ሰዋስው ☘☘☘☘
Open in Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
Show more1 161
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 161
የማቴዎስ ወንጌል 5:4 የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና።
የዮሐንስ ራእይ 21:4 እንባዎችንም ሁሉ ከዓይኖቻቸው ያብሳል፥ ሞትም ከእንግዲህ ወዲህ አይሆንም፥ ኀዘንም ቢሆን ወይም ጩኸት ወይም ሥቃይ ከእንግዲህ ወዲህ አይሆንም::
1 161
በአርባ ምንጭ አረጋዊ የእስልምና እምነት ተከታይ የሆኑ አባት እንዲህ በደ/መ/መድኃኔአለም ቤተክርስቲያን ተገኝተው የህዝበ ክርስቲያኑን ህመም ተጋርተዋል.....እናመሰግናለን!
በህመማችን የተሳለቃችሁ የሌላ ቤተ እምነት ግለሰቦች ልብ ይስጣችሁ።
ህመማችንን ተጋርታችሁ ከሃቅ ጋር የቆማችሁ የሌላ ቤተ እምነት ሰዎች ምስጋናችን ይድረስ!
1 161
አሐዱ ባንክ
***
ዓለም ፍትህ የላትም። ምድር ፍታሃዊነት አታውቅም።
ፍትህ ከራስህ ካልወጣ በስተቀር ከሌላው እጅ አትለምን።
አንተን የሚመስል ሌላውን ማይበድል ግዙፍ ተቋም እና ስርዓት ገንባ !!!
1 161
የካቲት 1(ነነዌ ረቡዕ)
#ዘቅዳሴ
መልእክታት -ሮሜ.5፡1-6
-ይሁዳ.1፡20-ፍ.ም
-ግብ ሐዋ.14፡21-24
ምስባክ፦41፡7
ኵሉ ማዕበልከ ወሞገድከ እንተ ላዕሌየ ኃለፈ፤
መዓልተ ይኤዝዝ እግዚአብሔር ሣህሎ ወሌሊተ ይነግር፤
እምኀቤየ ብፅዐተ ሕይወትየ ለእግዚአብሔር።
ወንጌል፦ማቴ.16፡1-5
ቅዳሴ፦ዘእግዚእነ
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለክሙ ማኅበረ ኢየሱስ ኬንያ። ጉቡአን ዘቊስጥንጥንያ። ምስለ ሰባልዮስ አብድ ለመቅዶንዮስ ሐራውያ። ታጽድፍዎ ውሳጤ ግብ ዘዕሙቅ ቀላያ። ለቤተ ክርስቲያን ቅድስት ኢይኪድ ባሕርያ። ትርጉም፦ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እንደ በረሓ ዓሣማ (ዕርያ) እንዳይረግጥ ከሰነፍ ሰባልዮሰሰ ጋር ከርከሮ መቅዶንዮስን ባሕሯ ጥልቅ የኾነ ጒድጓድ ውስጥ ትወረውሩት ዘንድ በቊሰሰጥንጥንያ ተሰብሳቢዎች የጠቢብ የኢየሱስ ማኅበሮች ሰላምተሠ ለእናንተ ይገባል። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የየካቲት 1።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ ጻድቁ በሐይቅ ደሴት የተቀበሩ ቢሆንም ቀድሞ በሚያገለግሉበት በድፍን ምስራቅ ጎጃም ድርቅና ርኃብ ስለሆነ በደብረ ፅሞና ገዳም ይኖሩ የነበሩት አባ መቃርስ ዐፅማቸውን አፍልሰው በማምጣት በደብረ ዲማህ አጠገብ በስማቸው በተሰራው በደብረ ፅሞና ቤተ ክርስቲያን በክብር ሲያሳርፉት ወዲያው ዝናብ ጥሎ ድርቁም ጠፍቷል፡፡ ዐፅማቸውን ተሸክማ ያመጣችው በቅሎም ወልዳለች፡፡ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ሲኖዳ ለማይወልዱ መካኖች እጅግ ልዩ ቃልኪዳን ነው የተሰጣቸው፡፡ መቃብራቸውን
