en
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

Open in Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

Show more
1 161
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
photo content
+1

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፫ (3) ቀን። ❤ እንኳን በቤተ ልሔምና አውራጃው ላሉ ንጉሥ ኄሮድስ በግፍ ለገደላቸው ለዐሥራ አራት እልፍ አራት ሺህ ለንጹሐን ሕፃናት ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓልና ከዘጠኙ ቅዱሳን ቀድመው ወደ አገራች ኢትዮጵያ ለመጡ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በስማቸው ለተሰየመላቸው ከዐለት ጠበል እያፈለቁ ድውያንን ለሚፈውሱት ለተአምረኛው ለታላቁ አባት ለአቡነ ሊባኖስ (መጣዕ) ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ የሴቶችን ጠጉር ሹሩባ ሲሠሩ ከኖሩ ከአባ አሞን፣ ከታላቁ ነቢይ ከኢሳይያስና ከቅዱስ ስምዖን ግብፃዊ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ በዚች ቀን ኄሮድስ ከሰብአ ሰገል እንደ ተረዳው ዘመን ልክ ሁለት ዓመት የሆናቸው ከዚያም በታች የሆኑ በቤተ ልሔምና በአውራጃዋ ሁሉ ያሉ ሕፃናት ተገደሉ። ቊጥራቸውም ዐሥራ አራት እልፍ ከአራት ሺህ ነው እነርሱም ከሴቶች እንደ ተወለዱ ንጹሐን የሆኑ ናቸው። ❤ በከበረ ወንጌል እንደተነገረ ሰብአ ሰገልም ከሔዱ በኋላ "እነሆ ኄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይሻዋልና ተነሣ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ምድረ ግብጽ ሽሽ ተመለስ ብዬ እስከምነግርህም ከዚያ ኑር" ብሎ የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ በሕልም ነገረው። እርሱም በሌሊት ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ይዞ ወደ ግብጽ ሔደ ኄሮድስ እስቲሞት ድረስም በዚያ ኖረ ከእግዚአብሔር ዘንድ "ልጄን ከግብጽ ጠራሁት" ተብሎ በነቢይ የተነገረው ይፈጸም ዘንድ። ከእነዚህ ውስጥ የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስ አንዱ እንደሚሆን ኄሮድስ አስቧልና። ❤ ጌታችንም ሥራውን ሁሉ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀር ሠራ በረቀቀ ጥበቡም ከኄሮድስ ፊት ሸሸ ኄድሮስ አግኝቶት ሊገድለው ቢአስብ ያለ ጊዜው መግደል ባልተቻለውም ነበርና ሰነፎች ሰዎች ሰው መሆኑን ምትሐት ነው ብለው በአሰቡ ነበር ስለዚህ የክብር ባለቤት ጌታችን ሸሸ ሁለተኛም እግዚአብሔር "በፈጣን ደመና ተቀምጦ ወደ ግብጽ ይወርዳል" ተብሎ የተነገረው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ዳግመኛም ከክፉ ነገር እንድንሸሽ ለእኛ ሊአስተምረን የግብጽንም ጣዖታት ያጠፋቸው ዘንድ ነው። ❤ ይህን ያህል ብዛት ያላቸውን ሕፃናት መሰብሰብና መግደል ለኄሮድስ እንዴት ተቻለው ተንኰለኛ ኄሮድስ ምክንያት ፈጥሮ "የሁለት ዓመትና ከዚያም ያነሱ ሕፃናትን አሳድገን ጭፍራ እንሠራለት ዘንድ የሚያዝ የንጉሥ ነገሥት ቄሣር ደብዳቤ ከእኔ ዘንድ ደርሷል ወርቅ፣ ብር፣ ቀለብ ልብስም እንሰጣለን" ብሎ ወደ አገሩ ሁሉ ላከ። ስለዚህም ከእናቶቻቸው ጋር ተሰብሰቡ ያን ጊዜ ከእርሱ ዘንድ አንድ ሽህ ሁለት መቶ ወታደሮችን አውጥቶ በተራራ ላይ አረዱአቸው። ነቢይ ኤርምያስም የተናገረው ተፈጸመ "ራኄል ስለ ልጆቿ ስታለቅስ ብዙ መከራ ጨኸት ሙሾ ልቅሶ ዋይታ በራማ ተሰማ ልቅሶ መተውን መጽናናትን እምቢ አለች ልጆቿ ልጆችን አልሆኗትምና"። ❤ ዮሐንስም በራእዩ እንዲህ አለ "በታላቅ ቃል ጮኹ የተመሰገንህ እውነተኛ አቤቱ እስከ መቼ ነው ስለ ደማችን ተበቅለህ በምድር ላይ በሚኖሩ ሰዎች አትፈርድባቸውምን?" አሉ። ከእነርሱም ወገን ለየአንዳንዱ ብሩህ ልብስ ሰጥተው "እንግዲህ ጥቂት ቀን ዕረፉ" አሉዋቸው። እንነርሱ ይሞቱ ዘንድ ያላቸው ወንድሞቻቸው እስከሚፈጸሙበት ቀን ድረስ እንዲህ የእሊህን ሕፃናት ነፍሳቸውን አይቷልና። ❤ ዳግመኛም እንዲህ አለ "በዙፋኑ ፊት በአራቱ እንስሶችና በሃያ አራቱ አለቆች ፊት አዲስ ምስጋና ያመሰግናሉ ከግብጽ ምድር ከተዋጁ ከዐሥራ አራት እልፍ አራት ሽህ በቀር ያቺን ምስጋና ሊያውቃት የሚቻለው የለም። እነርሱ ከሴቶች እንደ ተወለዱ ንጹሐን የሆኑ ናቸው"። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ የዕለቱ አንገሪጋሪ ግእዝ ዜማ ሃሌ ሉያ "አባ አቡነ አቡነ ሊባኖስ ዘኪያከ ኃርየ ክርስቶስ ጸሊ በእንቲአነ ይጉየዩ ይትኃፈሩ ጸላዕትነ በክርስቶስ እለ አመነ። ትርጉም፦ ክርስቶስ የመረጠኽ አባታችን አባ ሊባኖስ ስለ እኛ ጸልይ በክርስቶስ ያመንን ከኾንን ከእኛ ፊት ጠላቶቻችን ያፍሩና ይሸሹ ዘንድ። ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ። + + + ❤ አባ ሊባኖስ፦የዚህም የቅዱስ አባታችን የአባ ሊባኖስ የአባቱ ስም አብርሃም የእናቱ ስም ንግሥት ነው። እነርሱም በወርቅና በብር እጅግ የከበሩ ነበሩ ሀገራቸውም ሮም ትባላለች ይህቺውም በቊስጥንጥንያ ሀገር አቅራቢያ ናት፤ ከኒህም ደጎች ሰዎች አባታችን አባ ሊባኖስ ሐምሌ ሦስት ቀን ተወለዱ። ❤ ከዚህም በኋላ በመልካም አስተዳደግ አሳደጉት በነፃነትም ሁሉ መልካም ሆኖ አደገ የመልኩም ደም ግባት ያማረ ነገሩም እንደ ማር የጣፈጠ ነበር፤ ጥበብንና ተግሣፅን ብሉይና ሐዲስን ሁሉ ተማረ። ለዚህም ቅዱስ ሚስትን በአመጡለት ቀን የእግዚአብሔር መልአክ የከበረ ቅዱስ ገብርኤል በሌሊት ጠርቶ ከአባቱ ቤት አውጥቶ ወደ አባ ጳኵሚስ ገዳም አደረሰው በዚያም መነኰሰ። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሒዶ እየተጋደለ ብዙ ዘመን ኖረ ድንቅ ተአምራትንም በማድረግ ከዐለት ውኃን አፍልቋልና በሽተኞችንም አድኗልና የክብር ባለቤት ጌታችንንም አገልግሎ ደስ አሰኝቶ ጥር 3 ቀን በሰላም ዐረፈ። ከአባታችን አቡነ ሊባኖስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን። ምንጭ፦ገድለ አቡነ ሊባኖስና መዝገበ ቅዱሳን። + + + ❤ በዚች ዕለት የሴቶችን ጠጉር ሹርባ ሲሠራ የኖረ የአባ አሞን መታሰቢያው ነው። እንዲህ ባለ ሥራም ሲኖረሰ የኃጢአት ማዕበል ሊአሠጥመወሰ አልቻለም በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አመረን። ምንጭ፦ የጥር 3 ስንክሳር። + + + ❤ "ሰላም ለሊባኖስ እምቤተ አቡሁ ዘወጽአ። ከመ ቃለ መልአክ ሰምዐ። ኰኵሐ ዘቢጦ ማየ አንቀዐ። ሰላም ለአድኃኒ ወዓዲ አስትዓ በውስተ ገዳም ምስሌሁ ዘነበሩ ስንዐ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር 3። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "በርህ ሠረቀ ለጻድቃን። ወለርቱዐነ ልብ ትፍሥሕት። ይትፌሥሑ ጻድቃን በእግዚአብሔር። መዝ 96፥11-12። የሚነበበው ወንጌል ማቴ5፥1-17። + + + ❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "እስመ በእንቲአሁ ይቀትሉነ ኵሎ አሚረ። ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ። ንቃህ እግዚኦ ለምንት ትነውም። መዝ 43፥። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 11፥25-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 2፥1-11 እና የሐዋ ሥራ 28፥17-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 2፥13-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የቤተልሔም የመቶ አርባ አራት ሺህ ህፃናት የዕረፍት በዓልና የአቡነ ሊባኖስ የዕረፍት በዓልና የብርሃን ልደቱ በዓል ሰሞን ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

+6
06-ዘለሊባኖስ.amr1.65 KB

photo content
+4

ዘመነ አስተርእዮ ‹‹እግዚአብሔር እግዚእ አስተርአየ ለነ - ጌታ እግዚአብሔር ተገለጠልን፡፡›› /መዝ ፻፲፯፥፳፮ አስተርእዮ ማለት መገለጥ ፣ መታየት፣ በሰው ፊት እየተመላለሱ ማስተማር ማለት ነው፡፡ አስተርእዮ የሚለው ቃል በጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ ‹‹ ኤጲፋኒ›› ይባላል፡፡ ይህም ከላይ መታየት መገለጥ የሚለውን ለየት አድርጎ ያስረዳል፡፡ ስለዚህ አስተርእዮ ወይም ኤጲፋንያ የአምላክ መገለጥ መታየት ማለት ነው፡፡ የክርስትና ሃይማኖት የአምላክ መገለጥ /አፓካሊፕሰስ/ ይባላል በሰው አስተሳሰብ አልተፈለሰፈምና ከልደተ ክርስቶስ ዋዜማ ጀምሮ እስከ ዓቢይ ጾም ድረስ ባሉት ሳምንታትና ቀናት ተወልዶ አንሶሰው፣ አስተርአየ፥ ተጠመቀ ወዘተ የሚሉት ቃላት በብዛት ይነገራሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያንም እነዚህን ቀናት ዘመነ ጥምቀት ወአስተርዮ ብላ ታከብራለች፡፡ በነዚህ ዕለታትና ሳምንታት በቤተ ክርስቲያን የሚዘመረው መዝሙርም ሆነ የሚነበበው ንባብ ይህንኑ የጌታን መገለጥ የሚናገር፤ ስለ አምላክ ሰው መሆን፤ ስለ ሰማያዊ ሙሽራ መምጣት፣ መታየትና መገለጥ የሚያወሳ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ይህ ወቅት ዘመነ አስተርዮ የተባለበት ምክንያት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ በእስራኤል አውራጃዎች ሁሉ በመምህርነት ተገልጦ ስላስተማረ መሆኑን የቤተ ክርስቲያናችን አበው ጨምረው ያስረዳሉ፡፡ የረቂቅ አምላክን በሥጋ መገለጥ በዓይነ ትንቢት የተመለከተ ነቢዩ ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር እግዚእ አስርአየ ለነ-ጌታ እግዚአብሔር ተገለጠልን›› ሲል ተናግሯል፡፡ በዚህ ገጸ ንባብ ውስጥ የምንመለከተው እግዚአብሔር በየጊዜው በሕልም፣ በራእይ ወይም በልዩ ልዩ ተምሳሌት በዘፈቀደ የሚደረገውን መገለጥ ሳይሆን ዓመት ኩነኔን ለማሳለፍ ዓመት ምህረትን ለማወጅ ከመካከላችን የተገኘውን የመድኃኔዓለም መገለጥ ነው፡፡ ልዑለ ባሕርይ እግዚአብሔር ለፍርድና ለወቀሳ፤ ለበረከትም ሰውን የሚነጋገርበትና በተምሳሌት የሚገለጥበት ጊዜ አለው፡፡ አዳም ዕፅ በለስን በበላ ጊዜ፤ ቃየል ወንድሙ አቤልን በገደለ ጊዜ ወቅሷቸዋል፡፡/ዘፍ ፫፥፱‐፲፱፤፬፥፱‐፲፫/ ኖኅና አብርሃምን ሌሎችንም አርእስተ አበው እየተገለጠ ያነጋግራቸው ነበር፡፡ /ዘፍ ፮፥፯፤፲፭፥፲፯፤፲፩፥፴፩/ ሙሴን በደብረ ሲና ተገልጦ አነጋግሮታል፤ ለእስራኤል መተዳደሪያ የሚሆን ሕግን ሰጥቶታል፡፡ ከፈርዖን የግፍ አገዛዝ ነጻ ያወጣቸው እስራኤልውያንን በቃዴስ በርሃ ላይ ሳሉ በደመናና በእሳት ተከናንቦ በመካከላቸው ይገኝ ነበር፡፡ /ዘፀ ፵፥፴፬-፵፰/ ለነቢያትም እየተገለጠ ከየሥራ መስካቸው እየጠራ ትንቢት እንዲናገሩ ስለ እርሱ እንዲመስክሩ ትእዛዝ መመሪያ ሰጥቷቸዋል፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን እግዚአብሔርን በምሳሌ እንጂ ፊቱን ያየው አልነበረም ነበር፡፡ ሙሴ ከባለሟልነቱ የተነሳ በባሕርይ ሁነህ ልይህ ቢለው ፊቴን አይቶ ለአንዲት ደቂቃ ሰዓት እንኳን በሕይወት ለመቆየት የሚችል የለም ብሎታል፡፡ /ዘፀ ፴፭፥፲፯‐፳፭/ ኋላም ወንጌላዊው ዮሐንስ ‹‹እግዚአብሔርን በባሕርይው ያየው የለም›› ብሏል፡፡ ዮሐ ፩፥፲፰ አዳምና ሔዋን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ በማፍረሳቸው በመከራ ዓዘቅት ውስጥ ወድቀው ሲሰቃዩ ወደዚህ ዓለም መጥቶ ሰው ሆኖ ሥጋ ለብሶ ከድንግል ማርያም ተወልዶ ተጠምቆ እየተመላለሰ አስተምሮ፣ ተሰቅሎ፣ ሞቶ፣ ተነስቶ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍሶ እንደሚያድናቸው ተስፋ ሰጣቸው፣ የሰጣቸው ተስፋ ዕለቱን አልተፈጸመም፣ በትንቢት እየተነገረ በሱባኤ እየተቆጠረ በምሳሌም እየተመሰለ በመነጋገር ብዙ ዘመን ኑሯል፡፡ ስለ ክርስቶስ በሥጋ መገለጥ ነቢያት ብዙ ትንቢት ተናግራዋል፣ ሱባኤም ቆጥረዋል ምሳሌም እየመሰሉ ተናግረዋል፡፡ የተነገረው ትንቢት ሲፈፀም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ በአጭር ቁመት፤ በጠባብ ደረት ተገለጠ፡፡ ከተወለደም በኋላ አምላክ ነኝ ብሎ ዕለቱን አላደገም እንደ ሕጻናት ቀስ በቀስ አደገ እንጂ፡፡ የዕብራውያንንም ሕግና ሥርዓት አላፋለሰም በተወለደ በስምንተኛው ቀን ወደ ቤተ ግዝራት ገብቶ የግዝረት ሥርዓት ተፈፅሞለታል፡፡ ስሙም ኢየሱስ ተብሎ ተሰይሟል፡፡ በዓርባ ቀን ደግሞ ዕጉለ ርግብ ዘውገማ ዕነቅ ይዘው ወደ ቤተእግዚአብሔር ወስደውታል፡፡ በዓመትም ሦስት ጊዜያት ወደ ቤተ መቅደስ እየወሰዱ እጅ ያስነሡት ነበር፡፡ ይህ አስተርእዮ በዘመነ ብሉይ ከነበረው መገለጥ በመልእክትም በጠባይም ይለያል፡፡ ያኛው በሕልም፣ በራእይ፣ በተምሳሌት ነበር፡፡ አሁን ግን ራሱ ለማዳን ተገለጠ፥ የፊተኛው ለተወሰኑ ሰዎች ነበር፡፡ አሁን ግን ለመላው ዓለም ሆነ፥ የፊተኛው በሩቅ ነበር፡፡ አሁን ግን በቅርብ የእኛን ሥጋና ነፍስ ተዋሕዶ ታየ፡፡ በዚህ አስተርእዮ በሰማይ ያለው የእግዚአብሔር መቅደስ ተከፈተ /ራዕይ ፲፩፥፲፱/ የእግዚአብሔር ድንኳን በሰዎች መካከል ተተከለ፡፡ ማለትም በሰዎች መካከል ተገኘ ሰዎች ያለ ምንም ችግር የእግዚአብሔር ባለሟሎች ሆኑ፡፡ በእጃቸው ዳሰሱት በዓይናቸውም አዩት ሲያስተምር ሰሙት አብረውት ተመገቡ፡፡ /፩ዮሐ ፩፥፩፤ ዮሐ፲፥፬/ ሰው የእግዚአብሔርን ክብር አየ፡፡ /ዮሐ ፩፥፲፬፤፪፥፲፩/ በዚህ አስተርእዮ በምስጢረ ሥጋዌ ምስጢረ ሥላሴንም ተማርን፣ አየን፡፡ በዮርዳኖስና በደብረ ታቦር አብ ስለ ልጁ የተናገረውን የምስክርነት ቃል ሰማን፡፡ /ማቴ ፫፥፲፮ ማር ፩፥፰‐፲፩ ሉቃ ፫፥፳፩‐፳፪ ፩ ዩሐ ፩፥፴፪‐፴፬ መዝ ፪፥ ፯ ማቴ ፲፯፥፩‐፭/ ወልድም ከአባቱ ጋር አንድ መሆኑን ተረዳን፡፡ ዮሐ ፲፥፴፤ ፲፯፥፲፩፤ ፲፬፥፱፤ ፲፪፥፵፭/ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስንም በአስተርእዮ አየነው፡፡ /ዮሐ፩፥፲፬‐፲፮፤ ፩፥፴፱፤ ፲፭፥፳፪ ሉቃ ፳፬፥፳፱/ ይህ የአምላክ መገለጥ ለአንዳንዶቹ እንደ ፍላጎታቸው ሳይሆን በመቅረቱ አልተደሰቱበትም፡፡ እግዚአብሔርን ደጅ ሲጠኑ ለነበሩ ግን የአስተርዮ ፀሐይ ወጣላቸው፡፡ በተዛባ ሥርዓተ ማኅበር ተረግጠው ይኖሩ የነበሩ ነጻ ወጡ፡፡ ስለ ሰው ዘር ልጆች ሕይወት በማሰቡ ገዢዎች ታስረው ሲማቅቁ የኖሩት ሁሉ ከወህኒ ቤት ወጡ፡፡ በዘር ልዩነት የሚያምኑ ፈሪሳውያን አፈሩ፡፡ በመንፈስም በገንዘብም ድሆች ተብለው ተንቀው የነበሩት እግዚአብሔር በመካከላቸው ተገኘ፡፡ በዓለማዊ ሥልጣናቸው የሚመኩ ትዕቢተኞች ተዋረዱ፡፡ ትሑታን ከፍ ከፍ አሉ፡፡ የፍትሕ ሚዛን የሌላቸው ነገሥታት ተንኮታኩተው ወደቁ፡፡ የተራቡ በአስተርዮ በረከት ጠገቡ፡፡ የተጠሙት ረኩ፡፡ በኃላፊ ሀብታቸው በመመካት እግዚአብሔርን ንቀው የነበሩ ሀብታሞች ባዶ እጃቸውን ቀሩ፡፡ /ሉቃ ፩፥፶፩‐፶፫፤፬፥፲፱/ በዚህም ዓመተ ምህረት ታወጀ፡፡

photo content

☘☘☘☘☘☘☘☘☘☘ ስርዓተ ማሕሌት ዘጥር ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️ ሥርዓተ ነግሥ ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል @EOTCW @EOTCW መልክአሥላሴ ሰላም ለአዕዳዊክሙ እለ ተኬነዋ ብእሴ፤ ኦ ኄራን አጋዕዝትየ ሥላሴ፤ ድኅረ ጸሐፈ ኦሪት ሊቀ ነቢያት ሙሴ፤ መሐረኒ ሥላሴክሙ መጽሐፈ መምህሩ ቅዳሴ፤ወልደ ነጎድጓድ ዮሐንስ ዘፍሕሮ  ውዳሴ @EOTCW ዚቅ ነሥአ ሙሴ ሠለስተ አስማተ ከመ  ዘይወስድ አምኃ ለንጉሥ፤ ወሰማዕትኒ ይፀውሩ ሥላሴ። @EOTCW ወረብ ነሥአ ሙሴ ሠለስተ አስማተ/፪/ ከመ ዘይወስድ አምኃ ለንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ዮሐንስኒ ሥላሴ ይፀውር/፪/ @EOTCW ዓዲ ዚቅ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፤ በጽምረተ አሐዱ ጸሐፈ ወልደ ነጎድጓድ በክብርት እዱ። @EOTCW ዘጣዕሙ ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤ ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤ መሠረተ ህይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤ ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤ እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ። @EOTCW ዚቅ ዘመንክር በአርያሙ እግዚአብሔር ስሙ፤ዝንጓጌ መስቀል አመ ተወፈየ ነዋ ወልድኪ ይቤላ ለእሙ ፍቅረ ዮሐንስ ኢያንተገበ ጊዜ ሕማሙ፤ላዕለ ጒንደ መስቀል አመ ውኅዘ ደሙ። @EOTCW @EOTCW ነግሥ ወልደ ነጎድጓድ ዮሐንስ በራእዩ ዜነወነ ፤ዘከመ ሞዓ ሰይጣነ፤ ሚካኤልሃ ዘይትዓፀፍ ርስነ፤ ይቤ ወንጌላዊ ርኢክዎአነ ፤ታዎሎጎስ (ታዎጎሎስ) ዘረፈቀ እንተ ነድ ሕፅነ። @EOTCW ዚቅ ይቤ ዮሐንስ ለልየ ርኢኩ፤ ወአነ ሰማዕቱ ለሊቀ መላእክት። @EOTCW መልክአ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ማግቢያ፦ ባሕረ ጥበባት አበ ልሳናት ፤ንሥር ሠራሪ ልዑለ ስብከት ፨ #ዮሐንስ ወንጌላዊ ረዓዬ  ኅቡዓት ፤ ነገሩኒ ቅሱም በጼወ መለኮት @EOTCW መልክአ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘተወደሰ ብዙኃ፤ወለሥዕርትከ አቄርብ ፍሬ ከናፍር አምኃ፤ዘተረሰይከ ዮሐንስ ትርሢተ መላእክት ንጽሐ፤ቃል ኃደረ ላዕሌነ ወኮነ መሲሐ፤ ቃለ ዓዋዲ ቃልከ እንዘ ይብል ጸርሐ። @EOTCW አመላለስ ኃደረ ቃል ላዕሌነ/፪/ ወኮነ ወኮነ መሲሐ/፪/ @EOTCW @EOTCW ዚቅ ፈክር ለነ ወልደ ነጎድጓድ፤ ዘረፈቀ ውስተ ሕፅነ ነድ፤ ፈክር ለነ ዘትቤ በወንጌል ፤ውእቱ ቃል ኃደረ ላዕሌነ ፤ወተወልደ እምኔነ። @EOTCW ወረብ ፈክር ለነ ወልደ ነጎድጓድ ዘረፈቀ ውስተ ሕፅነ ነድ/፪/ ዘትቤ በወንጌል ፈክር ለነ ውእቱ ቃል ኃደረ ላዕሌነ/፪/ @EOTCW መልክአ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ሰላም ለእመትከ አረፍተ ቤተ ሕግ ዘሰፈረ፤ ወለእራኅቲከ ዘወርቅ እለ አጽንዓ በትረ ፤ፈለገ ሃይማኖት ዮሐንስ ዘታስተፌሥሕ ሀገረ፤ ማኅተምከ ደኃራዊ አመ ይትፈታሕ ድኅረ ፤ጥቃ ማኅደርከ ሀበኒ ማኅደረ። @EOTCW @EOTCW አመላለስ ፈለገ ሃይማኖት ዮሐንስ/፪/ ዘታስተፌሥሕ ሀገረ/፬/ @EOTCW @EOTCW ዚቅ ሃሌ ሃሌ ሉያ ምርሐኒ ፍኖተ ወእሑር ቤቶ፤ለአምላከ ዮሐንስ፤ እስመ ኪያሃ አኃሥሥ ዘአፈቀረት ነፍስየ ፤ማኅደረ ስምከ ከመ ተሀበኒ ተምኔትየ፤ ኲሎ አሚረ። @EOTCW ወረብ ምርሐኒ ፍኖተ ወእሑር ቤቶ ለአምላከ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ /፪/ እስመ ኪያሃ አኃሥሥ እስመ ኪያሃ አኃሥሥ ዘአፈቀረት ነፍስ ማኅደረ ስምከ/፪/ @EOTCW ዓዲ ዚቅ ይምርሐነ ፍኖቶ ለዘተወልደ እምድንግል፤ ያብዓነ ቤቶ ለዘሰከበ በጎል፤ ህየ ንሰግድ ኲልነ፤ለዘለብሶ ለአዳም፤ወለይእቲ ልብስ ዘንዝኅት በደም። @EOTCW @EOTCW መልክአ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ሰላም ለሕሊናከ ሀልዮ እከያት ዘኢለመደ፤ ወለአማዑቲከ ሐቅል በዋዕየ ፍቅረ ወልድ ዘነደ፤ ውስተ ኲለሄ ዮሐንስ ከመ ቃልከ አግሀደ፤ ሠለስተ አካላተ ወመለኮተ አሐደ፤ ሰባኬ ሃይማኖት እንበሌከ ኢነኃሥሥ ባዕደ። @EOTCW @EOTCW ዚቅ ወንጌለ መለኮት ሰበከ ስምዓ ጽድቅ ኮንከ፤ ወበእንተዝ አቡቀለምሲስ ተሰመይከ። @EOTCW @EOTCW ወረብ ስምዓ ጽድቅ ኮንከ ስምዓ ጽድቅ ኮንከ ወልደነጎድጓድ/፪/ ወበእንተዝ ተሰመይከ ተሰመይከ አቡቀለምሲስ/፪/ @EOTCW ዓዲ ዚቅ ሰባኬ ወንጌል መጋቤ ሃይማኖት፤ ቀዋሚሃ ለቤተክርስቲያን ፤ኮከብ ሥርግው ውስተ ሕፅነ ነድ ዘተሐጽነ በንጽሕ፤ ዘኅቡዕ ይኔጽር ምሥጢረ መለኮት፤ ዘመንክረ ይገብር እምኀበ መላእክት፤ ዮሐንስ  ድንግል ባሕረ ጥበባት ፤መምህረ ሰላም ለአሕዛብ። @EOTCW መልክአ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ በሕማሙ ብዙኅ ለዮሐንስ እኁክሙ፤ወበመንግስትክሙ ዘክቡር ሱታፌክሙ ፤ሐዋርያተ ሕግ ንዑ በበፆታክሙ፤ ሃበ ተጸውዓ ዝክረ ትፍሥሕተ ልብ ስሙ፤ እስመ ዘአሀዱ ክርስቶስ አባላት አንትሙ ዚቅ ወዮሐንስ አሐዱ እምሐዋርያት፤ እምቅዱሳን ቀደምት እስመ በዲበ ሠናይቱ ለሰብእ ለሰብእ ተአዛዚ @EOTCW ወረብ ወዮሐንስ አሐዱ እምሐዋርያት/፪/ እምቅዱሳን ቀደምት/፪/ @EOTCW ምልጣን ንዑኬ ጉባኤ ማኅበራ ለቤተክርስትያን ከመ ትስምዕዎ ለዮሐንስ ክቡር ወንጌላዊ ፤ዮሐንስ ታዎሎጎስ ዮሐንስ አቡቀለምሲስ ፤ዮሐንስ ዘረፈቀ ውስተ ሕፅኑ ለኢየሱስ። @EOTCW አመላለስ፦ ዮሐንስ ዘረፈቀ ውስተ ሕፅኑ/2/ ውስተ ሕፅኑ ለኢየሱስ/4/ @EOTCW ወረብ ንዑኬ ጉባኤ ማኅበራ ለቤተክርስቲያን ከመ ትስምዕዎ ለዮሐንስ ወንጌላዊ ክቡር/፪/ ዮሐንስ ታዎሎጎስ ዮሐንስ አቡቀለምሲስ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ/፪/ @EOTCW እስመ ለዓለም ሰባኬ ወንጌል ዮሐንስ አርጋኖነ ትንቢት፤ዘይደምፅ ለቤተክርስቲያን ፤ቀርን ነባቢ ዘይጼውዕ መሐይምናነ፤ ኮከብ ዘኤፌሶን ዓምደ ብርሃን ዘፍጥሞ፤መልአክ ዘበምድር ረዓዬ ምሥ ጢር ፤ምዑዝ ከመ ጽንሐሕወ ከመ ዕጣን ንጹሕ @EOTCW አመላለስ መልአክ ዘበምድር ረዓዬ ምሥጢር/፪/ ምዑዝ ከመ ጽንሐሕ ወከመ ዕጣን ንጹሕ/፪/ @EOTCW @EOTCW ወረብ ሰባኬ ወንጌል ሐዋርያ ትንቢት ለቤተክርስቲያንዘይደምፅ ቀርን ነባቢ ለቤተክርስቲያን/፪/ ዮሐንስ ኮከብ ዘኤፌሶን ዓምደ ብርሃን ዘፍጥሞ መልአክ ዘበምድር ዘበምድር መልአክ/፪/ @EOTCW ዓዲ እስመ ለዓለም ሠረገላተ መሠለት ቤተክርስቲያን፤ እንተ አርባዕቱ ገበዋቲሃ አርባዕቱ ወንጌላውያን፤ዘብእሲ ማቴዎስ ዘአንበሳ ማርቆስ ወዘላህምሉቃስ፤ ዘንሥር ዮሐንስ ዜናዊ፤ ዘልዑለ ይሠርርወይነግር በምሥጢር፤ ህላዌሁ ወሥጋዌሁለወልደ እግዚአብሔር። https://t.me/Eotcw     #Join & share

ወልደ ነጓድጓድ መኃትው ፡ወዜማ እስከ ሰላም @EOTCW

☘☘☘☘☘☘☘☘☘ ስርዓተ ዋዜማ ዘጥር ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️❄️ ዋዜማ በ6- ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ወለደቶ እስከበቶ ውስተ ጎል፤ ወሰመየቶ አማኑኤል፤ ዘነቢያት ሰበኩ ምሥጢሮ፤ ሐዋርያት ተለዉ አሠሮ፤ ለዮሐንስ፤ ፈድፋደ አፍቀሮ @EOTCW @EOTCW ምልጣን፦ ዘነቢያት ሰበኩ ምሥጢሮ፤ ሐዋርያት ተለዉ አሠሮ፤ ለዮሐንስ፤ ፈድፋደ አፍቀሮ ፤ ለዮሐንስ፤ ፈድፋደ አፍቀሮ @EOTCW @EOTCW አመላለስ፦ ለዮሐንስ ፈድፋደ አፍቀሮ /2/ ለዮሐንስ ፈድፋደ አፍቀሮ /4/ @EOTCW @EOTCW ለእግዚአብሔር ምድር በምላሕ፦ አስተምህር ለነ ሰአልናከ ወልደ ነጎድጓድ ዮሐንስ አስተምህር ለነ ሰአልናከ @EOTCW እግዚአብሔርን ነግሠ፦ ባሕረ ጥበባት አበ ልሳናት ንሥር ሠራሪ ልዑለ ስብከት ዮሐንስ ወንጌላዊ ረዓዬ ኅቡዓት ነገሩኒ ቅሱም በጼወ መለኮት @EOTCW ይትባረክ፦ ተወልደ ኢየሱስ እም ዘርዓ ዳዊት በቤተ ልሔም ዘይሁዳ እማርያም እምቅድስት ድንግል @EOTCW ስቡውኒ፦ ዘዮሐንስ ሰበከ ወንጌለ ጸጋሁ ወኩሎሙ አሕዛብ ርእዩ ስብሐቲሁ @EOTCW @EOTCW ሠለስት፦ አዳም ቃለ እግዚአብሔር ውስተ አፉሆሙ ለቅዱሳን ወማርቆስኒ ይቤ ቀዳሚሁ ለወንጌለ ኢየሱስ ክርስቶስ ዮሐንስኒ ይቤ ቀዳሚሁ ቃል ቃለ እግዚአብሔር @EOTCW ሰላም ወራእዩ ለዮሐንስ፤ ዘከመ ርእዮ ለኢየሱስ ክርስቶስ፤ ዘአዕጋሪሁ ከመ ብርተ ሊባኖስ ዘአርሰንዎ፤ወአዕይንቲሁ ከመ ነደ እሳት ለዘመጽአ እምዘርዓ ዳዊት፤ ተወልደ እምዓመቱ ወሰላመ ገብረ በልደቱ @EOTCW @EOTCW አመላለስ፦ ተወልደ እምዓመቱ እምዓመቱ ተወልደ/2/ ወሰላመ ገብረ በልደቱ/4/ https://t.me/Eotcw     #Join & share

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለአቤል ቅቱል ወግዱፍ ማዕከለ አድባረ በድው ወተሰምየ በኵረ ቅቱላን እለ በእግዚእ። ተዘከረኒ እግዚኦ በምሕረትከ በእንተ አቤል ወበእንተ ቊርባኑ በወእንተ ደሙ፤ መሐረኒ በእንቲአሁ በሰማይ ወበምድር ሊተ ለገብርከ አሜን"። ትርጉም፦ በጌታ ስም ከተገደሉት ውስጥ በኵር (መዠመሪያ) ተብሎ ለተጠራ ተገድሎ በድኑም በምድረ በዳ መኻከል ለተጣለው ለአቤል ሰላምታ ይገባል፤ አቤቱ ስለ አቤል፣ ስለ ቊርባኑ፣ ስለ ደሙም ብለኽ በምሕረቱኽ ዐስበኝ፤ በምድርም ኾነ በሰማይ እኔን አገልጋይኽን ስለ ርሱ ስትል ማረኝ። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ "ሰላም ለአቤል ዘውክፍት ምሥዋዑ። እስመ ለልዑል አቅረበ በኵረ አባግዑ። ወበእንተዝ ተጽሕፈ ኀበ ሐዋርያት ስምዑ። በአምሳሊሁ በኵረ እንስሳ ወሰብእ ለአምላክ ያብኡ። ወበአምሳሊሁ አበው ሠርዑ"። ትርጉም፦ መሠዊያው (መሥዋዕቱ) ተቀባይነት ላላት ለአቤል ሰላምታ ይገባል፤ ለልዑል እግዚአብሔር ከበጎቹ የመዠመሪያውን አቅርቧልና፤ ስለዚኽ ነገር ምስክርነቱ በሐዋርያት ተጻፈ፤ በርሱ አምሳል (ርሱን አብነት አድርገው) ለአምላክ ከእንስሳ እና ከሰው የመዠመሪያውን ይሰጡ ዘንድ አባቶች ሥርዐትን ሠሩ። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር 2። https://t.me/Eotcw

photo content
+1