en
Feedback
AACPPPDS

AACPPPDS

Open in Telegram

በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግስት ግዝና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት

Show more
308
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
'' ዚተለያዩ ዚፅህፈት መሣሪያዎቜ '' ግልፅ ጚሚታ ዹቮክኒክ ሰነድ ዚመክፈቻ ስነሥርዓት
+3
'' ዚተለያዩ ዚፅህፈት መሣሪያዎቜ '' ግልፅ ጚሚታ ዹቮክኒክ ሰነድ ዚመክፈቻ ስነሥርዓት

ዚሠራተኞቜ ዚደምብ ልብስ ጚሚታ ዚመክፈት ሥነስርዓት
+3
ዚሠራተኞቜ ዚደምብ ልብስ ጚሚታ ዚመክፈት ሥነስርዓት

ዚመንግስት ግዥ እና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት ዚስድስት ወር ዕቅድ አፈፃፀሙን ኚባለድርሻ አካላት ጋር ገመገመ አገልግሎቱ ሀሙስ ታህሳስ 2016 በአዜማን ሆቮል ባኚናወነዉ ዚእቅድ አፈፃፀም መድሚክ
+4
ዚመንግስት ግዥ እና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት ዚስድስት ወር ዕቅድ አፈፃፀሙን ኚባለድርሻ አካላት ጋር ገመገመ አገልግሎቱ ሀሙስ ታህሳስ 2016 በአዜማን ሆቮል ባኚናወነዉ ዚእቅድ አፈፃፀም መድሚክ ላይ በርካታ ተሳታፊዎቜ ዚታደሙ ሲሆን ኚፋይናንስ ቢሮ ፣ ኚአቅራቢዎቜ፣ ኹክፍለ ኚተሞቜ፣ ኹምክር ቀት እና ኹሮክተር መስሪያ ቀቶቜ እንዲሁም መሰል ተቋማት ዹተወኹሉ አካላት ተገኝተዋል ፡፡ መድሚኩ በተቋሙ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ አጥናፉ ዚእንኳን ደህና መጣቜሁ ንግግር ዹተኹፈተ ሲሆን በአገልግሎቱ በመጀመሪያ ስድስት ወራት ዉስጥ ዹተኹናወኑ ዚግዥ እና ዚማስወገድ እንዲሁም ጥራትን ዚተመለኚቱ ተግባራት ሪፖሚት ለተሳታፊ ቀርቧል ፡፡ ዚግዥ እና ዚማስወገድን በተመለኹተ ሪፖርቱን ያቀሚቡት ዚአገልግሎቱ እቅድ እና በጀት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ኀልያስ ወርቅነህ በሪፖርቱ ኹተፈፀሙ ዚግዥ እና ዚማስወገድ አፈፃፀሞቜ በተጚማሪ በመልካም አስተዳደር ፣ በቅሬታ አፈታት ፣ በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ እና ብልሹ አሰራሮቜን ለመኹላኹል ዹተኹናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ለተሳታፊ አቅርበዋል ፡፡ በመድሚኩ ላይ በጥራት ማሚጋገጥ እና ግንዛቀ ማስጚበጥ ቡድን በተኹናወኑ ዚጥራት ማስጠበቅ ስራዎቜ እና በስራ ክፍሉ እንዲቋቋም አስገዳጅ ምክንያቶቜ ዙሪያ ሪፖርት ዹቀሹበ ሲሆን በአጠቃላይ በቀሚቡት ሰነዶቜ ዙሪያ ሰፊ ዉይይት ተኹናዉኗል ፡፡ በመጚሚሻም በዋነኝነት በተነሱ አቅርቊት እና ጥራትን በተመለኚቱ ጥያቄዎቜ እና አስተያዚቶቜ ዚፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ በሆኑት አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን እና በአገልግሎቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ አጥናፉ ሰፊ ማብራሪያ እና ምላሜ በመስጠት እንዲሁም ቀጣይ ዚትኩሚት አቅጣጫዎቜን በማስቀመጥ መድሚኩ ያለመዉን በማሳካት እና ዉጀታማ በመሆን ተጠነቋል ፡፡

በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግስት ግዥና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት ። ዚኀሌክትሮኒክ ዚመንግስት ግዥ ሥርአትን ለማስፋፋት በሚደሹገው ጥሚት እና በአጠቃላይ በ ኢ.ጂ.ፒ ምንነት እንዲሁም በው
+1
በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግስት ግዥና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት ። ዚኀሌክትሮኒክ ዚመንግስት ግዥ ሥርአትን ለማስፋፋት በሚደሹገው ጥሚት እና በአጠቃላይ በ ኢ.ጂ.ፒ ምንነት እንዲሁም በውል እና በአስተዳደራዊ ዉል ዙሪያ ዚግንዛቀ ማሥጚበጫ ስልጠና ተኹናወነ

አገልግሎቱ በቅንጅታዊ አሰራር ዚትስስር ስምምነትን አስመልክቶ ኹሮክተር ተቋማት ጋር ዹአፈፃፀም ግምገማ አኹናወነ ። በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግስት ግዥና ንብሚት ማስወገድ ዹተሠጠውን ተልዕ
አገልግሎቱ በቅንጅታዊ አሰራር ዚትስስር ስምምነትን አስመልክቶ ኹሮክተር ተቋማት ጋር ዹአፈፃፀም ግምገማ አኹናወነ ። በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግስት ግዥና ንብሚት ማስወገድ ዹተሠጠውን ተልዕኮ ለማሳካት እና ውጀታማ ለመሆን በዹደሹጃው ኹሚገኙና ዚሚመለኚታ቞ው ተቋማት ጋር ትስስር ፈጥሮ በተቀናጀ ሁኔታ ዚድርሻ቞ውን እንዲወጡ በማስቻል ዚልማትና ዚመልካም አስተዳደር ቜግሮቜን ለመፍታት ትኩሚት ሰጥቶ እዚሠራ ይገኛል ። በመሆኑም አገልግሎቱ በ 2016 በጀት ዓመት እስካሁን በኹተማ አስተዳደሩ ኹሚገኙ ዚተለያዩ ተቋማት ጋር ያኚናወና቞ውን ተግባራት ባስቀመጠው ቅንጅታዊ አሠራር እና አቅጣጫ መሠሚት ሪፖርቱን በማቅሚብ አፈፃፀሙን ገምግሟል ። በሪፖርቱም ዹተገኙ ውጀቶቜን አስመልክቶ እንደተገለፀው በግዥና ንብሚት ማስወገድ ዚሱፐርቪዥን ስራ መሠራቱ ፣ ዚጥራት ማሻሻያ መደሹጉ ፣ ዹ 40/60 ድልድል በወቅቱ መኹናወኑ ፣ ለቀሚቡ ቅሬታዎቜ በወቅቱ ምላሜ መሠጠት መቻሉ ፣ ዚሚወገዱ ንብሚቶቜን በስፋት መለዚት መቻሉ ተጠቃሜ ናቾው ። መድሚኩ በተስተዋሉ ተግዳሮቶቜ እና በገጠሙ ቜግሮቜ ዙሪያ ውይይት ዹተኹናወነ ሲሆን ቀጣይ ዚትኩሚት አቅጣጫዎቜንም በማስቀመጥ ተጠናቋል ።

በአዲስ አበባ ኹተማ ዚመንግስት ሠራተኞቜ አዋጅ 56/2010 ዙሪያ ለዓመራሩና ባለሙያው ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስልጠና ተኚናወነ። ስልጠናው ዹተቋሙ ሠራተኞቜ በአዋጅ ዚተሠጣ቞ውን ዚአሠራር ሁኔታ እንዲሁም
+1
በአዲስ አበባ ኹተማ ዚመንግስት ሠራተኞቜ አዋጅ 56/2010 ዙሪያ ለዓመራሩና ባለሙያው ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስልጠና ተኚናወነ። ስልጠናው ዹተቋሙ ሠራተኞቜ በአዋጅ ዚተሠጣ቞ውን ዚአሠራር ሁኔታ እንዲሁም መብት እና ግዎታ቞ውን እንዲገነዘቡ ማስቻልን ዓላማ ያደሚገ መሆኑ ዹተገለፀ ሲሆን በተጚማሪም በዕውቀት ላይ ዚተመሚኮዘ ኃላፊነትን ዚመወጣት አቅምን በማዳበር ዚአገልግሎቱን ተልዕኮ ለማሣካት ምቹ መደላድል መፍጠር መሆኑም ተጠቅሷል ። ስልጠናው በስራ አፈፃፀም ፣ በደሹጃ እድገት ፣ በዝዉዉር ፣ ዚአሠሪ መሥሪያ ቀት ኃላፊነት ።፣ ዚሠራተኛ ግዎታ ፣ ዚሥራ ውል ማቋሚጥ እና ማራዘም እንዲሁም ዚሥራ ዲስፕሊን እና መሠል ጉዳዮቜ ዙሪያ ትኩሚት ያደሚገ ነበርም ተብሏል ።

በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚምንግስት ግዥ እና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት ለዓመራሩና ባለሙያው ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስልጠና ተሠጠ። ስልጠናው ለሁለት ተኚታታይ ቀናት ዹተኹናወነ ሲሆን በኊዲት አሰ
+3
በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚምንግስት ግዥ እና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት ለዓመራሩና ባለሙያው ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስልጠና ተሠጠ። ስልጠናው ለሁለት ተኚታታይ ቀናት ዹተኹናወነ ሲሆን በኊዲት አሰራር እና ዚዉስጥ ቁጥጥር ፀደምብና መመሪያን ዹተኹተለ ዚግዥ ስርዓት ፀእንዲሁም በግዥ አፈፃፀም ዙሪያ እና በአጠቃላይ በስራ ወቅት ሊኖሩ ስለሚገቡ ሙያዊ ስነምግባሮቜ ላይ ትኩሚት ያደሚገ እንደሆነም ተገልጿል ።

ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግስት ግዥና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ስር ዹሚገኙ ዚተለያዩ መ/ቀቶቜና ተቋማት ንብሚቶቜ ዚተለያዩ ያገለገሉ ቁርጥራጭ ብሚታ ብሚ
ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግስት ግዥና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ስር ዹሚገኙ ዚተለያዩ መ/ቀቶቜና ተቋማት ንብሚቶቜ ዚተለያዩ ያገለገሉ ቁርጥራጭ ብሚታ ብሚቶቜ፣ (ዚተሜኚርካሪ ጎማዎቜ፣ ባትሪዎቜ፣ ኚነመዳሪዎቜ፣ ቞ርኬዎቜፀ ፍላፖቜ፣ በርሜሎቜ፣ ዚተሞኚርካሪ መለዋወጫዎቜ፣ ያገለገሉ ዹህክምና ዕቃዎቜ፣ ያገለገሉ ዚኀሌክትሪክ መብራት ዕቃዎቜ፣ አዳዲስ ዚተሞኚርካሪ መለዋወጫ) እና ዚአገልግሎት ዘመናቾውን ዚጚሚሱ ወይም ተጠግነው አገልግሎት መስጠት ዚማይቜሉ ኮምፒውተርና ተያያዥነት ያላ቞ው ዚኀሌክትሮኒክስ ዕቃዎቜ ሌሎቜም በሜያጭ በግልፅ ጚሚታ ለማስወገድ ማስታወቂያ ታህሳስ 4 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አውጥቷል፡፡ በዚሁ መሰሚት መጫሚት ዹሚፈልግ ማንኛውም ተጫራቜ ኚታህሳስ 4 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስኚ ታህሳስ 18 ቀን 2016 ዓ.ም ድሚስ ሜክሲኮ ሰንጋ ተራ ዮቀክ ዚንግድ ማዕኹል 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 606 በመገኘት ዚጚሚታ ሰነድ በመግዛት መጫሚት ዚምትቜሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ጚሚታው ታህሳስ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ኚጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዕለቱ 4፡15 ላይ ይኚፈታል፡፡ ለተጚማሪ መሹጃ በስልክ ቁጥር 011-557-86-71 ይደውሉ፡፡ ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግሰት ግዥና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት

photo content

በወቅታዊ ዚገበያ ዋጋ መሹጃ ዙርያ ነጋዮው ማህበሚሰብ ትክኚለኛ መሹጃ መስጠት እንዲቜል ዚግንዛቀ ማስጚበጥ እንቅስቃሎ በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግስት ግዥ እና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት ዚገበያ ጥናት ዳይሬክቶሬት በኹተማ አስተዳደሩ ስር ዹሚገኙ መ/ቀቶቜ ክ/ኚተሞቜ እንዲሁም ለሌሎቜ ባለበጀት መ/ቀቶቜ ዚተለያዩ ዚአገልግሎት ዚዕቃዎቜን እና አገልግሎቶቜን ዚገበያ ዋጋ ጥናትፀ ዚገበያ ዋጋ መሹጃ ትንተና እና ዹዋጋ ማስተካኚያ በመስራት አገልግሎቱ በጥናት ዹተደገፈ ውሳኔ እንዲወስን ዚገበያ ዋጋ ጥናት በማኹናወን ዚበኩሉን ሚና እንደሚጫወት ይታወቃል፡፡ በገበያ ጥናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዚሆኑት ወ/ሮ በላይነሜ ደሹጄ እንደሚያስሚዱት ወቅታዊ ዚገበያ ዋጋ በሚጠናበት ወቅት ዹነጋዮው ማህበሚሰብ ስለወቅታዊ ዚገበያ ዋጋ ምንነትና አላማ ዚግንዛቀ ክፍተት ስላለ ጥናቱን ኹጊዜ ወደ ጊዜ ለዉሳኔ አዳጋቜ እና ጊዜ ዹሚፈጅ ዹመሆን ተግዳሮቶቜ እዚተስተዋሉበት በመሆኑ ለነጋዮው ማህበሚሰብ ዚግንዛቀ ማስጚበጥ ስራ ማኹናወን ይደር ዚማይባል ነዉ ይላሉ፡፡ በመሆኑም ዚግንዛቀ ማስጚበጥ ስራዉ በሙሉ አቅም ኹፍተኛ ትኩሚት በመስጠት ዹተኹናወነ መሆኑን ዚገለፁት ወ/ሮ በላይነሜ ደሹጄ በዚህም ለ 113 (መቶ አስራ ሶስት ) ዚንግድ ድርጅቶቜ ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስራ ዚተሰራ ሲሆን በዚህም ለፈርኒቾር ድርጅቶቜፀለፅህፈት መሳሪያ አቅራቢዎቜፀለፅዳት እቃ አቅራቢዎቜ ፀለተሞኚርካሪ እና ጎማ አቅራቢዎቜፀለደንብ ልብስፀለኀሌክትሮኒክስ እቃ አቅራቢዎቜ እና መሰል ድርጅቶቜ ዚግንዛቀ ማስጚበጫ መስጠት ስራ ተኹናዉኗል ብለዋል ፡፡ ኚግንዛቀ ማስጚበጫ ስራዉ በፊት ዚነበሩ ዹነጋዮው ማህበሚሰብ አመለካኚትን አስመልክቶ ያብራሩት ዚገበያ ጥናት ዳይሬክተሯ መሹጃዉን ዹሚሰጠዉ ነጋዮ ዚገበያ ዋጋ ጥናት መሙላታቜን ለኛ ዹሚሰጠን ምንም ጥቅም ዹለም ፣ለፕሮፎርማ ኹሆነ ብቻ በትኚክል ዋጋ ዚመሙላት እና መሰል ዚግንዛቀ ክፈተቶቜ እንደነበሩ ጠቅሰዉ ኚግንዛቀ ማስጚበጥ ተግባሩ በኀላ ግን በዚወቅቱ ዚገበያ ዋጋ መሹጃ መስጠት ማለት ትልልቅ ሃገራዊ ውሳኔዎቜ ላይ ተሳትፎ ማድሚግ ማለት በመሆኑ ትብብር ለማድሚግ ፈቃደኛ መሆና቞ውንፀእና መሹጃ መስጠት ዘመናዊነት ነውፀመሚጃ መደበቅ በራስ አለመተማመን በመሆኑ መሹጃ ለመስጠት ተነሳሜነታ቞ዉ መጚመሩን ጠቅሰዉ ፡፡ ዚሚያደርሰውን ዚተዛባ ውሳኔ በመሚዳትም በተቀመጠው ስፔስፊኬሜን መሰሚት ብቻ ዚእቃዎቜን እና ዚአገልግሎቶቜን ወቅታዊ ዋጋ በመሙላት ትብብራ቞ውን በቅንነት ለማድሚግ ዝግጁ መሆናቾውን ገልፀዋል ብለዋል ፡፡

በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግስት ግዥ እና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት ኚተቋቋመበት እና በአዋጅ ኹተሠጠው ተልዕኮ ባሻገር በተለያዩ ሀገራዊ እና ማህበራዊ ኀላፊነቶቜ ላይ በንቃት ሲሳተፍ እና
+3
በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግስት ግዥ እና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት ኚተቋቋመበት እና በአዋጅ ኹተሠጠው ተልዕኮ ባሻገር በተለያዩ ሀገራዊ እና ማህበራዊ ኀላፊነቶቜ ላይ በንቃት ሲሳተፍ እና ዚበኩሉን ሚና ሲጫወት መቆዚቱ ይታወቃል ። ተቋሙ ይህንን ኀላፊነቱን በማሥቀጠልም ኹ 13 በላይ ዚተለያዮ ይዘት ያላ቞ውን ለትምህርት አገልግሎት ዹሚውሉ በርካታ መፅሐፍትን ግዥ በመፈፀም ለ ሻውልደማ ትምህርት ቀት ድጋፍ አኹናውኗል ። ዚመንግስት ግዥና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ ዚሆኑት አቶ መንግስቱ አጥናፉ ድጋፉን አስመልክቶ እንደገለፁት << ዹተደሹገው ዚመፃህፍት ድጋፍ ዹኹተማ አስተዳደሩ እዚተገበሚው ላለው ትምህርት ቀቶቜን ዹማጠናኹር እና ዚማሻሻል እንቅስቃሎ ዚበኩሉን ሚና ይጫወታል >> ብለዋል ።

photo content
+2

‹‹ዚማህበሚሰብ መሪነት ለላቀ ዚኀቜ.አይ.ቪ መኚላኚል›› በሚል መሪ ቃል ዚዘንድሮዉ ዹዓለም ዹፀሹ-ኀድስ ቀን በደማቅ ሁኔታ ተኹበሹ ዚመንግስት ግዥ እና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት ሰራተኞቜ እና ዓመራቜ ዹዓለም ዹፀሹ-ኀድስ ቀንን በደማቅ ሁኔታ ያኚበሩ ሲሆን በዓሉ በሀገር አቀፍ ደሹጃ ለ 35ኛ ጊዜ ‹‹ዚማህበሚሰብ መሪነት ለላቀ ዚኀቜ.አይ.ቪ መኹላኹል ›› (let communities lead) በሚል መሪ ቃል ተኚብሮ ዉሏል ፡፡ ዓለም አቀፉ ዹፀሹ-ኀድስ ቀን በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎቜ ኀቜ.አይ.ቪ በደማቾዉ ለሚገኝባ቞ዉና በቫይሚሱ ጉዳት ለደሚሰባ቞ዉ ወገኖቜ ድጋፋ቞ዉን ለማሳዚት እንዲሁም በኀድስ ህይወታ቞ዉን ያጡትን ወገኖቜ ለማስታወስ በዚዓመቱ ህዳር 22 (ዲሎምበር 1) እንደሚኚበር ዚሚታወቅ ነዉ ነዉ ያሉት በዕለቱ ዹፀሹ-ኀድስ ቀን ላይ ዕለቱን አስመልክቶ ዚዉይይት መነሻ ሰነድ ያቀሚቡት ዚኮሚኒዩኬሜን ጉዳዮቜ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዚሆኑት አቶ ሙሉጌታ ይመር እንደገለፁት ዚኀቜአይቪ/ኀድስን ለመኹላኹልና ለመቆጣጠር በመንግሰት በህዝብ ና በአጋሮቜ በተደሹጉ ጥሚቶቜ በአገራቜን አበሚታቜ ዉጀቶቜ በዹደሹጃዉ ዚተመዘገቡ መሆኑን ገልፀዉ ዹአለም አቀፉ ዹፀሹ ኀድስ ቀን መኹበር ጠቀሜታን አስመልክተዉም መንግስታት እና ውሳኔ ሰጭዎቜ ለኀቜ አይ ቪ/ኀድስ ዚሚሰጡትን ትኩሚት እንዲያጠናክሩ ያግዛል፣ ህዝቊቜ ስለ ኀቜ አይ ቪ/ኀድስ ያላ቞ውን ግንዛቀ ይበልጥ እንዲያሳድጉ እና በወሚርሜኙ ዙርያ ሁሌም ንቁ ሆነው አንዲሳተፉ ይሚዳል፣ ኀቜ አይ ቪ/ኀድስ ዚደሚሰበትን አጠቃላይ ደሹጃ እና እዚተሰጡ ያሉ ምላሟቜን በጋራ እንድንገመግም እድል ይሰጣል፣ ኚኀቜ አይ ቪ/ኀድስ ጋር ተያይዞ ዚሚሰጡ አገልግሎቶቜን እንድናጠናክር ያበሚታታል፣በአዲስ መንፈስ እና በአዲስ አቅም እንድንነሳሳ ያደርጋል ብለዋል፡፡ በመድሚኩ በርካታ ጥያቄዎቜ እና ሀሳቊቜ ዚተነሱ ሲሆን በተነሱት ላይም ሰፊ ዉይይት ተደርጎ እና ዚጋራ መግባባት ላይ ተደርሶ ተጠናቋል፡፡

ዚጚሚታ መለያ ቁጥር፡ AAPPPDS/FA/NCB/PG/47/03/2016 ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግስት ግዥና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት ለአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ባለበጀት መስሪያ ቀቶ
ዚጚሚታ መለያ ቁጥር፡ AAPPPDS/FA/NCB/PG/47/03/2016 ዚአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግስት ግዥና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት ለአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ባለበጀት መስሪያ ቀቶቜ በማዕቀፍ ውል ስምምነት ግዥ ዚተለያዩ ዚተለያዩ ዚሰራተኞቜ ደንብ ልብሶቜ (Different types of Clothes for Employees) ዕቃዎቜ ግዥ ሀገር አቀፍ ግልፅ ጚሚታ አወዳድሮ መፈጾም ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም፡ • በጚሚታው መሳተፍ ዚምትፈልጉ ተወዳዳሪዎቜ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ኚወጣበት ኚህዳር 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ ኚጧቱ 2፡30 እስኚ 11፡30 ድሚስ ባሉት 20 ተኚታታይ ቀናት ሰንጋ ተራ በሚገኘው ዩቀክ ኮሜርሻል ሮንተር ህንፃ ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት 6ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 606 በአካል በመቅሚብ ዚማይመለስ 700 /ሰባት መቶ ብር/ በመክፈል ዚጚሚታ ሰነዱን መግዛት ዚምትቜሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ • ጚሚታው ታህሳስ 12/2016 ዓ.ም ኚሚፋዱ 5፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዛው ዕለት ኚሚፋዱ 5፡30 በአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር ዚመንግስት ግዥና ንብሚት ማስወገድ አገልግሎት 9ኛ ፎቅ ዚመሰብሰቢያ አዳራሜ ይኚፈታል፡፡ • አገልግሎቱ ዚተሻለ አማራጭ ካገኘ ጚሚታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በኹፊል ዹመሰሹዝ መብቱ ዹተጠበቀ ነው፡፡ ለበለጠ መሹጃ በስልክ ቁጥር +251- 11-557-31-70/40 በመደወል ተጚማሪ መሹጃ ማግኘት ትቜላላቜሁ፡፡