እየዞሩ እምነታቸውን እየተቀቡ ገድላቸውን እየታሹ የማይወልዱ መካኖች የሉም፡፡ ከሩቅም ሆነው በስማቸው ተስለው እምነታቸውን ተቀብተው የሚወልዱ በጣም ብዙዎች ናቸው፣ እንኳንስ ሰው ይቅርና ዐፅማቸውን የተሸከች በቅሎም ወልዳለችና!።
❤ የጻድቁ ሌላኛው በስማቸው የተሰየመውና እጅግ ተአምረኛው ታቦታቸው ዛሬም አቡነ ሲኖዳ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከአ.አ 180 ኪ.ሜ ርቆ ከጣርማ በር አልፎ ሞላሌ ከተማ ውስጥ ይገኛል፡፡ በሰሜን ሸዋ በሚገኘው በዚህ ቤተ ክርስቲያናቸው ውስጥ በዘመናችንም በጣም በርካታ ተአምራት ይደረጋሉ፡፡ ለጻድቁ የተሰጠችውን የስዕለት በግ ጅብ ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ገብቶ ሊበላ ሲል ቀንዱን ነክሶ ደርቆ ሞቶ ሲገኝ በጉ ግን ምንም አልሆነም፡፡ አቃቢቷም እንዲሁ ከትልቁ ተራራ ሥር በትልቅ ቅል ውኃ ቀድተው ሲመለሱ ገመዱ ተበጥሶ ቅሉ ከነውኃው ከትልቁ ገደል ገብቶ ድንጋይ ላይ ቢያርፍም ቅሉ ሳይሆን ድንጋዩ ነው የተሰበረው፡፡ የአካባቢው ነዋሪም "በጉ ጅብ ገደለ፣ ቅሉ ድንጋይ ሰበረ" እያሉ ጻድቁን ያወድሷቸዋል፡፡ ከአባታች ከአቡነ ሲኖዳ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ የካቲት ፩ (1) ቀን።
❤ እንኳን ለኢትዮያዊያኑ ጻድቅ ኤርትራ አገር የሚገኘው ታላቁ ገዳም ደብረ ጽጌ ሰፍኣ ለመሰረቱት ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ ደቀ መዝሙርቶቻቸው (ልጆቻቸውን) ከሰማይ ስንዴና ወርቅ በማዝነብ ውሃውን በመባረክ ወይን አድርገው ይመግባቸው ለነበሩ ለታላቁ አባት ለአቡነ እንድርያስ ዘደብረ ጽጌ ሰፍኣ ለዕረፍት በዓል፣ ለመካኖች ልዩ ቃል ኪዳን ለተሰጣቸው ለታላቁ አባት ለሰማዕቱ ለአቡነ ሲኖዳ ለፍልሠተ ዐፅማቸው በዓል በሰላም አደረሰን።
+ + +
❤ አቡነ እንድርያስ፦ የእናታቸው ስም ቅድስት ዓመተ መንፈስ ቅዱስ የአባታቸው ስም ቅዱስ ዘአማኑኤል ይባላል። የተወለዱትም ትግራ እንደርታ አካባቢ ነው። እናትና አባታቸው ልጅ ስሌላቸው ዘወትር ወደ እግዚአብሔር እየጸልዩ እናታቸውም "አንተ ደስ የሚያሰኝ ልጅ ካልሰጠኸኝ ማኅፀኔን ዝጋ" ይሉ ነበር። የእመቤታችንንም ዝክር በየወሩ ይዘክሩ ነበር። እመቤታችንም አንድ ቀን ተገልጻ "ደስ የሚያሰኝ ልጅ ትወልዳላችሁ የሚወለደውም እኔ በተወለድኩበት ቀን ነው" አለቻቸው። አባታችን ልክ ግንቦት አንድ ቀን ሲወለዱ በእናት በአባታቸው ቤት ብርሃን ወረደ። አርባ ቀን ሲሞላቸው ወደ ቤተ ክርስቲያን ክርስትና ሊያስነሷቸው ወሰዷቸው ሲጠመቁም አባታችን "በአብ ስም አምናለሁ በወልድ ስም አምናለሁ በመንፈስ ቅዱስ አምናለሁ" አሉ። ስመ ክርስትናቸውም መሐረነ እግዚእ ተባሉ።
