እስልምና እና ክርስትና
Open in Telegram
t.me//AkeelComparative የእስልምና እና የክርስትና ሐይማኖት ንፅፅሮችን በጥልቀት ይዳስሳል። ቻናሉን #join ሌሎችንም #add ያድርጉ!!
Show more315
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
✔ #የታዘዙ ፦ ማለት < اسلم > / < አስለም> ሲሆን < مسلم > /
< ሙስሊም> ከሚለው ስርወ ግንድ የተገኘ ቃል ነው።
ስለዚህ ኢስላም ማለት በኑፋቄአውያን የሚሰደበው የእውነተኛው መንገድ ወይም ሀይማኖት ሲሆን ሙስሊም ማለት ደግሞ ለአምላኩ የሚታዘዝ ፣ የታዘዘውን የሚፈፅም (የአምልዕኮ ክንውኖችን ለአምላኩ የሚያደርግ ( የሚሰግድ፣ የሚፆም፣...) ነው። ታድያ ጳውሎስ ለማን ነው የሚታዘዘው? ለማነው የሚሰግደው? በመጀመሪያ ደረጃ ስግደት ማለት ምን ማለት ነው?
✔ #ስግደት ፦ ማለት ለአንድ አካል መስገድ ማጎብደድ፣ ማምለክ፣ መታዘዝ.. ማለት ሲሆን
ስግደት በሁለት ይከፈላል፦ እነርሱም #የአምልኮ #ስግደት እና #የአክብሮት #ስግደት ናቸው።
1) የአምልኮ ስግደት፦ ይህ ስግደት ለፈጣሪ አምላክ በብቸኝነት መስገድ ፤ የአምልኮ ክንውኖችን ለአንድ ፈጣሪ ማድረግ ማለት ነው።
- ኦሪት ዘዳግም 10 ፥ 12-13
" እግዚአብሔር አምላክህን በፍፁም እውነት በፍፁም ልብህ አምልክ።"
41፡37
ومن آياته الليل والنهار والشمس والقمر ۚ لا تسجدوا للشمس ولا للقمر واسجدوا لله الذي خلقهن إن كنتم إياه تعبدون
ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ ለፀሐይና ለጨረቃ አትስገዱ፡፡ ለእዚያም ለፈጠራቸው #አላህ #ስገዱ፡፡ #እርሱን #ብቻ #የምትግገዙ እንደ ኾናችሁ ( #ለሌላ #አትስገዱ)፡፡
2) የአክብሮት ስግደት፦ ይህ ስግደት ከአምላክ ውጪ ላሉት ለባዕድ ነገሮች (ለጣኦታት) መስገድ ፣ ማምለክ... ማለት ነው።
✔ #ጣኦት ማለት ምን ማለት ነው?
ከአንድ ፈጣሪ አምላክ ውጪ ሌላ የሚመለክና የሚሰገድለት ማንኛውንም አካል ካለ እርሱ ጣኦት ይባላል። ለዚህም
29 ፥ 17
<< ከአላህ ሌላ የምትግገዙት ጣኦት ብቻ ነው። ውሸትንም ትቀጣጥፋላችሁ...። >>
#ጣኦት በሁለት ይከፈላል፦ #አስናም እና #አውሳን በመባል።
- አስናም ማለት ከእንጨት ፣ ከወርቅ፣ ከብር ፣ ከነሀስ የተቀረፁትን የሚያመልክ ማለት ነው።
- ትንቢተ ዳንኤል 5፥ 4 & 5፥23
" የወይን ጠጅም እየጠጡ ከወርቅ፣ ከብር፣ ከነሀስና ከእንጨት የተቀረፁትን ጣኦታት አመሠገኑ።"
#ከቁርዓን ደግሞ 6፥74 መመልከት
- አውሳን ማለት ደግሞ ፦ ከድንጋይ የተቀረፁትን የሚያመልክ ማለት ነው።
- ኦሪት ዘሌዋውያን 26፥ 1
" እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝ፥ ለእናንተ ጣኦት አታድርጉ፥ የተቀረፀ ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ፥ ትሰግዱለትም ዘንድ ምድራችሁ ላይ ከድንጋይ የተቀረፀ አታኑሩ።"
#ከቁርዓን ደግሞ 29፥17ን ማየት
ታድያ ጳውሎስ እንዴትና በምን መልኩ ነው ጣኦት አምላኪ ሰው ነው ሊባል የቻለው??
ጳውሎስ " የአባቶቼን አምላክ እነርሱ ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ" ብሏል። የጳውሎስ አምልኮ ይህ ከሆነ ታድያ አባቶቹ እነማን ናቸው? እነርሱስ ያመልኩት የነበረው ማንን ነው??
እሱ አባቶች ያላቸው ነብያትንና የቀደምት እስራኤላውያን ሰዎችን ነው። ታድያ ነብያት ከአንድ አምላክ ውጪ ሌላ ጣኦታት አምልከዋልን?? የለም አላመለኩም። ቀደምት እስራኤላውያን አባቶቹ ግን ጣኦታትን አምልከዋል። ለዚህም ደግሞ የሙሴ ህዝቦች በግብፅና ከግብፅ ከወጡ በኋላ የተከሠተው ክስተት እንደ አንኳር ነጥብ ማንሳት ይቻላል።
- መፅሐፈ እያሱ ወልደነዌ 24፥ 14
" እግዚአብሔርን ፍሩ፥ በእውነተኛም በፍጹም ልብ አምልኩ፥ #አባቶቻችሁ #ከወንዝ #ማዶ #በግብፅም #ውስጥ #ያመለኩአቸውን #አማልክት #ከእናንተ #አርቁ፥ እግዚአብሔርም አምልኩ።"
ቁርዓንንም ይህንን እውነት እንዲህ በማለት ይተርከዋል፦
.
#ኑፋቄ
(የጳውሎስ በጣኦት አምልኮ መንገድ)
******
#ኑፋቄ ማለት ራሱን የቻለ የአምልኮ ሁኔታ ሲሆን ይህም ደግሞ ጳውሎስ አምላኩን የሚያመልክበት የሆነ የክርስት ሐይማኖት መንገድ ነው። ጳውሎስ የአምልኮ ሁኔታዬን ለሚመረምሩኝ ሰዎች መልሴ ይህ ነው ይላል፦
- የሐዋርያት ስራ 24፥14
" ነገር ግን ይህን እመሰክርልሃለሁ፤ በሕጉ ያለውን በነቢያትም የተጻፉትን ሁሉ አምኜ የአባቶቼን አምላክ እነርሱ #ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ፤"
በማለት ይናገራል።
ጳውሎስ የሚያመልከው የአምልኮ አይነት ይህን ይመስላል። ታድያ ጳውሎስ " የአባቶቼን አምላክ እነርሱ ኑፋቄ ብለው በሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ" ይላልና ለመሆኑ ኑፋቄ ማለት ምን ማለት ነው? በዚህ መንገድ ማምለክ ሲባልስ እንዴትና በምን አይነት መንገድ ማምለክ ማለት ነው?
1.1 ኑፋቄ ምንድ ነው?
#ኑፋቄ ማለት ጥሬ ቃሉ ወይም ፍቺው መንፈቅ ፣ መክፈል፣ መግመስ፣ መቅደድ... ማለት ነው።
ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ ማምለክ የማለት ትርጉሙም፦ የአንድን ነገር እውነት ላይ ቀዳዳ በማበጀትና የሀሰት ፈጠራዎችን በመፍጠር እንዲሁም እውነተኛውን ሀሳብ ላይ የራስ ፈጠራዎችን በማካተት እውነተኛውን ሀሳብ ከእውነታው እንዲርቅ የሚያደርግ የአምልዕኮ ተግባር ነው። በሌላ አባባል በዚህ በኑፋቄ መንገድ ማምለክ ማለት እውነተኛውን አምላክ በመካድ የሚያጠፋ የሆነን ጣኦት ማምለክ ማለት ሲሆን ይህም ደግሞ እውነተኛውን ሀይማኖት በመተው አዲስና መጤ እምነትን መከተል ማለት ነው። ለዚህም ደግሞ፦
- 2ኛው የጴጥሮስ መልዕክት 2፥ 1 - 15
"... ነገር ግን ሀሰተኞች ነቢያት ደግሞ በህዝቡ መካከል ነበሩ እኝዲሁም በመካከላቸው ደግሞ ሀሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ። እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳን ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው እየሳቡ የሚያጠፋ #ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ። ብዙዎች በመዳራታቸው ይከተሏቸዋል፥ በእነርሱም #ጠንቅ #የእውነት #መንገድ ይሰደባል።... #ቅንን #መንገድ #ትተው #ተሳሳቱ።" ይላል!!
ስለዚህ የኑፋቄ ትርጉምና ኑፋቄ በሚሉት መንገድ ማምለክ ማለት ትርጉማቸው ይህ ከሆነ ለመሆኑ የጳውሎስ አባቶች(ነቢያት) መንገድ ምን ነበር? እንዲሁም በኑፋቄአውያን የሚሰደበው የእውነት መንገድ የትኛው ነው? የሚዋጅ ጌታስ ማነው?
የእነዚህን ጥያቄዎች መልስ በተመለከተ አሏህ(ሱወ) በቁርአን እንዲህ ይላል፦
3፡ 83
أفغير دين الله يبغون وله أسلم من في السماوات والأرض طوعا وكرها وإليه يرجعون
በሰማያትና በምድር ያሉ ሁሉ፤ በውድም በግድም ለርሱ የታዘዙ ወደርሱም የሚመለሱ ሲኾኑ (ከሓዲዎች) ከአላህ ሃይማኖት ሌላን ይፈልጋሉን
3፡84
قل آمنا بالله وما أنزل علينا وما أنزل على إبراهيم وإسماعيل وإسحاق ويعقوب والأسباط وما أوتي موسى وعيسى والنبيون من ربهم لا نفرق بين أحد منهم ونحن له مسلمون
«በአላህ አመንን፡፡ በእኛ ላይ በተወረደውም (በቁርኣን)፣ በኢብራሂምና በኢስማዒልም፣ በኢስሓቅም፣ በያዕቆብም፣ በነገዶችም ላይ በተወረደው፤ ለሙሳና ለዒሳም ለነቢያትም ሁሉ ከጌታቸው በተሰጠው (አመንን)፡፡ ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም፡፡ እኛ ለእርሱ ታዛዦች ነን» በል፡፡
3፡85
ومن يبتغ غير الإسلام دينا فلن يقبل منه وهو في الآخرة من الخاسرين
ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከርሱ ተቀባይ የለውም፡፡ እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው፡፡
.
