ ስለ ምን ቸር "እኔን" ትለኛለህ? ከአንዱ አምላክ በቀር ቸር ማንም የለም”። ὁ δὲ Ἰησοῦς εἶπεν αὐτῷ Τί με λέγεις ἀγαθόν; οὐδεὶς ἀγαθὸς εἰ μὴ εἷς ὁ θεός. And Jesus said unto him, Why callest thou me good? there is none good but one, that is, God. (King James version)

“እግዚእ” ማለት “ጌታ” ማለት ነው፥ የእግዚእ ብዙ ቁጥር ደግሞ “አጋዕዝት” ሲሆን “ጌቶች” ማለት ነው። የነቢያት እና የሐዋርያት አስተምህሮት፦ “አምላካችን አንድ ጌታ” የሚል ነው፦ ማርቆስ 12፥29 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ “ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ እስራኤል ሆይ ስማ! ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው”። ከዚህ በተቃራኒው የሥላሴአውያን ነገረ መለኮት ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ “እንዚራ ስብሐት” በተባለ መድብሉ ላይ፦ “እንቲ ውእቱ ዕፀት ዘነበርኪ ጥቃ ኀይመት ዘብኪ አጽለሉ ሠለስቱ አጋዕዝት” ትርጉም፦ “በአንቺ ሦስቱ ጌቶች የተጠለሉብሽ በድንኳን አጠገብ የቆምሽ ዕንጨት አንቺ ነሽ” “ሠለስቱ አጋዕዝት” ማለት “ሦስቱ ጌቶች” ማለት ሲሆን አብርሃም ቤት የገቡት ሰዎች ሥላሴ ከማድረግ ባሻገር ሦስት ጌቶች ማድረግ መድብለ-አማልክታዊነት”Polytheism” ነው፥ “አጋዕዝተ ዓለም” ማለት “የዓለም ጌቶች” ማለት ሲሆን “ዓለምን የሚያስተናብሩ ሦስት ጌቶች አሉ” ብሎ ማመን ሥሉሣዊ አምላክ አስተምህሮት”Tritheism” ነው። የአንጾኪያው ኤጲስ ቆጶስ ዲዮናስዮስ ወደ እስክንድርያው ኤጲስ ቆጶስ ወደ ሚናስ በላከው መልእክቱ፦ “አምላክ ሦስት ነው” ብሎ እንቅጩን ፍርጥ አርጎ ተናግሯል፦ ሃይማኖተ አበው ዘዲዮናስዮስ ምዕራፍ 99 “አምላክነስ ሥሉስ እንበለ ተሌልዮ”። ትርጉም፦ “አምላካችን ያለ መለየት ሦስት ነው”። የሐሙስ ሰይፈ ሥላሴ 366፦ “ሦስት ልዑላን ገዢዎች፥ ሦስት ጌቶች ናቸው” ከነቢያት እና ከሐዋርያት መካከል፦”ሦስት ጌቶች” ወይም “አምላክ ሦስት ነው” ብሎ ያስተማረ ማንም የለም። ስለዚህ «ሦስት ነው» አትበሉም! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፦ 4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ

ዕብራውያን 1፥1-2 "ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ፥ ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዘመናትን ባደረገበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን"።(Berean Literal Bible)

ሃይማኖተ-አበው ዘቄርሎስ ምዕራፍ 79 ቁጥር 21 ግዕዙ፦ ”መኑ ውእቱ ዘይብል እስመ ምግባር ዘእገብሮሙ በስመ አቡዬ ውእቶሙ ሰማዕትየ ወእንበይነ መኑ ይብል ከመ ውእቱ አቡሁ ዘእንበለ እግዚአብሔር?” ትርጉም፦ ”በአባቴ ስም የምሠራቸው ሥራዎች ምስክሮቼ ናቸው ያለ ማን ነው? ከእግዚአብሔር በስተቀር አባቴ የሚለው ማንን ነው?”

. #ስላሴ ሥላሴ የሚለው ቃል እና ቃሉ የወከለው እሳቤ በተለያየ ሰዎች እና ጉባኤያት የዳበረ እንደሆነ የተለያዩ ኢንሳይክሎፔድያዎች እና መዝገበ ቃላቶች እንዲህ ይላሉ፦ 1. ዘ ኒው ኢንሳይክሎፔድያ ብሪታኒካ፦ «ሥላሴ የሚለው ቃልም ሆነ በግልጽ የተብራራ የሥላሴ መሰረተ ትምህርት በአዲስ ኪዳን ውስጥ አይገኝም። ኢየሱስም ሆነ ተከታዮቹ በብሉይ ኪዳን ውስጥ የተጻፈውን፦ "እስራኤል ሆይ ስማ፣ አምላካችን ያህዌህ አንድ ያህዌህ ነው" ዘዳግም 6፡4 የሚለውን ለማስተባበል አላሰቡም። የሥላሴ እምነት ቀስ በቀስ የተስፋፋው በበርካታ መቶ ዓመታት ውስጥ ከብዙ ንትርክ በኋላ ነው። የሥላሴ መሠረተ ትምህርት አሁን ያለውን ቅርጽ የያዘው በአራተኛው መቶ ዘመን መጨረሻ ላይ ነው።» ዘ ኒው ኢንሳይክሎፔድያ ብሪታኒካ (1976)፣ ማክሮፔድያ፣ ጥራዝ 10፣ ገጽ 126. 2. ኒው ካቶሊክ ኢንሳይክሎፔድያ እንዲህ በማለት ይገልጻል:- "አንድ አምላክ በሦስት አካላት" የሚለው ድንጋጌ ጠንካራ መሠረት ያገኘው እና በክርስትና ሕይወትና የእምነት መግለጫ ውስጥ ሙሉ ተቀባይነት ያገኘው ከ4ኛው መቶ ዘመን በኋላ ነበር። ይሁን እንጂ የሥላሴ ቀኖና የሚለው ስያሜ የተሰጠው ለዚህ ድንጋጌ ነው። ሐዋርያዊ አባቶች እንዲህ ያለ አመለካከት ወይም ከዚህ እምነት ጋር የሩቅ ዝምድና እንኳን ያለው አስተሳሰብ እንደነበራቸው የሚያመለክት አንድም ማስረጃ አናገኝም።”— (1967)፣ ጥራዝ 14፣ ገጽ 299 3. ዘ ኢንሳይክሎፔድያ አሜሪካና ላይ እንዲህ እናነባለን:- “ክርስትና የበቀለው ከአይሁዳውያን ሃይማኖት ነው። አይሁዳውያን ደግሞ፦ "አምላክ አንድ አካል(person) ነው" ብለው የሚያምኑ ሕዝቦች ናቸው። ከኢየሩሳሌም ወደ ኒቅያ ያደረሰው መንገድ ጠመዝማዛነት የበዛበት ነበር። የአራተኛ መቶ ዘመኑ የሥላሴ እምነት የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ስለአምላክ ማንነት የነበራቸውን እምነት በትክክል አያንጸባርቅም። እንዲያውም እነርሱ ከነበራቸው እምነት ፈጽሞ የራቀ ነው።”—(1956)፣ ጥራዝ 27፣ ገጽ 294 ኤል 4. አዲሱ ዓለም አቀፋዊ መዝገበ ቃላት እንደሚለው፦ “የሕዝበ ክርስትና አብያተ ክርስቲያናት የሚያስተምሩት የሦስት ሃይፖስታሲስ ወይም የሦስት አካላት እምነት የተወለደው ከጥንት ዘመናት ጀምሮ የተለያዩ ሕዝቦች ያምኑባቸው ከነበሩት ሥላሴዎች ከተወረሰው የፕላቶ የባሕርይ ሥላሴነት ፍልስፍና ነው። ይህ ግሪካዊ ፈላስፋ ፕላቶ ስለ መለኮታዊ ሥላሴ የነበረውን ፅንሰ አሳብ በሁሉም የጥንት ፓጋናዊ ሃይማኖቶች ውስጥ ማግኘት ይቻላል።”—(ፓሪስ፣ 1865–1870)፣ በኤም ላሻትር የተዘጋጀ፣ ጥራዝ 2፣ ገጽ 1467 5. ጆን ኤል ማኬንዚ፣ ዲክሽነሪ ኦቭ ዘ ባይብል(የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት) በተባለው መጽሐፋቸው ውስጥ እንዲህ ብለዋል፦ “በባሕርይ አንድነት ውስጥ የሚገኘው የአካል ሦስትነት የሚብራራው የግሪካውያን የፍልስፍና ቃላት በሆኑት በ‘አካል’ እና ‘ኑባሬ’ ነው። እነዚህ ቃላት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሥላሴን ሐሳብ ለመግለጽ አገልግለው አያውቁም። ይህ ዓይነቱ የሥላሴ ፍቺ የተገኘው አንዳንድ ሃይማኖታዊ ሊቃውንት በስህተት እነዚህንና ‘ኤሰንስ’ እና ‘ሰብስታንስ’ የተባሉትን የእንግሊዝኛ ቃላት ስለ አምላክ ለመግለጽ በመጠቀማቸው ምክንያት ከተፈጠረው ውዝግብ ነው።”—(ኒው ዮርክ፣ 1965)፣ ገጽ 899 ለተጨማሪ መረጃ ቻናሉን ይቀላቀቀሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇 t.me//AkeelComparative