❤ አቡነ እንድርያስ የስለት ልጅ ስለ ነበሩ 3ዓመት ሲሆናቸው ወደ ቤተ ክርስቲያም አስገባቸው። እርሷቸው ቀን ቀን እያገለገሉ እየተማሩ ሌሊት ሌሊት እየጸለዩ ይሆሩ ነበር እመቤታች በሌሊት ሲጸልዩ ተገልጻ በክንፍ ጋረደቻቸው። ከዚያም ዕድምያቸው ለጋብቻ ሲደርስ እናትና አባታቸው "እናጋባህ" አሏቸው እርሳቸው ግን "አልፈልግም" ብለው በሌሊት ተነስተው ወደ ደብረ ፀሎላ ገብተው በአባ ገብረ ክርስቶስ እጅ በ12ዓመታቸው መነኰሱ። የምንኲስና ስማቸውም አባ እንድርያስ ተባሉ። በዚያ ጊዜ ዲቁንና ክህነት የሚሰጥ ጳስስ በኢትዮጵያ ስላልነበረ አበምኔቱሙ አባ ገብረ ክርስቶስ "ዲቁንናንና ክህነት እንድትቀበል ወደ ግብጽ እንሒድ" አሏቸው። አባታችን "አይሆኑም" ሲሉ ጌታችን በሌሊት ተገልጾ "እንድርያስ ወዳጄ ለምን እቢ አልክ እኔ ምርጬሃለሁና" አላቸው አባታችን ጠዋት ተነስተው "ኑ እሒድ" አሏቸው። ከዚም ወደ ግብጽ ሒደው ዲቁንናንና ክህነት ተቀብለው ወደ ገዳማቸው ተመለሱ።
❤ አንድ ቀን አባታችን ሲቀድሱ ከምድር አንድ ሜትር ከፍ ብለው እርሳቸው የቆሙበት ቦታ ውሃ አፈለቀ። ይህን ያዩ መነኰሳት ለአበምኔቱ ለአባ ገብረ ክርስቶስ ነገራቸው አበምኔቱ መጥተው የፈለቀው ውሃ አይተው እግዚአብሔርን አመሰገኑ አቡነ እንድርያስ አስጠርተው "አንተ ከዛሬ ጀምሮ ከእኛ ጋር ለሥራ መውጣት የለብህ ስእኛ ጸልይን እንጂ" አሏቸው እርሳቸው አይሆኑም ብለው ከእዛ ገዳም ወጥው "ወደ ኢየሩሳሌም ሔጄ ጌታ የተጠመቀበትን ማየ ዮርዳኖስ አያለው" ብለው ከኢትዮጵያ ተነስተው ወደ ኤርትራ አዲ ሞገስ ወደሚባል አካባቢ ሲደርሱ አንድ ታምነ እግዚእ የሚባል ገበሬ "አባቴ የንስሐ አባት ሁኑኝ" አላቸው። አባታችን "በአገራችሁ ካህን የለም እንዴ?" አሉት እርሱም "አዋ የለም" አላቸው አባታችንም ሕዝቡ አስተምረው አጥምቀው ጉዞ ወደ ኢየሩሳሌም ጀመሩ። ደብረ ጽጌ ሰፍኣ ሲደርሱ ጌታ ተገልጾ,"ይህን ቦታ ዳግማዊ ኢየሩሳሌም አድርጌልሀለው ውሃውም የዮርዳኖስ ውሃ ይሆንልሃል እና ከዚህ አትህድ" አላቸው።
❤ አባታችንን አቡነ እንድርያስ ተከትለው ወደዚህ ገዳም ዘጠኝ መቶ ዘጠና ዘጠኝ ተማሪዎች ወደ እሳቸው መጡ እነዚህ ልጆቻቸውን አመነኰሷቸው። ለእነዚህ ልጆቻቸው ቀድሞ በመንገድ ላይ አስተምረው ካጠመቁት ገበሬው ከታምነ በእግዚእ እንደ ሰው እየተላላከ እህል የፈጭልላቸው የሚያገለግላቸው ገብረ ኄር የሚባል አህያ ነበራቸው ሰይጣንም ቀንቶ ይህንን አህያ ብገለው ልጆቹ በርሃብ ምክንያት ይበተናሉ ብሎ አስቦ በአንበሳ አድሮ ገደለው። አንበሳው ደግሞ አቡነ እንድርያስ በአንድ መርገም ቃል ገደሉት። ልጆቻቸውም ምግብ ሲያጡ ጥለው ሊሆዱ ሲሉ አባታችን ትዕግስት ይኑራችሁ አላቸው። እነርሱም እንቢ ብለው ወደ ታምነ በእግዚእ ሆዱ። ታምነ በእግዚእ ባለቤቱን "ምግብ አዘጋጂላቸው" አላት እሷም "አቡነ እንድርያስ ሳይመጦ አላዘጋጅ" አለችው እነርሱም እቢ ስላለቻቸው ልጆቹም "እኛ የአባታችን ምክር ስልሰማን ነው የከለከለችን" ብለው ወደ ገዳማቸው ተመለሱ።