ጳውሎስ ከእስራኤል ውጪ ለአህዛብ የውሸት ሀይማኖትና የውሸት ህግ ሰባኪ ሰው ነው
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እየሱስ ወደ እስራኤል ተልከው በመጡበት ወቅት የክርስትና ሐይማኖት አስተምህሮዎችን በተመለከተ አንዲትን ነጥብ እንኳን አለማስተማራቸው በግልጽ ይታወቃል። ይህን ያደረገው ደግሞ ሐዋርያ ነኝ ባዩ ጳውሎስ ነው እናም በዚህ ርዕስ ላይ በእየሱስ የወንጌል አስተምህሮትና በጳውሎስ አስተምህሮት መካከል ያሉት ሰፊ ልዩነቶች እንቃኛለን።
እየሱስ አህዛብ ላይ የሰውም ስርአት በሆነ ትምህርት አማካኝነት በከንቱ እንደሚመለኩ ስላወቁ ለደቀመዛሙርታቸው ትክክለኛውን የወንጌል ስርዓት ለእስራኤላውያን ብቻ እንዲሠብኩ በላኳቸው ጊዜ የጳውሎስን አስተምህሮት የሚፃረር የሆነ ጠንካራ የሚባል ትዕዛዝ አስተላልፈው ነበር። ይህንም፦
- የማቴዎስ ወንጌል 10፥4-15 & - የማርቆስ ወንጌል 3፥ 15- 19
" እነዚህ 12ቱን እየሱስ ላካቸው እዘዛቸውም እንዲህም አለ፦ በአህዛብ መንገድ አትሂዱ ፣ ወደ ሳሞራውያንም ከተማ አትግቡ፥ ይልቅስ የእስራኤል ቤት ወደሚሆኑት ወደ ጠፉት በጎች ሂዱ እንጂ።"
- የማቴዎስ ወንጌል 15፥9 & የማርቆስ 7፥7
" እየሱስም የሰውን ስርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል ብሎ በእውነት ትንቢት ተናገረ።"
በማለት ለአህዛብ ያልሆነ ወንጌልን ለእስራኤላውያን እንዲሰብኩ ትዕዛዝ ሰጧቸው። በሌላም በኩል ደግሞ በእየሱስ ሳይመረጥ ሃዋርያ ነኝ ያለው ጳውሎስ ከእየሱስ ወንጌል ጋር የማይገናኝና ተቃራኒ የሆነ ትምህርት እርሱም ከእስራኤል ውጪ የግል ፍልስፍናውንና የራሱን ስርዓት ለአህዛብ የሚሰብክ ሠባኪ ብሎም የአህዛብ አስተማሪ ነበር።
ለዚህም ደግሞ ጳውሎስ እንዲህ ይላል፦
- 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ ሰዎች 2 ፥ 5-7
" አንድ እግዚአብሔር አለና በእግዚአብሔርም በሰውም መካከል ደግሞ የሆነ አንድ አለ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ እየሱስ ነው። #ራሱንም #ለሁሉም #ቤዛ #ሆነ፥ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበር። እኔም ለዚህ ነገር #አዋጅ #ነጋሪና #ሀዋርያ #በእምነትና #በእውነትም #የአህዛብ #አስተማሪ #ለመሆን #ተሾምሁ ።" ይላል።
እዚጋ ቆም ብለን ማሰብ ያለብን ነገር ቢኖር እንደ ጳውሎስ አነጋገር ከሆነ እየሱስ እኔ ስለህዝብ ብዬ እሞታለሁ ወይም እሰቀላለሁ ብሏል እያለን ነው። ይህ ደግሞ ፍፁም ውሸት ነው። ምክንያቱም ደግሞ እየሱስ በየትኛዉም ቦታ ላይ እኔ ለሰዎች ሀጢአት ብዬ እሰቀላለሁ ወይም እሞታለሁ ብለው አልተናገሩም። በእርግጥ አይሁዶች አንድን የሠው ልጅ ይዘው እንደሚገርፉትና የሞት ፍርድም እንደሚፈርዱበት አልፎም እንደሚሰቅሉት እንዲሁም በሶስተኛውም ቀን ከሞት እንደ ሚነሳ በማቴዎስ ወንጌል 20፥19 ላይ እየሱስ ትንቢት ተናግረዋል።
- የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 20
18፤ እነሆ፥ ወደ ኢየሩሳሌም እንወጣለን፥ የሰው ልጅም ለካህናት አለቆችና ለጻፎች ይሰጣል፤ የሞት ፍርድም ይፈርዱበታል፥
19፤ ሊዘባበቱበትም ሊገርፉትም ሊሰቅሉትም ለአሕዛብ አሳልፈው ይሰጡታል፥ በሦስተኛውም ቀን ይነሣል አላቸው።
እናም የዚህ የቤዛነት ጉዳይ ሲነሳ እየሱስ ስለ አንድ ሰው ተይዞ መሠቀል ነው እንጂ የሚያወሩት እየሱስ ስለራሳቸው ቤዛ መሆን አይደለም። በአንፃሩ ደግሞ ይህን አንድን ሰው ለብዙዎች ቤዛ እንደሚሆን የተናገረውም #ቀያፋ የሚባል ሰው ሲሆን አይሁዶች ፣ ካህናቶችና የካህናት አለቆች እየሱስን ይዘነዋል በማለት እየሱስ መስሏቸው የሆነን ሰው ይዘው ለፍርድ ካቀረቡት በኋላ እነርሱ የያዙት ሰውዬ በሚገርፉበት ወቅት ይህ #ቀያፋ የሚባል አንድ የካህናት አለቃ ነው ይህን የተናገረው። ለዚህም
- የዮሐንስ ወንጌል 11፥50 & 18 ፥ 14
" ከካህናት አለቆችም መካከል አንድ #ቀያፋ የሚባል ሰው ፦ #ህዝቡ #ሁሉ #ከሚጠፋ #አንድ #ሰው #ስለህዝብ #ይሞት #ዘንድ #ይሻላል ብላችሁ አታስቡም? ብሎ ለአይሁድ የመከራቸው ነበረ።"
ወደ ዋናው ነጥባችን እንመለስና ጳውሎስ ከእስራኤል ውጪ በመሄድ በዚህ መልኩ ለአህዛብ አዋጅ ነጋሪና የአህዛብ አስተማሪ በመሆን እንደተሾመም በ1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥6-7 ተናግሯል ።
እናም በምዕራፍ ሶስት ላይ ወንጌል ማለት ትርጉሙ የምስራች ማለት እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን የምስራቹንም ደግሞ እስራኤላውያን እንጂ አህዛብን የማይመለከት እንደሆነ እየሱስ የደነገጉት ጉዳይ ነው። ወይንም በሌላ አገላለፅ ይህንን የምስራች (ወንጌል) የሚሰበከው ቤተ እስራኤላውያን ለሆኑት (ለጠፉት የእስራኤል በጎች) ብቻና ብቻ መሆኑን ተመልክተን ነበር። ታድያ የጳውሎሱ አዋጅ ግን ከዚህ ከእየሱሱ የምስራች ጋር ፍፁም ይለያል።
በዚህም በ1ኛ የጢሞቴዎስ ምዕራፍ 2፥5-7 መሠረት ጳውሎስ የእየሱስን ወንጌል ሰባኪ ሳይሆን ለአህዛብ የራሱ ስርዓት የሆነ የውሸት ሀይማኖትና የውሸት አዋጅ የሚደነግግ ወይም ህግ የሚያወጣ የውሸት ሀይማኖት ህግ አውጪ ፣ ያወጣውንም ህግ በሀሰት የመንፈስ ትንቢት አዋጁን ወይም ህጉን የሚተረጉም የውሸት ሀይማኖትና የውሸት ህግ ተርጓሚ
እንዲሁም ያወጣውንም የውሸት አዋጅ ወይም ህጉን ከእስራኤል ውጪ በአህዛብ ለማስፈፀም አዋጁን የሚያውጅ፣ የሚናገርና የሚፈፅም የውሸት ሀይማኖትና የውሸት ህግ አስፈፃሚ በአጠቃላይ የአህዛብ የውሸት ሀይማኖትና የውሸት ህግ አስተማሪ ሰው ነው። ታድያም ጳውሎስ ይህንም ያደረግኩት ከአይሁድ ስለምበልጥና አይሁድን ለመጥቀም ብዬ ከእግዚአብሔር የተቀበልኩት አስተምህሮ ነው ይላል፦
- ወደ ገላትያ ሰዎች 1፥ 14-16
"... ከአይሁድ ስርአት እበልጥ ነበር። ነገር ግን በፀጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአህዛብ መካከል ስለርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ገለጠው።
- 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፥ 20
" አይሁድ እጠቅም ዘንድ ከአይሁድ ጋር አይሁዳዊ ሆንኩ።" ይላል
ይህንንም የጳውሎስ ውሸት በተመለከተ አሏህ(ሱወ) በቁርዓን ሲናገር እንዲህ በማለት ይናገራል፦
2፥ 79
فويل للذين يكتبون الكتاب بأيديهم ثم يقولون هذا من عند الله ليشتروا به ثمنا قليلا ۖ فويل لهم مما كتبت أيديهم وويل لهم مما يكسبون
ለነዚያም መጽሐፉን በእጆቻቸው ለሚጽፉና ከዚያም በርሱ ጥቂትን ዋጋ ሊገዙበት «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» ለሚሉ ወዮላቸው፡፡ ለነርሱም ከዚያ እጆቻቸው ከጻፉት ወዮላቸው፡፡ ለነሱም ከዚያ ከሚያፈሩት (ኃጢኣት) ወዮላቸው፡፡
.
የክርስትና ሀይማኖት
እና የሰይጣን ትስስር
******* **************
እንደሚታወቀው የክርስትና እምነት ተከታዮች መንግስተ ሰማይ መውረስ እንዲችሉ በእየሱስ መሠቀል ማመን መቻል አለባቸው። ይህም የሚሆነው እየሱስ ከተሠቀሉ ብቻ ነው። ይህ ካልሆነ ግን ከሰው ሁሉ ምስኪኖች እነርሱ ሲሆኑ እምነታቸውም ስብከታቸውም ከንቱ ነው፥ እንዲህ ብለው በመናገራቸውም ምክንያት ደግሞ ሐጢአተኞችም ናቸው።( 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ 15፥ 10- 17)
ስለእየሱስ የመሰቀልና አለመሠቀል ጉዳይ በሌላኛው ክፍል በሰፊው የዳሰስነው አጀንዳ ሲሆን ይህንንም በተመለከተ እየሱስ እንዳልተሰቀሉ አረጋግጠንም ነበር። ታድያ ይህ እንዲህ እንዳለ ይሁንና #ለጊዜው እየሱስ ለእነሱ ሐጢአት ሲሉ ሞተው ተሰቀሉ ብለን #እንስማማና በዚህም ህዝበ ክርስቲያኖች መንግስተ ሰማይ ይወርሳሉ እንበል። ነገር ግን እንዴትና በማን ምክንያት ነበር እየሱስ ተይዘው የተሰቀሉት!? እየሱስ ተይዘው ተሰቀሉ ብለን ተስማምተናል እየሱስ ተይዘው እንዲሠቀሉ ያደረገውም በሰይጣን ስራ አማካኝነት ነበር።
ምክንያቱም ሰይጣን በአስቆሮቱ ይሁዳ ላይ ገብቶበትም ነበር እየሱስን በሰላሳ ዲናር ለካህናቶችና ለካህናት አለቆች በመሸጥ አሳልፎ የሠጠው።
- የዮሐንስ ወንጌል 13፥ 21 - 30
"... እውነት እውነት እላችኋለሁ ከእናንተ አንዱ እኔን አሳልፎ ይሰጠኛል አለ። እነርሱም ማን ነው ብለው ጠየቁት። እየሱስም ቁራሽ እንጀራ አንስቼ የምሰጠው እርሱ ነው አለ። ቁራሹም አንስቶ ለስምኦን ልጅ ለአስቆሮቱ ይሁዳ ሰጠው፥ ቁራሹም ሲቀበል ያን ጊዜ #ሰይጣን #በአስቆሮቱ #ይሁዳ #ገባበት፥ ቁራሹም ከተቀበለም በኋላ ሌሊት ነበር ወዲያውኑ ወጣ።"
ይሁዳ በዚያች ሌሊት ቁራሽ ተቀብሎ ከወጣ በኋላም ወደ ካህናቶችና የካህናት አለቆች ጋር በመሄድ እየሱስን አሳልፎ እንዲሠጣቸው ዋጋ ጠየቀ። በዚህም ሰላሳ ዲናርን መዘኑለት ፥ ይሁዳ ሰላሳውን ብር ተቀብሎም ሰዎቹን በማስከተል እነርሱ ወደነበሩበት መጡ። በዚህም ጊዜ የምስመው ሰው እየሱስ ነውና ያዙት ብሎ ምልክት ሰጥቷቸው ስለነበር ይሁዳም ወደፊት ቀረብ በማለት መምህር ሆይ በማለት ሳመው። ያን ጊዜም የተሳመው ሰው እየሱስ ነው ብለው ያዙት። (ማቴዎስ 26፥ 14 -49) ከዚያም ያው ወስደው ሰቀሉት የሚለው ነው የሚቀጥለው።
ስለዚህ ይህ ሁሉ የሰይጣን ተግባር ነው። ምክንያቱም ለአስቆሮቱ ይሁዳ ሰይጣን ባይጠናወተው ኖሮ እንደ ሌሎቹ ቀሪ 11 ደቀመዛሙርት ሀሉ ታማኝ ይሆን ነበር እንጂ እየሱስን አሳልፎ ባልሠጠና ስቅለትም ባልነበረ ነበር። እናም ለክርስቲያኖች መንግስተ ሠማይ መግባት የእየሱስ መሠቀል የግድ ነውና፤ እንዲሁም ለእየሱስ መያዝ የአስቆሮቱ ይሁዳ በሠይጣን መለከፍም ዋናው መንስኤ ሲሆን የይሁዳ አሳልፎ መስጠትና የእየሱስ መሠቀል ደግሞ #የሰይጣን #ስራ #ውጤት #ነው ። በዚህም የተሰቀለው ሰውዬ እንዲሰቀል በማድረግ ሰይጣን አይነተኛ የሆነ ተግባር ፈፅሟልና በዚህም #ሰይጣን #ለክርስትና #እምነት #ተከታዮች #የጀርባ #አጥንት ነው። ይህም ብቻ አይደለም በሚስጥረ ታቦት ውስጥ ኪሩቤል የሚባለው ሠይጣን ዋነኛው ተዋናይ ነው ኢንሽ አላህ ወደፊት እንመለከተዋለን።
አሏህ ቀጥተኛውን መንገድ ይምራን ፅናቱንም ይስጠን። አላሁመ አሚን!!!
2፡ 117
بديع السماوات والأرض ۖ وإذا قضى أمرا فإنما يقول له كن فيكون
#ሰማያትንና #ምድርን #ያለብጤ #ፈጣሪ #ነው፤ ነገርንም (ማስገኘት) በሻ ጊዜ ለርሱ የሚለው፡- «ኹን ነው፤» ወዲያውም ይኾናል፡፡
✔ አል-ኻሊቁ ጌታችን አላህ(ሱወ) የሁሉ ነገር ብቸኛ ፈጣሪ መሆኑን በዚህ መልኩ ካየን ቀጥሎም ደግሞ #በሶስቱ የአላህ ስሞች ማለትም #አል_ኻሊቅ ፣ #አል_ባሪእ እና #አል_ሙሶዊር መካከል ያሉት ልዩነቶችን ማወቅ ይኖርብናል። እነኚህ ሶስት ስሞች ተቀራሪቢ ትርጉም ያላቸው ሲሆኑ የፍጥረትን አፈጣጠር የሚገልፁ ናቸው። አላህ (ሱወ) እንዲህ ብሏል፦
59፡ 24
هو الله الخالق البارئ المصور ۖ له الأسماء الحسنى ۚ يسبح له ما في السماوات والأرض ۖ وهو العزيز الحكيم
እርሱ አላህ #ፈጣሪው (ከኢምንት) #አስገኚው፣ #ቅርጽን_አሳማሪው ነው፡፡ ለእርሱ መልካሞች ስሞች አልሉት፡፡ በሰማያትና በምድርም ያለው ሁሉ ለእርሱ ያሞግሳል፡፡ እርሱም
- 1) አል-ኻሊቅ (ፈጣሪ) ማለት ካልነበሩበት ያስገኘና የፈጠረ ማለት ነው።
- 2) አል-ባሪእ ( ከምንም አስገኚው) ማለት ሁሉንም ፍጥረት ለተፈጠሩበት አላማ የሚያዘጋጅ ማለት ሲሆን
- 3) አል-ሙሶዊር (ቅርፅን አሳማሪው) ማለት ደግሞ ለእያንዳንዱ ፍጥረት የየራሱ ገፅታ (ቅርፅ) የሚያላብስ ወይም ፍጥረታትን በየቅርጻቸው አድርጎ የፈጠረ ማለት ነው። ለምሳሌ የሰው ልጅ የራሱ ቅርፅ አለውና ሰው የሚመስል ሌላ ፍጥረት የለም፣ ጨረቃ የራሷ ቅርፅ አላት ጨረቃ የሚመስል የለም፣ፀሀይ፣ፈረስ፣ጉንዳን፣ዝሆን፣አንበሳ...
... ይቀጥላል...
በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ የአዲስ ኪዳን አራማጆችና የክርስትና ሐይማኖት መስራቾች እግዚአብሔር ሰማያትና ምድር በፈጠረ ጊዜ እየሱስ ከርሱ ጋር ነበረ በማለት ሲሰብኩ በዚህም ደግሞ አምላክ የሆነው እየሱስ ስጋ ለብሶ በሠው መልክ ተገለጦ ወደዚህ ምድር መጣ በማለት አምላክ ሶስት መሆናቸውንን ያምናሉ። ነገር ግን እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ይናገራል፦
- ትንቢተ ኢሳያስ 43፥10
" ታውቁና ታምኑብኝ ዘንድ እኔም እንደሆንሁ ታስተውሉ ዘንድ፥ እናንተ የመረጥሁትም ባሪያዬ ምስክሮቼ ናችሁ ይላል እግዚአብሔር፤ #ከእኔ #በፊት #አምላክ #አልተሠራም #ከእኔም #በኋላ #አይሆንም። "
እግዚአብሔር ሰማያትና ምድር በፈጠረ ጊዜ አንድና ብቸኛ የሆነ አምላክ ነበረ በዚያን ጊዜ እየሱስም ሆነ ሌላ አካል ከርሱ ጋር ማንም አልነበረም። ይህንንም ተጨባጭ እውነት እንዲህ በማለት ይመሰክራል፦
- ትንቢተ ኢሳያስ 44፡24
" ከማኅፀን የሠራህ፥ የሚቤዥህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል ። #ሁሉን #የፈጠርሁ፥ #ሰማያትን #ለብቻዬ #የዘረጋሁ #ምድርንም #ያጸናሁ እግዚአብሔር እኔ ነኝ፤ #ከእኔ #ጋር #ማን #ነበረ? "
- ትንቢተ ኢሳያስ 45፥5-6
"5፤6፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ ከእኔም ሌላ ማንም የለም፤ ከእኔም በቀር አምላክ የለም፤ በፀሐይ መውጫና በምዕራብ ያሉ ከእኔ በቀር ማንም ሌላ እንደሌለ ያውቁ ዘንድ አስታጠቅሁህ፥ አንተ ግን አላወቅኸኝም፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ #ከእኔም #ሌላ #ማንም #የለም። "
- ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕ. 45
21፤ ይናገሩ ይቅረቡም በአንድነትም ይማከሩ፤ ከጥንቱ ይህን ያሳየ ከቀድሞስ የተናገረ ማን ነው? ያሳየሁም የተናገርሁም እኔ እግዚአብሔር አይደለሁምን? #ከእኔም #በቀር #ሌላ #አምላክ #የለም፤ እኔ ጻድቅ አምላክና መድኃኒት ነኝ፥ ከእኔም በቀር ማንም የለም።
22፤ እናንተ የምድር ዳርቻ ሁሉ፥ እኔ አምላክ ነኝና፥ ከእኔም በቀር ሌላ የለምና ወደ እኔ ዘወር በሉ ትድኑማላችሁ።
እንግዲህ እውነቱ ይህ ነው። እነርሱ ሶስት አምላኮች አሉ የሚሉት ጉዳይ በአላህ ላይ የተጠነሰሰ የውሸት ወሬያቸው ሲሆን ይህም ከእውነት የራቀ የፈጠራ ቅጥፈት ብቻ ነው። አላህ(ሱወ) ይህንን አስመልክቶ እንዲህ በማለት ይናገራል፦
4፡ 171
يا أهل الكتاب لا تغلوا في دينكم ولا تقولوا على الله إلا الحق ۚ إنما المسيح عيسى ابن مريم رسول الله وكلمته ألقاها إلى مريم وروح منه ۖ فآمنوا بالله ورسله ۖ ولا تقولوا ثلاثة ۚ انتهوا خيرا لكم ۚ إنما الله إله واحد ۖ سبحانه أن يكون له ولد ۘ له ما في السماوات وما في الأرض ۗ وكفى بالله وكيلا
እናንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ወሰንን አትለፉ፡፡ በአላህም ላይ እውነትን እንጅ አትናገሩ፡፡ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ዒሳ የአላህ መልክተኛ ወደ መርየም የጣላት «የኹን» ቃሉም ከእርሱ የኾነ መንፈስም ብቻ ነው፡፡ በአላህና በመልክተኞቹም እመኑ፡፡ « ( #አማልክት ) #ሦስት #ናቸው » #አትበሉም፡፡ ተከልከሉ፤ ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ #አላህ #አንድ #አምላክ #ብቻ ነው፡፡ ለእርሱ ልጅ ያለው ከመኾን የጠራ ነው፡፡ በሰማያትና በምድር ያለ ሁሉ የርሱ ነው፡፡ መመኪያም በአላህ በቃ፡፡
⓾ አል-ኻሊቅ (الخلاق )
[[[ ፈጣሪ ]]]
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
- #አል_ኻሊቅ ማለት ትርጉሙ የሁሉም ነገር ፈጣሪ፣ የሁሉም ነገር ጀማሪ፣ የሁሉም ነገር አስገኝ ማለት ነው። መፍጠር ማለት አንድን ያልነበረ ነገር ማስገኘት ማለት ነው። አል-ኻሊቁ አላህ ሁለመናው ፈጣሪ ስለመሆኑ ሲናገር እንዲህ ይላል፦
15፡ 86
إن ربك هو الخلاق العليم
ጌታህ እርሱ (ያልነበረን) #ፈጣሪው ዐዋቂው ነው፡፡
39፡ 62
الله خالق كل شيء ۖ وهو على كل شيء وكيل
አላህ #የነገሩ #ሁሉ #ፈጣሪ ነው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡
40፡62
ذلكم الله ربكم خالق كل شيء لا إله إلا هو ۖ فأنى تؤفكون
ይሃችሁ ጌታችሁ አላህ ነው፤ #የነገሩ #ሁሉ #ፈጣሪ ነው፤ ከርሱ ሌላ አምላክ የለም፤ ታዲያ (ከእምነት) ወዴት ትመለሳላችሁ፡፡
✔ ሁለት አይነት እውቀት አለ
1) በአላህ(ሱወ) መኖር ማመን። ይህንን እውቀት ሁሉም የሰው ልጆች(ሙስሊሙም፣ ክርስትያኑም፣ ሌላውም) በአንድነት ይጋሩታል። ነገር ግን እኛ ሙስሊሞች አላህ ብቸኛ ፈጣሪ መሆኑን ብናምንም ሌሎች ግን ይህንን አይቀበሉም። አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦
31፡25
ولئن سألتهم من خلق السماوات والأرض ليقولن الله ۚ قل الحمد لله ۚ بل أكثرهم لا يعلمون
ሰማያትንና ምድርንም የፈጠረ ማን እንደሆነ ብትጠይቃቸው በእርግጥ አላህ ነው ይላሉ፡፡ ምስጋና ለአላህ ይገባው በላቸው፡፡ ይልቁንም አብዛኛዎቹ አያውቁም፡፡
2) አላህ(ሱወ) የመውደድ እና ከሱ ሐያዕ የማድረግ እውቀት። እሱ ፈጥሮናልና ከሱ ሐያዕ እናደርጋለን። በሱ ከማመፅ እንጠነቀቃለን። የዚህ አይነቱ እውቀት የአምልኮ እውቀት ሲሆን በዚህም አላህን በብቸኝነት ማምለክና የተፈጠርንበት አላማ ከግብ ማድረስ ነው።
- አል-ኻሊቅ የፈጠረንን አምላካችንን የሚያስታውሰን ስም ነው። እርሱ ፍጥረታትን በሙሉ በብቸኝነት የፈጠረ ጌታ ነው።
አላህ ከሱ ውጪ ፈጣሪ የለም። ይህን በሌላ የቁርዓን አንቀጽ ውስጥ ደግሞ ያረጋግጥልናል። እንዲህ በማለት፦
7፡54
إن ربكم الله الذي خلق السماوات والأرض في ستة أيام ثم استوى على العرش يغشي الليل النهار يطلبه حثيثا والشمس والقمر والنجوم مسخرات بأمره ۗ ألا له الخلق والأمر ۗ تبارك الله رب العالمين
ጌታችሁ ያ ሰማያትንና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ አላህ ነው፡፡ ከዚያም (ስልጣኑ) በዐርሹ ላይ ተደላደለ፡፡ (አላህ) ሌሊትን በቀን ፈጥኖ የሚፈልገው ሲኾን ይሸፍናል፡፡ ፀሐይንና ጨረቃንም ከዋክብትንም በትእዛዙ የተገሩ ሲኾኑ (ፈጠራቸው)፡፡ ንቁ! መፍጠርና ማዘዝ የእርሱ ብቻ ነው፡፡ የዓለማት ጌታ አላህ (ክብሩ) ላቀ፡፡
የክርስትና እምነት በሚስጥረ ስላሴ ሚስጥር ውስጥ ፈጣሪ አምላክ ሶስት እንደሆኑ ይደነግጋል። ይህም ማለት ህዝበ ክርስትያኖች ፈጣሪ አምላክ በአካል ሶስት በመለኮት አንድ ናቸው በማለት ያምናሉ። ታድያ ከዚህ ከሚስጥረ ስላሴ ፅንሰ ሀሳብ አንጻር በመፅሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ ላይ የፈጣሪ አምላክ ሶስትነት እንዴት ይታያል?
.
99ኙ የአላህ መልካም ስሞች ትርጉም
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ክፍል 16
⓽ አል ሙተከቢሩ { المتكبار}
[[[[ ኩሩው ]]]]]
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
- አል-ሙተከቢር ፦ ማለት ትርጉሙ #ኩሩ ማለት ነው። ታድያ ብቸኛው ፣ንጉስ፣ ከጉድለት የጠራው፣ ሃያሉ፣ጥበበኛው... ከሆነው ጌታችን አላህ(ሱወ) የመልካም ስሞች መካከልም ይህ #አል_ሙተከቢር የሚለው ስም ሌላኛው የባህሪያቱ መገለጫውና የመጠሪያው ስሙ በመሆን ይታወቃል። እናም ይህ አል-ሙተከቢር ( ኩሩ) የሆነው ጌታም በቁርዓን ሲናገር እንዲህ ይላል።
59፡ 23
هو الله الذي لا إله إلا هو الملك القدوس السلام المؤمن المهيمن العزيز الجبار #المتكبر ۚ سبحان الله عما يشركون
<< እርሱ አላህ ነው። ያ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፤ ንጉሱ፣ ከጉድለት ሁሉ የጠራው፣ የሰላም ባለቤቱ ፣ ፀጥታን ሰጪው፣ ባሮቹን ጠባቂው፣ አሸናፊው፣ ሃያሉ፣ #ኩሩው ነው። አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ!።"
ራሱን ቻይና የተብቃቃ የሆነው ጌታ ኩራት የርሱ ልብሱ ነው። ለዚህም ረሱል(ሰዐወ) እንዲህ ይላሉ፦
በሀዲስ ቁዱስ ላይ አቡ ሁረይራ (ረዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- “ሃያሉ የተከበረው ጌታ እንዲህ ብሏል፦ ኩራት ካባዬ፤ ታላቅነት መታጠቂያዬ ነው። ከእነሱ ከአንደኛው እንኳ ከእኔ ጋር የሚፎካከረውን ወደ ጀሐነም እሳት እወረውረዋለሁ።" በማለት ተናግሯል።
ሙግት 1፦ አጋር እስማኤልን ስትወልድ አብረሐም 86 አመታቸው ነበር። (ዘፍጥ 16፥16)
ሙግት 2 ፦ አብረሐምና እስማኤል ቁልፈተ ስጋቸው ሲገረዙ አብረሐም 99 ዓመቱ ነበረ። እስማኤልም 13 አመቱ ነበረ።
- ኦሪት ዘፍጥረት ምዕ. 17
23፤ #አብርሃምም #ልጁን #እስማኤልን፥ በቤቱም የተወለዱትን ሁሉ፥ በብሩም የገዛቸውን ሁሉ፥ ከአብርሃም ቤተ ሰብ ወንዶቹን ሁሉ ወሰደ፥ የቍልፈታቸውንም ሥጋ እግዚአብሔር እንዳለው በዚያው ቀን #ገረዘ ።
24፤ አብርሃምም የቍልፈቱን ሥጋ በተገረዘ ጊዜ የዘጠና ዘጠኝ (99) ዓመት ሰው ነበረ፤
25፤ #ልጁ #እስማኤልም የቍልፈቱን ሥጋ በተገረዘ ጊዜ የአሥራ ሦስት(13) ዓመት ልጅ ነበረ።
26፤ በዚያው ቀን አብርሃም ተገረዘ፥ ልጁ እስማኤልም።
ሙግት 3፦ ኢስሐቅ ሲወለድና በስምንተኛው ቀን ሲገረዝ የአብረሐም እድሜ 100 አመት ነበረ
- ኦሪት ዘፍጥረት ምዕ. 21
3፤ አብርሃምም የተወለደለትን ሳራ የወለደችለትን የልጁን ስም #ይስሐቅ ብሎ ጠራው።
4፤ አብርሃምም ልጁን ይስሐቅን እግዚአብሔር እንዳዘዘው በስምንተኛ ቀን ገረዘው።
5፤ አብርሃምም ልጁ #ይስሐቅ በተወለደለት ጊዜ የመቶ(100) ዓመት ዕድሜ ነበረ።
✔ በዚህም የመፅሐፍ ቅዱስ መረጃ መሠረት ብቻ የሔድን እንደሆነ አብረሐም ለመስዋዕትነት ያቀረበው የበኩር ልጁ #እስማኤል ነበረ ማለት ነው። ምክንያቱም ደግሞ የእስማኤል እድሜ ለማግኘት፦
ℹ አጋር እስማኤልን ስትወልድ አብረሐም 86 አመቱ ነበረ፣ አብረሐምና እሰማኤል ሲገረዙ አብረሐም 99 አመቱ ነበረ፣ እንዲሁም እስማኤል ሲገረዝ 13 ዓመቱ ነበረ። 99-86= 13
ℹ ይስሐቅ ሲወለድ አብረሐም እድሜው 100 ነበረ። 100 - 99 = 1
ስለዚህ (13+1 =14) እስማኤል ከኢስሐቅ በ14 አመት ይበልጣል ማለት ነው።
ታድያም እንደ አዲስ ኪዳን ምዕራፎች በተለይም እንደ የጳውሎስ አስተምህሮ ከሆነ አብረሐም ለመስዋዕትነት ያቀረበው አንደኛው ልጁ ኢስሐቅ እንደሆነ ይናገራል። ለዚህም፦
- ወደ ዕብራውያን 11፡17-18
" አብርሃም በተፈተነበት ጊዜ #ይስሐቅን #በእምነት #አቀረበ፥ የተስፋን ቃል የተቀበለው። በይስሐቅ ዘር ይጠራልሃል የተባለለት እርሱም #አንድ #ልጁን #አቀረበ፤"
- የያዕቆብ መልእክት ምዕ. 2
21፤ አባታችን #አብርሃም #ልጁን #ይስሐቅን #በመሠዊያው #ባቀረበ #ጊዜ በሥራ የጸደቀ አልነበረምን?
22፤ እምነት ከሥራው ጋር አብሮ ያደርግ እንደ ነበረ፥ በሥራም እምነት እንደ ተፈጸመ ትመለከታለህን?
እውነቱ ግን ከላይ እንደተመለከትነው ነው በዚህም ለእርድ የቀረቡት እስማኤል ናቸው ማለት ነው። ስለዚህም ጉዳይ አሏህ(ሱወ) በቁርዓን ሲናገር፦
37፡ 102
فلما بلغ معه السعي قال يا بني إني أرى في المنام أني أذبحك فانظر ماذا ترى ۚ قال يا أبت افعل ما تؤمر ۖ ستجدني إن شاء الله من الصابرين
ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
37፡103
فلما أسلما وتله للجبين
ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
37፡104
وناديناه أن يا إبراهيم
ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!
37፡105
قد صدقت الرؤيا ۚ إنا كذلك نجزي المحسنين
ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
37፥106
إن هذا لهو البلاء المبين
ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡
37፡ 107
وفديناه بذبح عظيم
በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
✔ ነብዩ አብረሃም/ኢብራሒም (ዐሰ) ለእርድ ያቀረቡት ልጃቸው ጉዳይ ይህን ይመስላል።
ለሌሎችም ሼር ያድርጉ!
t.me//AkeelComparative
.
#አብርሐም ለእርድ ያቀረበው የበኩር ልጅ
#ኢስሐቅ ነው ወይስ #ኢስማኤል?
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
✔ ኢድ አል አድሃ አረፋ እና መስዕዋት
የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል ታሪካዊ ዳራው ነብዩ ኢብራሂም የበኩር ልጃቸውን ለአላህ ለመስዋት ያደረጉት ቁርጠኝነት የተመላበት ውሳኔ እና ለመስዋዕትነት የቀረበውም ልጅ ያሳየው የተለየ ጽናት ነው። በዚህም ደግሞ የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል ይከበራል። ዋናው ነጥብ ግን የዚህ የመስዕዋት ጉዳይ ሲነሳ ብዙ ጊዜ በእስልምና እና የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ዘርፈ ብዙ ክርክር ይነሳበታል።
ታድያም ነብዩ አብረሃም/ ኢብራሂም (ዐሰ) የበኩር ልጃቸውን ያገኙት በእርጅና ዘመናቸው ነበር። አብረሃም/ኢብራሂም (ዐሰ) ታላቅ ሚስታቸው ሳራ መሐን ስለነበረችና ለፍሬ ባለመብቃቷም " ያ አላህ ያለ ዘር አታስቀረኝ፤ እኔን የሚተካ ሷሊህ ልጅ ስጠኝ" ብለው ዱዓ አደረጉ።
- ኦሪት ዘፍጥረት ምዕ. 11
30፤ ሳራም #መካን ነበረች፤ #ልጅ #አልነበራትም።
በዚህ መሠረት በሳራ ፈቃደኝነት ነብዩ አብረሃም/ ኢብራሂም (ዐሰ) #ሐጀር ወይም አጋር# የምትባለውን ግብጻዊ የሆነችውን የቤት ሰራተኛቸውን አገቡ።
- ኦሪት ዘፍጥረት ምዕ. 16
1፤ የአብራም ሚስት #ሳራ ግን #ለአብራም #ልጅ #አልወለደችለትም ነበር፤ ስምዋ #አጋር የተባለ ግብፃዊት ባሪያም ነበረቻት።
2፤ ሳራም አብራምን። እነሆ፥ እንዳልወልድ እግዚአብሔር ዘጋኝ፤ ምናልባት ከእርስዋ በልጅ እታነጽ እንደ ሆነ ወደ እርስዋ #ግባ #አለችው።
3፤ አብራምም የሳራን ቃል ሰማ። አብራምም በከነዓን ምድር አሥር ዓመት ከተቀመጠ በኋላ፥ የአብራም ሚስት #ሳራ ግብፃዊት ባሪያዋን #አጋርን ወስዳ #ለባልዋ #ለአብራም #ሚስት #ትሆነው ዘንድ ሰጠችው።
4፤ እርሱም ወደ #አጋር #ገባ፥ #አረገዘችም።
ከዚህም በኋላ የነብዩ አብረሃም/ ኢብራሂም(ዐሰ) ሁለተኛዋ ሚስት የሆነችው ሐጀር/አጋር ለአብረሃምም የመጀመሪያቸው የሆነውን #እስማኤል የሚባል ወንድ ልጅን ወለደችላቸው።
- ኦሪት ዘፍጥረት ምዕ. 16
11፤ የእግዚአብሔር መልአክም አላት። እነሆ አንቺ ፀንሰሻል፥ ወንድ ልጅንም ትወልጃለሽ፤ ስሙንም #እስማኤል #ብለሽ #ትጠሪዋለሽ፥ እግዚአብሔር መቸገርሽን ሰምቶአልና።
15፤ #አጋርም ለአብራም ወንድ ልጅን ወለደችለት፤ አብራምም አጋር የወለደችለትን የልጁን ስም #እስማኤል ብሎ ጠራው።
16፤ አጋር እስማኤልን ለአብራም በወለደችለት ጊዜ አብራም የሰማንያ ስድስት (86) ዓመት ሰው ነበረ።
የእስማኤል እናት ሐጀር/አጋር እስማኤልን ከወለደች ከ14 አመት በኋላም መሐን የነበረችውና የአብረሀም የመጀመሪያዋ ሚስት የሆነችው ሳራም ደግሞ በእርጅናዋ ዘመንም #ኢስሐቅን አረገዘች።
-ኦሪት ዘፍጥረት ምዕ. 17
19፤ እግዚአብሔርም አለ። በእውነት ሚስትህ #ሳራ ወንድ ልጅን ትወልድልሃለች፥ ስሙንም #ይስሐቅ ብለህ ትጠራዋለህ፤ ከእርሱ በኋላ ለዘሩ የዘላለም ቃል ኪዳን እንዲሆን ቃል ኪዳኔን ከእርሱ ጋር አቆማለሁ።
እንግዲህ ሁሉን ማድረግ የሚችለው አምላክም በእርጅና ዘመንዋ ለሳራ ወንድ ልጅ ሰጣት ስሙንም #ኢስሐቅ ተብሎ ተጠራ። ይህንን አውነት በመፅሐፍ ቅዱስ እንዲህ ተጠቅሷል፦
- ኦሪት ዘፍጥረት ምዕ. 21
2፤ #ሳራም #ፀነሰች፥ እግዚአብሔርም በተናገረው ወራት ለአብርሃም በእርጅናው ወንድ ልጅን ወለደችለት።
3፤ አብርሃምም የተወለደለትን #ሳራም #የወለደችለትን የልጁን ስም #ይስሐቅ ብሎ ጠራው።
ከዚህ ቀጥሎም ደግሞ አብረሐም ለመስዋዕትነት ያቀረበው #የበኩር #ልጅ ማነው? እስማኤል ወይስ ኢስሐቅ ወደሚለው የመከራከሪያ ነጥብ እናምራ፦
#ሶሒሕ #ቡኻሪ
ቅጽ 2 መጽሐፍ 15 ቁጥር 85
በአል-ባራእ የተተረከ
ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ኹጥባውን በነህር (ኢድ አል-አድሓ) ቀን አቅርበው እንዲህ አሉ፡- "በዚህ እለት ልንሰራው የሚገባን የመጀመሪያው ነገር ሶላትን መስገድ ከዚያም መመለስ እና ማረድ ነው (የእኛን መስዋዕትነት)። ስለዚህ ማንም የሰራ ሰው። በሱናችን መሰረት ሰራ። ከሶላት በፊትም ያረደ ለቤተሰቦቹ ያቀረበው ስጋ ብቻ ነው በምንም አይነት መልኩ መስዋዕት ተደርጎ አይቆጠርም።አጎቴ አቡ ቡርዳ ቢን ናይ ተነሥቶ እንዲህ አለ። የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ከሶላት በፊት መስዋዕቱን አረድኩ ነገር ግን ከትልቅ በግ የምትበልጥ አንዲት የፍየል ጠቦት አለችኝ" ነብዩም "በመጀመሪያው ምትክ አርደዋታል እና እንደዚህ አይነት ፍየል ለማንም እንደ መስዋዕትነት አይቆጠርም" ብለዋል. ካንተ በኋላ"
*****
ቅፅ 2፣ መጽሐፍ 15፣ ቁጥር 99
አል ባራእ ቢን አዚብ ዘግበውታል።
በነህር የአላህ መልእክተኛ እለት ከዒድ ሰላት በኋላ ኹጥባውን አቅርበው እንዲህ ብለዋል፡- “እንደኛ የሰገደና መስዋዕቱን እንደ እኛ የገደለ ሰው በኛ (ኑሱክ) የመስዋዕት ባህላችንን ሰራ። ከዚህ በፊትም መስዋዕቱን ያረደ ሰው ነበር። ጸሎቱ፣ ከዚያ ያ የበግ ሥጋ ብቻ ነበር (ማለትም መስዋዕት አይደለም)። አቡ ቡርዳ ቢን ናይየር ተነሥቶ እንዲህ አለ፡- "የአላህ መልእክተኛ ሆይ! በአላህ እምላለሁ ሶላትን (ኢድ) ከመስገዴ በፊት መስዋዕቴን አርጄ ዛሬ የመብላትና የመጠጣት ቀን (የአልኮል መጠጥ የሌለበት መጠጥ) መስሎኝ ነበር እናም አዘጋጀሁ። (በማረድ) ቸኮልኩ እና በላሁ እንዲሁም ቤተሰቦቼንና ጎረቤቶቼን አበላሁ። የአላህ መልእክተኛም "ይህ የበግ ስጋ ብቻ ነበር (መስዋዕት አይደለም)" ብለዋል። አቡ ቡርዳም "እኔ አንዲት የፍየል ጠቦት አለችኝ እና ምንም ጥርጥር የለውም ከሁለት በጎች ትበልጣለች ይህ ለእኔ መስዋዕት ይበቃኛል?" ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) “አዎ፣ ካንተ በኋላ ግን ለሌላ (ለመስዋዕትነት) በቂ አይሆንም” ሲሉ መለሱ።
****
ቅጽ 2 መጽሐፍ 15 ቁጥር 101
በJundab የተተረከ
በነህር ቀን ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ሶላትን ሰግደው ኹጥባ ካደረሱ በኋላ መስዋዕቱን አርደው እንዲህ አሉ፡- “ከሶላት በፊት ያረደ ሰው በእሱ ምትክ ሌላ እንስሳ ያርዳል። በላዩ ላይ የአላህን ስም የሚያወሳ መስዋዕት ማረድ አለበት።
*****
ቅጽ 2 መጽሐፍ 15 ቁጥር 102
ጃቢር ብን አብደላህ ዘግበውታል።
በዒድ ቀን ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ከሄዱበት መንገድ በተለየ መንገድ ይመለሱ ነበር።
*****
ቅጽ 2 መጽሐፍ 15 ቁጥር 103
በኡርዋ የተተረከው በአኢሻ (ረዐ) ነው።
በሚና ቀናት (በዙልሂጃ 11፣12 እና 13) ሁለት ወጣት ልጃገረዶች አታሞ እየደበደቡ ነቢዩም በልብሳቸው ተኝተው ሳለ አቡ በክር ወደ እርሷ መጣ። አቡበክርም ወቀሳቸውና ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ፊታቸውን ገለጥ አድርገው አቡ በክርን እንዲህ አላቸው፡- “እነዚህ ቀናት የዒድ ቀናት እና የሚና ቀናት ናቸውና ተዋቸው። ዓኢሻ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አለች፡- “አንድ ጊዜ ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) እያጣሩኝ ነበር እና በመስጂዱ ውስጥ የጥቁር ባሮችን ትርኢት እያየሁ (ዑመር) ወቀሳቸው። ደህና ናቸው (የተጠበቁ)"
*****
ቅጽ 2 መጽሐፍ 15 ቁጥር 104
ኢብኑ አባስ ዘግበውታል።
ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ወጥተው በኢድ አልፈጥር ቀን ሁለት ረከዓ ሰላት ሰገዱ እና ከዚያ በፊትም ሆነ በኋላ ምንም አይነት ሶላት አልሰገዱም እናም በወቅቱ ቢላል አብሮት ነበር
.
ስለ ኢድ አል አድሐ አረፋ
#ሶሒሕ #ቡሓሪ
ቅፅ 2፣ መጽሐፍ 15፣ ቁጥር 71
በአል-ባራእ የተተረከ
ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ኹጥባ ሲያደርሱ ሰምቻለሁ፡- “በዚህ ቀን (በኢድ አል አድሓ የመጀመሪያ ቀን) መጀመሪያ መደረግ ያለበት ነገር መስገድ ነው፣ እናም ከሶላት ከተመለስን በኋላ መስዋዕቶቻችንን እናርዳል (በአላህ ስም ለኢድ አል አድሃ) ። ይህን የሚያደርግ ሰው የኛን ሱና (ባህሎቻችንን) መሰረት አደረገ።"
*****
ቅፅ 2፣ መጽሐፍ 15፣ ቁጥር 72
በአኢሻ ዘግበውታል።
አቡበክር ወደ ቤቴ መጣ ሁለት ትናንሽ አንሷሪ ልጃገረዶች ከጎኔ የቡአትን ቀን አስመልክቶ የአንሷሮችን ታሪክ እየዘፈኑ ነበር። ዘፋኞችም አልነበሩም። አቡበከርም ተቃውሟቸውን ሲገልጹ "በአላህ መልእክተኛ ቤት ውስጥ የሰይጣን የሙዚቃ መሳሪያዎች?!"
የአላህ መልእክተኛም "አቡበክር ሆይ! ለእያንዳንዱ ህዝብ የራሱ መታወቂያ አለው ይህ ደግሞ የእኛ ኢድ ነው" አሉ።
ቅጽ 2 መጽሐፍ 15 ቁጥር 73
አነስ ቢን ማሊክ ዘግበውታል፡-
የአላህ መልእክተኛ በዒድ-አልፈጥር ቀን ጥቂት ተምር ካልበሉ በቀር (ለሶላት) አልሄዱም። አነስም እንደተረከው፡- ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ዊትር የሆነ የተምር ቁጥር ይበሉ ነበር።
*****
ቅጽ 2 መጽሐፍ 15 ቁጥር 74
በአናስ የተተረከ
ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) “ከዒድ ሰላት በፊት (የእርሱን መስዋዕትነት) ያረደ ሰው እንደገና ያርደው” አሉ። አንድ ሰው ተነስቶ "ይህ ቀን የስጋ ምኞት ያለበት ቀን ነው" አለ እና ስለ ጎረቤቶቹ አንድ ነገር ጠቅሷል. ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ያመንኩት ይመስላል። ከዚያም ያ ሰው “ከሁለት በግ ሥጋ ይልቅ የምትወደድ አንዲት የፍየል ጠቦት አለችኝ” ብሎ ተናገረ። ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ለመስዋዕትነት እንዲያርደው ፈቀዱለት። ያ ፍቃድ የሚሰራው ለእሱ ብቻ ይሁን ለሌሎችም እንደሆነ አላውቅም።
ቅፅ 2፣ መጽሐፍ 15፣ ቁጥር 75
አል ባራእ ቢን አዚብ ዘግበውታል።
ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ኹጥባውን ያደረሱት በነህር ቀን ሶላትን ከሰገዱ በኋላ ነው፡- "እንደኛ ሰላት የሰገደ እንደኛም ያረደ ኑሱኩን (መስዋዕቱን) በአላህ ዘንድ ተቀባይነት ይኖረዋል። ከኢድ ሰላት በፊትም መስዋዕቱን ያረደ ሰው ነው። ከዚያም መሥዋዕቱን አልሠራም" የአል-በራእ አጎት አቢ ቡርዳ ቢን ኒያር እንዲህ አለ፡- "የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ከኢድ ሰላት በፊት በጎቼን አርጄአለሁ እናም ዛሬ የመብላትና የመጠጣት ቀን (የአልኮል መጠጥ ሳይሆን) መስሎኝ ነበር እናም ያንን ወደድኩት። በቤቴ ውስጥ መጀመሪያ የሚታረዱት በጎቼ ናቸው፤ ስለዚህ ለጸሎት ከመምጣቴ በፊት በጎቼን አርጄ ምግቤን ውሰድ። ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) “ያረጃችሁት በግ የበግ ስጋ ብቻ ነው (ኑሱክ አይደለም)። እሳቸውም (አቡ ቡርዳ) እንዲህ አሉ፡- "የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ለእኔ ከሁለት በጎች የበለጠ የምትወደድ አንዲት የፍየል ግልገል አለችኝ። ይህ በእኔ ምትክ ኑሱክ ይበቃኛልን?" ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) "አዎ ይበቃሃል ግን (ኑሱክ ሆኖ) ካንተ በኋላ ለሌላ ሰው አይበቃም።
ቅፅ 2፣ መጽሐፍ 15፣ ቁጥር 79
ኢብኑ አባስ ዘግበውታል።
የኢድ ሶላትን ከአላህ መልእክተኛ ከአቡበክር፣ ከዑመር እና ከኡስማን ጋር ሰገድኩ እና ሁሉም ኹጥባ ከማድረጋቸው በፊት ሶላቱን ሰገዱ።
*****
ቅጽ 2 መጽሐፍ 15 ቁጥር 80
ኢብኑ ዑመር ዘግበውታል።
የአላህ መልእክተኛ አቡበክር እና ዑመር! ኹጥባ ከማድረጋቸው በፊት ሁለቱን የኢድ ሶላቶች ይሰግዱ ነበር።
*****
ቅጽ 2 መጽሐፍ 15 ቁጥር 81
ኢብኑ አባስ ዘግበውታል።
ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) በኢድ አል ፊጥር ቀን ሁለት ረከዓ ሰላት ሰግደዋል ከዛ በፊትም ሆነ በኋላ አልሰገዱም። ከዚያም ከቢላል ጋር ወደ ሴቶች ሄዶ ምጽዋት እንዲሰጡ አዘዛቸውና የጆሮ ጌቶቻቸውንና የአንገት ሐብልቶቻቸውን (በምጽዋት) መስጠት ጀመሩ።
ቅጽ 2 መጽሐፍ 15 ቁጥር 82
አል ባራእ ቢን አዚብ ዘግበውታል።
ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- "በዚህ እለት ልንሰራው የሚገባን የመጀመሪያው ነገር ሶላት መስገድ ከዚያም መስዋዕቱን ለማረድ መመለስ ነው። ይህን የሚያደርግ ሰው በሱናችን (በባህላችን) መሰረት የሰራ ሲሆን ያረደ ሰው ነው። ከሶላት በፊት የተከፈለው መስዋዕት ለቤተሰቦቹ ያቀረበው ስጋ ብቻ ነው እንጂ እንደ ኑሱክ አይቆጠርም። ከአንሷሮች መካከል አቡ ቡርዳ ቢን ናይይ የሚባል ሰው እንዲህ አለ፡- "የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ኑሱክን (ከሶላት በፊት) አርጄ ነበር ግን አንዲት ፍየል አለችኝ ከትልቅ በግ ትበልጣለች።" ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) “በመጀመሪያው ምትክ ሰዋው፤ ነገር ግን ካንተ በኋላ ለማንም አይበቃም” አልኩ።
*****
የተሕሪፍ ትርጉም በዚህ መልኩ ካየን #ኑፋቄ ማለት ደግሞ ምን ማለት ነው? የሚለውን እንይ፦ ነፋቄ ማለት ማጣመም ማለት ነው። ቁርዓን ውስጥ ምንም የተጣመመ ነገር እንደሌለበት አላህ (ሱወ) ሲናገር እንዲህ ይላል፦
18፡1
بسم الله الرحمن الرحيم الحمد لله الذي أنزل على عبده الكتاب ولم يجعل له عوجا ۜ
ምስጋና ለአላህ ለዚያ መጽሐፉን በውስጡ መጣመምን ያላደረገበት ሲሆን በባሪያው ላይ ላወረደው ይገባው፡፡"
የመፅሐፍ ቅዱስ ፀሐፊዎች እና የክርስትና እምነት መስራቾች ከሆኑት በተለይም ጳውሎስ የኦሪት ህጎችን በማጣመም ኑፋቄ እንደሚሉት መንገድ ያመልክ ነበር። ለዚህም ጳውሎስ በራሱ አንደበት ሲናገር እንዲህ ይላል፦
- የሐዋርያት ሥራ ምዕ. 24
13፤ አሁንም ስለሚከሱኝ ያስረዱህ ዘንድ አይችሉም።
14፤ ነገር ግን ይህን እመሰክርልሃለሁ፤ በሕጉ ያለውን በነቢያትም የተጻፉትን ሁሉ አምኜ የአባቶቼን አምላክ እነርሱ #ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ፤
ኑፋቄ ምንድ ነው?
#ኑፋቄ ማለት ጥሬ ቃሉ ወይም ፍቺው መንፈቅ ፣ መክፈል፣ መግመስ፣ መቅደድ... ማለት ነው።
ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ ማምለክ የማለት ትርጉሙም፦ የአንድን ነገር እውነት ላይ ቀዳዳ በማበጀትና የሀሰት ፈጠራዎችን በመፍጠር እንዲሁም እውነተኛውን ሀሳብ ላይ የራስ ፈጠራዎችን በማካተት እውነተኛውን ሀሳብ ከእውነታው እንዲርቅ የሚያደርግ የአምልዕኮ ተግባር ነው። በሌላ አባባል በዚህ በኑፋቄ መንገድ ማምለክ ማለት እውነተኛውን አምላክ በመካድ የሚያጠፋ የሆነን ጣኦት ማምለክ ማለት ሲሆን ይህም ደግሞ እውነተኛውን ሀይማኖት በመተው አዲስና መጤ እምነትን መከተል ማለት ነው። ለዚህም ደግሞ፦
- 2ኛው የጴጥሮስ መልዕክት 2፥ 1 - 15
"... ነገር ግን ሀሰተኞች ነቢያት ደግሞ በህዝቡ መካከል ነበሩ እኝዲሁም በመካከላቸው ደግሞ ሀሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ። እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳን ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው እየሳቡ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ። ብዙዎች በመዳራታቸው ይከተሏቸዋል፥ በእነርሱም ጠንቅ የእውነት መንገድ ይሰደባል።... ቅንን መንገድ ትተው ተሳሳቱ።"
.
" #ተሕሪፍ " ( تَحْرِيف) እና #ኑፋቄ
▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
1-ተሕሪፍ ምን ማለት ነው ?
2-ቁርዓን ስለ ተሕሪፍ ምን ይላል ?
3-ነቢያችን ስለ ብርዘት ምን አሉ ?
4-ቀደምት ሙስሊም ሊቃውንት ስለ ተሕሪፍ ምን ይላሉ ?
1⃣ "ተሕሪፍ" تَحْرِيف ማለት "ብርዘት" ማለት ሲሆን የቃለትን ብርዘት "Textual corruption" ያሳያል "ሐርፍ"حرف ማለት በራሱ "ፊደል" ማለት ነው።
The original meaning of the word Tahreef is "to lean from the pen in a certain direction" or 'to twist words to correspond to one's own desire
"ተሕሪፍ" ለሚለው ቃል ትክክለኛ ትርጉሙ "በብዕር አንድን ቃል ወደ ሌላ አቅጣጫ ዘንበል ማድረግ ወይም "ከራስ ፍላጎት ጋር እንዲሄድ ቃልን ማጣመም ማለት ነው"
[📚አል-ራጊቡ አል-ኢስፋሀኒ፣ አልሙፍረዳት ፊ ገሪብ አል-ቁርዓን 1995: ቅፅ 1 ገፅ 122]
Ash Shahrastani remarked that Tahreef means "changing the written word to an alternative to give it a corrupted meaning.
አሽ-ሻራስታኒ እንዳስቀመጠው ታሕሪፍ ማለት “የተፃፈውን ቃል ወደ ሌላ በመለወጥ የተዛባ ትርጉም እንዲኖረው ማድረግ ማለት ነው።
[📚አሽ-ሻራስታኒ ቅፅ 3 ገፅ 11]
ይህን እንደዚህ ከተረዳን የመጨረሻው ኪዳን የሆነው የአምላካችን አላህ ቅዱስ ቃል (ቁርዓን) ስለ "ተሕሪፍ" ምን ይላል የሚለውን ከብዙ ጥቂቱን ብቻ እንመልከት።
2⃣ ቁርዓን ስለ ብርዘት "Corruption" ምን ይላል ?
فَوَيْلٌ لِّلَّذِينَ يَكْتُبُونَ الْكِتَابَ بِأَيْدِيهِمْ ثُمَّ يَقُولُونَ هَٰذَا مِنْ عِندِ اللَّهِ لِيَشْتَرُوا بِهِ ثَمَنًا قَلِيلًا ۖ فَوَيْلٌ لَّهُم مِّمَّا كَتَبَتْ أَيْدِيهِمْ وَوَيْلٌ لَّهُم مِّمَّا يَكْسِبُونَ
ለነዚያም መጽሐፉን በእጆቻቸው ለሚጽፉና ከዚያም በርሱ ጥቂትን ዋጋ ሊገዙበት «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» ለሚሉ ወዮላቸው፡፡ ለነርሱም ከዚያ እጆቻቸው ከጻፉት ወዮላቸው፡፡ ለነሱም ከዚያ ከሚያፈሩት (ኃጢኣት) ወዮላቸው።
ሁለን ፈጣሪ በሆነው በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩሕ በጣም አዛኝ በሆነው።
[📚Qur'an 2:79]
فَبِمَا نَقْضِهِم مِّيثَاقَهُمْ لَعَنَّاهُمْ وَجَعَلْنَا قُلُوبَهُمْ قَاسِيَةً ۖ يُحَرِّفُونَ الْكَلِمَ عَن مَّوَاضِعِهِ...
ቃል ኪዳናቸውንም በማፍረሳቸው ረገምናቸው፡፡ ልቦቻቸውንም ደረቆች አደረግን፡፡ ቃላትን ከቦታዎቻቸው ይለውጣሉ...
[📚Qur'an 5:13]
يَا أَهْلَ الْكِتَابِ لِمَ تَلْبِسُونَ الْحَقَّ بِالْبَاطِلِ وَتَكْتُمُونَ الْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ
«የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! እውነቱን በውሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ እውነቱንም እናንተ የምታውቁ ስትኾኑ ለምን ትደብቃላችሁ»
[📚Qur'an 3:71]
۞ أَفَتَطْمَعُونَ أَن يُؤْمِنُوا لَكُمْ وَقَدْ كَانَ فَرِيقٌ مِّنْهُمْ يَسْمَعُونَ كَلَامَ اللَّهِ ثُمَّ يُحَرِّفُونَهُ مِن بَعْدِ مَا عَقَلُوهُ وَهُمْ يَعْلَمُونَ
(አይሁዶች) ከነሱ የኾኑ ጭፍሮች የአላህን ቃል የሚሰሙና ከዚያም ከተረዱት በኋላ እነርሱ እያወቁ የሚለውጡት ሲኾኑ ለናንተ ማመናቸውን ትከጅላላችሁን?
[📚Qur'an 2:75]
በእነዚህ የዘረዘርናቸው አናቅጽ ላይ "የሚለውጡት" ለሚለው ቃል የገባው "ዩሀሪፉነሁ" يُحَرِّفُونَهُ የሚል ሲሆን "የሚበርዙት" የሚል ትርጉም ይሰጠናል። የሚበርዙት ደግሞ "ሐርፍ" حَرْف "ፊደል" ሲሆን ፁሁፋዊ ብርዘትን "Textual Corruption" ያሳያል ይህም "ተሕሪፍ" ይባላል።
3⃣ የአላህ መልዕክተኛ ስለ ብርዘት ምን አሉ ?Prophet Mohammed About corruption.
عن أبي موسى قال : قال رسول الله - صلى الله عليه وسلم - : " إن بني إسرائيل كتبوا كتابا فاتبعوه ، وتركوا التوراة
The Messenger of Allah (ﷺ) said:The Bani Israel wrote a book, they followed it and left the Torah.
[📚አል-ጠበራኒ ሲልሲለ ሰሂሐ 2832]
በዚህ ሐዲስ ላይ በግልጽ የምንረዳው እስራኤላውያን ከአላህ የወረደውን መፅሐፍ ትተው የራሳቸው የሆነን መፅሐፍ እንደ ፃፉና በዚያ ሲመሩ እንደነበር ነው።
t.me//AkeelComparative
🌴📣የ25ቱ_ነቢያት_ስም_ከነአመጣጡ_እና_ሀገራ
ቸውን !!!
👉ካነበባችሁ በኋላ ለሌሎች ማስተላለፍ አትርሱ
1✍አደም(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ9 ሱራዎች በ25 አንቀጾች ውስጥ 25 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
2✍ኢድሪስ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ2 ሱራዎች በ2 አንቀጾች ውስጥ 2 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
3✍ኑሕ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ30 ሱራዎች በ50 አንቀጾች ውስጥ 50 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
4✍ኢብራሒም(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ25 ሱራዎች በ63 አንቀጾች ውስጥ 69 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#5ሉጥ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ14 ሱራዎች በ27 አንቀጾች ውስጥ 27 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
6✍ኢስማዒል(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ8 ሱራዎች በ12 አንቀጾች ውስጥ 12 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
#7ኢስሐቅ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ12 ሱራዎች በ16 አንቀጾች ውስጥ 17 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
8✍የዕቁብ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ10 ሱራዎች በ10 አንቀጾች ውስጥ 16 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
9✍ሁድ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ 3 ሱራዎች በ7 አንቀጾች ውስጥ 7 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
10✍ሷሊሕ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ9 ሱራዎች በ25 አንቀጾች ውስጥ ለ 25 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
11✍ሹዐይብ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ10 አንቀጾች ውስጥ 11 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
12✍ሙሳ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ34 ሱራዎች በ131 አንቀጾች ውስጥ 136 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
13✍ሀሩን(ዐለይሂ ሰላም)፡- ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ13 ሱራዎች በ20 አንቀጾች ውስጥ ለ 20 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
14✍ዳዉድ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርአን ውስጥ በ9 ሱራዎች 16 አንቀጾች ውስጥ ለ 16 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
15✍ሱለይማን(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ7 ሱራዎች 16 አንቀጾች ውስጥ ለ 17 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
16✍ኢልያስ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ 1 ሱራ በ2 አንቀጾች ውስጥ ለ 2 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
17✍አዩብ( ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ4 አንቀጾች ውስጥ ለ 4 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
18✍ዩኑስ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ4 አንቀጾች ውስጥ ለ 4 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
19✍ዩሱፍ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ 3 ሱራዎች በ26 አንቀጾች ውስጥ ለ 27 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
20✍አል-የሰዕ(ዐለይሂ )፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ2 ሱራዎች በ2 አንቀጾች ውስጥ ለ 2 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
21✍ዙል-ኪፍል(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ2 ሱራዎች በ2 አንቀጾች ውስጥ ለ ስም2 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
22✍ዘከሪያ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ6 ውስጥ ለ 7 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
23✍የሕያ(ዐለይሂ ሰላም)፡- አንቀጾችይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ5 አንቀጾች ውስጥ ለ 5 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
24✍ዒሳ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ11 ሱራዎች በ25 አንቀጾች ውስጥ ለ 25 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
25✍ሙሐመድ(ዐለይሂ ሶላቱ ወስ-ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ4 አንቀጾች ውስጥ ለ 4 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡
⬇➡➡~የነቢያቶች ሀገር 👇👇
#1አደም (ዐ.ሰ) = ስሪላንካ (Sirilanka)
#2ኑህ (ዐ.ሰ) = ጆርዳን (Jordan)
#3ሹዓይብ (ዐ.ሰ) = ሶሪያ (Soria)
#4ኢብራሂም (ዐ.ሰ) = ፍልስጤም (Palistain)
#5ኢስማኤል (ዐ.ሰ) = ሳኡዲ (Saudi)
#6ያእቆብ (ዐ.ሰ) = ፍልስጤም (Palistain)
7,ያህያ (ዐ.ሰ) = ፍልስጤም (Palistain)
8,ዘከሪያ (ዐ.ሰ) = ፍልስጤም (Palistain)
9,ኢስሃቅ (ዐ.ሰ) = ፍልስጤም (Palistain)
10,የሱፍ (ዐ.ሰ) = ፍልስጤም (Palistain)
11ሉጥ (ዐ.ሰ) = ኢራቅ (Iraq)
12,ኢዩብ (ዐ.ሰ) = ጆርዳን (Jordan)
13,ሁድ (ዐ.ሰ) = የመን (Yemen)
14,ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) = ሳኡዲ (Saudi) ( ከሁሉም በተለየ መልኩ የተላኩት ለአለም ህዝቦች ነው )
15 ,ሙሳ (ዐ.ሰ) = ግብፅ (Egypt)
16,ሀሩን(ዐ.ሰ) = ግብፅ (Egypt)
17,ሷሊህ (ዐ.ሰ) = የመን (Yemen)
18,ሱለይማን (ዐ.ሰ) = ግብፅ (Egypt)
19,ኢሊያስ (ዐ.ሰ) = ጀሩሳሌም (ፍልስጤም)
20,ዳውድ (ዐ.ሰ) = ኢራን (Iran)
21, ኢሳ (ዐ.ሰ) = ጀሩሳሌም (ፍልስጤም)
22,ኢድሪስ (ዐ.ሰ) = ኦማን (Oman)
23 ,ዩኑስ (ዐ.ሰ) = ኢራን (Iran)
24, ዙልኪፍል (ዐ.ሰ) = ጆርዳን ( Jordan )
25,አልየስእ (ዐ.ሰ) = ሶሪያ ( Soria)
የአላህ እዝነት እና ሰላም በሁሉም ላይ ይስፈን
☞︎︎︎ join በማለት ወደ ቻናሉ ይቀላቀሉ ይጠቀማሉ!!!
👇👇👇👇👇👇👇
t.me//AkeelComparative
3) አምላክ በባህርያቱ ( በስሞቹ) ብቸኛ የሆነ ነው!!
አምላክ በባህርያቱ(በስሞቹ) ብቸኛ ነው ሲባል ምን ማለት ነው? - - ይህ ማለት አምላካችን ስለራሱ (ስለነፍሱ) ባፀናቸው ስሞቹና በባህርያቶቹም ብቸኛ ነኝ ብሎ የተናገረውን ማመንና ማፅደቅ ማለት ነው።
- ይህ ማለት አምላካችን በስሞቹ ወይም በባህርያቶቹ ከሌሎች ፍጡራኑ ጋር ፍፁም የማይገናኝና ብቸኛ መሆኑን ያለመጠራጠር አምኖ መቀበል ማለት ነው።
ለምሳሌ ፦ ፍጡራኑን በብቸኝነት የሚመግብ፣ አዛኝ፣ ቸር... ናቸው። ይህን በተመለከተ አምሳያም ሆነ ብጤ የሌለው ጌታችን በቁርዓን እንዲህ ሲል ይናገራል።
ከቅዱስ ቁርዓንና ከሀዲስ
59፥24
" እርሱ አላህ ፈጣሪው፥ ከኢምንት አስገኚው፥ ቅርፅን አሳማሪው ነው። ለእርሱ መልካሞች ስሞች አልሉት...።"
51፥58
" አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ ፥ የብርቱ ሀይል ባለቤት ነው።"
96፥ 1-5
"... ጌታህ በጣም ቸር ሲሆን ፥ ያ በብዕር ያስተማረ፥ ሰውንም ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀው ሲሆን።"
ነብዩ(ሰ.ዓ.ወ) በሐዲሳቸው አላህ(ሱ.ወ) ሐያዕ ያለውና የተከበረ (ቸር) ነው። ባሪያው ሁለት እጆቹን ወደርሱ ያነሳ እንደሆነ ባዷቸውን ሊመልሳቸው ያፍራል።" ብለዋል።
ከመጽሐፍ ቅዱስ
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ አምላክ ባህሪያቶቹ(ስሞቹ) እየሱስ ከተናገሩት፦
- የማቴዎስ ወንጌል 6፥ 25-26
" ወደ ሠማይ ወፎች ተመልከቱ አይዘሩም አያጭዱምም የሠማዩ አምላክ ይመግባቸዋል።" [[ አምላክ ሲሳይ ሰጪ ነው ]]
- የሉቃስ ወንጌል 18፥ 19
" እየሱስም መልሶ ስለምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ እግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም አለው።" [[ ቸር የሆነው አምላክ ብቻ ነው]]
አስተውል!!!
አምላክ በባህርያቱ(በስሞቹ) ብቸኛ የሆነ ነው። በዚህም መሠረት አምላክ ብቸኛ መጋቢ፣ቸርና ፣ በሌሎችም ባህርያቱ ብቸኛ የሆነ አምላክ የሆነ መሆኑን እየሱስም መስክረዋል።
ቀጥሎም በመጽሐፍ ቅዱስና በቅዱስ ቁርዓን ውስጥ ከተገለፁት መካከል ተመሳሳይ የሆኑ የአምላክ (የአላህ) የባህርያቱ መገለጫ (ስሞች) በጥቂቱ እንመልከት፦
1⃣ አስ- ሰላም ( ሰላምን ሰጪ የሠላም ባለቤት)
ከመፅሐፍ ቅዱስ
- እግዚአብሔር የሰላም አምላክ ነው (1ኛ ቆሮንቶስ 14፥33)
ከቅዱስ ቁርዓን
- አላህ የሰላም ባለቤት ነው። (59፥23)
2⃣ አል- ሙንተቂም(ተበቃይ)
- እግዚአብሔር ጠላቶቹን የሚበቀል ነው
( ዘዳግም 32፥41) &(ት. ኤርሚያስ 46፥10)
- አላህም አሸናፊ የመበቀል ባለቤት ነው።( 3፥4), (5፥95)
3⃣ አር -ረዛቅ ፣ አል-ወህሃብ ( ሲሳይን ሰጪና የሲሳይ ባለቤት)
ከመፅሐፍ ቅዱስ እና ከቅዱስ ቁርዓን
- የሠማይ አምላክ ይመግባቸዋል። ( የማቴዎስ ወንጌል 6፥25)
- አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ የብርቱ ሀይል ባለቤት ነው። (51፥58)
4⃣ አዚዙን ሀኪም ( የሀይልና የጥበብ ባለቤት)
ከመፅሐፍ ቅዱስ
- ሀይልና ጥበብ የእግዚአብሔር ናቸው።(መፅሐፍ እዮብ 12፥16)
ከቅዱስ ቁርዓን
- "... ሀይል ሁሉ በሙሉ የአላህ ብቻ ነው።
እርሱ ሰሚው አዋቂው ነው።" ( 10፥65)
- "... አምላክም ከአላህ በስተቀር ምንም የለም። አላህም እርሱ
በርግጥ አሸናፊ ጥበበኛው ነው።" (3፥62)
5⃣ ሀሊቅ ( ሁሉንም ነገር የፈጠረ (ፈጣሪ))
ከመፅሐፍ ቅዱስ
- እግዚአብሔር ሰማይና ምድርን በእርሱ የሚገኙትን ሁሉን
የፈጠረ ነው። ( መዝሙረ ዳዊት 146፥6)
- እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ሁሉን የፈጠርሁ፥
ሰማያትን ለብቻዬ የዘረጋሁ ምድርንም ያፀናሁ አምላክ
እግዚአብሔር እኔ ነኝ ከኔ ጋር ማን ነበረ!?"
( ትንቢተ ኢሳያስ 44፥24)
ከቅዱስ ቁርዓን
- ያ እርሱ ሰማይና ምድርን በስድሰት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ
ነው።...።" (11፥7)
- ሰማያትና ምድርን በእውነት ፈጠረ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ"(16፥3)
6⃣ አል ባሪኡ፣ አል- ሙብዲኡ( አስገኚው)
ከመፅሐፍ ቅዱስ እና ከቅዱስ ቁርዓን
- " እግዚአብሔር ፍጥረታትን ሁሉ ካልነበሩበት ያስገኛቸው
የሁሉ ፈጣሪ ነው።" (ኦሪት ዘፍጥረት 1፥21)
- " የፈጠረህና ያፀናህ እርሱ ነው።" ( ዘዳግም 32፥6)
- እርሱ አላህ ከአንዲት ነፍስ ያስገኛችሁ ነው።..." (6፥98)
2) አምላክ በተግባሩ( በስራው) ብቸኛ ነው!!
አምላክ በተግባሩ (በስራው) ብቸኛ ነው ማለት ምን ማለት ነው!? ይህ ማለት ሀያሉ ጌታችንና አምላካችን በተግባሩ (በሚከውናቸው ስራዎቹ) ብጤ የሌለውና ብቸኛ ማድረግ ማለት ነው። ለምሳሌ፦ በመፍጠር ፣ በንግስና፣ ነገራትን በማስተናበር ፣... ከፍጡራን መለየት ወይም መነጠል ማለት ነው። ፍጥረት የተባለውን በሙሉ በብቸኛው ፈጣሪ አምላክ የተፈጠሩ መሆኑን መፅሐፍ ቅዱስ የሚደግፈው ቢሆንም የክርስትና እምነት መስራቹ ጳውሎስ ግን ይህን ይቃወማል። ለማንኛውም ግን ይህን ጉዳይ በመረጃ እናስደግፈው፦
ከመፅሐፍ ቅዱስ
✅ መፍጠር
- ሁሉንም ፍጥረት ያለቢጤ ፈጣሪ የሆነው አንድ አምላክ ብቻ ነው። ይህንንም መፍጠርን በተመለከት ደግሞ
- ትንቢተ ኢሳያስ 44፥24
" ሁሉን የፈጠርሁ ሠማያትን ለብቻዬ የዘረጋሁ ምድርንም ያፀናሁ እግዚአብሔር እኔ ነኝ ፤ ከእኔ ጋር ማን ነበረ? "
በማለት እግዚአብሔር ይጠይቃል።
ከቅዱስ ቁርዓንም
✅ መፍጠርን
- እኛ ሙስሊሞች የሁሉን ነገር ብቸኛው ፈጣሪ አንድ አላህ መሆኑን እናምናለንም እንመሠክራለንም። በአንጻሩ ከእስልምና ውጪ ያሉት ሌሎች ሰዎች ግን ይህንን እውነት እያመኑም ቢሆን እውነቱን ይክዳሉ።
እናም ሁሉን ብቻውን የፈጠረውና ብቸኛው የሁሉ አስተናባሪ የሆነው አምላካችን ሲናገር እንዲህ ይላል፦
31፥25
" ሠማያትንና ምድርን የፈጠረው ማን እንደሆነ ብትጠይቃቸው በርግጥ አላህ ነው ይላሉ።"
7፥54
"... ንቁ! መፍጠርና ማዘዝ የርሱ ብቻ ነው።..."
39፥62
" አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው። እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው።
59፥23
" እርሱ አላህ ነው፤ ያ ከርሱ በቀር አምላክ የሌለ፣ ንጉሱ፣ ከጉድለት ሁሉ የጠራው፣ የሠላም ባለቤቱ፣ ፀጥታን ሰጪው፣ ባሮቹን ጠባቂው፣ አሸናፊው፣ ሀያሉ፣ ኩሩው ነው። አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ።"
አምላክ ሁለመናውን ፈጣሪ መሆኑንና የውስጡም የውጩም ስለመፍጠሩን እየሱስ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፦
- የሉቃስ ወንጌል 11፥ 40
" እናንተ ደንቆሮዎች የውጭውን የፈጠረ የውስጡን ደግሞ አልፈጠረምን? " ይላሉ።
አስተውል!!!
አምላክ በተግባሩ(በስራው) ብቸኛ የሆነ መሆኑን ፤ በዚህም መሠረት ብቸኛ ፈጣሪና አስተናባሪ የሆነውም ብቸኛው አምላክ ነው እንጂ እየሱስ አይደሉም። ለዚህም ደግሞ በገዛ አንደበታቸው ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
#እየሱስ #አምላክ #አለመሆኑ #ከመፅሐፍ #ቅዱስና ከቁርዓን
የአምላክና የእየሱስ ልዩነቶችን ምን እንደሆነ ለመረዳት 3 ነጥቦችን ማወቅ ያስፈልጋል።
1) አምላክ ብቸኛ ተመላኪ መሆኑን
2) አምላክ በተግባሩ(በስራው) ብቸኛ መሆኑን
3) አምላክ በባህርያቱ(በስሞቹ) ብቸኛ መሆኑን
👇👇👇👇👇👇👇👇
@AkelComparative
☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️☝️
1) አምላክ ብቸኛ ተመላኪ ነው!!
▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷
አምላካችን ብቸኛ ተመላኪ ነው ሲባል ምን ማለት ነው!? አምላክ ብቸኛ ተመላኪ ነው ማለት የአምልኮ ተግባራቶችን እሱ ባዘዘን መልኩ መታዘዝና ለእርሱ ብቻ መፈፀም እንዲሁም ደግሞ እርሱንም ብቻ በብቸኝነት ማምለክ ማለት ነው። ለምሳሌ፦ ፀሎት(ልመና) ፣ ስግደት፣ ፆም፣ መመካት፣ ፍራቻ፣ መገዛት፣ ... የመሳሰሉትን አምልኮዎችን ለእርሱ ብቻ ማድረግ ነው። ከዚህ ጋር በተገናኘ ከቁርአንና ከሀዲስ እጅግ ብዙ ማስረጃዎችን መጥቀስ የሚቻል ሲሆን በአንፃሩ ከመፅሐፍ ቅዱስም የተለያዩ ማስረጃዎችን በጥቂቱ እንመልከት፦
አብደላህ ኢብን ኡመር(ረ.ዓ) የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዓ.ወ) እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ አለ። " እስልምና አምስት ነገሮች ላይ ተገንብቷል። በእውነት የሚመለክ ጌታ አንድ አላህ ብቻ ነው ብሎ ማመን እና ሙሀመድ የአላህ መልዕክተኛ ናቸው ብሎ መመስክር ፣ ሶላትን በወቅቱና ቀጣይነት ባለው መልኩ መስገድ፣ ዘካን ማውጣት፣ ረመዳን መጾም፣ የአላህ ቤትን ከቻል መጎበኘት።"
( ሀዲሱን ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
ከመፅሐፍ ቅዱስ
✅ ልመና(ፀሎት)
- ልመና(ፀሎት) ለአንድ አምላክ ብቻ ነው እነደሚገባው እየሱስ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ።
- የማቴዎስ ወንጌል 7፥ 8
" እየሱስ እንዲህ ይላሉ፦ ለምኑ ይሰጣችሁማል ፈልጉ ታገኙማላችሁ... የሚለምነው ሁሉ ይቀበላልና።"
✅ ስግደት
- ስግደት የሚገባው ለአንድ አምላብ ብቻ መሆኑን እየሱስ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፦
- የዮሐንስ ወንጌል 4፥ 25
" እግዚአብሔር መንፈስ ነው የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሠግዱለት ያስፈልጋቸዋል።"
- የማቴዎስ ወንጌል 4፥10
" ... ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ተፅፏልና።"
✅ ፆም
- ፆም ለአምላክ ብቻ የተገባ መሆኑንና እየሱስ ራሳቸው ለአምላካቸው መፆማቸውንን ያስረዳል።
- የማቴዎስ ወንጌል 4፥ 1-2
" እየሱስ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ከጦመ በኋላ ተራበ።"
✅ መመካት
- መመካት ያለበት በአንድ አምላክ ብቻ መሆኑን እንዲህ ተገልጿል።
- 1ኛ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፥ 30-31
"... የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ ተፅፏልና።"
✅ መገዛት
- ማንም መገዛት ያለበት ለአንድ አምላክ ብቻ መሆኑን እየሱስ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፦
- የማቴዎስ ወንጌል 6፥24 & የሉቃስ ወንጌል 16፥13
" ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚችል ማንም የለም። "
አስተውል!!!
አምላክ ብቸኛ ተመላኪ ነው፤ አምላክ አምልኮ የተፈፀመለት ሲሆን እየሱስ ደግሞ የአምልኮ ተግባሮችን የፈጸሙ ናቸው።
ከቁርአንና ከሀዲስም
✅ ልመና (ፀሎት)
- ልመና(ፀሎት) የሚገባው ብቸኛ አምላክ ለሆነው ለአላህ(ሱ.ወ) ብቻ መሆኑንና እርሱም ፀሎት ተቀባይ የሆነ ብቸኛ ጌታ መሆኑን
2 ፥186
"... እኔ ቅርብ ነኝ የለማኝን ፀሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ። ስለዚህ ለእኔ ይታዘዙ በኔም ይመኑ፤ እነርሱ ሊመሩ ይከጀላልና።"
✅ ስግደት
- ሊሰገድለትና ስግደት ሊገባው የሚችል ከአላህ ውጪ ሌላ ምንም አይነት አካል የለምና በዚህም ብቸኛ የሆነ አምላክ ነው።
30፥17
" አላህንም በምታመሹም ጊዜ በምታነጉም ጊዜ አጥሩት (ስገዱለት)።
41፥37
"... ለዚያም ለፈጠራችሁ አላህ ስገዱ። እርሱንም ብቻ የምትግገዙ እንደሆናችሁ ለሌላ አትስገዱ።"
53፥62
" ለአላህም ስገዱ ተገዙትም።"
✅ ጾም መጾም
- አንድ ሰው ጾም የሚፆመው ለአንድ አምላኩ ብሎ ነው መሆን ያለበት። ምክንያቱም የእሱ ትዕዛዝ ነውና። በዚህም ጾም የሚገባው ብቸኛው አምላክ ነው።
2፥183
" እናንተ ያመናችሁ ሆይ ጾም ከእናንተ በፊት በነበሩት ህዝቦች ላይ እንደተጻፈ በናንተ ላይም ተጻፈ(ተደነባ)፤ ልትጠነቀቁ ይከጀላልና።"
... ይቀጥላል
።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ለዚህና ለሌሎችም ንጽጽሮችን ለማግኘት ወደ ግሩፓችን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇👇👇
t.me//AkeelComparative
.
#እየሱስ #አምላክ #አይደለም
( ከመፅሐፍ ቅዱስና ከቁርዓን)
▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷
እየሱስ ጌታ ሊባሉ ይችላል ነገር ግን ፈጣሪ/ #አምላክ #አይደሉም። ሆኖም ግን እየሱስ ጌታ ነው በማለት ያስተማረው ጳውሎስ ነው።
ጳውሎስ እየሱስ አምላክ(ጌታ) ነው እንዲሁም የሠው ልጅ እንዲድን ከፈለገ ማመን ያለበት በእየሱስ ነው በማለት አዋጅ በማወጅና ህዝቡንም የውሸት ትምህርት በማስተማር ትወናውን ከተወሰነባቸው ቦታዎችም፦
- ወደ ሮሜ ሰዎች 10፥9
" እየሱስ አምላክ እንደሆነ በአፍህ ብትመሠክርና በልብህ ብታምን ትድናለህ።"
- ወደ ሮሜ ሰዎች 9፥5
" እየሱስ በስጋ መጣ እርሱም ከሁሉ በላይ ሆኖ ለዘላለም የተባከ አምላክ ነው።"
- 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 4፥5
" እየሱስ ጌታ እንደሆነ እንጂ ራሳችንን አንሰብክም።"
- ወደ ቆላስይስ ሰዎች 1፥ 15-16
" እየሱስ የማይታይ አምላክ ምሳሌ ነው።"
- ወደ ሮሜ ሰዎች 3፥ 22
" በእየሱስ ማመንና በእግዚአብሔር ማመን ልዩነት የላቸውም።"
ጳውሎስ ካስተማራቸው ትምህርቶች መካከል እነዚህን በጥቂቱ አነሳን እንጂ የርሱን አስተምህሮዎች ለማወቅ መፅሐፍ ቅዱስን የአዲስ ኪዳን ምዕራፎች(ከአራቱ ወንጌሎች በስተቀር) ማንበብና መረዳት በቂ ነው።
ታድያ ጳውሎስ እየሱስ ጌታ ነው ብሎ ለማስተማሩ ጉዳይ ምንም ተጨባጭ ምክንያት የሌለው ቢሆንም እርሱ ግን ይህንም ሆነ ምንም ይበል ምንም እውነቱን አንብቦ ማወቅ ግን የኛ ስራ ነው። ነገር ግን "እየሱስ ጌታ እንደሆነ እንጂ ራሳችንን አንሰብክም" ከሚለው የጳውሎስ ንግግር አንፃር በመፅሐፍ ቅዱስ የብሉይ ኪዳን የተለያዩ ምዕራፎች አስተምህሮዎች የተመለከትን እንደሆነ ለብዙ ሰዎችና ለብዙ ነብያት ጌታ ተብለው መጠራታቸውን ይገልፃሉ።
ለምሳሌ ፦
✅ ለዮሴፍ ፦ ኦሪት ዘፍጥረት 42፥33, 45፥8-9
✅ ለዳዊት ፦ 1ኛ መፅሐፈ ነገስት 1፥11-13
✅ ለኢዮብ ፦ 2ኛ ሳሙኤል 11፥11
✅ ለኤልያስ ፦ 1ኛ ነገስት 18፥ 7
✅ ለሳኦል ፦ 1ኛ ሳሙኤል 24፥8
✅ ለሙሴ፦ ኦሪት ዘሁልቅ 12፥11, 11፥28, ኢያሱ 5፥13-14, ዘካሪያስ 6፥4 እነዚህንና ሌሎችም ነቢያትን ጌታ ተብለው ተጠርተዋል። በጳውሎስ ጌታ ተብለው የተሠየሙት እየሱስ ግን እነዚያ ነብያት በተጠሩበት የጌትነት መጠሪያ ስም ብቻ ሳይሆን በአምላክነትም ስያሜ መፈረጃቸውን የተናገረ ሲሆን መላእክትም ሆነ የሠው ልጅ ሁሉንም ለእየሱስ እንዲሠግድ ማዘዙን ነው። ለዚህም በወደ ዕብራውያን 1፥6 ላይ የእግዚአብሔር መላእክት ሁሉ ለእየሱስ ይስገዱ" በማለት ተናግሯል። በዚህ የጳውሎስን ንግግር መሠረት ያመንንም ከሆነ አምላካችንና ፈጣሪያችን እየሱስ ናቸው ብለን መናገራችን የማይቀር ይሆናል። ይህ ትልቅ ስህተት ነው። ምክንያቱም ደግሞ የዚህ ምድር ትልቁ ውሸት ከአላህ ውጪ ሌላ አምላክ አለ ብሎ ማመን፣ መመስከርና መናገር ነው። እየሱስም ቢሆኑ በተደጋጋሚ ከሚናገሩት ንግግር መካከል እኔን መልዕክተኛ አድርጎ ልኮኛል፣ መልዕክተኛም ከላኪው አይበልጥም፣ ከእኔ አብ ይበልጣል ፣ ባሪያም ከጌታው አይበልጥምና ባሪያ ነኝ በማለት ተናግረዋል።
ለመሆኑ የአምላክና የእየሱስ ልዩነቶች ምን ይመስላሉ!???
▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷▷
