en
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

Open in Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

Show more
1 161
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
"በዘመኑም ትልቅ ፈተና ሆነ። ተዋህዶ ማቅ ለበሰች። ቤተክርስቲያንም አጥሯን በጥቁር ግምጃ ሸፈነች። ክርስቲያኖችም ጥቁር ማቅ ለብሰው እጆቻቸውን ወደ ሰማይም ዘርግተው እንደ ራሔል አለቀሱ። በአደባባዮች ተሰብስበውም እምባቸውን ወደ መንበረ ፀባኦት ረጩ። ቤተመቅደሱ ተደፈረ። በምድሪቱም ግፍና መከራ በዝቶ ነበር። የንፁሃን ደም በየቀኑ ይፈስ ነበር። በዘመኑም ጦርነት፣ ረሃብ፣ ቸነፈር ስደትና ሞት የአዘቦት ሆኖ ነበር። ቅዱስ ዳዊት እንዳለው ለእምነታቸው ቀናኢ የሆኑ ብዙ ምዕመናን ስለ አንዲት ተዋህዶ ሰማዕትነትን ተቀበሉ። ካህናቱም ስለ አንዲት ሃይማኖትና ስለ ምድሪቱ በግንባራቸው ተደፍተው እምባቸውን በቤተመቅደሱ አፈሰሱ። እንደ ዲዎቅልጢያኖስ ዘመን፣ የመሪዎችም ልብ በክፋትና በተንኮል ደንድኖ ነበር። ማስተዋልን ስተዋል፣ መስማትንም አይሰሙም ነበርና። በመጨረሻም........" ተብሎ የሚፃፍ ዘመን ላይ እያለፍን ነው😓

በአሁኑ ሰዓት‼️ አዲስ አበባ‼️ - ኮልፌ ልኳንዳ አሸዋ ሜዳ በሚወስደው መንገድ ያለች ፊሊዶሮ ልደታ ቤተክርስቲያን ጥቁር ለብሰው በገቡ ምህመናን ላይ ከባድ ድብደባ እየተፈፀመ ይገኛል የክልሉ ፓሊስ
+2
በአሁኑ ሰዓት‼️ አዲስ አበባ‼️ - ኮልፌ ልኳንዳ አሸዋ ሜዳ በሚወስደው መንገድ ያለች ፊሊዶሮ ልደታ ቤተክርስቲያን ጥቁር ለብሰው በገቡ ምህመናን ላይ ከባድ ድብደባ እየተፈፀመ ይገኛል የክልሉ ፓሊስ ከቤተክርስቲያን ውጡ ብለው በኃይል ሲያስወጡ የተዘጋጁ ህገወጥ ሰዎች ከየቤቱ በመውጣት ምህመናችን ላይ ዱላ ድብደባ ፈፈጽመዋል የአዲስ አበባም ሕዝብ እንዳይሄድ በዚህ መልኩ መንገድ ተዘግቷል። - ቀራኒዮ ወይብላ ማርያም ምህላ ለማድረስ የመጡ ምእመናን ይዘው ሄደዋል ከኬላው ማለፍም አይቻልም ብለው እየመለሱ ይገኛሉ።

29 tir.mp31.82 MB

photo content

photo content

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፳፱ 29 ቀን ❤ እንኳን ጌታችን በአካል ተገልጦ በደሃ ሰው ተመስሎ ከማኅበረ ዴጔ ጋር በመካከላቸውም ተገኝቶ የጽዋ ማኅበር እየጠጣ ተራው ደርሶ ተዓምር አድርጎ አምላክነቱ ለገለጠበት ቀን ለመታሰቢያ በዓል፣ የስሟ ትርጓሜ መጻተኛ ለሆነ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በራእይ ለተገለጠላትና ከከበሩ ነገሥታት ወገን ለሆነችው ዓለምን ንቃ በመመንኰስ በምትተኛ ጊዜ ያለ ምንጣፍ በምድር ላይ እየተኛችና ጥሬ ባቄላን ብቻ እየተመገበች በታላቅ ተጋድሎ ለኖረችው ለከበረች ቅድስት አክሳኒ ለዕረፍቷ በዓል መታሰቢያ፣ ተጋዳይ ለሆነ በበረሃ ውስጥ የሞተ ሰው ራስ ቅል አግኝተው የራስ ቅሉን ላነጋገሩና ሥራውን መርምረው ለተረዱ በኋላም አማልደውት ምሕረትን ላሰጡት አባ እስጢፍኖስ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከድንግል እመቤታችን ማርያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ከተወለደበት ከልደቱ መታሰቢያ፣ ከመስተጋድል ከከበረ ሰማዕት ከሰርያኮስ ከመታሰቢያው፣ ከሮሜ ሰዎች ውስጥ ከንጹሐት ሴቶች ከመታሰቢያቸው፣ ከፊልንማ፣ ከኢያልኒ፣ ከሰረባሞኒና ከቃውት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ ቅድስት አክሳኒ፦ ይችም ቅድስት የስሟ ትርጓሜ መጻተኛ ለማለት ነው። እርሷም ከሮሜ አገር ለከበሩ ሰዎች ልጅ ናት ወላጆቿም ከርሷ በቀር ልጅ የላቸውም እርሷም የምትጋደል ሆነች በቀንና በሌሊትም ትጾማለች ትጸልያለች በሮሜ አገር ወዳለ የደናግል ገዳም በመሔድ ከእርሳቸው ጋር ታገለግላለች ትጸልያለች በሮሜ አገር ወዳለ የደናግል ገዳም በመሔድ ከእሳቸው ጋር ትጋደላለች ከአባቷ ቤት የሚያመጡላትን ምግብ ለድኆችና ለምስኪኖች ሰጥታ እርሷ ከደናግል ምግብ ትመገባለች የደናግል መነኵሳይትንም ገድል አዘውትራ ታነባለች ከእርሳቸውም ጋር አንድ ያደርጋት ዘንድ እግዚአብሔርን አብዝታ ትለምን ነበር። ❤ ከዚህም በኋላ ወላጆቿ ሊአገቧት አስበው ከሮሜ አገር ታላላቆች ለአንዱ አጭዋት የወርቅ ልብሶችን ከወርቅና ከብር የተሠሩ የከበሩ ሽልማቶችንና ጌጦችንም አዘጋጁላት። የጋብቻውም ቀን ሲደርስ እናቷን "እናቴ ሆይ በምታጋቡኝ ጊዜ ወደ ደናግል መሔድ አይቻለኝም እኔ ዛሬ ሔጄ በረከታቸውን ተቀብዬ ሰላምታ ሰጥቻቸው ፈጥኜ መመለስ እሻለሁ" አለቻት። እናቷም የነገሥታት የሆነ የወርቅ ልብሶችን አልብሳ ሴቶች አገልጋዮችን ከእርሷ ጋር አድርጋ አሰናበተቻት። ❤ እርሷም ግን ወደ ባሕር ወደብ ተጉዟ መርከብንም አግኝታ ተሳፈረችና ወደ ቆጵሮስ ደሴት ሔደች። ወደ ከበረ ኤጲፋንዮስም ደርሳ ኀሳቧን ሁሉ አስረዳችው የከበረ ኤጲፋንዮስም ወደ እስክንድርያ አገር ሰደዳት ወደዚያም በደረሰች ጊዜ በሕልሟ የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ተገልጾ ስሙን ነገራትና የምትሠራውን ሁሉ አስተማራት። በማግሥቱም ወደ ሊቀ ጳጳስት ቴዎፍሎስ ገባች የራሷንም ጠጉር ተላጭታ የምንኵሴና ልብስን ለበሰች ከርሷ ጋር ያሉ ሽልማቶችንና ጌጦችን የወርቅ ልብሶችንም ሸጠችና በሰማዕታት መጀመሪያ በከበረ እስጢፋኖስ ስም ቤተ ክርስቲያን ሠራች አባ ቴዎፍሎስም ብዙዎች ደናግል መነኰሳይትን ሰበሰበላትና በዚያ ገዳም ከርሷ ጋር የሚኖሩ ሆኑ። ❤ ይቺም ቅድስት አክሳኒ ታላቅ ተጋድሎን ጀመረች እርሷ ከጥሬ ባቄላ በቀር በእሳት ያበሰሉትን አትቀምስና በምትተኛም ጊዜ ያለ ምንጣፍ በምድር ላይ ትተኛ ነበር እንዲህም እየተጋደለች ሃያ ዓመት ያህል ከዚያም የሚበዛ ኖረች ከዚህም በኋላ ጥቂት ታመመችና ዐረፈች። ልዑል እግዚአብሔር የሰጣትን ልዕልና ሊገልጥ ወደደ። በአረፈችበትም ዕለት ሰዎች በቀትር ጊዜ የብርሃን መስቀል በሰማይ ውስጥ አዩ ብርሃኑም የፀሐይን ብርሃን ሸፍኖ ነበር የሚያበሩ ከዋክብትም አክሊላትም በዙሪያው ሁነው ሥጋዋን ከደናግል ሥጋ ጋር አስከ አኖሩ ድረስ የሚያበሩ ሆኑ ከዚያም በኋላ ተሠወረ ይህም ስርሷ እንደተገለጠ ሕዝቡ አወቁ። ❤ በዚያንም ጊዜ እነዚህ ሁለት አገልጋዮቿ የዚችን ቅድስት አክሳኒ ከመጀመሪያው እስከ ዕረፍቷ ያለ ገድሏን ለሊቀ ጳጳሳቱና ለሕዝቡ ሁሉ ስማቸውን ለውጣ እኅቶቿ እንዳለቻቸው እርሷንም እመቤታችን ማለት ሳይሆን እኅታችን እንዲሏት ምሥጢሯንም ሁሉ እንዲሠውሩ እንዳማለቻቸው ተናገሩ። ሊቀ ጳጳሳቱና ሕዝቡም ሁሉ አደነቁ ገድሏንም እስከመጨረሻው ጻፉ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት አክሳኒ በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ አባ እስጢፋኖስ፦ ይህም ቅዱስ ቅዱሳን ገዳማውያንን በመፈለግ በበረሀ ውስጥ ሲዞር የወደቀች የሰው ራስ አገኘ እርሷም ሥጋ የልላት ዐጥንት ብቻ ናት። ሥራዋንም ያስረዳው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመነ በዚያንም ጊዜ ከዚያች ራስ ውስጥ እንዲህ የሚል ቃል ወጣ "እኔ በብዝበዛ ጭምር የማተርፍ ነጋዴ ነበርኩ መመጽወትንም አላውቅም በእኔ ዘንድ ሩቅ ወደ ሆነ አገር ስጓዝ ውኃ ወደ ሌለበት በረሀ ደረስኩ የቀን ሐሩርም በጸና ጊዜ ግመሎቼ ሞቱ ባሮቼም ሸሹ ብቻዬንም ቀረሁ። በሦስተኛውም ቀን ዐይኖቼ ከበዱኝ እንደፋጨትም ያለ ሰማሁ ያንጊዜ ነፍሴ ወጣች እንደሥራዬም ቅጣቴን ልቀበል ወደ ሥቃይ ቦታ ወሰዱኝ አንተም በለመንክ ጊዜ ሥራዬን እነግርህ ዘንድ ወዳንተ አመጡኝ አሁንም ወደ ሥቃይ ቦታ እንዳይመልሱኝ እግዚአብሔርን ስለ እኔ ምሕረትን ትለምነው ዘንድ እማልድሃለሁ" አለው። ❤ ቅዱስም ወደ እግዚአብሔር ስርሱ ለመነለት በዚያንም ጊዜ ስለ አንተ ምሬዋለሁ የሚል ቃልን ሰማ ይህንንም ሰምቶ ወደ በዓቱ ሔደ እስከ ዐረፈ ድረስም እያለቀሰና ደረቱን እየደቃ ኖረ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ እስጢፋኖስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 29 ስንክሳር። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ምስሌከ ቀዳማዊ በዕለ ኃይል። ወብርሃኖሙ ለቅዱሳን። ወለድኩከ እምከርሥ እምቅድመ ኮከበ ጽባሕ"። መዝ 109፥3 ወይም መዝ 38፥12-13።የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 12፥16-40 ወይም ዮሐ1፥7-15። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "እስመ ፈላሲ አነ ውስተ ምድር። ወነግድ ከመ ኵሉ አበውየ። ስሐተኒ ከመ አፅርፍ"። መዝ 38፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 3፥14-1ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 1፥9-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 3፥12-17። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 1፥7-15። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የጌታችንን በማኅበረ ዶጌ ያደረገ የተአምር በዐል፣ የአቡነ ታዴዎስ፣ የአቡነ ማትያስና የአቡነ ገብረ ናዝራዊ የዕረፍታቸው በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

photo content
+4

ለየች፡፡ ለወንዶቹ ለብቻ፣ ለሴቶቹም ለብቻ ገዳም መሥርታ ዘወትር እንዳይተያዩ አደረገች"፡፡ ❤ ሌላው የአቡነ ገብረ ናዝራዊ ደብረ ኀረይክዋ ገዳማቸውን ልዩ ከሚያደርጉት ነገሮች ውስጥ ጻድቁ በዘንዶ አማካኝነት ወደ ተራራው ሲወጡ መጀመሪያ የረገጡት ዓለት የእግር ጣታቸው ምልክት ያለበት መሆኑ ነው፡፡ እናቶች ምጥ ሲይዛቸው ወይም ሰዎች ሲታመሙ ድርቅና ቸነፈር ሲከሰት የሚፈውስና ምሕረት የሚያወርድ እንዲሁም የተጣሉ ሰዎች የሚታረቁበት ነባኢ መስቀል (የሚያነባ መስቀል) በገዳሙ ይገኛል፡፡ በየዓመቱ ጥር 29 ቀን የዕረፍታቸው በዓል በድምቀት ይከበራል፡፡ ከአባታች ከአቡነ ገብረ ናዝራዊ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

እስመ ኀረይክዋ-ይህቺ ማረፊያዬ እንድትሆን መርጫታለሁ" በማለት ጻድቁ የሰየሙት ስያሜ መሆኑ በቅዱስ ገድላቸው ላይ ተጽፏል፡፡ ጻድቁ ወደ ዓምባው ላይ የወጡት እንደ አቡነ አረጋዊ በዘንዶ ታዝለው፡፡ ❤ ጻድቁ አቡነ ገብረ ናዝራዊ በሰሜን ሸዋ ይፋትና ጥሙጋ ደብረ ሲና ውስጥ ቀወት በምትባለው ቦታ በ13ኛው መ/ክ/ዘ ተወለዱ፡፡ አባታቸው ስቡሐ አምላክ እናታቸው ክርስቶስ ክብራ የሚባሉ የነገሥታት ወገን ናቸው፡፡ የአባታችን የስማቸው ትርጉም "በስዕለት ለእግዚአብሔር የተሰጠ ልዩና የተቀደሰ" ማለት ነው፤ ይህም የበኩር ልጅ ስለሆኑና በስዕለት የተሰጡ ስለሆነ ነው፡፡ ወላጆቻቸውም ፈሪሃ እግዚአብሔርንና የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በሚገባ እያስተማሩ በምግር በሃይማኖት ኮትኩተው አሳደጓቸው፡፡ ዲቁናን ከተወበሉ በኋላ በሸዋ አካባቢ እየተዘዋወሩ ወንጌልን መስበክ ጀመሩ፡፡ ነገር ግን በዚህ በሐዋርያዊ አገልግሎታቸው ጊዜ ብዙ ፈተና ገጠማቸው ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ከላይ በአቡነ ታዴዎስ ገድል ላይ እንዳየነው ሰይጣን በንጉሡ በዓምደ ጽዮን ፍቅረ ዝሙት አሳድሮበት በክፉዎችም ምክር አታሎት የአባቱን ሚስት በማግባቱ ምክንያት አቡነ ገብረ ናዝራዊም ይህን ሲሰሙ እንደ ነቢዩ ኤልያስና እንደ መጥምቁ ዮሐንስ በቀጥታ ሄደው ንጉሡን ገሥጸው አወገዙት፡፡ በዚህም ምክንያት ንጉሡ በማሠር ብዙ አሠቃያቸው፡፡ ጳጳሱ አባ ያዕቆብን ጨምሮ ብዙ ቅዱሳንም ለስደት ተዳረጉ፡፡ ❤ አቡነ ገብረ ናዝራዊም አካባቢውን ለቀው እንዲሄዱ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው ከእሥር እንደተፈቱ ወደ ላሊበላ በመሄድ 12 ዓመታት በተጋድሎ ኖሩ፡፡ ወደ ሐይቅ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ገዳምም በመሄድ ካገለገሉ በኋላ ወደ ትግራይ ሄዱ፡፡ ከዚያም ግብፅን አቋርጠው ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ ከጳጳሱ አባ ያዕቆብ ጋር ሲነሡ አባ ያዕቆብ "በዓትህ ኢትዮጵያ ብቻ ናት" ብለው ስለነገሯቸው ሀሳባቸውን ትተው የጳጳሱን ምክራቸውን ተቀበሉና ከጉዞአቸው ቀሩ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ወደ አዲግራት በመሻገር ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን ፈጽሙ፡፡ መጀመሪያ እንደመጡ ያረፉባት አጋዝና በተባለቸው ተራራማ ቦታ ነበር፡፡ የአባታችን ሁለተኛ ቤተ ክርስቲያናቸው በዚህ ቦታ ላይ ታንጾ ይገኛል፡፡ በቦታውም ላይ 8 ዓመት ኖረውበታል፡፡ ወደሸለቆመም ዘቅዝቀው ወርደው ወደ ማየ ኢየሱስ በመሄድ ሓባ በምትባለው ተራራ ላይ የቁፋሮ ሥራ ጀምረው ባለ ሁለት ዓምድ የሆነ አንድ በር ያለው ቤተ ክርስቲያን አንጸው ሲያበቁ አሁን ወዳለው ገዳማቸው ደብረ ኀረይክዋ መጡ፡፡ ❤ አቡነ ገብረ ናዝራዊ ደብረ ኀረይክዋ ዓምባ ላይ ከወጡ በኋላ በመጀመሪያ የተለያየ መጠንና መጠሪያ ስም ያላቸውን ከዓለት ላይ የተፈለፈሉ አስደናቂ የሆኑ ከ44 በላይ የውኃ ጉድጓዶችን አንጸዋል፡፡ ከጉድጓዶቹም በተአምራት ጸበሎች ፈልቀውላቸዋል፡፡ እነዚህንም ጸበሎች እስከዛሬ ድረስ መጠናቸው ምንም ሳይጎድል ገዳማውያኑ ይጠቀሙባቸዋል፡፡ ጻድቁ በዚሁ ቦታ ከዓለት ላይ ፈልፍለው ያነጹት አስደናቂ ቤተ መቅደስ ይኛል፡፡ መካነ መቃብራቸውም በዚሁ ገዳማቸው ውስጥ በክብር ተቀምጦ ይገኛል፡፡ ❤ አቡነ ገብረ ናዝራዊ በጾምና በጸሎት ተወስነው ሕዝቡን በማስተማር ብዙ አስገራሚ ተአምራትን በመፈጸም ላይ እንዳሉ የቀድሞ ጓደኛቸው የነበሩትና በኋላም የነገሡት ዐፄ ዓምደ ጽዮን በትግራይ ከፍለ ሀገር አጋሜ አውራጃ ዓምባ ጽዮን በተባለው ተራራ ላይ ሽፍቶች ተነሥተው መሽገው ነበር፡፡ ንጉሡም እነዚህን የተነሡባቸውን ሽፍቶች ለመያዝ ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት ብለው 10 ሺህ ሠራዊት ይዘው ወደ አካባቢው ዘመቱ፡፡ ንጉሡም በአካባቢው እንደደረሱ አቡነ ገብረ ናዝራዊ በዚያ እንዳሉ ስለሰሙ መልእክተኞችን ልከው አስመጧቸውና የመሸጉትን ሽፍቶች በምን ዓይነት ዘዴ ድል ማድረግ እንደሚችሉ የጠቋቸው፡፡ አቡነ ገብረ ናዝራዊም "ለሦስት ቀናት ያህል በቤተ ክርስቲያን ጸሎትና ምህላ ይደረግ፣ ሕፃናት የእናቶቻቸውን ጡት እንዳይጠቡ ይከልከሉ፣ የሚጠቡ የቀንድ ከብቶችም ከጥጃዎቻቸው ጋር እንዳይገናኙ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ይደረግ" ብለው ነገሯቸው፡፡ ንጉሡም ጻድቁ እንዳሏቸው ቢያደርጉ በሦስተኛው ቀን ሽፍቶቹን በቀላሉ ማረኳቸውና አገሪቱ ሰላም ሆነች፣ ንጉሡም እጅግ ደስ አላቸው፡፡ አቡነ ገብረ ናዝራዊንም በማስጠራት "ያልከው ተፈጸመ፣ ድል አድርጌያለሁና ደስ ብለኛል፡፡ የትኛውን አካባቢ ርስት ጉልት አድርጌ ልስጥህ?" አሏቸው፡፡ ጻድቁም ለመነኰሳት ልጆቻቸው የእርሻ ቦታ የሚሆን ርስትን ተቀበሉ፡፡ አቡነ ገብረ ናዝራዊ ገዳማቸው ደብረ ኀረይክዋ በቁና በነጹ መነኮሳት እንዲገለገል ካላቸው ፍላጎት አኳያ መነኮሳቱንም ከዓለማዊ ፈተና ለመታደግ ሲሉ ሴቶች ወደ ገዳሙ እንዳይወጡ ከልክለዋል፡፡ አንዲት ሴት የጻድቁን ቃል በመተላለፍና በመደፋፈር ወደ ተራራው በመውጠቷ አፋፉ ላይ እንደደረሰች ከያዘችው ድፎ ዳቦ ጋር ድንጋይ ሆና ቀርታለች፡፡ ይህ ምስሏ አሁንም ድረስ ከነሙሉ የሰውነቷ ቅርጽ በግልጽ ይታያል፡፡ ❤ ሴቶች አንዳንድ ገዳማት ላይ እንዳይገቡ ገዳሙን የገደሙት ቅዱሳን የከለከሉበትን በቂ የሆነ መንፈሳዊ ምክንያት ስላላቸው ነው እንጂ እንዲሁ ያወጡት ሕግ አይደለም፡፡ ለዚህም ተጨማሪ ማሳያ ይሆን ዘንድ የእመ ምዑዟ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ የወንዶችና የሴቶች ገዳም የተለያየ እንዲሆን ያደረገችበት ምክንያት ከገድሏ ላይ እንይ፡- "እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ቤተ መቅደሷን በአንዲት ቀን ብቻ ሠርታ እንደጨረሰች ጌታችን ከመንበሩ ሆኖ ተገለጠላትና በቦታው ላይ ትልቅ ቃልኪዳን ሰጣት፡፡ ተአምራቶቿንና የትሩፋቷን ዜና የሰሙ ሁሉ ወደ እርሷ እየመጡ ተሰብስበው በተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ ቅድስት እናታችንም ትመክራቸውና ታስተምራቸው ነበር፡፡ በመንፈስ ቅዱስም ኃይል ተገልጾላት የበጎ ሥራ ጠላት የሆነው ሰይጣን በማኅበሩ ልቡና እርሻ ላይ እንክርዳድ ሽንገላን እንደዘራ ባየች ጊዜ ከዚህ በኋላ የወንዶቹንና የሴቶቹን ቦታ ለየች፡፡ ለወንዶቹ ለብቻ፣ ለሴቶቹም ለብቻ ገዳም መሥርታ ዘወትር እንዳይተያዩ አደረገች፡፡ ልጆቿንም ሁሉ የእግዚአብሔር መልአክ ይጠብቃቸው ነበር፡፡ እርሷም የአርባውን ጾም ስትጾም ምንም ሳትቀምስ በምድር ላይም ሳትቀመጥ ቆማ ትጨርሳለች፡፡ እንደዚሁም በሌሎች አጽዋማት እንዲሁ ታደርግ ነበር፡፡ በስግደትና በግርፋትም ብዛት ሰውነቷን እጅግ ትጎዳና ታደክም ነበር፡፡ መላእክትም ምግቧን ከሰማይ ኅብስትና ወይን ያመጡላት ነበር፡፡ ውዳሴ አምላክንና አርጋኖንን በጸለየች ጊዜ ጌታችንና እመቤታንም በየጊዜው እየመጡ እየባረኳት ይሄዳሉ፡፡ የዕረፍት ጊዜዋም ከመድረሱ በፊት መላእክትም በብርሃን ሠረገላ ወደ ብሔረ ሕያዋን ወስደው ሥጋ ወደሙን እንትድቀበል አድርገዋታል"፡፡ ❤ አንዳንድ አላዋቂ ሰዎች በተለይም ከእኛ እምነት ውጭ ያሉ ሰዎች የሴቶችን ወደ አንዳንድ ገዳማት መግባት አለመቻል በዘመኑ የእኩልነት ስሌት ያሰሉታል፡፡ ይህን ሀሳብ የሚጋሩ አንዳንድ ኦርቶዶክሳውያን እኅቶችና እናቶችም አይጠፉም፡፡ እውነታው ግን ይህ ነው፡- ቅዱሳን አባቶቻችንና ቅዱሳት እናቶቻችን ይህን ሕግ የሠሩበት ምክንያት ግን ከላይ እንዳየነው በውል የታወቀና የተረዳ እውነት ነው፡፡ "ገዳማቸው በቁና በነጹ መነኮሳት እንዲገለገል ካላቸው ፍላጎት አኳያ መነኰሳቱንም ከዓለማዊ ፈተና ለመታደግ ሲሉ ሴቶች ወደ ገዳሙ እንዳይወጡ ከልክለዋል"፡፡ ፤ "ለቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስም ኃይል ተገልጾላት የበጎ ሥራ ጠላት የሆነው ሰይጣን በማኅበሩ ልቡና እርሻ ላይ እንክርዳድ ሽንገላን እንደዘራ ባየች ጊዜ ከዚህ በኋላ የወንዶቹንና የሴቶቹን ቦታ