❤ አቡነ እድርያስም ልጆቹ ከተመለሱ በኋላ ውሃ የሞሉ እንስራዎች ነበሩና ቢባርኩት የወይን ጠጅ ሆነ። እንደ ገናም "እግዚአብሔር ዘላለም" ብለው ሲጸልዩ ከሰማይ አርያም ስንዴ ዘነበላቸው ያንን ለ14 ዓመታት ተመገብ ይህ ሲያልቅ ደግሞ ወርቅ አዘነቡላቸው ወርቁ በእህል እየለወጡ ተመገበሩ። አባታችን ልጆቻቸውን "እኔ ወደ እግዚአብሔር የምሄድበት ቀን ደርሷል" አሏቸው። ልጆቹም "አንተ ከሆድክ ማን ከሰማይ ስንዴና ወርቅ እያዘነበ ውሃው ወይን እያደረገ ይመግበናል" አሏቸው እሷቸው "እኔ ከሞትኩ በኋላ እናተም ከዐሥር ቀን በኋላ ወደ ትመጣላች እኔ ቦታ ላዘጋጅላችሁ ነው የምሆደው" ብለዋቸው በ126 ዓመታቸው የካቲት 1 ቀን ዐርፈዋል። ልጆቻቸውም እንዳሏቸው በአንድ ቀን በአረማውናን ሰማዕትነት በመቀበል የካቲት 10 ቀን ዐርፈዋል። ከአባታች ከአቡነ እንድርያስ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ ከኤርትራ ደብረ ጽጌ ሰፍኣ ገዳም የተገኘ ማስታወሻ።
+ + +
❤ አቡነ ሲኖዳ፦ ሲኖዳ ማለት "ታማኝ" ማለት ነው፡፡ ትውልድ አገራቸው ጎጃም ሲሆኑ የሸዋ ባላባት ልጅ ናቸው፡፡ በጎጃም ደብረ ዲማህ አጠገብ ደብረ ፅሞና በተባለው ቦታ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ያመልኩት የነበረውን ትልቅ ዘንዶ አቡነ ሲኖዳ በመስቀል ባርከው ከሁለት ሰንጥቀውታል፡፡ ሰዎቹንም አስተምረው አሳምነው አጥምቀው የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን ሠርተውላቸዋል፡፡ ጻድቁ የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስ ዓይነት ገድል አላቸው፡፡ ለዘንዶ ምግብ እንዲትሆን ግብር ሆና የተሰጠችውን ሴት ልጅ ከጫካ አግኝተው ዘንዶውን በመስቀላቸው አማትበው ገድለው ልጅቷን አድነዋታል፡፡
❤ በዘመናቸው ነግሦ የነበረው "ሕዝበ ናኝ" የተባለው ንጉሥ በሰዎች ወሬ "ንግሥናዬ ለሌላ ይሰጣል ትላለህሳ" በማለት ጻድቁን እጅና እግራቸውን አስሮ ካሠቃያቸው በኋላ እጃቸውን አስቆረጣቸው፡፡ ነገር ግን ለአቡነ ሲኖዳ እመ ብርሃን የብርሃን እጅ ተከለችላቸው፡፡ በጌቴሴማኒ ያለችው ሉቃስ የሳላትና ስርጉት የተባለችው የእመቤታችን ሥዕል በየጊዜው እየተገለጠች ታነጋግራቸው ነበር፡፡ ንጉሡ በስደትና በግዞት ብዙ እያሠቃያቸው ሳለ መልአክ መጥቶ ዕለተ ዕረፍታቸውን ነግሯቸው እሳቸውም ደቀ መዛሙርቶቻቸውን ጠርተው ከተሰናበቷቸው በኋላ ነው ንጉሡ በኅዳር 17 ቀን አንገታቸውን ያሰየፋቸው፡፡ ከአንገታቸው ውኃ፣ ደምና ወተት ፈሷል፡፡
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ የባረከ የየካቲት ወር መዓልቱ ዐሥራ አንድ ሰዓት ነው ከእግዲህም ይጨምራል።
❤ የካቲት ፩ (1) ቀን።
❤ እንኳን በታላቁ ቴዎዶስዮስ ዘመነ መግሥት በቊስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት ስለሆነው የክብር ባለቤትን የሆነ መንፈስ ቅዱስን በከፋች ኀሳቡ ፍጡር ነው ስለ ብሎ ስለ ካደው ስለ መቅዶንዮስ፣ አንድ ገጽ ስለሚሉ ስለ ሰባልዮሳውያንና ወልድ ከብቻው ሥጋ በቀር ነባቢት ለባዊት ነፍስን አልነሣም መለኮቱ በነፍስና በልቡና ፈንታ ሆነው ስለሚሉ ስለ አቡሊናርዮሳውያን መቶ ኃምሳ ኤጲስቆጶሳት በቊስጥንጥንያ ከተማ 381ዓ.