1 146
Subscribers
-224 hours
-47 days
-1930 days
Posts Archive
1 146
እንኳን ለመቶኛ አመት አደረሰን ተወዳጁ ሬዲዮ ጣቢያ ሸገር ኤፍኤም 102,1 በአላችንን በማስመልከት ዛሬ 18/8/2017 ከቀኑ ስምንት ሰአት ጀምሮ በምርጡና ተወደጁ ጋዜጠኛ ተፈሪ አለሙ ልዩ ዝግጅት ይቀርባል እንከታተለው ቢቻል በቲኤምኤስ አየር ላይ ግቢው ውስጥ ቢለቀቅ አንዱ የበአሉ ድምቀት ይሆንልናል
መልካም በአል
1 146
ለወጣቶች የህይወት ክህሎት እና የስራ ፍለጋ ስልጠና እየተሰጠ ነዉ።
ሚያዝያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም
የኢፌዴሪ መንግስት እና የአለም ባንክ ከጉለሌ ክ/ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ለስራ አጥ ወጣቶች ወደ ስራ የሚያስገባ የ12 ቀን የህይወት ክህሎት ፣ ስራ ፍለጋ እና የዲጅታል ክህሎት ስልጠና በተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ እየተሰጠ ይገኛል።
የፕሮግራሙ አላማ እንደ ሀገር የሰፋዉን የወጣቶች ስራ አጥነት መቀነስ እንዲሁም የመንግስት እና የግል ሴክተሩን ማስተሳሰር እንደሆነ ለክፍላችን የገለጹት የጉለሌ ክ/ከተማ የብቃት ወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ስፔሻሊስት አቶ ፍቅረስላሴ ንጉሴ እንዳሉት ይህ ስልጠና የአሰልጣኝነት ስልጠና በወሰዱ ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኞች የሚሰጥ ሲሆን ሰልጣኞቹ በመረጡት የስልጠና ዘርፍ ከቀጣሪ ድርጅቶች ጋር በስራ አውደርዕይ (job fair)እንዲገናኙ በማድረግ ፣ የስራ ላይ ልምምድ እና ስልጠና በመስጠት ወደ ስራ የሚሰማሩበት ፕሮግራም መሆኑን ተናግረዉ አያይዘዉም እንደ ሀገርም እንደ ክ/ከተማማ ይህ ፕሮግራም ለ3ኛ ጊዜ የተዘጋጀ መሆኑን አዉስተዉ ከዚህ በፊት በተሰጡት 2 ዙሮች መቶ በመቶ ዉጤታማ መሆናቸዉን ገልጸዋል ።
ዛሬ አራተኛ ቀኑን ባስቆጠረዉ መርሃግብር እድሜያቸዉ ከ18 እስከ 25 አመት የሆናቸዉ ከጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 07፣ወረዳ 08 እና ወረዳ 09 የተመለመሉ 12ኛ ክፍል ያጠናቀቁ እና ከዚያ በታች የሆኑ ስራ አጥ ወጣቶች ስልጠናዉን በአግባቡ እየተከታተሉ እንደሆነ እና 60 በመቶዉ ተሳታፊዎች ሴቶች እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።
የጉለሌ ክ/ከተማ የብቃት ወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ስፔሻሊስት አቶ ፍቅረስላሴ ንጉሴ በመጨረሻም የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ ስራዉ የጋራችን ነዉ በማለት በፋሲሊቲ ፣ በማቴርያል ፣ በሞራል እና በሌሎች በኩል ላደረገላቸዉ ድጋፍ የኮሌጁን አመራሮች ፣ ሰራተኞች እና አሰልጣኞችን አመሰግነዋል።
የኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
Repost from TMPC 1917
ለኮሌጁ ማህበረሰብ እና ወዳጆች በሙሉ !
የኮሌጃችን 100ኛ አመት ክብረበዓል ለማክበር ከተለያዪ የአለማችን አገራት ለመጡ የቀድሞ የተፈሪ መኮነን ት/ቤት ተማሪወች ''የእንኳን ደህና መጣችሁ" ልዩ መርሃግብር ስለተዘጋጀ ሚያዝያ 18 እና 19 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 03:00 እስከ 11:00 በሚኖሩ የተለያዪ ዝግጅቶች ( ቲያትር ፣ ሙዚቃ ፣ ኤግዚቢሽን ፣ ዉይይት ፣ የስልጠና ወርክሾፕ እና ግቢ ጉብኝት ወዘተ) እንድትታደሙ በአክብሮት እንጋብዛለን ።
የኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ለኮሌጁ ማህበረሰብ እና ወዳጆች በሙሉ !
የኮሌጃችን 100ኛ አመት ክብረበዓል ለማክበር ከተለያዪ የአለማችን አገራት ለመጡ የቀድሞ የተፈሪ መኮነን ት/ቤት ተማሪወች ''የእንኳን ደህና መጣችሁ" ልዩ መርሃግብር ስለተዘጋጀ ሚያዝያ 17 እና 18 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 03:00 እስከ 11:00 በሚኖሩ የተለያዪ ዝግጅቶች ( ቲያትር ፣ ሙዚቃ ፣ ኤግዚቢሽን ፣ ዉይይት ፣ የስልጠና ወርክሾፕ እና ግቢ ጉብኝት ወዘተ) እንድትታደሙ በአክብሮት እንጋብዛለን ።
የኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የፕሮግራም ማስተካከያ !!!
የወገኔ ስፖርት ፌስቲቫል ነገ ሀሙስ እና አርብ ሊደረጉ የነበሩት የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች የመጫወቻ ሜዳው ለጨዋታ ዝግጁ አለመሆኑን ተከትሎ የውድድር ፕሮግራሞችን በዚህ መልኩ ተስተካክሏል
❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️❇️
የ ተቀየረው ግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች ፕሮግራም !
⚽️ ጂ ኤም ኤፍ ከ ቴክስታይል ጋርመንት 1
👉 ሰኞ 2ዐ/08/17
🕐 6:00 ሰዓት
⚽️ አስተዳደር ከ ኤሌክትሮኒክስ
👉 ማክሰኞ 21/08/17
🕐 6:00 ሰዓት
ቡድኖች ተዘዋወረ መሆኑን ታሳቢ አድርጋችሁ በአዲሱ ፕሮግራም መሰረት እንድትዘጋጁ ስንል በትህትና እንጠይቃለን።
ወገኔ
1 146
ወገኔ ስፖርት ፌስቲቫል
የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች ፕሮግራም !
⚽️ ጂ ኤም ኤፍ ከ ቴክስታይል ጋርመንት 1
👉 ሀሙስ 16/08/17
🕐 6:00 ሰዓት
⚽️ አስተዳደር ከ ኤሌክትሮኒክስ
👉 አርብ 17/08/17
🕐 6:00 ሰዓት
ወገኔ
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
