en
Feedback
Harari People Regional State Center Of Competence(COC)

Harari People Regional State Center Of Competence(COC)

Open in Telegram

Assess and Certifide

Show more
371
Subscribers
+324 hours
+117 days
+5130 days
Posts Archive
በዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናዎች ላይ የተመዘገቡ ዝቅተኛ ውጤቶች የትምህርት ማህበረሰቡን አንቅተዋል - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ******* በ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናዎች ላይ የተመዘገቡ ዝቅተኛ ውጤቶች የትምህርት ስርዓቱ "የወደቀባቸውን" መሰረታዊ ችግሮች በግልጽ ከማሳየት ባለፈ የትምህርት ማህበረሰቡን ማንቃታቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል፡፡ የመግቢያ ፈተናዎቹ ውጤት ማሽቆልቆል ትምህርት ቤቶች፣ ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የተማሪዎች ወላጆች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለትምህርት ጥራት ከፍተኛ ትኩረት እንዲሰጡ ማንቃቱን ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ በትምህርት ስርዓቱ ላይ የተወሰዱ ማሻሻያዎች አውንታዊ ለውጦችን እያመጡ መሆናቸውን ጠቁመው፤ የለውጦቹን ፍሬ በምልዕት ለማየት ግን ጊዜ እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡ በሀገር አቀፍ ፈተናዎች ላይ የተመዘገቡት ዝቅተኛ ውጤቶች ወላጆች ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት ከመላክ ባለፈ ትምህርታቸውን በቅርበት እንዲከታተሉ በር መክፈቱን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አንስተዋል፡፡ ይህ ገንቢ ልምድ ወላጆች የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ከትምህርት ቤቶች እና ከመምህራን ጋር በቅርበት እንዲሰሩ ማስቻሉን "በትምህርት ለትውልድ" ንቅናቄ በግልጽ መታየቱን አመላክተዋል፡፡ የመለኪያ ፈተናዎቹ ተማሪዎች ትምህርታቸውን በስርዓት እንዲከታተሉ፣ መምህራን በኃላፊነት ስሜት እንዲያስተምሩ፣ ርዕሳነ መምህራን የትምሀርት ሂደቱን በአግባቡ እንዲመሩ መልካም ጅምሮችን መፍጠራቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

ጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ የማልማት እና የማስዋብ ስራዎች 💫🌟✨ ✍️ታሪካዊ አሻራችንን አሳርፈናል እንኳን ደስ አለን..... በክልላችን ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ኦርዲን በድሪ ሀሳብ አመንጪነትና ድንቅ አመራር ሰጪነት በሁለተኛ ዙር የጀጎል አካባቢ መልሶ ማልማትና ማስዋብ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ይታወቃል :: በዚህ ታሪካዊ ተግባር የሀረሪ ክልል የልህቀት ማዕከል የተረከበዉን የጀጎል ውስጥ ለውስጥ መንገዶች  የመጠገንና የማስዋብ ስራን አጠናቀቀ፡፡ መንገዱ ከዚህ በፊት ለጎርፍና ላልተፈለገ የፍሳሽ ውሃ የተጋለጠና ምቹ እንዳልነበረ በመግለጽ አሁን መንገዱ በዚህ ደረጃ መሠራቱ በጣም እንዳስደሰታቸው አካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል፡፡ የሀረሪ ክልል የልህቀት ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ኮሚሽነር ካሊድ ኑሬ  እንደገለፁት ከዚህ በፊት ሰፈሩ ለከፍተኛ ጎርፍ  ላልተፈለገ የፍሳሽ ውሃና ለሌሎች ችግሮች የተጋለጠ እንደነበር በመግለፅ በአካባቢው የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት እንዲያስችል  መንገዱን ከፍተኛ ወጪ በማዉጣት የመጠገንና የማስዋብ ስራ መሠራቱን  ገልፀዋል፡፡ መንገዱን በማስዋብ ሂደት እገዛና ትብብር ላደረጉ የአካባቢው ነዋሪዎች የማዕከሉ ሰራተኞች  ምስጋና አቅርበው በቀጣይም መንገዱ እንዳይበላሽ ማህበረሰቡ በባለቤትነት ሊጠብቁት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ ከዚህ በፊት መንገዱ ለብዙ ችግሮች የተጋለጠ መንገድ እንደነበረ የገለፁት የአካባቢው ነዋሪዎች ችግሩ ተቀርፎ በዚህ ደረጃ አምሮና ተዉቦ በመሰራቱ መደሰታቸውን ገልፀዉ በቀጣይ በባለቤትነት መንፈስ ለመጠበቅና ለመንከባከብ ቃል በመግባት ለክልሉ መንግስትና ለማዕከሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ የሚሰሩ እጆች አብዝተዉ ይባረኩ !! Shining Harar !!! መጋቢት 9/2016ዓ.ም ‹‹የሙያ ብቃት ምዘና ጥራትን እናረጋግጥ!›› የተቋማችንን ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት ቴሌግራም ቻናላችንን https://t.me/HRCOC የፌስቡክ ገፃችንን  https://www.facebook.com/hararicoc ይቀላቀሉ።

በዘንድሮው ዓመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ የተማሪዎች ምዝገባ ተካሂዷል፡- የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ***** በዘንድሮው ዓመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ የተማሪዎች ምዝገባ መካሄዱን የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ገለጸ። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ለዘንድሮው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የተሳካ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ ነው። ይህንንም ተከትሎ ተማሪዎች የሚፈተኗቸውን የትምህርት ዓይነቶች አውቀው ዝግጅት እንዲያደርጉ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር መከናወኑን አንስተዋል። ተማሪዎች በሥነ-ልቦና እራሳቸውን እንዲያዘጋጁ የተለያዩ ተግባራት መከናወናቸውንም ጠቅሰዋል። ለሀገር አቀፉ የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚቀመጡ የተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ ከየካቲት 3 እስከ የካቲት 30/2016 ዓ.ም እንደሚያከናውን ተቋሙ መግለጹ ይታወሳል። ይህንንም ተከትሎ ተቋሙ የፀጥታ ችግር ካለባቸው አንዳንድ አካባቢዎች በስተቀር በአብዛኛው ሀገሪቱ አካባቢዎች የተማሪዎች ምዝገባ ተካሂዶ መጠናቀቁን ጠቁመዋል። በዚህም እስካሁን ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውን ገልፀዋል። የተቀሩት የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ተፈታኝ ተማሪዎች ምዝገባ ደግሞ በዚህ ሣምንት እንደሚከናወን ነው ያረጋገጡት። የፈተና ዝግጅት ሥራው የሀገሪቱን ሥርዓተ ትምህርት የተከተለና ተማሪዎቹን በአግባቡ መመዘን በሚያስችል መልኩ መዘጋጀቱን ጠቅሰዋል። የፈተናው ዝግጅት እየተገባደደ መሆኑን አንስተው፤ በቀጣይ የፈተናው ሕትመት እንደሚጀመርም መግለጻቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው። የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የመስጫ ሰሌዳ ወደፊት ይፋ እንደሚሆንም ጠቁመዋል።

የብቃት ምዘና ፈተና ለወሰዳችሁ ተመዛኞች በሙሉ ___ በ Medicine, Nursing, Public Health, Anesthesia, Pharmacy, Medical Laboratory Science, Midwifery, Dental Medicine, Medical Radiology Technology, Environmental Health, Psychiatric Nursing, Pediatric & Child Health Nursing እና Emergency & Critical Care Nursing ሙያዎች በየካቲት 06/2016 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር እና በጤና ሚኒስቴር በጋራ የተሰጠውን የመውጫ እና የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች በሙሉ ከመጋቢት 04/2016 ዓ.ም ጀምሮ http://hple.moh.gov.et/hple/candidates/index4 ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና በትምህርት ሚኒስቴር የተሰጣችሁን የፈተና መለያ ቁጥር (Username) በማስገባት የብቃት ምዘና ፈተና ውጤታችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። ማሳሰቢያ፦ ተመዛኞች ዲግሪ መያዝና የጤና ሚኒስቴርን የማለፊያ ነጥብ ማሟላት የሚጠበቅባችሁ ሲሆን እነዚህን መስፈርቶች ያሟላችሁ ተመዛኞች ስም ዝርዝራችሁ ለክልል የጤና ተቆጣጣሪ አካላት የሚላክ በመሆኑ በክልላችሁ በመሄድ የሙያ ስራ ፍቃድ ማውጣት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን የተለያዩ ጥያቄዎች ያላችሁ ተመዛኞች ውጤት ከተገለጸበት ዕለት አንስቶ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት በስልክ ቁጥር 0118275936 በመደወል ወይም በኢሜይል regulatory.moh@moh.gov.et ብቻ ሙሉ ስም፣ ሙያ እና የፈተና መለያ ቁጥር (Username) በማስገባት ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

የ114 ተፈታኞች ውጤት ተሰረዘ #Ethiopia | በመውጫ ፈተና ኩረጃና ሌሎች የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ተሰረዘ። በመውጫ ፈተና ኩረጃና ሌሎች የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ መሰረዙን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ በመውጫ ፈተና ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት፣ መኮረጅና የተለያዩ የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 114 ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ መሠረዙን ነው ሚኒስቴሩ ዛሬ ለሁሉም የመንግስትና የግል ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ ያስታወቀው፡፡ የፈተና ስነምግባር ጥሰት የፈጸሙት 114 ተፈታኞች ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ መሠረዙንና የሚወሰዱ ተጨማሪ እርምጃዎች በቀጣይ የሚገለጽ መሆኑ ተመልክቷል ። ከየካቲት 6 እስከ 11 ቀን 2016 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ የመንግስት ተቋማት በተሰጠው ሁለተኛ ዙር የመውጫ ፈተና 119 ሺህ 145 ተፈታኞች ተፈትነዋል ።

የሐረሪ ክልል ፕላንና ልማት  ኮሚሽን በዛሬው ዕለት የሐረሪ ክልል ልህቀት ማዕከልን የ2016 በጀት አመት የ6ወር ዕቅድ አፈፃፀም ምዘና አካሄደ። ግምገማውም የክልሉ የፕላንና ልማት ኮሚሽን ከፍተኛ ባለሙያዎች ፣ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ ባለሞያዎች ፣ ከፕሬዝዳንት ጽ/ቤት እና ከብልጽግና ፓርቲ ፅ/ቤት ከተውጣጡ አመራሮች ተመርቷል። የተካሄደው የአፈጻጸም ምዘና አንድ ዕቅድ አንድ ሪፖርት መርህን የተከተለ ነበር። በግምገማው ላይ የልህቀት ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ  ካሊድ ኑሬን ጨምሮ  የማዕከሉ ሁሉም የማኔጅመንት አባላት ተገኝተዋል። መጋቢት 2/2016ዓ.ም ‹‹የሙያ ብቃት ምዘና ጥራትን እናረጋግጥ!›› የተቋማችንን ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት ቴሌግራም ቻናላችንን https://t.me/HRCOC የፌስቡክ ገፃችንን  https://www.facebook.com/hararicoc ይቀላቀሉ።

ለመላው የክርስትና እና የእስልምና እምነት ተከታይ ወንድሞችና እህቶች እንኳን ለአብይ ፆም እና ለረመዳን ፆም በሰላም አደረሳችሁ! መልካም የጾም ወራት ይሁንልዎ! የሐረሪ ክልል ልህቀት ማዕከል (COC)

-- ማሳሰቢያ -- የሥራና ክህሎት ሚኒስቴርዜጎች በሃገር ውስጥ እና በውጭ በሚፈጠር የሥራ ዕድል በህጋዊ መንገድ መብታቸው ደህንነታቸው እና ጥቅማቸው ተጠብቆ መስራት እንዲችሉ የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል ስምሪት ስምምነት በመፈፀም ለፓስፖርት እና ለጤና ምርመራ ከሚከፈል ክፍያ ውጪ በነፃ አገልግሎት እንዲያገኙ እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህ አገልግሎት በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት የባዮሜትሪክስ መረጃዎቻቸውን የሰጡ፣ ማንነታቸው የተረጋገጠ፣ ስልጠና የወሰዱ ከ189,430 በላይ ዜጎች ባለፉት 6 ወራት ወደ ተለያየ ሃገር ተሰማርተዋል፡፡ በስምሪቱ ከፍተኛ ስኬት ያስመዘገቡ ክልሎች እንደሚከተለው ይቀርባሉ፡፡  ኦሮሚያ ክልል = 94,106  አማራ ክልል = 39,205  ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል = 27,500  ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል = 14,947  አዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር = 6,331  ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል = 3,613  ሲዳማ ክልል = 1,430  ትግራይ ክልል = 822  ሐረር ክልል = 286  አፋር ክልል = 205  ድሬዳዋ ከተማ መስተዳደር = 193  ሱማሊ ክልል = 193  ቤንሻንጉል ክልል = 181  ጋምቤላ ክልል = 83 በዚህ በውጭ ሃገር የሥራ ስምሪት በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ግብዓት በማሟላት ከዚህ በፊት ወደ ውጪ ሃገር ሰራተኛ አሰማርተው የማያውቁ ክልሎች ጭምር የዕድሉ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ምቹ ሁኔታ የፈጠረ በመሆኑ የስምሪቱ ተጠቃሚ መሆን የምትፈልጉ ዜጎች በአቅራቢያቹ በቀበሌ ደረጃ በሚገኙ አንድ ማዕከላት በመሄድ እንድትመዘገቡ ጥሪ እናቀርባለን:: ከዚህ ውጪ የሚደረግ ወደ የትም ሃገር "ለስራ እናሰማራቸዋለን" እና "በቀላሉ ስራ እንድታገኙ እናማክራቸዋለን” የሚል ቅስቀሳ ዜጎችን ለከፋ አደጋ የሚጥል እንዲሁም ከፍተኛ የገንዘብ ማጭበርበር በመሆኑ ራሳቸውን እንድትጠብቁ እናሳስባለን፡፡ የባዮሜትሪክስ ምዝገባ የሚያከናውኑ አንድ ማዕከላትን ዝርዝር (https://lmis.gov.et/ossc-lists ) ከዚህ ላይ ማግኘት ይቻላል፡፡ የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!!

በሀረሪ ክልል ልህቀት ማዕከል አስተባባሪነት ከተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች በተውጣጡ የኢንዱስትሪ መዛኞች ለተከታታይ አስር ቀናት ሲካሄድ የነበረዉ  የምዘና መሳሪያ ዝግጅት በምስል !!!

💚💛❤እንኳን ለ128 ኛው የአድዋ ድል በዓል አደረሰን፡፡ የአድዋ ድል የኢትዮጵያውያን ድል እና የመላው የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ድል ነው፡፡ የዓድዋ ድል የጥንካሬያችንና የአሸናፊነታችን መሠረት ነው! እንኳን አደረሰን!!💚💛❤