ም ተሰብስበው ሦስቱንም መናፍቃን ላወገዙበት ቅድስት ተዋሕዶ ሃይማኖትን ላጸኑበትና በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ መንግሥት በሰማዕትነት ለሞተ ከሀዲ አርዮስም ላወገዘ ለሰማዕታትም ፍጻሜ ለሆነ ለሊቀ ጳጳስ ለቅዱስ ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን ለከበረችበት በዓል በሰላም አደረሰን። ከእነዚህ ቅዱሳን እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ ሰላም ለ፻ወ፶ እለ በቊስጥንጥንያ ኤጲስ ቆጶሳት እለ በሃይማኖት ቅደስት"። ትርጉም፦በቀናች ሃይማኖት የጸኑ ለኾኑ በቊስጥንጠሰንያ ለሰበሰቡ ለመቶ ኃምሳው ሊቃውንት ሰላምታ ይገባል።
+ + +
❤ የከበሩ የመቶ ሃምሳ ኤጲስቆጶሳት ስብሰባ በቊስጥንጥንያ ከተማ በታላቁ ቴዎዶስዮስ ዘመነ መንግሥት መደረግ፦ ስብባቸውም የሆነው በቊስጥንጥን አገር ላይ ሊቀ ጳጳሳት ስለ ሆነው የክብር ባለቤት የሆነ መንፈስ ቅዱስን በከፋች ኀሳቡ ፍጡር ነው ብሎ ስለ ካደው ስለ መቅዶንዮስ ሁለተኛም አንድ ገጽ ስለሚሉ ስለ ሰባልዮሳውያን ሦስተኛም ወልድ ከብቻው ሥጋ በቀር ነባቢት ለባዊት ነፍስን አልነሣም መለኮቱ በነፍስና በልቡና ፈንታ ሆነው ስለሚሉ ስለ አቡሊናርዮሳውያ ነው
❤ የእሊህ ከሀድያንም ስሕተት ግልጽ በሆነ ጊዜ አሰባስቦ የአንድነት ጉባኤ ያደርግላቸው ዘንድ ንጉሥ ቴዎዶስዮስን ለመኑት እርሱም ቃላቸውን ተቀብሎ ወደ ሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ኢየሩሳሌምም ሊቀ ጳጳሳትም መልክትን ላከ ምሁራን የሆኑ ኤጲስቆጶሶቻቸውንም ይዘው እንዲመጡ አዘዛቸው እሊህም አባቶች በቊስጥንጥንያ ከተማ ተሰብሰቡ የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ግን አልመጣም ምሁራን የሆኑ ሰዎችን ላከ እንጂ ከእርቸውም ጋር በእጁ የጻፋትን ደብዳቤ ላከ።
❤ የጉባኤውም ሊቀ መንበር የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጢሞቴዎስ ነው መቅዶንዮስንም ጠርቶ የረከሰች ሃይማኖቱን ይናገር ዘንድ አዘዘው ያ ከሀዲም "እንደ ፍጥረቶች ሁሉ መንፈስ ቅዱስ የተፈጠረ ነው" አለ። ጢሞቴዎስም መልሶ "መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ሕይወቱ እንደሆነ አታውቅምን የእግዚአብሔርን ሕይወት እንዴት ፍጡር ታደርገዋለህ አሁንም ከዚች ከረከሰች ሃይማኖትህ ተመለስ ወደ ዘላለማዊ እሳት ገሃገም ከመግባትህ በፊት ንስሓ ግባ" አለው። እርሱ ግን ሰምቶ አልተመለሰም እነርሱም አወገዙት ከሹመቱም ሻሩት ከቤተ ክርስቲያንም አሳደዱት።
❤ ከዚህም በኋላ ሰባልዮሳውያን ጠርቶ "እናንተስ ስለ ሃይማኖታችሁ ምን ትላላችሁ ተናገሩ" አላቸው። እነርሱም "አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ ገጽ አንድ ህላዌ ነው በምንም በምን ሦስት አይሆንም" አሉ። አባ ጢሞቴዎስም መልሶ እንዲህ አላቸው "በዮርዳዮስ ውስጥ ወልድ ቁሞ ሳለ በፀዓዳ ርግብ አምሳል መንፈስ ቅዱስ ወርዶ በራሱ ላይ የተቀመጠ አብም ከደመና ውስጥ ሁኖ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት ብሎ አሰምቶ ተናገረ ያለው የወንጌል ቃል ተሻረን? እናንተ እንደምትሉት ከሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የተጠመቃችሁት የክርስትናችሁ ጥምቀት ተሽሮአል አሁንም ክህደታችሁን ተዉ ብትመለሱም ይሻላችኋል። አርዮስም አስቀድሞ ወልድን ካደው ይህ መቅዶንዮስም መንፈስ ቅዱስን ካደው እናንተም የእነርሱ ተሳታፊዎች ሆናችሁ"። እነርሱም ሰምተው አልተመለሱም የአንድነት ጉባኤም አውግዞ ከምእመናን አድንነት ለያቸው።
❤ ከዚህም በኋላ ደግሞ ወልድ ነባቢት ለባዊት የሆነች ነፍስን አልነሳም ሥጋን ብቻ እንጂ የሚለውን አቡሊናርዮስን ትምህርት አወገዙ። እሊህ መቶ ኃምሳ የሆኑ ኤጲስ ቆጶሳት አባቶቻችንም በጸሎተ ሃይማኖት ላይ "ጌታ አዳኝ በሚሆን ከአብ በሠረፀ በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን እንሰግድለት እናመሰግነውም ዘንድ ከአብና ከወልድ ጋራ በነቢያት አድሮ የተናገረ" የሚለውን ጨመሩ።
❤ ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም እናምናለን። ኃጢአትን ለማስተስረይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን። የሙታንም መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ለዘላለሙ ተስፋ እናደርጋለን። ሃይማኖታቸው የቀና ሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት አባቶቻችን የተናገሩት ለመንግሥቱ ፍጻሜ የለውም እስከሚል ነው። እሊህ መቶ ኃምሳው አባቶች የሰበሰቡት ስለ መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ ስለርሱ የእርሱን ነገር አብራሩ። ለእርሱም ምስጋና ይሁን የአባቶቻችንም በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ሣህሉ ለእግዚአብሔር መልአ ምድረ። ወበቃለ እግዚአብሔር ፀንዐ ሰማያት። ወእምእስትንፋሰ አፋሁ ኵሉ ኃይሎሙ"። መዝ 32፥5-6 ወይም መዝ 72፥7-8። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 15፥17-26 ወይም ማቴ 12፥31-38።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ
የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 4፥1-6፣ 1ኛ ጴጥ 1፥10-13 እና የሐዋ ሥራ 8፥18-25። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 11፥29-33። የሚቀደሰው ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም የጾምና፣ የጸሎት የምሕላ፣ በቊስጥንጥንያ ከተማ የተሰበሰቡ የኃምሳ ኤጲስቆጶሳት መታሰቢያ በዓልና የአቡነ እንድርያስ የዕረፍት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።
https://t.me/Eotcw