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፳፱ 29 ቀን ❤ እንኳን ለኢትዮጵያኑ ጻድቃን እንደ ሐዋርያው ቅዱስ ታዴዎስ ግመልን በመርፌ ቀዳዳ ላሾለኩ ለታላቁ አባት ለአቡነ ታዴዎስ ዘጽላልሽና ለአቡነ ማትያስ ዘጽላልሽ ገደል ውስጥ በመጣል ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል፣ በገዳማቸው ደብረ ኀረይክዋ ከዓለት ላይ የተፈለፈሉ 44 የተለያዩ ጸበሎች ለሚገኙበትና እንደ ደብረ ዳሞ በገመድ ብቻ ለሚወጣው ለታላቁ አባት ለአቡነ ገብረ ናዝራዊ ዘደብረ ኀረይክ ለዕረፍታቸው በዓልና ለታላቁ አባት ለአቡነ ገብረ መርዓዊ ለልደታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። + + + ❤ አቡነ ታዴዎስ ዘጽላልሽ፡-አባታቸው ካህኑ ሮማንዮስ የደብረ ሊባኖሱ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት አጎት ሲሆኑ እናታቸው ማርታ ይባላሉ፡፡ የትውልድ ቦታቸው ጽላልሽ ዞረሬ ነው፡፡ ሲወለዱ ዓምደ ብርሃን ተተክሎ የታየ ሲሆን እርሳቸውም በብርሃን ልብስ ተጠቅልለው ታይተዋል፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ለሊቀ ካህናቱ ለሕይወት ብነ በጽዮን ተሰጥተው ሃይማኖትን በሚገባ ተምረዋል፡፡ ❤ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዳሞት ተሻግረው ሞተሎሚን አስተምረው ካሳመኑት በኋላ አቡነ ታዴዎስን ወደ እርሳቸው እንዲመጡ ልከውባቸው ሄደው አቡነ ተክለ ሃይማኖትን እያገለገሉ ዘጠኝ ዓመት ተቀመጡ፡፡ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ግን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አባ በጸሎተ ሚካኤል ሲሄዱ አቡነ ታዴዎስም ወደ ጽላልሽ ተመልሰዋል፡፡ ሁለቱም ከ32ዓመት በኋላ ተመልሰው በጽላልሽ ተገናኘተው አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለአቡነ ታዴዎስ ማዕረገ ምንኩስናን ሰጥተዋቸዋል፡፡ ❤ አቡነ ታዴዎስም በሥጋ ዕድሜ ታላቅ ቢሆኑም እንደታናሽ ብላቴና አቡነ ተክለ ሃይማኖትን እያገለገሉ በደብረ ሊባኖስ ተቀምጠዋል፡፡ ከዚህ በኋላ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አቡነ ታዴዎስን ወደ ጽጋጋ እንዲሄዱ ነገሯቸው ምክንያቱም አቡነ አኖሬዎስ በዚያ ሲያስተምሩ ከሃዲያን ደብድበው አስረዋቸው ነበር፡፡ እሳቸውም ታስረው ሳለ ወደ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘንድ የሚላካቸው ሲያስቡ ቁራ መጥቶ "እኔ እላክሃለሁ" ቢላቸው "ክፋትህ እንደ መልክህ ነው"ብለው እምቢ አሉት፡፡ ፀአዳ ኦፍ መጥቶ እኔ ከሀገራችሁ ኮዞረሬ የመጣሁ ነኝ "እኔ እላክሃለሁ" ብትላቸው "መጥተህ አድነኝ" ብለው በክንፏ ላይ ጽፈው ልከዋት እርሷም መልእክቱን ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት አድሳ ነበር፡፡ ስለዚህም ነው አቡነ ታዴዎስን ሕዝቡን ከኃጢአት ግዞት አኖሬዎስን ከእስራት እንንዲያስፈቱ የላኳቸው፡፡ ❤ አቡነ ታዴዎስም ከደብረ ሊባኖስ ወደ ደብረ ማርያም በሠረገላ ነፋስ ተጭነው በአንድ ሰዓት ደርሰው መዩጥ ከተባለውና አኖርዮስን ካሰራቸው ንጉሥ ፊት ቢደርሱ ንጉሡ በግንጋጤ መልአክ የመጣበት መስሎት ሲፈራ ከሰው ወገን መሆናቸውን ነግረው ክርስትናን አስተማሩት፡፡ ጋኔን ከእሳት ጥሎት ሲሠቃይ የሚኖርና ሊሞት የደረሰ ልጁን ቢፈውሱለት በትምህርታቸውና በተአምራታቸው አምኖ ሕዝቡ ክርስትናን እንዲቀበል በአዋጅ አስነገረ፡፡ አፍጃል የሚባለው ባለጸጋ ወደ አቡነ ታዴዎስ ቀርቦ ሲማር "ባለጸጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ይልቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልክ ይቀላል" ማቴ 19፥24፣ ማር10፥25፣ ሉቃ18፥25) የሚለውን የወንጌል ቃል ሲሰማ ለአእምሮው ረቆበት "እስቲ አድርገህ አሳየኝ?" አላቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም እናቲቱን ግመል ከነጇ ቀጥሎም 28ግመሎችን በየተራ በመርፌ ቀዳዳ እያሾለኩ አሳይተውታል፡፡ ሕዝቡ ሁሉ በእጅጉ ሲገረምና "በአምላከ ታዴዎስ ስም አምናለሁ" ሲል የባለጸጋው ልጅ ሙሳ ግን "በምትሀት አሳይቶን ነው እንጂ የእውነት አይደለም" በማለት አባቱንም እንዳያምን ይናገር ጀመር፡፡ ይህንንም ሲናገር በመጀመሪያ ያለፈችው እናቲቱ ግመል እረግጣ ገደለችው፡፡ ❤ አቡነ ታዴዎስም ንጉሡን፣ አባቱን አፍጃልንና ሕዝቡን የሞተ እንደሚነሣ ሲያስምሯቸው "የሞተ ይነሣልን? እስኪ ይህ የሞተው ልጅ ይነሳና ሁሉም አይቶ ይመን" አሏቸው፡፡ እሳቸውም "ዛሬ ተቀብሮ ይዋልና ነገ በሦስተኛው ቀን ይነሣል" ብለዋቸው ተቀብሮ ዋለ፡፡ በማግሥቱም አፍጃልን ጠርተው "አልዓዛርን ከሞት ባስነሣው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ልጄ ሆይ ና ውጣ" ብለህ ከልጅህ መቃብር ላይ አኑረው" ብለው ዘንጋቸውን ሰጡት፡፡ ሄዶም እንዳሉት ቢያደርግ ልጁ አፈፍ ብሎ ተነሥቷል፡፡ ይህንን ያዩ የአገሩ ሰዎች ሁሉም አምነው ተጠምቀዋል፡፡ እሳቸውም 12አብያተ ክርስቲያናትን አሳንጸው ሞቶ የተነሳውን ሙሳን ሙሴ ብለው ሰይመው አስተምረው ሊቀ ካህናት አድርገው ሾመውት አቡነ አኖሬዮስን ይዘው ወደ ጽላልሽ ዞረሬ ተመልሰዋል፡፡ ❤ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ካረፉ በኋላ አባ ያዕቆብ የተባሉ ጳጳስ ከግብፅ መጡ፡፡ የአቡነ ታዴዎስን ዜና ሲሰሙ ተደስተው ከአቡነ ፊሊጶስ ጋር ሆነው አስጠርተዋቸው "የአባታችሁን ዜና ገድል ንገሩኝ" አላቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም ጨዋታ በአስተርጓሚ አይሰምርም" ብለው ወደ ጌታችን ቢጸልዩ የጳጳሱ ቋንቋ ለአቡነ ታዴዎስ፣ የአቡነ ታዴዎስም ቋንቋ ለጳጳሱ ተገልጦላቸው የመሸ የነጋ ሳይመስላቸው40 ጾምን ሲጨዋወቱ ቆይተዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ጳጳሱ ከንጉሡ ተማክረው "ሊቀ ካህናት ዘጽላልሽ" ብለው ሾመዋቸዋል፡፡ ❤ በነግህና በሰርክ ቤተ ክርስቲያንን እያገለገሉ፣ ቀን ወንጌልን እየሰበኩ፣ ሌሊት ከባሕር ገብተው ሲጸልዩ እያደሩ በታላቅ ተጋድሎ እየኖሩ ሳለ ከ10ዓመት በኋላ ሰይጣን በንጉሡ በዓምደ ጽዮን ፍቅረ ዝሙት አሳድሮበት በክፉዎችም ምክር አታሎት የአባቱን ቅምጥ አገባ አቡነ ታዴዎስም ይህን ሲሰሙ እንደ ነቢዩ ኤልያስና እንደ መጥምቁ ዮሐንስ በቀጥታ ሄደው ንጉሡን ገሥጸው አወገዙት፡፡ ገሥጸውና አውግዘው አቡነ ማትያስን አስከትለው ሲመለሱ ቅምጧ የንጉሡ ሚስት በፈረስ ተከትላ ደርሳ የኋሊት አሳስራ ዛሬ "ማርያም ገዳም" ከሚባለው ቦታ ፊት ለፊት ካለው ትልቅ ገደል ውስጥ ሁለቱንም ጣለቻቸውና ጥር29 ቀን በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ ❤ በሰማዕትነት ዐርፈው ደማቸው ከፈሰሰበት ከገደሉ ስር በፈለቀው ጸበላቸው "ታዴዎስ ወማትያስ" እያለ ሦስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ እያለ የተጠመቀ ሰ እንደ 40 ቀን ሕፃን እንደሚሆን ጌታችን ቃል ኪዳን ገብቶላቷቸዋል፡፡ ይህ ሰማዕትነት በተቀበሉበት አካባቢ የተሠራው ቤተ ክርስቲያናቸው በጠላት ወረራ ጊዜ ፈርሶ ቦታው ጠፍ ሆኖ የኖረ ቢሆንም የአካባቢው ሕዝብ ቦታውን ከልሎ በክብር ሲጠብቀው ስለኖረ ፈቃደ እግዚአብሔር ሆኖ የአቡነ ታዴዎስ ታቦታቸው በ2005ዓ.ም ከኢቲሣ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ወጥቶ ጻድቁ ሰማዕትነት በተቀበሉበት አካባቢ በተሠራው መቃኞ ቤተ ክርስቲያናቸው በታላቅ ክብር ገብቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑም ከኢቲሣ በእግር የአንድ ሰዓት ተኩል ርቀት ላይ ይገኛል። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳንና የጣና ሐይቅ ደብረ ማርያም ገዳም አጭር ታሪክ ከምትላው መጸሐፍ። + + + ❤ አቡነ ገብረ ናዝራዊ ዘደብረ ኀረይክዋ፡- ሐውዜን እንዳጋ ሥሉስ ውስጥ የሚገኘው ገዳማቸው 44 የተለያዩ ጸበሎች የሚገኙበትና 28 ሜትር ርዝመት ያለው ነው፡፡ ይህ ድንቅ ገዳም እንደ ደብረ ዳሞ በገመድ ብቻ ነው የሚወጣው፡፡ ከአዲግራት በስተ ደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ በ27 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘው ገዳሙ ኀረይክዋ የሚለውን ስያሜ ያገኘው ከራሳቸው ከአቡነ ገብረ ናዝራዊ ነው፡፡ ይኸውም ጻድቁ ብዙ ቦታዎቸን ሲያስሱ ከኖሩ በኋላ በመጨረሻ ይህን ስፍራ ተመልከተው እግዚአብሔርም የፈቀደላቸው በዓታቸው መሆኑን ዐውቀው "ዛቲ ይእቲ ምዕራፍየ

​​ጾመ ነነዌ ክፍል ሁለት ከፈለገ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ 2.ለኃጢአት ሌላ ተጠያቂ መፈለግ ሌላው ከንስሐ ሲያርቀን የሚገኘው ምክንያት በሰዎች መፍረድ ነው፡፡ በሰዎች የሚፈርድ ሰው ራሱን የሚያጸድቅ ነው፡፡ ራሱን ያጸደቀ ደግሞ ንስሐ መግባትና ከኃጢአት መመለስ ዳገት ይሆንበታል፡፡ ከነነዌ ሰዎች የንስሐ ታሪክ ውስጥ ለንስሐ በጣም አስቸጋሪ የነበረው ነቢዩ ዮናስ ነው፡፡ መርከበኞቹና የነነዌ ሰዎች በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ወደ እግዚአብሔር ሲመለሱ ዮናስ ግን ከታሪኩ መጀመሪያ እስከ መጨረሻዋ ጊዜ ድረስ በእግዚአብሔር ያጉረመርም ነበር፡፡ ለዚህም ምክንያቱ ከእግዚአብሔር መኮብለሉና የነነዌ ሰዎችን ድኅነት መቃወሙን እንደ ስህተት እንጂ እንደራሱ ስህተት አለመቁ ጠሩ ነው፡፡ ለዚህ ነበር ከእግዚአብሔር ኮብልሎ ሲሔድ እንኳ ምንም ዓይነት ጭንቀት ሳይሰማው "በከባድ እንቅልፍ" ተኝቶ የነበረው ዮና ፩፥፭ በተመሳሳይ መልኩ አንዳንድ ሰዎች ለራሳቸው ኃጢአት እግዚአብሔርን ተጠያቂ ሲያደርጉ ሌሎች ደግሞ ሰዎችን ተጠያቂ ያደርጋሉ፡፡ በዚህም በራሳቸው ከመፍረድ ይልቅ በሰዎች መፍረድ ይጀምራሉ፤ ወይም የኃጢአታቸው ምክንያት እግዚአብሔርን አድርገው ይገኛሉ፡፡ ነቢዩ ዮናስ የራሱን ክብር ፈላጊነት ሳይሆን የእግዚአብሔርን ምሕረት የኃጢአቱ ምክንያት ማድረጉ የሚያስገርም ነው፡፡ ይህም ለብዙ ጊዜ ከንስሐ እንዳዘገየው ከታሪኩ እንማራለን፡፡ በተቃራኒው ለንስሐ ቅርብ የሆኑት መርከበኞች በዮናስ ላይ ለመፍረድ ምን ያህል እንደተጨነቁ ስናይ ቀድሞውኑ በዮናስ አለመታዘዝ ምክንያም ቢሆን እግዚአብሔር ወደ ንስሐ ሊመልሳቸው የፈለገ ይህን አይቶ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ በጾመ ነነዌ የመጀመሪያው ቀን/ሰኞ/ የሚነበበው የቅዱስ ጳዉሎስ መልእክትም የሚያስተምረን ይህንኑ ነው፡- "ስለዚህ አንተ የምትፈርድ ሰው ሁሉ ሆይ፣ የምታመካኘው የለህም በሌላው በምትፈርድበት ነገር ራስህን ትኮንናለህና፡፡ አንተም ፈራጁ እነዚያን ታደርጋለህና፡፡ እንደዚህም በሚያደርጉት ላይ የእግዚአብሔር ፍርድ እውነተኛ እንደሆነ እናውቃለንና፡፡ . . . ወይስ የእግዚአብሔር ቸርነት ወደ ንስሐ እንዲመራህ ስታውቅ የቸርነቱንና የመቻሉን የትዕግሥቱንም ባለጠግነት ትንቃለህን? ነገር ግን እንደ ጥንካሬህና ንስሐ እንደማይገባ ልብህ የእግዚአብሔር ቅን ፍርድ በሚገለጥበት በቁጣ ቀን ቁጣን በራስህ ላይ ታከማቻለህሮሜ፪፥፩-፭ በተቃራኒው ግን በሰው ላይ ከመፍረድ በራሳቸው ላይ መፍረድን የሚመርጡ ሰዎች ለንስሐ ቅርብ ናቸው፡፡ በሚቀጥለው ቀን ማክሰኞ የሚነበበው የቅዱስ ጳውሎስ መልእክትም የሚያብራራው ይህንኑ ነው።፩ጴጥ፬፥፩ 3.የእግዚአብሔርን ተግሳጽ አለመቀበል በነነዌ ሰዎች የንስሐ ታሪክ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ሰዎችን ሲገስጽ እንመለከታለን፡፡ ነቢዩ ዮናስን በማዕበል፣ ወደባሕር እንዲወረወር በማድረግ፣ አሳ አንበሪ እንዲውጠው በማድረግእግዚአብሔር ወደ ትክክለኛ መንገዱ ሊመልሰው ቢጥርም በዚህ ሁሉ ሊመለስ አልቻለም፤ ከአሳ አንበሪ አፍ ወጥቶ ሔዶ ቢሰብክም እግዚአብሔር ይቅር ሲላቸው ግን በእግዚአብሔር ላይ ማጉረምረም ጀምሯልና፡፡ ድሮም ቢሆን በፍርሃት እንጂ ስህተቱን ተቀብሎ አልነበረም ወደ ነነዌ ሔዶ የሰበከው፡፡ ግዕዛን የሌላቸው ፍጥረታት /ነፋስ፣ አሳ አንበሪ፣ ትል፣ ፀሐይ/ እንዴት እንደሚታዘዙለት እርሱ ግን ታላቅ ነቢይ ሲሆን አልታዘዝም ማለቱን በማሳየትም ገስጾታል፡፡ በመጨረሻም ለንስሐ በቅቷል፡፡ መርከበኞቹም በመርከባቸው ላይ የተነሣው ማዕበል ተግሳጽ ሆኗቸው ወደ ንስሐ ተልሰዋል፡፡ ከዘላለም ሕይወት እንዳንለይ አጥብቆ የሚፈልገው እግዚአብሔር ልዩ ልዩ መከራዎችንም በማምጣት ወደ ንስሐ እንድንመለስ ያደርጋል፡፡ ለዚህ ተግሳጽ ግን በትክክለኛ ወይም በተሳሳተ መንገድ መልስ ልንሰጥ እንችላለን፡፡ ካወቅንባቸውና ከተጠቀምንባቸው ችግሮችና መከራዎች ወደ ንስሐ የሚመሩ መንገዶች ናቸው፡፡ የነነዌ ታሪክም የሚነግረን ይህንኑ ነው፡፡ በነነዌ ጾም በቅዳሴ የሚነበቡት የሚከተሉት ምንባባትም በአጽንኦት የሚገልጹት ይህንኑ ነው፡፡ ምስባክ:- "ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ በላዬ አለፈ፡፡እግዚአብሔር በቀን ቸርነቱን ያዛል በሌሊትም ዝማሬው በእኔ ዘንድ ይሆናል የእኔ ስዕለት ለሕይወቴ አምላክ ነው፡፡"መዝ፵፩፥፯-፰ መልእክት:- ". . . ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል. . ."ሐዋ፲፬፳፪ በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ አሳዛኙ ነገር ሰው ካለፈ ሕይወቱ አለመማሩ ነው፡፡ በነቢዩ በዮናስ ታሪክም የምናገኘው ይህንኑ ነው፡፡ እግዚአብሔር የተሳፈረበትን መርከብ ካናወጠ፣ ዮናስ በአሳ አንበሪ እንዲዋጥ ካደረገ በኋላ እንኳ እግዚአብሔር በነነዌ ሰዎች ላይ ያሳየው ምሕረት ዮናስ ሞትን እስኪመኝ ድረስ እንዲያዝንና በእግዚአብሔር ላይ እንዲያጉረመርም አድርጎታልና፡፡ በእኛም ሕይወት ተመሳሳይ ተግሳጻት ከእግዚአብሔር ዘንድ ቢመጣም ከኃጢአት ባለመመለስ ከዮናስ ያልተለየ መልስ ነው የምንሰጠው፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ራሳችንን የምናይበት፣ በሕይወታችን ያደረጋቸውን የእግዚአብሔር ሥራዎች የምንመረምርበት፣ በውስጣችን ያደፈጡትን አውሬዎች የምናድንበት የተረጋጋና ሰፋ ያለ ጊዜ ስለሌለን ነው፡፡ ይህን አጥብቃ የተረዳችው ቅድስት ቤተክርስቲያናችን በልዩ ልዩ መንገድ የሚጠራንን የእግዚአብሔር ድምፅ የምናዳምጥበት፣ በመልካም ምክንያቶች የተሸፈኑ ነገር ግን መልካም ያልሆኑና መልካም ልንሠራበት የምንችለውን የሕይወት ጊዜዎችን የሚያቃጥሉ ከንቱ ምኞቶቻችን፣ የማይጨበጡና የማይደረስባቸው "ክፉ ተስፋዎቻችን" ሁሉ የምንመረምርበት፣ መልካሟንና እውነተኛዋን ነገር ግን አስቸጋሪዋንና ጠባቧን የሕይወት መንገዳችን አጉልተን "የምናስምርበት" ሰፋ ያለ ጊዜ ሰጥታናለች፤ ይህም ዐቢይ ጾም ነው፡፡ በዚህ ጊዜ በአግባቡ ከተጠቀምንበትም የዚህን አስቸጋሪና አወናባጅ ዓለም በድል የተወጡ ሰዎች የሚያዩትን የዘለዓለማዊን ሕይወት "ቀብድ" የትንሣኤውን ብርሃን እናያለን፡፡ ዐቢይ ጾምን እንደሚገባ ያላሳለፈ ክርስቲያን ግን የትንሣኤን ድግስ በልቶ ሆዱን ይሞላ እንደሆነ እንጂ የትንሣኤን ታላቅ ደስታ መቅመስ አይችልም፡፡ ስለዚህም ዐቢይ ጾም ለክርስቲያን ታላቅ ስጦታ መሆኑን ልናውቅ ይገባል፡፡ ለዚህም ነው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ስለጾም በጻፉት መጽሐፋቸው በዐቢይ ጾም ሕይወቱን ያልቀየረ ክርስቲያን በሌሎች አጽዋማት ይቀይራል ማለት ይከብዳልበማለት የጻፉት፡፡ 4.ክፉ እኔነት ክፍል ሦስት ይቀጥላል... ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮ @yamazemur_getemoche ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯

​​ጾመ ነነዌ ክፍል አንድ ከፈለገ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ የነነዌ ጾም ከሰባቱ የቤተክርስቲያን አጽዋማት አንዱና የዐቢይ ጾም ማዘጋጃ ደወል ነው፡፡ ይህ የነነዌ ሰዎች የንስሐ ታሪክ በቤተክርስቲያናችን በጣም ታላቅ ዋጋ ያለውና የራሱ መዝሙር የሚዘመርለት፣ ቅዳሴ የሚቀደስበት ታላቅ መታሰቢያ ያለው ታሪክ ነው፡፡ ራሱ ጌታችንም የነዌ ሰዎችን የንስሐ ታሪክ በመጥቀስ አይሁድን ገስጾበታል፤ በፍርድ ቀንም በዚያ ትውልድ ዘንድ እንደሚፈርዱበት ተናግሯል፡፡ ይህም የሆነበት የነነዌ ሰዎች ደስ የሚያሰኝ የንስሐ ታሪክ ስላላቸው ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ ይህን አስደሳች የንስሐ ታሪክ በጾመ ነነዌ ከሚነበቡ የቅዳሴ ምንባባት አንጻር ለመመርመር እንሞከራለን፡፡ ኃጢአት ከእግዚአብሔር መለየት እንደሆን ሁሉ ንስሐ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር መመለስ ነው፡፡ በዚህ ከእግዚአብሔር ሊለዩ የሚችሉ ብዙ ፈተናዎች ባለቡት ዓለም እስካለን ድረስ ሕይወታችን ሁሉ የንስሐ ጊዜ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ከሁሉም ጊዜ በተለየ ወደ እግዚአብሔር የምንመለስባቸው የጾም ወቅቶች ሲሆኑ ከእነዚህም ታላቁና ዋነኛው ዐቢይ ጾም ነው፡፡ ቅድስት ቤተክርስቲያናችን በዐቢይ ጾም ከእያንዳንዱ ምእመን ልቦና የንስሐ ፍሬን ትፈልጋለች፤ ያለትንሣኤ ልቦና /ንስሐ/ የክርስቶስን ትንሣኤ በእውነትና በደስታ ማክበር አይቻልምና፡፡ ለመሆኑ ከንስሐ የሚያሰናክሉን ነገሮች ምን ምን ናቸው? የነነዌ ሰዎች ታሪክ ስለዚህ ምን ያስተምረናል? 1.ቅንጦትን መውደድ ምንም እንኳን በደፈናው ገንዘብ የኃጢአት ምንጭ ነው ባንልም እንደ ወንጌል ትእዛዝ በክርስቲያናዊ መንገድ ካልተያዘ ግን እግዚአብሔርን ሊያስረሳና የኃጢአት ማስፈጸሚያና ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡ ብዙ ጊዜም ገንዘብና ባለጸግነት ከእግዚአብሔር በመለየታችን ያጣነውን ሰላምና ደስታ ለማግኘት ተስፋ የምንጥልበት ጣኦት ሆኖ ሊቀየር ይችላል፡፡ በሀብታችን በምናገኘው ጊዜያዊ ደስታና ሰላም ዘላለማዊውንና ፍጹምን የእግዚአብሔር ስጦታ መፈለግ፣ ወደ እግዚአብሔር መመለስን መናፈቅ ልናቆም እንችላለን፡፡ በዚህ መልኩ ብልጽግና ከንስሐ የሚያሰናክል ወጥመድ ይሆናል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር ሀብት እንኳ ቢሰጠን ለተቸገረ በመመጽወት፣ ልጆቻችን በክርስቲያናዊ መንገድ በማሳደግ፣ የቤተክርስቲያንን አገልግሎት በማፋጠን የእውነተኛ ደስታና የጽድቅ መንገድ እንድናደርገው እንጂ እግዚአብሔርን የተጠማች ነፍሳችንን ጥሪዋን በማደናቀፍና ጩኸቷን በማፈን በሥጋ ድሎት ውስጥ የምንደበቅበት መሣሪያ እንድናደረገው አይደለም፡፡ ለ"ታላቂቷ ከተማ" ነነዌም የጥፋት መንገድ የሆናት በብልጽግናዋና በታላቅነቷ እግዚአብሔርን ረስታ የኃጢአት ከተማ መሆኗ ነው፡፡ በነቢዩ በዮናስ ታሪክ ውስጥ ገንዘብ ለዮናስ ከእግዚአብሔር የመከለያ መሣሪያ ሲሆን እናገኘዋልን፡፡"... ከእግዚአብሔርም ፊት ኮብልሎ ከእነርሱ ጋር ወደ ተርሴስ ይሔድ ዘንድ ዋጋ ሰጥቶ ወደ እርሷ /ወደ መርከቧ/ ገባ"እንዲል ዮና፩፥፫ በዚህ ሰዓት ለዮናስ ገንዘብ ባይኖረው ይሻል ነበር፡፡ እኛም ቢሆን ከንስሐ የሚመልስ፣ ለኃጢአት መሣሪያ የሚሆን ሀብት ከሚኖረን በድኅነት ብንኖር ይሻለናል፡፡ ምንም እንኳ በቤተክርስቲያናችን ትውፊት ዐቢይ ጾም አብዝተን የምንጸልይበት፣ በጾም በስግደትና በምጽዋት ልናሳልፈው የሚገባ ወቅት ቢሆንም ፤ አሁን አሁን ግን ገንዘብ ማግበስበሻ እየሆነ እንደሆነ እናያለን፡፡ በመሠረቱ በጾም ወቅት ከሆዳችን የምንቀንሰው ገንዘብ እንድናጠራቅመው ሳይሆን እንድንመጸወተው የሚገባ ነው፡፡ ለማጠራቀምማ የማያምኑ ሰዎችስ ምግብ ይቀንሱ የለ? ለዚህ ነው በነነዌ ጾም በመጀመሪያው ቀን /ሰኞ/ የሚነበበው የቅዱስ ያዕቆብ መልእክት "አሁንም እናንተ ባለ ጠጎች ስለሚደርስባችሁ ጭንቅ ዋይ ዋይ እያላችሁ አልቅሱ፡፡ ሀብታችሁ ተበላሽቷል፣ ልብሳችሁም በብል ተበልቷ፡፡ ወርቃችሁም ብራችሁም ዝጓል፤ ዝገቱም ምስክር ይሆንባችኋል፤ ሥጋችሁንም እንደ እሳት ይበላል፡፡ ለኋለኛው ቀን መዝገብን አከማችታችኋል፡፡ እነሆ እርሻሁን ያጨዱት የሠራተኞች ደመወዝ በእናንተ ተቀምቶ ይጮኻል፣የአጫጆችም ድምፅ ወደ ጌታ ጸባዖት ጆሮ ገብቷል፡፡ በምድር ላይ ተቀማጥላችኋል፤ በሴሰኝነትም ኖራችኋል፤ ለእርድ ቀን እንደሚወፍር ልባችሁን አወፍራችኋል፡፡" ያዕ ፭፥፩ በማለት አስፈሪ ተግሳጽ የሚያስተላልፈው፡፡ ስለዚህ በዐቢይ ጾም አብዝተን የምንመጸውትበት፣ ከእግዚአብሔር የሆነውን ስጦታ የምንፈልግበት፣ የንስሐ ጊዜ ሊሆን ይገባል፡፡ 2.ለኃጢአት ሌላ ተጠያቂ መፈለግ ክፍል ሁለት ይቀጥላል... ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮ @yamazemur_getemoche ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯

የእናታችን የደብራችን ጥሪ ላልሰሙት አሰሙ !!! " ነነዌ ኢትዮጵያ " ❖ ፀሎተ ምህላ ,ስብከተ ወንጌል, ዝማሬ ❖ ከጥር 29 እስከ የካቲት 01 ለሶስት ተከታታይ ቀናት ❖ ሰዓት ከ11:00 ጀምሮ እ
የእናታችን የደብራችን ጥሪ ላልሰሙት አሰሙ !!! " ነነዌ ኢትዮጵያ " ❖ ፀሎተ ምህላ ,ስብከተ ወንጌል, ዝማሬ ❖ ከጥር 29 እስከ የካቲት 01 ለሶስት ተከታታይ ቀናት ❖ ሰዓት ከ11:00 ጀምሮ እስከ ምሽት 1:30 ሰዓት የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም

የካቲት 1 የማንቂያው ደወል ሳሪስ በሚገፕው ብሔረ ፅጌ መካነ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤ/ክ የካቲት 1 እንገናኝ።ሼር ሼር ሼር
የካቲት 1 የማንቂያው ደወል ሳሪስ በሚገፕው ብሔረ ፅጌ መካነ ሰላም ቅድስት ማርያም ቤ/ክ የካቲት 1 እንገናኝ።ሼር ሼር ሼር

"እስከ ሞት ድረስ የታመንህ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ" ----------------------------- የዮሐንስ ራእይ 2÷10 --------------------------

"…… ዓለም ምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው።" 1ኛ ዮሐንስ 5÷4

ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን፣ ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን። ሮሜ ፮:፭ በክርስቶስ ደም የተመሰረተችው ክርስትና ፣ሚዛኗ ሰማዕትነት ነው። እስከ ሞት ለታመነልን ኢየሱስ ክርስቶስ እስከ ሞት መታመን ነው።ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ መከራን በመከራ ላይ እየተቀበለ እሱ አልታወከም ነበር፣እስከ ሞት ድረስ ፀና እንጂ!!! #አንዲት_ቤተክርስቲያን #አንድ_ሲኖዶስ #አንድ_ፓትርያርክ

ከአርሲ የተላከልኝ በርቱ አሁን በዚህ ሰአት ኔትወርኩ ጸጥ ወደማለቱ ነው! አሁን እየተገናኘን ያለነው በ ሳፋሪኮም መስመር ነው! ከከተማው መግቢያ ትንሽ አለፍ ብሎ የምትገኘው ጎንዴ የምትባል ቦታ ደር
+2
ከአርሲ የተላከልኝ በርቱ አሁን በዚህ ሰአት ኔትወርኩ ጸጥ ወደማለቱ ነው! አሁን እየተገናኘን ያለነው በ ሳፋሪኮም መስመር ነው! ከከተማው መግቢያ ትንሽ አለፍ ብሎ የምትገኘው ጎንዴ የምትባል ቦታ ደርሰዋል ተብሎ "ወልዳ ዱከ ቡኦታ" የቸባሉት ማሕበር አባላት ሊቀበሏቸው በፓትሮል ታጅበው በውለት ቅጥቅጥ ሆነው ለባብሰው ሄደዋል! በሆቴሉ አቅራቢያ የነበረው ድርጊት ማደናገሪያ ይሁን አይሁን ጠብቀን ውጤቱን እነግርሃለው! ጸልዩልን ውጤቱ ጥሩ የሚሆን አልመሰለኝም!

photo content

😭 የሻሸመኔ ልደታ ማርያም ትሑቱ አገልጋይ አየለ ማንደፍሮ ወደ አገለገለው እና ወደሚናፍቀው አምላኩ በሰማዕትነት ሄዷል። በረከቱ ይደርብን!። 😭 "ደሞሙ ለሰማዕታትኪ ውኅይዘ ከመ ማይ። ደምፀ ነጎድጓዶሙ በጻ እስከ ሰማይ ኢትዮጵያ" ። ትርጉም፦ ደማቸው የምስክሮችሽ ፈሰሰ እንደ ውሃ። የደማቸውም ድምጽ ተሰማ እስከ ሰማይ ኢትዮጵያ። https://t.me/Eotcw