ሰዋስው ☘☘☘☘
Open in Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
Show more1 161
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1 161
#ሰበር_ዜና #አሁን_በወለቴ_ቅዱስ_ዮሐንስ_ቤተ_ክርስቲያን_በልዩ_ሀይል_የተገደሉት_ክርስቲያኖች።
እባካችሁ ኦርቶዶክሳውያን ሸር እያደረጋችሁ እየደረሰብን ያለውን ግፍና መከራ ለአለም ይይልን።
1 161
መረጃ!
አየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ካቴድራል ደወሏን አሰምታለች።
ሕገ ወጡ ቡድን በመንግሥት የጸጥታ ኃይል ታጅቦ እየመጣ ነው መባሉን ተከትሎ ነው ቤተ ክርስቲያኗ ጥሪዋን ያሰማችው።
ይህንን ጥሪ በመስማት በርካታ ኦርቶዶክሳውያን ወደ ካቴድራሉ እየጎረፉ ይገኛሉ።
በሕገ ወጡ ሹመት ከተሳተፉት ሰዎች መካከል የቀድሞ የካቴድራሏ አስተዳዳሪ ይገኙበታል።
1 161
የጾመ ነነዌ የሦሶተኛ ቀን የምሕላ ጸሎት በሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም 01/06/2015 ዓ.ም
#እግዚአብሔር_ፀሎት_ልመናችንን_ይቀበልልን 🙏🙏🙏
የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም ሰንበት ት/ቤት
1 161
ሰላም ኦርቶዶክሳውያን ወንድማችን #ሚኪያስ_ተሾመ ዛሬ 01/06/2015 ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን ተለዋጭ ቀጠሮ ለ05/06/2015 ፍርድ ቤቱ ሰቶታል ያው ቀኑ እሁድ ስለሚውል ሰኞ በ6 ይቀርባል እንዲሁም #ማህበረ_ቅዱሳን ጠበቃ አቁሞለታል ።
#ቤተክርስቲያን_አንዲት_ናት
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሰላም ለጳውሊ በውሳጤ ገዳም ዘተጸምደ። እንዘ ኢይሬኢ እምሰብእ መነሃ አሐደ። ፃመወ ብዙኀ ወተጋደለ ፈድፋደ። ድኅረ ሞቱሂ ከመ በሕይወቱ ለመደ። ለእግዚአብሔር ተረክበ ከዊኖ ስጉደ"። ትርጉም፦ ከሰው ወገን ማንንም ማን አንድ ሳያይ በገዳም ውስጥ የተጠመደ ለኾነ ለጳውሊ ሰላምታ ይገባል፤ በብዙ ወገን ደክሞ በብዙ ወገንም ተጋደለ፤ ከሞቱም በኋላ በሕይወቱ እንደለመደው ለእግዚአብሔር የሰገደ ኾኖ ተገኘ። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የየካቲት 2።
https://t.me/Eotcw
1 161
ከዚህም በኋላ አባ ሉክያኖስ ዐረፈ።
❤ የኬልቄዶንን ጉባኤ በሰበሰበ በከሀዲው መርቅያኖስም ዘመን ወደ አገሮችም ሁሉ መልእክተኞችን ላከ ከእርሳቸውም ጋር አንዱን ክርስቶስን ወደ ሁለት ባሕርይ የምትከፍል የረከሰች የሃይማኖቱ ደብዳቤ አለች። ከንጉሥ መልእክተኞች ሦስቱ ወደ ደብረ ዝጋግ በደረሱ ጊዜ ያንን ደብዳቤ ለአባ ለንጊኖስ ሰጡት በዚህ "ጽሑፍ እንድታምኑ በውስጡም እንድትፈርሙ ንጉሥ መርቅያኖስ አዝዞአል" አሉት። አባ ለንጊኖስም "ከቅዱሳን አባቶቼ ጋር ሳልማከር እኔ ምንም ምን መሥራት አልችልም እንድንማከርም እናንተም ከእኔ ጋር ኑ" አላቸውና የቅዱሳን በድኖች ወደ አሉበት ዋሻ ውስጥ አስገባቸውና "የከበራችሁ አባቶቼ ሆይ እናንተ ዐርፈን ተኝተናል አትበሉ እነሆ አንዱን ክርስቶስን ሁለት ባሕርይ የሚያደርግ በውስጡ የተጻፈበትን ይህን ደብዳቤ አምጥተዋልና በቃሉ አምን ዘንድ በውስጡም እፈርም ዘንድ ታዙኛላችሁን ወይም አታዙኝም የምሠራውንም ካልነገራችሁኝ ሕያው እግዚአብሔር ዐፅማቻችሁን ከዚህ ቦታ አወጣለሁ" አላቸው።
❤ ያን ጊዜ ሰዎች ሁሉም እየሰሙ ከአስከሬናቸው "የአባቶቻችንን የሐዋርያትንና የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንቱን የቀናች ሃይማኖትን አትተው ይህንንም የረከሰ ደብዳቤ አትከተል ከአስከሬናችን ቦታ አርቀው እንጂ" የሚል ቃል ወጣ የንጉሥ መልክተኞችም ይህን ነገር ሰምተው እጅግ አደነቁ በላያቸውም ታላቅ ፍርሀት አደረባቸው ወደ ንጉሡም አልተመለሱም ራሳቸውን ተላጭተው መነኰሱ እንጂ እስከ ዐረፉም ድረስ ብዙ ዘመን እየተጋደሉ ኖሩ። የከበረ አባ ለንጊዮስ ያማረ ተጋድሎውን ጨርሶ እግዚአብሔርንም አገልግሎ የካቲት 2 ቀን በሰላም ዐረፈ የሕይወት አክሊልንም ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ለጊዮኖስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የካቲት 2 ስንክሳር።
+ + +
❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ለስሒት መኑ ይሌብዋ። እምኅቡዓትየ አንጽሐኒ። ወእምነኪር መሐኮ ለገብርከ። መዝ 18፥12። የሚበበው ወንጌል ማቴ 5፥32-33።
+ + +
❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ኵሉ ማዕበልከ ወሞገድከ እንተ ላዕሌየ ኃለፈ። ዓልተ ይኤዝዝ እግዚአብሔር ሣህሎ ወሌሊተ ይነግር። እምኀቤየ ብፅዐተ ሕይወትየ ለእግዚአብሔር"። መዝ 41፥7-8። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 5፥1-6፣ ይሁ 1፥20-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 14፥21-24። የሚበበው ወንጌል ማቴ 16፥1-5። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም የጾም፣ የጸሎት፣ የምሕላ ጊዜና መልካም የአቡነ ጳውሊ የዕረፍት በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ ከዚህም በኋላ አባ እንጦኒ አባ ጳውሊን "አባቴ ሆይ ይህ አስኬማ በምድር ላይ ይበዛ እንደሆነ ወይም አለመብዛቱን ትነግረኝ ዘንድ እሻለሁ" አለው። የከበረ ጳውሊም ወደ ሰማይ ተመለከተና ፈገግ አለ። ከዚህም በኋላ አዘነ ጩኾም አለቀሰ አባ እንጦንዮስም "ፈገግ ስትል በአየውህ ጊዜ ደስ አለኝ በአዘንክም ጊዜ አዘንኩ" አለው። የከበረ ጳውሊም እንዲህ ብሎ መለሰለት "እሊህ ተራሮችና በረሐዎች እግዚአብሔር ከሁሉ አገሮች መርጦ ለሚሰበስባቸው ንጹሐን ርግቦች ማደሪያዎች ይሆናሉ"።
❤ "ዳግመኛም ይህ ስም ያልፋል ስማቸውም መነኰሳት ይባላሉ እነርሱም ብዙ ዘመናት ደስ ይላቸዋል እግዚአብሔርም ከቁጣው ቀን አስቀድሞ ከዚያ ያፈልሳቸዋል። ከእነርሱም በኋላ ሰምተው ለመምህሮቻቸው የማይታዘዙ ትውልድ ይነሣሉ ስለ ነፍሳቸውም ድኅነት በቀንና በሌሊት የማይተጉና የማይጸልዩ ናቸው። ያን ጊዜ እግዚአብሔር ተቆጥቶ ይፈርዳል የማያስተውሉ ሕግ የሌላቸው አረማውያንም ተነሥተው ገዳማቱንና አድባራቱን ያጠፋሉ ብዙ ዘመናትም ምድረ በዳ ይሆናሉ የቅዱሳን መታሰቢያቸው አይጠፋም እግዚአብሔርም በሌሎች ሰዎች ልቡና ይቅርታውን ያሳድርባቸዋል እነርሱም ወደ ገዳማቱና ወደ አድባራቱ በመሔድ በውስጣቸው ዳግመኛ ይኖራሉ ሰይጣንም ወደ ገዳማት ሔዶ በመካከላቸው ጸብን ይዘራል እነርሱም የእግዚአብሔርን ፍቅር ገንዘብ በማድረግ ጨክነው አልታገሡባትምና ምንኵስናቸውን አስኬማቸውን ትተው ወደ ዓለም ይወርዳሉ "በትዕግሥታችሁ ነፍሳችሁን ገንዘብ ታደርጓታላችሁ" የሚለውን ጽሑፍ አላስተዋሉምና"።
❤ እንጦንዮስም "የከበርክ አባቴ ጳውሊ ሆይ ፊትህን አይ ዘንድ የታደልኩባት ሰዓት የተባረከች ናት" አለ። የከበረ አባ ጳውሊም "አሁን ወደ ማደሪያህ ሒድ ቈስጠንጢኖስ ለሊቀ ጳጳሳት አትናቴዎስ የሰጠውን ልብስ እርሱም አንተን ያለበሳትን ያቺን ከአንተ ጋር ይዘሃት ና ሥጋዬን በርሷ ትገንዝ ዘንድ" ብሎ ተናገረው የተሠወረውን በማወቁ እጅግ አደነቀ የተነበየለትንም ትንቢት ሁሉ አመነ። ዳግመኛም እንዲህ አለው "በሰው ሁሉ ላይ እንደተሠራ ከዓለም የምወጣበት ጊዜዬ ቀርቧልና ፈጥነህ ሒድና ተመለስ እርሱም ከአባ ጳውሊ ዘንድ ወጥቶ ወደ በዓቱ እስኪደርስ የሁለት ቀን ጎዳና ተጓዘ ያቺንም ልብስ ይዞ ተመለሰ በመንገድም እየተጓዘ ሳለ በአየር ውስጥ አባ ቡላን የመላእክትንም ማኅበር አየ "ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን" ይሉ ነበር።
❤ ሁለተኛም "እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ የመረጠህ ሰላምታ ፍቅር አንድነት ይገባሃል የእግዚአብሔር ሰው አንተ ጳውሊ የተመሰገንክ ነህ እንግዲህስ በሰማያዊ መንግሥት ከመላእክት ጋር ደስ ይበልህ የጨለማውን ዓለም ትተህ የብርሃን ሀገርን አግኝተሃልና ወደ ዘላለማዊ ተድላ ደስታ ይወስዱሃልና የእግዚአብሔር ማደሪያ የሆንክ አንተ ገዳማዊ ጳውሎስ በትውልድህ የከበርክና የተመሰገንክ ነህ" እንዲህ እያሉ ተሠወሩ።
❤ የከበረ እንጦኒም "ይህች ወደ ሰማይ የሚያሳርጓት የአባቴ የጳውሊ ነፍስ ናት" አለ ወደ በዓቱም በገባ ጊዜ እንደ ሰገደ ሁኖ እጆቹም በመስቀል ምልክት ተዘርግተው አገኘው አንሥቶም ሸፈነው "አባቴ ሆይ በሰማያዊ ማደሪያህ ሁነህ አስበኝ" ብሎ በላዩ አለቀሰ።
❤ ከዚህም በኋላ ተነሥቶ በዚያች ልብስ ሥጋውን ገነዘና በላዩ የቤተ ክርስቲያንን የጸሎት ሥርዓት ፈጸመ አደረሰም ከዚህም ቀጥሎ ከእርሱ ጋር የተማከርኩት ነገር የለም ምን ላድርግ ብሎ አሰበ በዚያንም ጊዜ አንበሶች መጡ እጅ ነሡትም ቀድሞ እንደሚያውቁትም ዘንበል ብለው የእግሩን ትቢያ ላሱ መቃብሩን በየት ቦታ እንቆፍርለት እንደሚሉ አመለከቱት እርሱም ምልክታቸውን አውቆ በቁመቱ ልክ ለክቶ ሰጣቸው አንዱ በራስጌ አንዱ በግርጌ ሁነው ቆፈሩ በአደረሱም ጊዜ "በቃችሁ" ብሎ አመለከታቸው እሊህ አንበሶችም ወጥተው ሰገዱለት። እርሱም ባረካቸውና ወደ ቦታቸው ሔዱ የከበረ እንጦኒ ወደ መቃብር አስገብቶ ዘጋው። ከሰኔል ቅጠልም የተሠራች ዐጽፉን ወሰደ የአባቱን ገንዘብ እንደሚወርስ ልጅ ነውና ወደ እስክንድርያም ሔደ፡፡ ወደ ሊቀ ጳጳሳት አትናቴዎስም ገብቶ ከከበረ አባ ጳውሊ የሆነውን ሁሉ ነገረውና ያቺን ከሰኔል የተሠራች ዐጽፍ ሰጠው።
❤ ሊቀ ጳጳሳት አትናቴዎስም የከበረ ጳውሊን ዜና በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደስ አለው ያቺንም ዐጽፍ ተቀብሎ በእርሱ ዘንድ አኖራት በየዓመቱም በከበረ በልደት በዓል በጥምቀትም በዓል በመድኃኒታችን ክርስቶስ ትንሣኤ በዓልም ሦስት ጊዜ ይለብሳት ነበር።
❤ ጌታችንም የቅዱስ ጳውሊን የልብሱን ክብር ሊገልጥ ወደደ በዚያችም ወቅት አንድ ወጣት ልጅ ሞተ አባ አትናቴዎስም ያቺን ልብስ በሞተው ላይ አኖራት ወዲያውኑ ተነሣ ይህንንም ያየ ኤጲስቆጶስ አባ ኤስድሮስ ምስክር ሆነ ይችም ተአምር በአገሮች ሁሉ ተሰማች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረ በአባ ጳውሊ ጸሎት ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ያደረገው ተአምር፦ ጌታችን ወደ አዘዘው ሊአስተምር በወጣ ጊዜ ከመንገድ ጥቂት ፈቀቅ አለ ድንገትም የሞተ ጐልማሳ አየ መልኩ እጅግ የሚያምር ነበር ሐዋርያውም "አቤቱ ይህን ጥፋት አይ ዘንድ ወደዚህ አመጣኸኝን ነገር ግን ፈቃድህ ይሁን" አለ።
❤ ከዚህም በኋላ ስለሞተው ሰው ጸለየ ያን ጊዜ ታላቅ ከይሲ ከደንጊያዎች ውስጥ ወጥቶ በጅራቱ ምድሩን እየደበደበ መጣ "የክርስቶስ ሐዋርያ ሆይ እኔ ካንተ ጋር ምን አለኝ ሥራዬን ልትዘልፍ መጣህን" ብሎ በታላቅ ድምጽ ጮኸ ሐዋርያውም "አዎን ሥራህን ተናገር" አለው። ከሲውም እንዲህ አለ "በዚህ ቦታ አንጻር መልከ መልካም ሴት ነበረች እኔ የምወዳት ናት ይህም ጐልማሳ ሲሰማት አየሁት በሰንበት ቀንም ከርሷ ጋር አደረ ስለዚህም ነክሼ በመርዝ ገደልኩት" ሐዋርያውም "መርዝህን ከሱ ትወስድ ዘንድ በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም አዝዤሃለሁ" አለው። ሒዶም ከዚህ ከሞተው መርዙን መጠጠና ወሰደ ወዲያውኑ ተነፍቶ አበጠ ተሠንጥቆም ሞተ የሞተውም ሰው ድኖ ተነሣ። ስለዚች ምልክትም ብዙዎች በክብር ባለቤት ጌታችን አመኑ እርሱም ሃይማኖትን አስተምሮ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያው በአባታችን በቅዱስ ቶማስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ የደብረ ዝጋግ ገዳም አበ ምኔት አባ ለንጊኖስ፦ ይህም ቅዱስ ከኪልቅያ አገር ነው በዚያም መነኰሰ መምህሩም ክርስቶስን የሚወድ ሰው ከሚሰጠውም ክብር የሚሸሽ ነበር። በዚያንም ጊዜ የገዳማቸው አበ ምኔት ዐረፈ ይህንንም ስሙ ሉክያኖስ የተባለ አረጋዊ መምህሩን አበ ምኔትነት ሊሾሙት መነኰሳቱ ወደዱ እርሱም ደቀ መዝሙሩን ለንጊኖስን ይዞ በጭልታ ከኪልቅያ ወጥቶ ወደ ሶርያ አገር ሔደ በአንዲት ቤተ ክርስቲያንም ግቢ በአንድነት ተቀመጡ በእጆቻቸውም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶችን ያደርግ ዘንድ ከንቱ ውዳሴና ክብር ሆነባቸው።
❤ አባ ለንጊኖስም በመምህሩ ምክር ወጥቶ ወደ ግብጽ አገር ሔደ ወደ ደብረ ዝጋግ ገዳምም በገባ ጊዜ በደስታ ተቀበሉትና ከእርሳቸው ጋራ ኖረ ከዚያም በኋላ አበ ምኔቱ ዐረፈ ተጋድሎውን ትሩፋቱንና ደግነቱን ስለ አወቁ በደብረ ዝጋግ ገዳም ላይ አባ ለንጊኖስን አበ ምኔት አድርገው ሾሙት። ከጥቂትም ወራት በኋላ መምህሩ አባ ሉክያኖስ መጣ የመርከቦችን ጣሪያዎች እየሠራ በእጆቻቸውም ከሚሠሩት እየተመገቡ በአንድ ልብ በመሆንም በአንድነት ኖሩ እግዚአብሔርም በእጆቻቸው ብዙዎች የሆነ ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ የካቲት ፪ (2) ቀን።
❤ እንኳን ለመላእክት ወገን ለሆነ ለገዳማውያን ባሕታውያን (መናንያን) ሁሉ አለቃ ለሆነ ለከበረ ለታላቁ አባት ለአባ ጳውሊ ለዕረፍት በዓል፣ ለከበረ ለሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ አንድ ከይስ ነድፎ የገደለው ሰው ተምራትን በማድረግ ከሞት ላስነሳበትና ከይሲውን በመግደል ብዙዎችን አስተምሮ ላጠመቀበትና ከእስክንድርያ ውጭ ለደብረ ዝጋግ ገዳም አበ ምኔት የቅዱሳን ዐፅም ቃል በቃል በማጋገር የሃይማኖት ነገር ለተረዳ ለከበረ አባት ለአባ ለንጊኖስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። ከእነዚህ ቅዱሳን እግዚአብሔር ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ "ሰላም ለአባቱ ጳውሊ ዘንጉሥ ወዓሊ፤ ገዳማዊ ዘበአማን ኅሩይ፤ ርእሶሙ ለፈላስያን እለ በገዳም"። ትርጉም፦ በበረሓ ላሉ ባሕታውያን (መናንያን) አለቃቸው፤ በእውነት የተመረጠ ገዳማዊ፤ የንጉሥ ሎሌ ለኾነ ለአባ ጳውሊ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።
+ + +
❤ ርዕሰ ገዳማውያን ባሕታውያን(መናንያን) አቡነ ጳውሊ፦ ይህም ቅዱስ ከእስክንድርያ አገር ጴጥሮስ የሚባል ወንድም አለው አባታቸውም የገንዘቡ ብዛት ሊቈጠር የማይቻል እጅግ ባለጸጋ ነበር በዐረፈም ጊዜ የኀዘናቸው ቀን ሲፈጸም ርስቱንና ገንዘቡን ሊካፈሉ ጀመሩ ጴጥሮስም ታላቁን ክፍል ወደራሱ በመውሰድ የሚያንሰውን ለጳውሊ የሚሰጠው ሆነ። ስለዚህም ጳውሊ አዘነና "ከአባቴ ርስት በትክክል ለምን አትሰጠኝም?" አለው እርሱም "አንተ ወጣት ስለሆንክ ታባክነዋለህ እስከ ምታድግ እኔ እጠብቅልሃለሁ" ብሎ መለሰለት።
❤ ስለዚህም ጳውሊ ተቆጣና እርስ በርሳቸው ተጣሉ ይፈርድላቸውም ዘንድ ወደ ዳኛ ሔዱ እነርሱም ወደ ዳኛ ሲሔዱ ሰዎች ተሸክመውት ወደ ሚቀብሩበት ሲወስዱት ብዙዎችም የተከተሉትን የሞተ ሰውን አገኙ ጳውሊም ከተከተሉት አንዱን ሰው "ዛሬ የሞተው ማን?" ነው ብሎ ጠየቀው። ያም ሰው እንዲህ ብሎ መለሰለት "ልጄ ሆይ ዕወቅ አስተውል ይህ የሞተ ሰው በወርቅ በብር እጅግ ባለጸጋ የሆነ ሁል ጊዜ ደስ የሚለው ነበር አሁንም እነሆ ይህን ሁሉ ትቶ ራቁቱን ወደ መቃብር ወደማይመለስበት መንገድ ይሔዳል በኃጢአት ማዕበል ውስጥ እያለ ሙቷልና። አሁንም ልጄ ሆይ ስለ ነፍሳችን ድኅነት ልንታገል ይገባናል እኛ መቼ እንደምንሞት አናውቅምና ነገር ግን በዚህ ዓለም ውስጥ ገንዘብ ኑሮት ሥልጣንም ኑሮት ሳለ ይህን ሁሉ የተወ የተመሰገነ ነው እርሱ የቅዱሳን ሀገር በሆነች በኢየሩሳሌም ሰማያዊት ታላቅ ክብርን ይቀበላልና"።
❤ የከበረ ጳውሊም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ከልቡ አዘነ እንዲህም አለ "የዚህ የኃላፊው ዓለም ገንዘብ ምኔ ነው ምን ይጠቅመኛል ከጥቂት ቀኖች በኋላ ትቼው ራቁቴን የምሔድ አይደለሁምን" አለ። ከዚህም በኋላ ወደ ወንድሙ ተመልሶ "ወንድሜ ሆይ ወደ ቤታችን እንመለስ ከእንግዲህ ስለ ገንዘብ ምንም ምን ከአንተ ጋር አልነጋገርም" አለው።
❤ ከዚህም በኋላ ከወንድሙ ሸሽቶ ከሀገሩ ወጣ ከመቃብር ቤት ውስጥም ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት መንገዱን ይመራው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እየጸለየና እየማለደ ኖረ። ወንድሙ ጴጥሮስም በሀገር ውስጥ እየዞረ ሲፈልገው ሰነበተ ግን አላገኘውም ታላቅ ኃዘንንም አዘነ። የተመሰገነ ጳውሊ ግን ሦስት ቀኖች ያህል በዚያች መቃብር ቤት ሲኖር መብልና መጠጥን አላሰበም ፍርሀትና ድንጋፄም አልደረሰበትም አምላካዊ ኃይል ትጠብቀው ነበርና።
❤ በአራተኛዪቱም ዕለት እግዚአብሔር ወደርሱ መልአኩን ላከ ከዚያም ነጥቆ ወሰደው በምሥራቅ በኵል በምትገኝ በረሀ ውስጥ አኖረው በዚያም የውኃ ምንጭ አለ መልአኩም ሰላምታ ሰጥቶት ወደ ሰማይ ዐረገ የከበረ ጳውሊም አራዊት የሚኖሩበትን ጒድጓዶች አግኝቶ ወደ አንዲቱ ፍርኩታ ገባ ልብሱንም ሰኔል ሠርቶ ለበሰ። እንዲህም ብሎ ጸለየ "የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ርኀራኄ ከሌለው ጠላት እጅ ጠብቀኝ አድነኝም ተጋድሎዬን እስከምፈጽም ተጸናኝ ዘንድ ቸርነትህ ወደእኔ ትምጣ የትውልድ ሁሉ ንጉሥ ሆይ ኃይል ጌትነት ክብር ገንዘብህ ነውና ለዘላለሙ"።
❤ በዚያችም ዋሻ ውስጥ ሰማንያ ዓመት ኖረ ከሰውም ከቶ ማንንም አላየም ልብሱም ከሰኔል ቅጠል የተሠራ ነው እግዚአብሔር ወደ ማታ ሁል ጊዜ ወደርሱ ቁራን ይልክለታል ከርሱም ጋራ ግማሽ እንጀራ አለ ያንን ለከበረው ጳውሊ ይሰጠዋል።
❤ የክብር ባለቤት እግዚአብሔርም ቅድስናውንና ጽድቁን ይገልጥ ዘንድ በወደደ ጊዜ መልአኩን ወደ ታለቅ አባት ወደ እንጦንዮስ ላከ ይህም እንጦንዮስ በበረሀ ውስጥ መኖርን የጀመረ እርሱ እንደሆነ በልቡ ያስብ ነበር መልአኩም እንዲህ አለው "እንጦንዮስ ሆይ ከአንተ የሁለት ቀን ጎዳና ርቆ በበረሀ ውስጥ ሰው አለ የዓለም ሰዎች ከሚረግጥባቸው የእግሩ ጫማዎች እንደ አንዲቱ ሊሆኑ የማይገባቸው ስለ ርሱም ጸሎት ዓለም ተጠብቆ የሚኖር ምድርም ፍሬዋን የምትሰጥ ጠል በምድር ላይ የሚወርድ በምድር በሚኖሩ ኃጢአተኞች ሁሉ ላይ ፀሐይ የሚወጣ የሰውም ፍጥረት በእግዚአብሔር እጅ ውስጥ ተጠብቆ የሚኖር"።
❤ አባ እንጦንዮስም ይህን ቃል በሰማ ጊዜ ተነሥቶ ወደ በረሀው መካከል ተጓዘ እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ሁኖ ጎዳናውንም እንደሚጠርግለት አምኖ ሲጓዝ የሰውና የአራዊትን ፍለጋ አገኘ ያንንም ፍለጋ ተከትሎ ከቅዱስ ጳውሊ በዓት ደረሰ በሩንም አንኳኳ የከበረ አባ ጳውሊ ግን ከሰይጣን ሥራ እንደሆነ አስቦ ታላቅ ደንጊያ ወስዶ ከመዝጊያው ጀርባ አኖረ አባ እንጦንዮስም "ይሰጠኝ ዘንድ ፈለግሁ አገኝ ዘንድ ለመንኩ ይከፈትልኝም ዘንድ ቡሩን አንኳኳሁ" ብሎ አሰምቶ ተናገረ። በዚያንም ጊዜ ከፈተለትና ገባ እርስ በርሳቸውም በመንፈሳዊ ሰላምታ አጅ ተነሣሥተው በአንድነትም ጸልየው ተቀመጡ።
❤ አባ እንጦንዮስም "አባቴ ሆይ ስምህ ማነው?" አለው አባ ጳውሊም "አንተ ስሜን ካላወቅህ እስከዚች ቦታ ለምን ተጓዝክ" ብሎ መለሰለት በዚያችም ሰዓት እግዚአብሔር የእንጦንዮስን ልቡን ገለጠለትና "ገዳማዊ ጳውሎስን አየው ዘንድ ስለተገባኝ እኔ ብፁዕ ነኝ" አለ ከዚህም በኋላ እርስ በእርሳቸው የእግዚአብሔርን ልዕልናውን ቸርነቱን ይነጋገሩ ጀመር በመሸም ጊዜ ቍራ መጥቶ አንዲት ሙሉ እንጀራ ጣለለት አባ ጳውሊም አባ እንጦኒን "አንተ የእግዚአብሔር አገልጋይ እንደሆንክ አሁን አወቅሁ እስከ ዛሬ ሰማንያ ዓመት በዚህ በረሀ ስኖር እግዚአብሔር ሁልጊዜ የሚልክልኝ ግማሽ እንጀራ ነበር እነሆ አሁን ምግብህን ላከልህ" አለው።
❤ ከዚህም በኋላ ተነሥተው የማዕድ ጸሎት ጸለዩ በልተውም እግዚአብሔርን አመሰገኑት መላ ሌሊቱንም ሲጸልዩ አደሩ። ነግቶ ፀሐይ በወጣ ጊዜም እርስ በርሳቸው ሰላምታ ተሰጣጡ አባ እንጦኒም "አባቴ ሆይ በዚህ ሁሉ ዘመን ሥጋውንና ደሙን ከወዴት ትቀበላለህ?" አለው የከበረ ጳውሊም "እግዚአብሔር መልአኩን ይልክልኛል በቀዳሚት ሰንበትና በእሑድ ሰንበት በየሳምንቱ ከሥጋውና ከደሙ ያቀብለኛል በዘመኑም ሁሉ እንዲህ ያደርግልኛል" ብሎ መለሰለት።
1 161
ግብጻዊው አቡነ ቄርሎስም ካይሮ ላይ ስላረፉ ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ጥር 6 ቀን 1943 ዓ/ም ካይሮ ላይ በአቡነ ዮሳብ እጅ ተቀብተው የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ሊቀ ጳጳሳት ሆኑ። የፓትርያርኩንም ፈቃድ ካገኙ በኋላ በሚቀጥለው ነሐሴ ወር ላይ 5 ኢትዮጵያውያን ጳጳሳትን ሾሙ።
ከግብጽ ቤተ ክርስቲያን ጋር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አመራር ላይ ብዙ ጊዜ የወሰደ ድርድር ከተደረገ በኋላ ስምምነት ተደርጎ፥ እሑድ፣ ሰኔ 1 ቀን 1951 ዓ/ም፤ ንጉሠ ነገሥቱም በተገኙበት ሥነ ሥርዓት ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ 6ኛ በብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ላይ የሢመቱን ሥርዓተ ጸሎት አድርሰው፤ የፓትርያርክነቱን ዘውድ ባርከው ደፉላቸው። ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ አቡነ ባስልዮስ በግብጽ ፓትርያርክ እጅ በዚህ ማዕርግ ሲቀቡ የመጀመሪያውም የመጨረሻውም ኢትዮጵያዊ ናቸው።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስለልዮስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት እየተባሉም እስከ ዕለተ ኅልፈታቸው ቆዩ። አቡነ ባስልዮስ በተወለዱ በ79 ዓመታቸው ጥቅምት 2 ቀን 1963 ዓ/ም አርፈው ጥቅምት 4 ቀን በደብረ ሊባኖስ የተቀበሩ ሲሆን፤ አቡነ ቴዎፍሎስ ተተክተው ሁለተኛው ፓትርያርክ ሆኑ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስም ደርግ እስከሚረሽናቸው ድረስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት እየተባሉ ተጠርተዋል።
እንግዲህ እጨጌ የተሰኘው ማእረግ ይሰጥ የነበረው ከግብጻዊው ሊቀ ጳጳስ ቅጥሎ ያለ ትልቁ ሹመት ሲሆን፥ እጨጌ ሆኖ የሚሾመው አባት የደብረ ሊባኖስም ገዳም አበምኔትም ነበር፡፡ ከመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ሊቀ ጳጳስና ኋላም የመጀመሪያው ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስና ሁለተኛው ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ እጨጌነትንም ደርበው ይዘው ነበር፡፡ በመጀመሪያው የሃገራችን የመደብ አብዮት ዘመን በመንግሥት የተሰየመው የተሐድሶ ምክር ቤት እጨጌነቱን ከፓትርያርኩ በመቀማት የመንግሥት ተወካይ የሆነው የቤተ ክህነት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ እንዲሠራው በመወሰኑ ሦስተኛውና አራተኛው ፓትርያሪኮች እጨጌ አልነበሩም፡፡ በሁለተኛው የዘውግ አብዮት ዘመን ከመንግሥት የሚመደበው ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ በመቅረቱና ቅዱስ ሲኖዶስ የሚመርጠው ሊቀ ጳጳስ ጠ/ሥራ አስኪያጅ እንዲሆን በመወሰኑ አምስተኛውና አሁን በመንበሩ ላይ ያሉት ፓትርያርክ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመሰኘት የእጨጌነትን መንበር የመሠረቱት ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም የስያሜው አካል ሆነዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ እጨጌነት የፓትርያሪኩ ሥልጣን ስለሆነ የደብረ ሊባኖስ አበምኔት ጸባቴ ተብሎ ይጠራል ።
https://t.me/Eotcw
1 161
‹‹ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት››
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታሪክ ቀዳማዊ አቡነ ባስልዮስ 1952 የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ በመሆን የተሾሙ ናቸው። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የተባሉ የመጀመሪያው ፓትርያርክ ነበሩ። ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ እስከ አሁኑ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ 6 ፓትሪያርኮች ተሹመዋል።
1.ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ (1952-1963)
2.ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ1964-1969)
3.ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት( 1969-1980)
4.ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ (1980-2014)
5.ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ (1983-2003)
6. ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ (2004- )
"ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት" የሚለውን ማዕረግ ከ6ቱ ፓትርያርኮች የመጀመሪያዎቹ ሁለቱ (ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ እና ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ)፣ 5ኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ እና አሁን ያሉት 6ኛው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከማዕረጎቻቸው ጋር ይጠሩበታል።
በ3ኛውና በ4ኛው ፓትርያርኮች የማዕረግ መጠሪያ ያልነበረው "ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት" በ5ኛው ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ ዘመነ ፕትርክና ሥራ ላይ እንዲውልና ፓትርያርኩም "ብፁዕ ወቅዱስ ዶክተር አቡነ ጳውሎስ ቀደማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቀነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት" ተብለው እንዲጠሩ የተደረገው ከ1984 ዓ/ም ጀምሮ ነው።
ምናልባት ከሰሙነኛው የቤተክርስቲያን ፈተና ጋር ተያይዞ መንበራችን "ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት" ነው የሚሉም ብቅ ብለዋል። ይህም ቅዱሳን ፓትርያርኮቻችን በማዕረግ ስሞቻቸው ሲጠሩ "ወእጨጌ ዘመንበረ ተከለ ሃይማኖት” እየተባሉ ከመጠራታቸው ጋር በተያያዘ ይመስላል። በአጭሩ "ለመንበረ ተክለ ሃይማኖት" የእጨጌነት እንጂ የፓትርያርክነት ማዕረግ አልተሰጠም። "ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ" ሲባል የኢትዮጵያ ጳጳሳት አለቃ (የበላይ) ማለት ነው። በመቀጠል "ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም" ሲባል የርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን የበላይ ሊቀ ጳጳስ፤ በመቀጠልም "ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት" ሲባል የመንበረ ተክለሃይማኖት እጨጌ ማለት ይሆናል።
እጨጌ ምን ማለት ነው? ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትስ?
የእጨጌ ትርጉሙ ሲብራራ፦ እጨጌ ቃሉ ከወላይትኛው ጨጋ (ጮጌ) የመጣ ሳይሆን መሠረቱ ከግእዙ ሐፄጌ የመጣ ነው፤ ሐጼጌ ማለት የምድር ጠባቂ ማለት ሲሆን በአማርኛ ዐጨ (አጨ) ዕጮኛ ጠባቂ፤ አጨጌ የሃገር ጠባቂ የገዳማትና የአድባራት ዋና ሹም አቡን ማለት ነው፡፡ የአጼው ሁለተኛ ረዳት (ከእቴጌ ቀጥሎ) ያለ ባለሲሶ ድርሻ የሆነ ሹም የሚሰጥ የማዕረግ ስም ነው፡፡ አጨ ጠበቀ፥ እጮኛ ጠባቂ፤ ጌ፦ ስፍራ ቦታ ሃገር፤ (እቴጌ እጨጌ ሰላምጌ ንብጌ ቅዱስጌ ደረስጌ አምባላጌ አሸንጌ ሐረርጌ ጉራጌ እጅጌ አንገትጌ ወገብጌ እራስጌ ግርጌ ወዘተ…) በተገናኘ ጊዜ እጨጌ፦ የሃገር ጠባቂ፥ ባለአደራ፥ የምድር ዕጮኛ ማለት ነው፤ በግአዝ ሐጼጌ (ሐፄጌ) ትርጉሙ ተመሳሳይ ነው፡፡ (የቋንቋዎች መወራረስ ቢኖርም እንደ አካባቢው ማይት ይቻላል ለምሳሌ በአራዳ ጮጋ ዝም ማለት እንዲሁም ጮጌ (ጨጋ) በወላይትኛ አባት ማለት ሲሆን፤ ጌ በክስታኒኛ ቤት ማለት ነው ሁሉም ከእጨጌ ጋር በድምጽ እንጂ በትርጉም አይገናኙም፡፡) ተወራራሽ ድምጾች፦ ሐጼ አጼ (ዐፄ) አጤ አጨ (ዐጨ)፡፡
‹እጨጌ›› የሚለው ማዕረግ ስም በደብረ ሊባኖስ ገዳም በጻድቁ በአቡነ ተክለ ሃይማኖት መንበር ተተክተው ይሰሩ የነበሩ ብዙ ቅዱሳን አባቶች ለምዕታት ዓመታት ሲጠሩበት የቆዩበት ስም ነው፡፡ ማዕረጉ ግን በአንድ ገዳም አበ ምኔትነት ብቻ የሚወሰን ሳይሆን ቀደምት ጳጳሳት ከግብጽ ይመጡ በነበረበት ዘመን ከጳጳሳቱ ቀጥሎ በሁለተኛ መንፈስ አባትነት የተመደበው ቅዱስ ኢትዮጵያዊ የሚጠራበት ስም ነበር፡፡ ለገዳሙ አስተዳደር ከበታች ‹‹ጸባቴ›› የተባለ እንደራሴ እየተሸመ እጨጌውን በበላይነት በአገር አቀፍ ደረጃ ይሰራ ነበር፡፡
በተለይ በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመን ጀምሮ የደብረ ሊባኖስ መሪ የገነነ ስም እያገኝ ሄዷል፡፡ ከውጭ የሚመጡት ጳጳሳት የሀገር ቋንቋ የማይናገሩ ፤ የሕዝቡን ባህልና ወግ የማያውቁ ፤ በአስተርጓሚ ክህነት ለመስጠት ብቻ የመጡ ባይተዋሮች ስለነበሩ እጨጌው ትልቅ ስልጣን ነበረው፡፡
ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ከመጰጰሳቸው በፊት እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ ተብለው ለብዙ ዓመታት የተጠሩበት ሲሆን፤ ከጵጵስና በኋላም ማዕረጉን ደርበው ተጠርተውበታል።
ቀዳማዊ አቡነ ባስልዮስ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት እና የመጀመሪያው ፓትርያርክ ነበሩ።
አቡነ ባስልዮስ ሲወለዱ የተሰጣቸው ስም ገብረ ጊዮርጊስ ሲሆን የተወለዱት መጋቢት 14 ቀን 1884 ዓ/ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መንዝ ላሎ ምድር ነው። የ14 ዓመት ታዳጊ ወጣት እያሉ በ1899 ዓ/ም ደብረ ሊባኖስ ገዳም ገብተው ትምህርታቸውን ከመምህር ገብረ ኢየሱስ ሲከታተሉ ቆይተው በዚያው ገዳም መዓርገ-ምንኩስናቸውን እስከተቀበሉበት ድረስ ለሦስት ዓመታት በእርድና አገልግለዋል።
የካቲት 24 ቀን 1927 ዓ/ም በአቡነ ተክለ ሃይማኖት መንበር፥ ብፁዕ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ ዘነበረ በመንበረ ተክለ ሃይማኖት ተብለው፥ አምሣ-ዘጠነኛው ዕጨጌ ሆነው ተሾሙ። በዚሁ በዕጨጌነታቸው ዘመን የፋሺስት ወረራ ኢትዮጵያን ባጠቃ ጊዜ፣ በጦርነቱ ግምባር ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር ተሰልፈው አብያተ ክርስቲያናትንና መጻሕፍትን የሚያቃጥል የምእመናንን ዘር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና በሃይማኖት፤ በጸሎት፣ በምህላ በርታ እያሉ የኢትዮጵያን ሕዝብ ሲያጽናኑ ቆዩ። ንጉሠ ነገሥቱ በስደት ከነበሩበት ከ’ባዝ’ (ብሪታንያ) ፥ ጥር 13 ቀን 1929 ዓ/ም በጊዜው በስደት ኢየሩሳሌም ለነበሩት ወደ ብፁዕ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ አንድ ፅላትና ለአገልግሎት የሚበቁ አምስት መነኮሳትን ወደ እንግሊዝ አገር እንዲልኩላቸው በአባ ሐና ጅማ በላኩት ደብዳቤ መሠረት፣ ዛሬ ምስካዬ ኅዙናን መድኀኔ ዓለም የተባለውን የመድኀኔ ዓለምን ጽላት ወደ ንጉሠ ነገሥቱ ወዳሉበት ባዝ የላኩት እሳቸው ነበሩ፡፡
ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፥ ጥር 12ቀን 1933 ዓ/ም በኢትዮጵያ ጠረፍ በኡም-ኢድላ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ሲተክሉ ዕጨጌ ገብረ ጊዮርጊስም አብረዋቸው ነበሩ። ከዚያም ንጉሠ ነገሥቱ በምድረ ጎጃም፤ በቡሬ፤ በደብረ ማርቆስ፤ በደብረ ሊባኖስ እና በእንጦጦ በኩል አድርገው ሚያዝያ 27 ቀን 1933 ዓ/ም አዲስ አበባ ሲገቡ ዕጨጌው ሳይለዩ አብረው ነበሩ።
ከድል በኋላም ከእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን ጋር ፥ በጠላት ወረራ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን ግንኙነት እንዲታደስና እንዲቀጥል ለማድረግ በየካቲት ወር 1934 ዓ/ም ንግግር ተጀመረ። ሐምሌ 17 ቀን 1940 ዕጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ ፥ አቡነ ባስልዮስ ተብለው ከአቡነ ቴዎፍልስ፤ አቡነ ሚካኤል፤ አቡነ ያዕቆብ እና አቡነ ጢሞቴዎስ ጋር በእስክንድርያው ፓትርያርክ አቡነ ዮሳብ እጅ ተቀቡ።
1 161
ጾመ ነነዌ
ከፈለገ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ
ክፍል አራት
7.የእግዚአብሔርን ኃይል ማየት
በነነዌ ሰዎች የእግዚአብሔር ኃያልነት በግልጥ ተገልጧል፡፡ የእግዚአብሔር ኃያልነትም በትዕግሥቱ፣ በፍቅሩ፣ ፍጥረትን በመግዛቱ፣ ለሰው ልጆች በሰጠው ድንቅ ነፃነት ወዘተ ተገልጧል፡፡
በዚህ ታሪክ ውስጥ አንዲትም ነፍስ ሳትጠፋ ሁሉም ይድኑ ዘንድ እግዚአብሔር ያሳየው የትዕግሥቱ ኃያልነት እንዴት ድንቅ ነው! የእግዚአብሔርን ፈቃድ ያስተምር ዘንድ ነቢይ የሆነው ዮናስ እንኳ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ትቶ ሲኮበልል በሔደበት ሁሉ እየተከተለ በተለያየ መንገድ ወደ መንገዱ እንዲመለስ ይሠራ ነበር፡፡
ምናልባትም ሰው ዮናስን ይህን ያህል አይታገሰውም፡፡ ሰዎች እግዚአብሔርን 'የመምከር' ዕድል ቢሰጠን "ጌታ ሆይ አንተ ሁሉን ማድረግ ትችላለህ፤ ከነዚህ ድንጋዮት እንኳ ለአብርሃም ልጆች ማስነሣት ትችላለህ፡፡ ለምን ዮናስን ትለምነዋለህ? ተወው ሌላ ነቢይ ወደ ነነዌ ላክ፡፡ ዮናስን ርግፍ አድርገህ ተወው ከነነዌ ሰዎች የራሱን ክብር አስቀድሟልና፡፡" እንል ይሆናል፡፡
በባሕሪዩ ታጋሽ የሆነው እግዚአብሔር ግን ዮናስ በንስሐ ይመለስ ዘንድ ጠብቆታል፤ በመጨረሻም ለክርስቶስ ምሳሌ የሚሆን ታላቅ ነቢይ አድርጎታል፡፡
በነነዌ ታሪክ የእግዚአብሔር የፍቅሩ ታላቅነትም ተገልጧል፡፡ የእስራኤል አምላክ ይባል እንጂ ከአሕዛብ መካከል ለንስሐ የተዘጋጀ ሕዝብ ሲያይ ነቢዩን ልኮ ሕዝቡ አድርጓቸዋል፡፡
ቀና ልብ ያላቸው፣ ዮናስ ሲተኛ እንኳ ለማያውቁት አምላክ ሲጸልዩ የነበሩትን መርከበኞችንም በዮናስ ምክንያት እንዲያውቁት አድርጓል፡፡
በርግጥም እግዚአብሔር ወደርሱ የምታይን ነፍስ፣ እርሱን የተጠማችን ልቦና አይተዋትም፡፡
በነነዌ ሰዎች ታሪክ የታየው ሌላው የእግዚአብሔር ኃይል በፍጥረቱ ላይ ያለው ሥልጣን ነው፡፡ ግዕዛን የሌላቸው ፍጥረታት /ፀሐይ፣ ማዕበል፣ ትል፣ ዛፍ፣ አሳ አንበሪ. . . / የእግዚአብሔርን ፈቃድ ያለምንም ተቃውሞ ሲፈጽሙ እናያለን፡፡
በዚህም እግዚአብሔር ለሰው ልጆች የሰጠውን ታላቅ ስጦታ 'ነፃነትን' እናደንቃለን፡፡
ፍጥረታት የሚታዘዙለት ኃይል እግዚአብሔር በነፃነት የፈጠረው የሰው ልጅ ፈቃዱን ሲጥስ ይመለስ ዘንድ በሚታዘዙት ፍጥረታት፣ በነቢያት. . . ይናገራል እንጂ ልቦናን በኃይሉ ቀይሮ እንደፈቃዱ እንዲኖር አያደርግም፡፡
ከዚህም በተጨማሪ መቀየር የፈለገን ልብ መቀየር የሚችል የሁሉ ፈጣሪ መሆኑን ፍጥረታቱን በማዘዝ አሳይቷል፡፡
ከዚህ ታሪክ ለእኛ የሚሆን ብዙ ነገሮችን እናገኛለን፡፡ የመጀመሪያው በንስሐ የምንኖር ከሆነ ወደዚህ ሕይወት እንደርስ ዘንድ እግዚአብሔር የታገሰባቸውን ያለፉትን የኃጢአት ዘመናት አስተውለን የእግዚአብሔርን የትዕግሥቱን ብርታት በሕይወታችን እናውቃለን፡፡
ከዚህ በኋላ ስለ እግዚአብሔር ታጋሽነት ሰዎች ሊነግሩን አያስፈልግም፤ በሕይወታችን አይተነዋልና፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ወደ እርሱ እንመለስ ዘንድ በሕይወታችን ውስጥ የሠራውን የፍቅሩን ብርታትም እናውቃለን፡፡
ምንም እንኳ በዚህ ምድር ላይ ከቢሊዮኖች መካከል አንድ ብንሆንም በእግዚአብሔር ዘንድ ግን በንስሐ መመለሳችን ሁሌ በእግዚአብሔር ሕሊና ውስጥ ሲታሰብ የኖረ፣ በሰማያት ካሉ ቅዱሳን ይልቅ የአንድ ኃጢአተኛ መመለስ ለሰማያትና ለእግዚአብሔር ደስታ የሚሰጥ መሆኑን ስናውቅ በርግጥም እግዚአብሔር እንዴት ሰውን ወዳጅ ነው? ነፍሳችንስ በእግዚአብሔር ዘንድ ምን ያህል የምትወደድ ናት? እንላለን፡፡
ከዚህ ሌላ ፍጥረታት የእግዚአብሔር ሁሉን የማድረግ ሥልጣን በመታዘዝ እንዳሳዩ ሁሉ በንስሐ የተመለሰ ኃጢአተኛም የእግዚአብሔር ሁሉን ቻይነት የሚታይበት ይሆናል፡፡
በኃጢአት የኖረን፣ አያሌ ዘመናትን በዲያብሎስ ምክር በጠማማ መንገድ የኖረን ልቦና መቀየር ከኃያሉ ከእግዚአብሔር በቀር ለማን ይቻለዋል? ኃጢአተኛን 'ቅዱስ' ማድረግ የእግዚአብሔር የብቻው የኃያልነቱ ውጤት ነውና፡፡
ለዚህ ነው 'ተነሳሕያን' ሰማዕታት ናቸው የሚባለው፤ የእግዚአብሔርን ሥራ በሕይወታቸው ይመሰክራሉና፡፡
ጥንታውያን ክርስቲያኖች በደማቸው የእግዚአብሔርን ክብር መስክረው ከሆነ ለዚህ ትውልድ ደግሞ "የንስሐ" ሰማዕትነት ቀርቶለታል፡፡
በአጠቃላይ ከነነዌ ሰዎች ታሪክ ስለንስሐ ብዙ እንማራለን፡፡ ለዚህም ነው ከብዙ የንስሐ ታሪኮች መርጣ ቅድስት ቤተክርስቲያን በተለየ ክብር የምታስበው፡፡
ለዚህም ነው ለታላቁ የንስሐ ወቅት ለዐቢይ ጾም ማዘጋጃ መግቢያ ያደረገችው፡፡ እኛም ከዚህ ታሪክ ተምረን፣ የተማረነውንም በንስሐ ወቅታችን /በአሁኑ ጾም/ በተግባር ልናውለው ይገባል፡፡
ለዚህም የተነሳሕያን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ይርዳን! አሜን፡፡
~~~~ ተፈጸመ ~~~~
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯
